Ethiopian Digital Library


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Education


በዚህ ቻናል ስለ
👉ትምህርት፣
👉ሥራ እና
👉ማህበራዊ ጉዳይ
መረጃ ያገኛሉ!
Contact: @ethiodlbot

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Education
Statistics
Posts filter


እንኳን ለ114ኛው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (March 8) በሠላም አደረሳችሁ!

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

5.3k 0 16 4 100

የአውሮፓ ዩኒቨርስቲዎች አማርኛ ማስተማር ከጀመሩ 100 ዓመት አልፏቸዋል

ኔፕልስ፣ ፓሪስ እና ሐምቡርግ ዩኒቨርስቲዎች አማርኛ ማስተማር ከጀመሩ 100 ዓመት አልፏቸዋል። በኔፕልስ አማርኛን ማስተማር የጀመሩት አፈወርቅ ገብረየሱስ ናቸው። ይህ ማለት በ1890ዎቹ መሆኑ ነው። ጥንት በዓድዋ ዘመን።

አማርኛ በጀርመን፣ ሐምቡርግም ዩኒቨርስቲም ይሰጣል። እዚያም ድሮ ነው የተጀመረው። ዛሬም ድረስ አለ፤ ለዚያውም ሳይቋረጥ። ይቆጠር ከተባለ 105 ዓመት ሆኖታል፣ ዘንድሮ። የመጀመሪያው መምህር ወልደማሪያም ደስታ የሚባሉ ሰው ናቸው። በ1909 ከአንኮበር-ሐምቡርግ ሄደው አምስት ዓመት አስተምረዋል።

በፖላንድ አማርኛን ማስተማር የጀመሩት ፕሮፌሰር ስቴፋን ስትሬልሲን ናቸው።የዛሬ 75 ዓመት ገደማ። እሳቸው አማርኛን ያጠኑት በ2ኛው የዓለም ጦርነት ጊዜ ነው። ቋንቋውን የተማሩት ደግሞ በፈረንሳይ ነው። እኚህ ሰው ከባድ የኢትዮጵያ ወዳጅ ነበሩ ይባላል።

BBC Amharic

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


መምህራን የሥራ ማቆም አድማ

በኦሮሚያ ክልል በሸገር ከተማ አስተዳደር ሥር በሚገኙ በርካታ ትምህርት ቤቶች የሚያስተምሩ መምህራን ከረቡዕ የካቲት 26 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ በሥራ ማቆም አድማ ላይ እንደሚገኙ መምህራንና የተማሪ ወላጆች ተናግረዋል፡፡
መምህራኑ፣ ለሥራ ማቆም አድማው መነሻ የኾነው፣ “ጥያቄዎቻችን ምላሽ አለማግኘታቸውና ጥቅማችንን የሚጎዳ አሠራር መጀመሩ ነው፤” ብለዋል፡፡

ለደኅንነታቸው እንደሚሰጉ በመግለጽ ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁን አስተያየት ሰጪዎቹ፣ አድማው ከአንደኛ እስከ ኹለተኛ ደረጃ እና መሰናዶ ድረስ ባሉ በርካታ ትምህርት ቤቶች ውስጥ፣ የመማር ማስተማር ሒደቱ እንዲቋረጥና እንዲስተጓጎል ማድረጉን ገልጸዋል፡፡
#VOA

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

9.4k 0 11 13 69

የ4 ዓመት ከ10 ወር እድሜ ያላት ህጻን ልጅ ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመው የ72 አመት አዛውንት በ12 ዓመት ፅኑ እስራት መቀጣቱን የቦሌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ ገለጸ።

አቶ ተስፋዬ ደመቀ የተባሉ የ72 ዓመት እድሜ ባለ ፀጋ ነሐሴ 14 ቀን 2016 ዓ/ም በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ቦታው ቦሌ ቡልቡላ ዶክተሮች ሠፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከቀኑ 5:00 ሠዓት ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀሉን ፈፅመዋል።

የ4 ዓመት ከ10 ወር እድሜ ያላት ህጻን በአካባቢው እየተጫወተች ሳለ የኢትዮ ቴሌኮም ታወር ጥበቃ ሠራተኛ የሆኑት አቶ ተስፋዬ ደመቀ ህፃኗን ነይ እንጫወት በማለት የድርጅቱ የጥበቃ ሠራተኞች የሚያድሩበት ማረፊያ ውስጥ በማስገባት የአስገድዶ መድፈር ወንጀሉን ሲፈጽሙባት የአካባቢው ህብረተሰብ ደርሶባቸው ለፖሊስ በደረጉት ጥሪ ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ውለዋል።

ጥር 21 ቀን 2017 ዓ/ም በዋለው ችሎት ተከሳሽን ያርማል ሌሎች ወንጀል ፈጻሚዎችን ያስጠነቅቃል በማለት በ12 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ የጥፋተኝነት ውሳኔ አስተላልፎባቸዋል።

ወላጆች ወይም አሰዳጊዎች ህጻናት ልጆቻቸው የት እና ከማን ጋር እንደሚውሉ በቂ ቁጥጥር ማድረግ እንዳለባቸው የተገለፀ ሲሆን በህፃናት ላይ የሚደርሱ የአስገድዶ መደፈር ወንጀሎችን ለመከላከል ፖሊስ ከሚያከናውነው የቅድመ ወንጀል መከላከል እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ባሻገር አጠራጣሪ ነገሮችን ሲመለከት ህብረተሰቡ ጥቆማ የመስጠት ተግባሩን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የአዲስ አበባ ፖሊስ መልዕክቱን ያስተላልፋል።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

9.6k 0 17 11 108

ትምህርት ሚኒስቴር የሶስተኛውን ዙር የ2017 ዓ.ም የድህረምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) የምዝገባ ጊዜ ይፋ አደረገ።

ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) አመልካቾች ምዝገባ ከየካቲት 27 እስከ መጋቢት 1/2017 ዓ.ም ማታ 12፡00 ሰዓት ድረሰ ብቻ በ
https://ngat.ethernet.edu.et/registration የመመዝገቢያ ሊንክ በኩል እንደሚከናወን አሳውቋል።

ከምዝገባው ጋር ለተያያዘ ማንኛውም ጥያቄ በሥራ ሰዓት በኢሜል አድራሻ ngat@ethernet.edu.et ወይም በስልክ ቁጥር 0920157474 እና 0911335683 ማብራሪያ መጠየቅ እንደሚቻልም አመልክቷል።

የመፈተኛ ' USER NAME ' እና " PASSWORD ' በመመዝገቢያ ፖርታል በኩል ይላካል ያለው ሚኒስቴሩ የመመዝገቢያ ክፍያ ብር 750 እንደሆነና በቴሌብር በኩል ብቻ እንደሚፈጸም ገልጿል።

ትምህርት ሚኒስቴር ፈተናው የሚሰጥበትን ቀን በቀጣይ እንደሚያሳውቅ አመልክቷል። ተፈታኞች በፈተና ወቅት የተሰጣቸውን User Name እና Password፣ እንዲሁም ማንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ ይዘው መቅረብ ይጠበቅባቸዋል ብሏል።
#MoE #NGAT


የካራማራ ድል የካቲት 26፣ 1970 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ጦር የሶማሊያን ጦር በማሸነፍ ካራማራ ተራራ ላይ ደማቅ ታሪክ የፃፈበት 47ኛ ዓመት!

ዛሬ 47ኛው የካራማራ ድል በዓል ቀን ነው። እንኳን አደረሰን! ከወራሪዋ ሶማሊያና ግብረ አበሮቿ ጋር የተደረገው አልህ አስጨራሹ ጦርነት እልፍ አዕላፍ ሕይወት ተገብሮበት በኢትዮጵያ አሸናፊነት ተደምድሟል።

በዚህ ጦርነት ወደ 15 ሺህ የሚጠጉ የኩባ ሰራዊቶች እንዲሁም የየመን ወታደሮች ስለኛ መስዕዋትነት መክፈላቸው በታሪክ ተዘግቧል።

እንኳን ለድሉ መታሰቢያ በዓል አደረሰን!

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


ከነ መሀይምነቴ አስመርቆኛል በሚል ትምህርት ቤቷን የከሰሰችው ተማሪ

አሌይሻ ኦርቲዝ የተባለችው የ19 ዓመት ተማሪ ከአንድ ዓመት በፊት ነበር የሁለተኛ ደረጃ ትምህረቷን በከፍተኛ ውጤት አጠናቃለች የተባለችው፡፡ በአሜሪካዋ ኮኔክቲከት ግዛት ባለ ትምህርት ቤት ትምህርቷን የተከታተለችው ይህች ተማሪ፤ ከፍተኛ ውጤት ማምጣቷን ተከትሎ የስኮላርሽፕ እድል ተመቻችቶላት በመማር ላይ ነበረች፡፡

ይሁንና የተማሪ አሌይሻ መጻፍ፣ ማንበብ እና ተያያዥ ክህሎት አብረዋት ከሚማሩት ተማሪዎች በብዙ እጥፍ ወደኋላ እንደቀረች ትረዳለች፡፡ ከክፍል ጓደኞቿ ጋር እኩል መጓዝ ያልቻለችው ተማሪዋ፤ ትምህርቷን ለማቋረጥ መገደዷን ኦዲቲ ሴንተራል ዘግቧል፡፡

“እኔ መሀይም ሆኜ ሳለ ትምህርት ቤቴ ግን በከፍተኛ ማዕረግ ብሎ ማስመረቁ ትክክል አይደለም” ያለችው አሌይሻ የቀድሞ ትምህርት ቤቷ ላይ ክስ መመስረቷን ተዘግቧል፡፡ ተማሪዋ አሁን ላይ ያላት እውቀት አንደኛ ክፍል ካለ ተማሪ ጋር ተመሳሳይ ነው የተባለ ሲሆን እርሳስ መያዝ እና የተወሰኑ ቃላትን ብቻ ማንበብ ትችላለችም ተብሏል፡፡

የትምህርት ቤቱ አማራሮች በግዴለሽነት በእኔ ላይ ላደረጉት ጥፋት መቀጣት አለባቸው የምትለው ተማሪዋ ሌሎች ተማሪዎች መሰል ጉዳት እንዳይደርስባቸው በሚል ክስ መመስረቷ ተገልጿል፡፡

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


Bloom’s Taxonomy

Bloom’s Taxonomy is a hierarchical classification system that categorizes educational learning objectives into different levels of complexity and specificity.

Developed originally by Benjamin Bloom and collaborators in 1956 and later revised by Anderson and Krathwohl in 2001, it has been instrumental in designing curricula, assessments, and instructional strategies.

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


Trade War

ፕሬዝዳንት ትራምፕ የቻይና ሸቀጦች ላይ ጥለውት የነበረውን የ10% ቀረጥ በእጥፍ ወደ 20% ከፍ አደረጉት። ቻይና በበኩሏ ከአሜሪካ የሚገቡ የግብርና ውጤቶችና ሌሎች ቁሳቁሶች ላይ የ15% የቀረጥ ግብር ጥላለች።

ትራምፕ በካናዳ እና በሜክሲኮ ላይ 25% ታሪፍ እና በቻይና ላይ 20% ታሪፎችን ይፋ አድርገዋል፡፡

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library




በአማራ ክልል 4.7 ሚሊዮን ተማሪዎች ከትምህርት ጋር ተሰነባብተዋል❗️

የህፃናት ጋብቻ ተጧጡፏል ይገርማል ❗️

ትምህርት መከልከል ግን ምን ይሉታል ❗️

መምህራን ይታገታሉ ይገደላሉ ❗️

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


🛑 ስለ Canva የምታውቁ ታውቁታላችሁ ምን
አይነት ዲዛይኖችን እንደሚሰራ! ግን PRO አካውንቱ በጣም ውድ ነው።

📌 እኛ ግን ነፃ በሚባል ዋጋ አቅርበንላችኋል።

ሙሉ ቪድዮውን አይታችሁ ምርጥ Graphic Designer ሁኑ! 👇👇👇
https://youtu.be/Kab_ldt9yLE


ትልቁ ዳቦ ሊጥ ሲሆን
*****************
እንግዲህ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፌስቡክ ገጽ ላይ ነው እንዲህ የሆነው ።" እችላለሁ " መባል የነበረበት " እችላለው " ፣ " እፈልጋለሁ " መባል የነበረበት " እፈልጋለው " ፣ " አመሰግናለሁ " መባል የነበረበት " አመሰግናለው " ተብሎ የተጻፈው ። አሁን አሁን ስህተቱ ተለምዶ ማንሳትም እየቀረ ነው ። ስህተቱ ልክ እየሆነ ነው ። ይህ ግን አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ነው ። የቋንቋ ጉዳይን ለማረቅ ስልጣን ያለው ፣ ሌሎች ሲሳሳቱ ማረም ያለበት ተቋም ። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ አማርኛን የማያውቅ ምሩቅ ለምን በአማርኛ ይጽፋል ? አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲም " ሁ " - " ው " ቢባል ምንም ለውጥ እንደሌለው ያስባል ? አይመስለኝም ። እንግዲህ ማን ነው የሚመለከተው ? ሁሉን አቅልለን አቅልለን ቀለልን እኮ ጎበዝ ።

Tewodros Teklearegay

13.9k 0 14 23 189

የመውጫ ፈተና - ፋይዳ መታወቂያ

በሰኔ 2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ዕጩ ተመራቂዎች የፋይዳ መታወቂያ ሊያወጡ ይገባል - ትምህርት ሚኒስቴር

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


▶️🔴 The Ethiopian victory at the Battle of Adwa (1896) was a significant event in African history.

Three key reasons for Ethiopia's success were:

☄️Strong Leadership – Emperor Menelik II and Empress Taytu Betul demonstrated exceptional strategic and diplomatic skills. Menelik successfully united Ethiopia's diverse regions, while Taytu played a crucial role in diplomacy and war strategy.

☄️Superior Numbers and Preparation – The Ethiopian army outnumbered the Italians, with around 100,000 troops compared to Italy's 15,000-20,000. They were also well-equipped, having acquired modern weapons from France and Russia.

☄️Geographical Advantage and Strategy – The Ethiopians had better knowledge of the terrain and effectively used it to their advantage. They cut off Italian supply lines, executed well-coordinated attacks, and surrounded the enemy, leading to a decisive victory.

This victory secured Ethiopia’s independence, making it the only African nation to resist European colonization during the Scramble for Africa.

Source: ChatGPT


በአካል ጉዳቱ ምክንያት መማር አትችልም ተብሎ የነበረው ቢንያም ልዩ ተሸላሚ ሆኖ በድል አጠናቋል።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


ነፃ የትራንስፖርት አገልግሎት

ኩላሊት ዲያሌሲስ ለሚያረጉ ሰዋች ከቤት ወደ ሀኪም ቤት ነፃ የትራንስፖርት አገልግሎት እሰጣለሁ 0904085582 / 0923087298

ሚኪያስ

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

12k 0 16 9 132

እምዬ ምኒልክ ህዝቡ ጫማ እንዲያደርግ በአዋጅ ያስነገሩ ምርጥ መሪ ናቸው።

እምዬ ምኒልክ የመጀመሪያዎቹን ዘመናዊ ትምህርት ቤቶች እና ሆስፒታሎች አስገቡ።

The Battle of Adwa was a landmark event in African and world history, fought on March 1, 1896, between the Ethiopian Empire, led by Emperor Menelik II, and the Kingdom of Italy.

It was a decisive victory for Ethiopia and is celebrated as a symbol of African resistance to colonialism.

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


ከ3,700 በላይ ሠራተኞች ከሥራ ተሰናበቱ

በአፋር ክልል ዱላሳ ወረዳ የሚገኘው ከሰም የስኳር ፋብሪካ፣ በክልሉ እየተከሰተ ባለው ለወራት የቀጠለ ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰበት ይፋ ባደረገ በወሩ፣ ከ3,700 በላይ ሠራተኞቹን ከሥራ ማሰናበቱ ታወቀ። 

Ethiopian Reporter

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቁጥጥሩን ጠበቅ አድርጓል

ከየካቲት 17 ጀምሮ ከንግድ ባንክ ስራ አስኪያጅ በተላከው ደብዳቤ መሰረት የባንኩ ቴለሮች/ገንዘብ ከፋዮች/ የባንኩን ደንበኞች ተቀማጭ ቀሪ ገንዘብ መጠን ማየት እንደማይችሉ ምንጮች ገልጸዋል።

የደንበኞችን ቀሪ ሂሳብ ማየት የሚችሉት ከፍተኛ ማኔጅሮች ብቻ ናቸው።

ባንኩ ይህን እርምጃ የወሰደው እየተንሰራፋ የሄደውን የገንዘብ ማጭበርበር ለከት ለማስያዝ እንደሆነ ተጠቁሟል።

Ethiopian banking information

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

20 last posts shown.