የ4 ዓመት ከ10 ወር እድሜ ያላት ህጻን ልጅ ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመው የ72 አመት አዛውንት በ12 ዓመት ፅኑ እስራት መቀጣቱን የቦሌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ ገለጸ።
አቶ ተስፋዬ ደመቀ የተባሉ የ72 ዓመት እድሜ ባለ ፀጋ ነሐሴ 14 ቀን 2016 ዓ/ም በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ቦታው ቦሌ ቡልቡላ ዶክተሮች ሠፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከቀኑ 5:00 ሠዓት ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀሉን ፈፅመዋል።
የ4 ዓመት ከ10 ወር እድሜ ያላት ህጻን በአካባቢው እየተጫወተች ሳለ የኢትዮ ቴሌኮም ታወር ጥበቃ ሠራተኛ የሆኑት አቶ ተስፋዬ ደመቀ ህፃኗን ነይ እንጫወት በማለት የድርጅቱ የጥበቃ ሠራተኞች የሚያድሩበት ማረፊያ ውስጥ በማስገባት የአስገድዶ መድፈር ወንጀሉን ሲፈጽሙባት የአካባቢው ህብረተሰብ ደርሶባቸው ለፖሊስ በደረጉት ጥሪ ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ጥር 21 ቀን 2017 ዓ/ም በዋለው ችሎት ተከሳሽን ያርማል ሌሎች ወንጀል ፈጻሚዎችን ያስጠነቅቃል በማለት በ12 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ የጥፋተኝነት ውሳኔ አስተላልፎባቸዋል።
ወላጆች ወይም አሰዳጊዎች ህጻናት ልጆቻቸው የት እና ከማን ጋር እንደሚውሉ በቂ ቁጥጥር ማድረግ እንዳለባቸው የተገለፀ ሲሆን በህፃናት ላይ የሚደርሱ የአስገድዶ መደፈር ወንጀሎችን ለመከላከል ፖሊስ ከሚያከናውነው የቅድመ ወንጀል መከላከል እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ባሻገር አጠራጣሪ ነገሮችን ሲመለከት ህብረተሰቡ ጥቆማ የመስጠት ተግባሩን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የአዲስ አበባ ፖሊስ መልዕክቱን ያስተላልፋል።
@Ethiopian_Digital_Library@Ethiopian_Digital_Library