Posts filter


ተቃዋሚዎች ከስልጣን የተወገዱትን ጠቅላይ ሚኒስትር ቤት አወደሙ

በባንግላዲሽ የሚገኙ ተቃዋሚዎች ከስልጣን የተወገዱት የጠቅላይ ሚኒስትር ሼክ ሃሲና የቀድሞ ቤተሰብ መኖሪያ ቤትን እና ሌሎች የፓርቲያቸውን አባላትን ቤት አወደሙ።
ብጥብጡ የተቀሰቀሰው ሃሲና ባለፈው አመት በተማሪዎች የተመራ ተቃውሞ ከስልጣን ከተባረሩበት ጊዜ አንስቶ በስደት ላይ ከነበሩበት ህንድ በማህበራዊ ድረ-ገጾች መልዕክት ማስተላለፋቸውን ተከትሎ ነው።

ባንግላዲሽን ለ20 ዓመታት የመሩት የ77 ዓመቷ ሃሲና መንግስታቸው ያለ ርህራሄ በተቃዋሚዎች ላይ ጨካኝ እንደነበረ ይነገራል ፡፡ለሀገሪው ሰውም ቢሆን ፈላጭ ቆራጭ ተደርገው ይታዩ ነበር።

ተቃዋሚዎች ትላንት ዕሮብ ምሽት ላይ፣ የባንግላዲሽ መስራች ፕሬዝዳንት የሆኑትን የሃሲናን አባት ሼክ ሙጂቡር ራህማንን ቤት በኤካቫተር አፈራረሰዋል ።




በኤሌክትሮኒክ የነዳጅ ግዥ ስርአት ውስጥ ሁሉም ባንኮች ሊካተቱ መሆኑ ተገለጸ

በነዳጅ ሽያጭ እየተሳተፉ የሚገኙት ቴሌ ብር፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና አንድ የግል ባንክ ብቻ የነበሩ ሲሆን አሁን ግን መንግስት ሌሎች የፋይናንስ ተቋማት መሳተፍ እንዲችሉ የወሰነ መሆኑ ታውቋል።

የነዳጅ ገበያውን ለማዘመን እና ህገወጥ አሰራርን ለማስቀረት በማሰብ መንግስት የነዳጅ ሽያጭ በሞባይል የክፍያ ስርአት ብቻ እንዲከናወን ወስኖ እየተተገበረ እንደሚገኝ ይታወሳል።

በዚህም ዘመናዊውን የግዥ መተግበሪያ/አፕ ያበለፀገው ኩባንያ ሌሎች ባንኮችን ለማካተት እየሰራ ሲሆን ባንኮቹ ግን ከመቼ ጀምሮ ወደ ስርአቱ ይገባሉ የሚለው አለመታወቁን ነው የተገለጸው ።


መሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ለኢትዮጵያ ሰላም እንዲጸለይ አወጀች

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ባሉት ቀጣናዎች፣ ክልሎች እና አጥቢያዎች በሙሉ
የኢትዮጵያን ሰላም አስመልክቶ ከየካቲት 1 ጀምሮ እስከ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በጌታ ፊት ጸሎት እንዲደረግ በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር መሪዎች ጉባኤ ተወስኗል::


የአሜሪካው የስለላ ድርጅት ሲአይኤ ሁሉንም ሰራተኞቹን ሊያሰናብት ነው

ሲአይኤ የስራ መልቀቂያ ለሚያስገቡ ሰራተኞቹ የስምንት ወራት ደመወዝ እከፍላለሁ ብሏል።

ሲአይኤ በአሜሪካ ህግን ተከትለው ከማይፈጸሙ ጥፋቶች ጀርባ እጁ አለበት የሚል ቅሬታ ቀርቦበታል።


በስዊድን በመሳሪያ ጥቃት አስረ አንድ ሰዎች ተገደሉ

በስዊድን አንድ መሳሪያ የታጠቀ ግለሰብ በፈጸመው ጥቃት እራሱን ጨምሮ 11 ሰዎች ተገደሉ። በጥቃቱ 5 ሰዎችም ክፉኛ ቆስለዋል።

ጥቃቱ የተፈጸመው በስዊድን ዋና ከተማ ስቶክሆልም በስተምዕራብ በሚገኝ አንድ የወጣቶች ትምህርት ቤት ነው። ትምህርትቤቱ ለወጣት ስደተኞች የቴክኒክና ሙያ እንዲሁም የስዊድሽ ቋንቋ ትምህርቶች የሚሰጥበት ሲሆን የተገደሉትም ስደተኞች ሳይሆኑ እንዳልቀረ ታውቋል።




ትራምፕ አሜሪካ ጋዛን እንድታስተዳድር ያቀርቡትን ጥያቄ የሙስሊም ሀገራት መሪዎች አወገዙ

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በትላንትናው ዕለት ከእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታኒያሁ ጋር በነበረው ውይይት አሜሪካ የፍልስጤም ግዛት የሆነቸውን ጋዛን እንድታስተዳድር ጠይቋል።

የሳዑዲ ቱርክ ጆርዳንና ግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ይህ ተግባር የፍልስጤምን ልዑላዊነት የሚጥስ በመሆኑ በፍፁም ተቀባይነት የለውም ብለዋል።

ሳዑዲ አረቢያ በይፋ ባወጣችው መግለጫ ፍልስጤማውያን በሀገራቸው ተከብረው እንዲኖሩ ሙሉ ድጋፍ እንደምታደርግ በመግለፅ ትራንፕ የተናገረው ሀሳብ በፅኑ እንደምታወግዝም ገልፃለች።


የምስራቅ ወለጋ አባገዳዎች የሰላም ጥሪ አቀረቡ

የምሥራቅ ወለጋ ዞን የአባዳዎች ሕብረት ሰብሳቢ አባገዳ ደሳለኝ ፈይሳ ውስብስብ እየሆነ የመጣውን የሰላም እጦት ችግር ለመፍታት ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ ሸማቂዎችና መንግሥት የሕዝቡን የሰላም ጥያቄ በመቀበል ወደ እርቅ መምጣት እንደለባቸው አመልክተዋል።

ከዚህ ቀደም ተጀመሩ የተባሉ ድርድሮችም በተለያዩ ቦታዎች የተሟላ ሰላም ባለመኖሩ ለተፈጠሩ ለችግሮች ዘላቂ መፍትሄ ያመጣል ተብሎ እምነት ተጥሎበት እንደነበር በማንሳት አሁንም ለሕዝቡ ሰላም ቅድሚያ በመስጠት ሁለቱም አካላት ድርድር በመቀመጥ ይሄን ችግር መፍታት አለባቸው ሲሉ መናገራቸውን ዶቼቬሌ ዘግቧል።


ቻይና ለአሜሪካ ርምጃ የመልስ ምት ሰጠች

በአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በምርቶቿ ላይ ታሪፍ የተጣለባት ቻይና የአጸፋ እርምጃ መውሰድ መጀመሯን አስታውቃለች።

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በቻይና ምርቶች ላይ ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ የ10 በመቶ ታሪፍ መጣሉን አስታቋል።

ይህንን ተከትሎም ቻይና ከአሜሪካ ወደ ሀገሯ የሚገቡ የኃይል ምርተች ላይ የ15 በመቶ ታሪፍ እንደምትጥል አስታውቃለች።

በተጨማሪም ቻይና በአሜሪካው ጎግል ኩባንያ ላይ በዛሬው እለት ተዓማኒነት ምርመራ እንደምትጀምርም አስታውቃለች።
የቻይና የንግድ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፤ በአሜሪካ የክሰል ድንጋይ እና ፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ ላይ የ15 በመቶ ታሪፍ እንደሚጣል አስታውቋል።


በኦሮሚያ ክልል ጉጆ ዞን በደረሰ የአፈር መደርመስ አደጋ የ8 ሰዎች ሕይወት አለፈ

በጉጂ ዞን ሳባ ቦሩ ወረዳ በደረሰ የአፈር መደርመስ አደጋ በባሕላዊ መንገድ ማዕድን በማውጣት ላይ የነበሩ 8 ሰዎች ሕይወት አልፏል፡፡

አደጋው በትናንናው ዕለት 9 ሰዓት ላይ የደረሰ ሲሆን፤ በባሕላዊ መንገድ ማዕድን በማውጣት ሥራ በተሰማሩ ዜጎች ላይ መድረሱን የወረዳው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡

በአደጋው ሕይወታቸውን ያጡ ሰዎችን አስከሬን ከተደረመሰው አፈር ውስጥ የማውጣት ሥራ መከናወኑም ተገልጿል፡፡




ኤም-23 የተነጣል ተኩስ አቁም አወጀ

በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጉ የአማፂዎች ትብብር ቡድን ከዛሬ ማክሰኞ፣ጥር 27/2017 ዓ.ም የሚጀምር የሰብዓዊ የተኩስ አቁም አውጇል።

በሩዋንዳ እንደሚደገፍ የሚነገረውን ኤም-23 አማፂ ያቀፈው ቡድኑ በምስራቃዊ የአገሪቱ ክፍል ግዛቶችን መቆጣጠሩን ተከትሎ የተኩስ አቁም ለሰብዓዊነት ሲል ማወጁን ገልፆል።


በሞት የተለዩ ተጠርጣሪዎችን ንብረት እንዲወረስ የሚያደርገው አዋጅ ሊተገበር ነው


በአዲሱ የንብረት ማስመለስ አዋጅ  በጥፋተኝነት ላይ ያልተመሰረተ የንብረት ማስመለስ አዋጁ እንደሚያካትት ተገልጿል።  ይህም ተጠርጣሪው በሞት ቢለይ ወይም ከሀገር የሸሸ ቢሆን ንብረቱ እንዲሁ የሚቀር ሳይሆን እንዲታገድና ጉዳዩ ተጣርቶ ግለሰቡ በሌለበት እንዲወረስ ይደረጋል ሲል ፍትህ ሚኒስትር አስታውቋል።


በሩሲያ መዲና በደረሰ ፍንዳታ የሰው ህይወት አለፈ

በሩሲያ ዋና ከተማ ሞስኮ በሚገኝ ቅንጡ የመኖሪያ ሕንጻ ላይ ላይ በደረሰ ፍንዳታ አንድ ሰው ሲሞት አራት ሰዎች መቁሰላቸው ተገልጿል፡፡

ፍንዳታው ከክሬምሊን በሰባት ማይል ርቀት ላይ በሚገኘውና በሩሲያ ዋና ከተማ ሰሜናዊ ምዕራብ በሚገኘውን አሌዬ ፓሩሳ (ስካርሌት ሴልስ) ቅንጡ የመኖሪያ ሕንጻ ላይ ሲሆን፤ "በአደጋው ከተጎዱት ውስጥ የዩክሬን ተገንጣዮች ይገኙበታል" ሲሉ የሩሲያ የዜና ወኪሎች ዘግበዋል።

የፍንዳታው መንስኤ ምን እንደሆነ እስከአሁን ባይገለጽም፤ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በከባድ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ተነግሯል።

ይህንንም ተከትሎ የሩሲያ ባለስልጣናት የወንጀል ምርመራ መጀመራቸው ነው የተዘገበው።


ቢዮንሴ የመጀመሪያዋ ጥቁር ምርጥ የሃገረሰብ ሙዚቃ አልበም አሸናፊ ሆነች

አሜሪካዊቷ አቀንቃኝ ቢዮንሴ ጂሴል ኖልስ በግራሚ ሽልማት የ21ኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያዋ ጥቁር ምርጥ የሃገረሰብ ሙዚቃ አልበም አሸናፊ ሆናለች።

ቢዮንሴ በ67ኛው ግራሚ ሽልማት በምርጥ የሃገረሰብ ሙዚቃ አልበም ዘርፍ አሸናፊ መሆን ችላለች።

በዚህም ከ1975 በኋላ በክፍለ ዘመኑ የመጀመሪያዋ ጥቁር የዘርፉ አሸናፊ ለመሆን በመብቃት ታሪክ ሰርታለች።

አቀንቃኟ “ካው ቦይ ካርተር“ በሚለው የሃገረሰብ ሙዚቃ አልበሟ ነው አሸናፊ መሆን የቻለችው።




ቻይና በትራምፕ የተጣለውን ታሪፍ አወገዘች


የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከካናዳ እና ከሜክሲኮ በሚገቡ ምርቶች ላይ የ25% ታሪፍ መጣላቸው ይታወቃል።

የቻይና መንግስት በፕሬዝዳንት ትራምፕ የተጣለውን ታሪፍ በጽኑ ያወገዘ ሲሆን፤ ቤጂንግ ትራምፕ የሚያቀርቡትን ቤጂንግ ወደ አሜሪካ የሚፈሰውን ገዳይ የሆነውን ኦፒዮይድን መግታት ዙሪያ እና እየከፋ የንግድ ግጭት እንዳይፈጠር ለውይይት በሯን ከፍት መሆኑን አስታውቃለች።

 ቻይና ህጋዊ መብቷን እንዲሁም ጥቅሟን ለማስጠበቅ አጸፋዊ እርምጃ እንደሚኖራትም አሳስባለች።


በአፋር ክልል በደረሰው የድሮን ጥቃት የ8 ሰዎች ሕይወት ማለፋን የክልሉ ፖሊስ አስታወቀ

በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት አውሲ ረሲ ዞን፤ ኤሊዳር ወረዳ፣ ሲያራ ቀበሌ በጅቡቲ ድንበር አቅራቢያ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት 8 ሰዎች መገደላቸውን የክልሉ ፖሊስ ለአሐዱ አስታውቋል።

የአፋር ክልል ፖሊስ የማህበረሰብ አቀፍ ጥናትና ምርምር ዳይሬክተር ዋና ሳጅን ዋሱ ናስር በጥቃቱ የ8 ሰዎች ሕይወት ማለፋን የገለጹ ሲሆን፤ በተጨማሪም ሌሎች አራት ሰዎች መቁሰላቸውን ተናግረዋል።

የጂቡቲ መከላከያ ሚኒስቴር አካሄድኩት ባለው በዚህ የድሮን ጥቃት ስምንት አሸባሪዎች ገድያለሁ ብሏል። ይህ ጥቃት ሲፈጸም በጂቡቲ ንጹሐን ዜጎች ላይ አላስፈላጊ ጉዳት መድረሱን አምኖ ነገር ግን ጉዳቱ ምን እንደሆነ በዝርዝር አልገለጸም።

በጉዳዩ ዙሪያ በፌደራል መንግሥት በኩል እስከአሁን ምንም የተባለ ነገር የለም።


የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በቀጣይ በሚያካሔደው የአመራር ምርጫ ሕዝበ ሙስሊሙ በንቃት እንዲሳተፍ ጠቅላይ ምክር ቤቱ ጥሪ አቀረበ

ጠቅላይ ምክር ቤቱ ይህን ጥሪ ያቀረበው በዛሬው ዕለት ካከናወነው ሦስተኛ ዓመት አንደኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባዔ በኋላ ባወጣው የአቋም መግለጫ ነው።

ዛሬ ቅዳሜ ጥር 24/2017 ባካሔደው አስቸኳይ ስብሰባው በገለልተኛ የባለሙያዎች ቡድን ተዘጋጅቷል ያለውን የምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያና የምርጫ ማስፈፀሚያ መመሪያ ሠነድን መርምሮ በሙሉ ድምጽ ማጽደቁንም አሳውቋል።

20 last posts shown.