TGStat
TGStat
Type to search
Advanced channel search
English
Site language
Russian
English
Uzbek
Sign In
Catalog
Channels and groups catalog
Search for channels
Add a channel/group
Ratings
Rating of channels
Rating of groups
Posts rating
Ratings of brands and people
Analytics
Search by posts
Telegram monitoring
TGAlertsBot
Monitoring of keywords in channels and chats
Subscribe
ad
SearcheeBot
Your guide in the world of telegram channels
Start bot
ad
Telegram Analytics
Subscribe to stay informed about TGStat news.
Read channel
ad
TGStat Bot
Bot to get channel statistics without leaving Telegram
Start bot
ad
Statistics
Favorites
Natinael Mekonnen
@NatinaelMekonnen21
Channel's geo and language:
Ethiopia, Amharic
Category:
Shock content
ይህ ቻናል ቴሌግራሜ hacked በተደረገበት ሳት ለግዝያዊነት የከፈትኩት ቻናል ነው ለችግር ጊዜ ይጠቅማል ተቀላቀሉ
በቀጥታ መረጃዎችን ለመስጠት ከፈለጉ
@NatnaelMekonnen7
በማለት መረጃዎችን ይላኩልን
I blog about marketing and sales
Buy ads: https://telega.io/c/NatinaelMekonnen21
Related channels
|
Similar channels
Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Shock content
Statistics
Favorites
Is this your channel?
Confirm
Канал в реестре блогеров РКН?
Confirm
Channel history
Posts filter
Select month
February 2025
January 2025
December 2024
November 2024
October 2024
September 2024
August 2024
July 2024
June 2024
May 2024
April 2024
March 2024
February 2024
January 2024
December 2023
November 2023
October 2023
September 2023
August 2023
July 2023
June 2023
May 2023
April 2023
March 2023
February 2023
January 2023
December 2022
November 2022
October 2022
September 2022
August 2022
July 2022
June 2022
May 2022
Hide deleted
Hide forwards
Natinael Mekonnen
21 Feb, 20:51
Open in Telegram
Share
Report
Prev
Next
ኢ-ፓስፖርቱ ለዜጎች ጥራት እና ግልፅነት የተላበሰ አገልግሎት ለመስጠት ያግዛል፡- ፕሬዚዳንት ታየ አፅቀ ሥላሴ
ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ በመጠቀም በኢትዮጵያ የተመረተው እና ዛሬ ይፋ የተደረገው ኢ-ፓስፖርት ለዜጎች ጥራት እና ግልፅነት የተላበሰ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያግዝ ፕሬዚዳንት ታየ አፅቀ ሥላሴ ገለጹ።
አዲሱ ኢ-ፓስፖርት ይፋ በተደረገበት ወቅት ፕሬዚደንት ታየ እንደገለፁት፤ የኢትዮጵያ ፓስፖርቶች እና የጉዞ ሰነዶች ዘመኑን የዋጁ እና የተራቀቁ የደህንነት ባህሪያት እንዲኖራቸው መደረጉ ትልቅ እመርታ ነው።
የኤሌክትሮኒክ ፓስፖርት ተግባራዊ መደረጉ የሀገርን ገጽታ ከመገንባት ባሻገር ለዜጎች የተሰጠውን ዋጋ የሚገልፅ ነው ብለዋል።
ፓስፖርቱ ማንኛውንም አይነት ማጭበርበር ለመግታት የማይተካ ሚና እንደሚኖረው ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል።
ዘመናዊ ሰነዶች የሰዎችን እንቅስቃሴ ከማፋጠን ባሻገር ንግድን ለማሳለጥና ህጋዊ የስራ ዕድል ለማግኘት አስፈላጊ መሆናቸውንም አክለዋል።
ኢ-ፖስፖርቱ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ እና በቶፓን ሴኪዩሪቲ ኢትዮጵያ አክሲዮን ማህበር አማካኝነት በሀገር ውስጥ መመረቱ በመድረኩ ላይ መገለጹን ኢዜአ ዘግቧል።
በመርኃ ግብሩ ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፣ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ቴዎድሮስ ምሕረት፣ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ፣የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
409
0
0
2
Natinael Mekonnen
21 Feb, 20:51
Open in Telegram
Share
Report
Prev
Next
Ethiopiaዬ ሰላምሽ ይብዛ! ከጫካ ወደ ሰላማዊ ትግል የመጡት የቀድሞ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት አመራሮች ሹመት ተሰጠ::
Good News : የኦሮሚያ ክልል የመንግስትን የሰላም ጥሪ ለተቀበሉ የቀድሞ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት አመራሮች ሹመት ሰጥቷል፡፡
በዚህ መሰረትም፡-
1. አቶ ያደሳ ነጋሳ
በቢሮ ሃላፊ ማዕረግ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የሰላምና ደህንነት ጉዳዮች አማካሪ
2. አቶ ኦሮሚያ ረቡማ
የኦሮሚያ ክልል ዓቃቤ ሕግ ምክትል ሃላፊ
3. አቶ ቶሌራ ረጋሳ
የኦሮሚያ ክልል ጸጥታና አስተዳደር ቢሮ ምክትል ሃላፊ
ሁሉም ቢተሳሰብ፥
ሁሉም ቀና ቢያስብ፥
. . .
መተሳሰብ ቢኖር፥
ሁሉም ቢተባበር፥
የት ይደረስ ነበር?
394
0
0
Natinael Mekonnen
21 Feb, 13:19
Open in Telegram
Share
Report
Prev
Next
አዲስ የኤሌክትሮኒክስ ፓስፖርትን ይፋ ተደረገ
የኢሚግሬሽን እና የዜግነት አገልግሎት አዲስ የኤሌክትሮኒክስ ፓስፖርትን ይፋ አደረገ ፡፡
አዲሱ ፓስፖርት ደህንነቱ የተጠበቀ እና በሀገር ዉስጥ የሚመረት ነዉ ተብሏል፡፡
ፓስፖርቱ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኘዉ የለሚ ኢንደስትሪያል ፓርክ የሚመረት ሲሆን ጥራቱ አለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ስለመሆኑም ተነግሯል፡፡
በፓስፖርቱ ገፆች ላይ የሀገር ገፅታ የሚያስተዋዉቁ የኢትዮጵያ መለያዎች እንደተካተቱበትም ለማወቅ ተችሏል፡፡
805
0
1
2
Natinael Mekonnen
21 Feb, 13:19
Open in Telegram
Share
Report
Alert News ‼️
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር፣ የትግራይ ጸጥታ ኃይል አባላት በደቡባዊ ምሥራቅ ዞን ሰሓርቲ ወረዳ አዲስ ዓለም በተባለ ቀበሌ ገበሬ ማኅበር በነዋሪዎች ላይ ጥቃት አድርሰዋል በማለት ዛሬ ባወጣው መግለጫ ድርጊቱን አውግዟል።
ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ የተወሰኑ የክልሉ ጸጥታ ኃይል አመራሮች የጊዚያዊ አስተዳደሩን መዋቅሮች ለማፍረስ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ናቸው በማለት ከሷል። ጸጥታ ኃይሉ የአንድ ቡድን የሥልጣን መወጣጫ መሳሪያ ሊኾን እንደማይችል የገለጠው ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ ኹኔታዎች በዚህ ከቀጠሉ ክልሉ ከባድ ቀውስ ሊገባ ይችላል በማለት አስጠንቅቋል።
ጊዜያዊ አስተዳደሩ ይህን ያለው፣ ትናንት የተወሰኑ የጸጥታ ኃይል አባላት የቀበሌ አስተዳደሩ ማኅተሙን እንዲያስረክቡ ባስገደዱበትና፣ በዚሁ ወቅት ድርጊቱን በተቃወሙ ነዋሪዎች ላይ የኃይል ርምጃ በወሰዱበት ወቅት እንደኾነ ተገልጧል ።
783
0
0
Natinael Mekonnen
20 Feb, 16:39
Open in Telegram
Share
Report
“ዘለንስኪ ትሁትና ውጤታማ ኮሜዲያን ነው” ትራንፕ 😂
“ዜለንስኪ ጥሩ የነበረበት ብቸኛው ነገር ባይደንን ማታለል ብቻ ነው” ብለዋል ትራምፕ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሊድሚር ዘለንስኪን “ትሁትና ውጤታማ ኮሜዲያን ነው” ሲሉ ወርፈዋል።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትሩዝ በተባለው የማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ የዩክሬኑን ፕሬዝዳንት ቮሊድሚር ዘለንስኪን “ያለ ምርጫ የተቀመጠ አምባገነን ነው” ብለዋል።
ትራምፕ “ትሁቱና ውጤታማ ኮሜዲያን ዘለንስኪ አሜሪካን 350 ቢሊየን ዶላር በማስውጣት መጀመር ያልነበረባቸው እና የማያሸንፉት ጦርነት ውስጥ ገብተዋል” ብለዋል።
“ዩክሬን ጦርነቱን ያለ አሜሪካ እና ትራምፕ በፍፁም መቋቋም አትችልም” ሲሉም ገልጸዋል።
ዜለንስኪ ከላክንለት ገንዘብ ግማሹ “የጠፋ” መሆኑን አምኗል ያሉት ትራምፕ “ምርጫ ለማድረግ ፈቃደኛ አይደለም፣ በዩክሬን የሕዝብ ዘንድ ያለው ተቀባይነት በጣም ዝቅተኛ ነው” ብለዋል።
“ዜለንስኪ ጥሩ የነበረበት ብቸኛው ነገር ባይደንን ማታለል ብቻ ነበር” ሲሉም ገልጸዋል።
“ያለ ምርጫ የተቀመጠ አምባገነን ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ በፍጥነት መንቀሳቀስ ይኖርበታል፤ ካልሆነ ግን የሚያተርፈው ሀገር አይኖርም” ብለዋል ትራምፕ።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አክውም “ዩክሬንን እወዳለሁ፣ ነገር ግን ዘለንስኪ አስከፊ ስራ ሰርቷል፣ ሚሊዮኖችም ያለምክንያት ሞተዋል እየሞቱም ነው” ሲሉ ገልጸዋል።
የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሊድሚር ዘለንስኪ “ዶናልድ ትራምፕ የሀሰት መረጃ ውስጥ እየኖሩ ወይንም በሀሰት መረጃ እየተነዱ ነው” ብለዋል።
1.1k
0
0
7
Natinael Mekonnen
20 Feb, 16:39
Open in Telegram
Share
Report
የመሳይ መኮንን (ቦምብነሽ) ቦምቦች 😄
መሳይ መኮንን (ቦምብነሽ) አዲስ አበባ ላይ “አራት ቦምብ ፈነዳ” ብሎ ዘግቧል።😄 እንደዘገባው ከሆነ የነመሳይ ምናባዊ ቦምቦች የፈነዱት አንዱ አራት ኪሎ አካባቢ ነው። ሌላው ደግሞ ፒያሳ የከንቲባዋ office አካባቢ ነው 😄 አንዱ ደግሞ ፌደራል ፖሊስ ሲሆን የመጨረሻው ደግሞ ቦሌ ኤርፖርት መግቢያ በሩ ጋር ነው 😄 (የነመሳይ ቦምቦች የፈነዱት የኮሪደር ልማቱን ተከትለው ይመስላል 😄)
የነመሳይ ቦምቦች ከአለም ለየት የሚያደርጋቸው አራቱንም ቦምብ መሀል ከተማ ውስጥ ሲያፈነዱ የአዲስ አበባ ሠው ምንም አለመስማቱ ነው 😄 በርግጥ ከውስጥ አዋቂ ምንጮች እንደሰማነው ቦምቡን ያፈነዱት በሳቅ ነው ተብሏል 😄
ቦምቡ ፍቅርሽ ሲፈነዳ
ላንቺ ብዬ ገባሁ ዕዳ 😂
አይ ቦምብነሽ
1.1k
0
0
3
Natinael Mekonnen
19 Feb, 12:30
Open in Telegram
Share
Report
ወይዘሮ ኬሪያ ኤብራሂም ‹‹የታክሲ ሰልፍ ጠብቄ እየሄድኩ ነው›› በማለት ተናገሩ፡፡ የቀድሞው የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤ የሆኑት ወይዘሮ ኬሪያ በአሁኑ ወቅት ከቤተሰባቸው ጋር በአዲስ አበባ እንደሚኖሩ ገልፀው መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ውስጥ እየሰሩ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ከቪኦኤ ትግርኛ ቋንቋ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ‹‹እኔ ስልጣን ላይ በነበርኩበት ጊዜ አጃቢና ሹፌሮች ነበሩኝ፡፡ አሁን ግን የታክሲ ሰልፍ ጠብቄ እየሄድኩ እገኛለሁ፡፡ ምንም ችግር የለውም፡፡ ህይወት ይቀጥላል›› ብለዋል፡፡
ስልጣን መልቀቅ የህይወት መጨረሻና ሞት ማለት እንዳልሆነም አስረድተዋል፡፡ ‹‹በረሀ ወርደን መስዋእትነት የከፈልነው ለስልጣን ነበር ወይ?›› የሚል ጥያቄ ያነሱት ወይዘሮ ኬርያ ስልጣን መያዝ የመጨረሻ ግብ መሆን እንደሌለበት አሳስበው እሳቸው ግን እንደማንኛውም ሰው በህዝብ ጋር እየኖሩ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ወይዘሮ ኬርያ ከፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤነታቸው በፈቃዳቸው ከለቀቁ በኋላ በጦርነቱ ወቅት ታስረው የነበረ ሲሆን ከእስር ከተፈቱ በኋላ ከህወሀት መባረራቸው ይታወሳል፡፡
1.4k
0
0
7
Natinael Mekonnen
19 Feb, 12:30
Open in Telegram
Share
Report
Good Morning #Ethiopiaዬ : ኢትዮጵያ እና ሱማሊያ አንካራ ውስጥ ያካሄዱትን የመጀመሪያ ዙር የቴክኒክ ድርድር ትናንት አጠናቀዋል።
ኹለቱ ወገኖች፣ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይና ፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሐመድ በአንካራው ስምምነት ያስቀመጡትን ራዕይ ወደ ተግባር ለመለወጥ ቁርጠኛ መኾናቸውንና ኹለቱን አገራት ተጠቃሚ ለሚያደርግ ዘላቂ ልማት መሠረት መጣላቸውን በጋራ ባወጡት መግለጫ ገልጸዋል።
ኹለቱ ወገኖች ለኹለተኛው ዙር የቴክኒክ ድርድር በመጋቢት ወር ለመገናኘት ከስምምነት ላይ መድረሳቸውንም ጠቅሰዋል።
በቴክኒክ ድርድሩ የኢትዮጵያን ልዑካን ቡድን የመሩት ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ ሲኾኑ፣ የሱማሊያን ልዑካን ቡድን የመሩት ደሞ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ደኤታ ዓሊ ኦማር ናቸው።
1.3k
0
0
2
Natinael Mekonnen
18 Feb, 18:01
Open in Telegram
Share
Report
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሥራ ዘመን ለአንድ አመት ተራዘመ።
ኮሚሽኑ ዛሬ የሦስት አመታት ሪፓርቱን ለፓርላማ ያቀረበ ሲሆን፣ የፓርላማ አባላት በሪፓርቱ ላይ የተለዩዩ ጥያቄዎችንና አስተየቶችን ሰጥተዋል።
በመጨረሻም ሦስት አመቱን የካቲት 14 ቀን በመድፈን የሥራ ዘመኑ ይጠናቀቅ የነበረው ኮሚሽኑ፣ በፓርላማው ቋሚ ኮሚቴ የአንድ አመት ተጨማሪ ጊዜ ተሰጥቶታል።
በቋሚ ኮሚቴው የተሰጠው የአንድ አመት ተጨማሪ ጊዜ ውሳኔው የቀረበበት ሦስት የተቃውሞ ድምፅ ብቻ ነው።
በተለይ የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ስላለው ሁኔታ የፓርላማ አባላት ያነሷቸውን ነጥቦችና የተሰጡ ምላሾችን በተመለከተ ተጨማሪ ይኖረናል።
1.5k
0
0
7
Natinael Mekonnen
18 Feb, 18:01
Open in Telegram
Share
Report
ልዩ ዜና ትግራይ
“ በሃይማኖት አባቶች የተጀመረው የሽምግል እና የእርቅ እንዲሁም የካቲት 11 በጋራ የማክበር እንቅስቃሴ አልተሳካም አሉ “ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ።
ፕሬዜዳንቱ ለእርቅ እና ሽምግልና አለመሳካት “ ቡድን “ ሲሉ የጠሩትን አካል ተጠያቂ አድርገዋል።
ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ባወጡት መግለጫ “ መንግስት የማያውቀው ርችት በመተኮስ የሚያጋጥም ችግር ካለ ተጠያቂው ቡድኑ ነው “ ብለዋል።
አላስፈላጊ የአመፅ እንቅስቃሴዎች እየታዩ መሆናቸው የገለፁት ፕሬዜዳንቱ ፤ ህዝቡ አከባቢውን በልዩ ሁኔታ በመጠበቅ በዓሉ እንዲያከብር አሳስበዋል።
ከቀናት በፊት ለእርቅና ሽምግልና ፍቃደኛ መሆናቸው በትግራይ የሃይማኖት አባቶች መግለጫ የተሰጠባቸው ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳና የህወሓት ሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በትናንቱ የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እጅ ለእጅ ሲጨባበጡ የሚያሳይ ፎቶ መለቀቁ ብዙዎች አስደስቶ ነበር።
1.4k
0
0
2
Natinael Mekonnen
8 Feb, 21:36
Open in Telegram
Share
Report
ካይሮ በማለት የሚያንቆለጳጵሰው ሃይማኖት አፈወርቅ ከነታጣቂው ተደምስሷል!
እራሱን የአማራ ፋኖ በጎጃም በማለት የሚጠራዉን የጃውሳ ክንፍ ከሚመሩት ታጣቂዎች መካከል አንዱ የነበረው ሃይማኖት በተወሰደበት እርምጃ ተደምስሷል። ሃይማኖት ብቻ ሳይሆን ሲመራው የነበረ ታጣቂ በሙሉ ሙት እና ቁስለኛ መሆኑን የደረሱኝ መረጃዎች ጠቁመዋል። ሃገርን የማፍረስ እድቅ ይዞ የተነሳው ጽንፈኛው ቡድን የሚገባውን እያገኘ ያለ ሲሆን አሁን አሁን ቡድኑ የሰራዊቱን ክንድ መቋቋም እያቃተው እንደሆነም ከየቦታው የሚደርሱኝ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
3.2k
0
0
12
Natinael Mekonnen
8 Feb, 21:36
Open in Telegram
Share
Report
Prev
Next
ኢትዮጵያ በዚህ አመት የማዳበሪያ ግዢ የፈፀመችው ሙሉ በሙሉ ከራሺያ ሲሆን የኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር አ.ማ ዋና ስራ አስፈፃሚ በትናንትናው እለት የጭነት እና የማውረድ ሂደትን ለማሳየት የአርካይቭ ፎቶ መጠቀማቸውን እንደ ማሳያ በማቅረብ ከቅርብ ግዜ ወዲህ የወረደ የፌስቡክ “ትግል” እያደረገ የሚገኘው ጃዋር መሀመድ ግዜው ያለፈበት ማዳበሪያ ለአርሶ አደር ሊከፋፈል ነው የሚል የተዛባ መረጃ ሲያሰራጭ አምሽቷል::
እራሱን የፓለቲካ ስትራቴጂስት አድርጎ የሚያቀርበው እና በብዙዎች እንደ ጥልቅ አሰላሳይ እና የመረጃ ሰው የሚታየው ጀዋር ኢትዮጵያ በዚህ አመት ስላስገባችው ማዳበሪያ ኢ/ር ታከለ በስህተት የለጠፋትን የቆየ ምስል ብቻ እንደ ማስረጃ በማቅረብ ብዙ ትንታኔ እና ከ 6 በላይ ፖስቶችን አጋርቷል::
“ስትራቴጂስቱ “ ጃዋር እውነት ግዜው ያለፈበት ማዳበሪያ ገብቶ ከሆነ በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ ምርመራ በማድረግ እና ማስረጃዎችን በማቅረብ መንግስትን ቢሞግት ተገቢ ይሆን ነበር:: ለማንኛውም ግዜው ያለፈበት ማዳበሪያም የለም የተፈጠረው በተራ ስህተት ምክንያት ብቻ የተፈጠረ ውዥንብር ነው::
1.8k
0
0
1
6
Natinael Mekonnen
7 Feb, 20:20
Open in Telegram
Share
Report
Prev
Next
በቋራ ወረዳ ነብስ ገበያ ቁጥር 1 እና በመተማ ወረዳ ቱመት መንዶካ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች በሰላማዊ መንገድ ለመንግስት እጃቸውን ሰጡ።
ሻለቃ መሪ ይታያል ውዱ ተገኘ በማለት ራሱን እየገራ በመተማ ወረዳ በቱመት-መንዶካ ፣ እና በቋራ ወረዳ ቀጥር 1 እና ነብስ ገበያ 22 ራሱን ሆኖ ሲንቀሳቀስ የነበረ ታጣቂ በሽንፋ ለሚገኘው ጥምር የጸጥታ በሰላም እጃቸውን ሰጥተዋል።
ታጣቂው ሃይሉ 15 ባለመሳሪያ እና 7 ጀሌ ሆነው ለመንግስት በሰላማዊ መንገድ እጅ ሰጥተዋል።
ታጣቂ ሀይሉ የሰላምን መንገድ የመረጥነው የማያዋጣ እና አላማ የሌለው ትግል በመሆኑ ማህበረሰባችን ጋር ተቀላቅለን እንዲሁም ከመንግስት ጎን ሆነን ለአገራችን ሰላምና ልማት የበኩላችን ለመወጣት ነው ብለዋል።
የመተማ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ደሳለኝ ሞገስ በቦታው ተገኝተው እነደተናገሩት ለህዝብ በማሰብ የሰላምን መንገድ መርጣችሁ በሰላም ወደ ማህበረሰባችሁ ሰለተቀላቀላችሁ ስልጡንነታችሁን ያሳያል።
በመንግስት በኩል የተለያዩ የተሃድሶ ስልጠና ወስዳችሁ ከህዝባችሁ እና ከመንግስት ጎን ሆናችሁ የበኩላችሁን እንድትወጡ ያደርጋል ብለዋል።
ዘገባው የመተማ ወረዳ ኮሚዩኒኬሽን ነው።
2.1k
0
0
13
last posts shown.
Show more
7 513
subscribers
Channel statistics
Popular in the channel
የማጨው ነዋሪዎች ፥ የህወሓት ጀነራሎች ያወጁትን መፈንቅለ መንግስት በመቃወም በዛሬው ዕለት ተቃውማቸው በሰላማዊ ሰልፍ ገልፀዋል‼️ በስሙ ሲነገድበትና ከ...
ካይሮ በማለት የሚያንቆለጳጵሰው ሃይማኖት አፈወርቅ ከነታጣቂው ተደምስሷል! እራሱን የአማራ ፋኖ በጎጃም በማለት የሚጠራዉን የጃውሳ ክንፍ ከሚመሩት ታጣቂ...
“ ህዝቡ በመረጣችሁት መንገድ ይታገላችኋል “ - በእነ አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት በምክትል ሊቀ-መንበር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራ ህወሓት ፤ ትና...
ኢትዮጵያ በዚህ አመት የማዳበሪያ ግዢ የፈፀመችው ሙሉ በሙሉ ከራሺያ ሲሆን የኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር አ.ማ ዋና ስራ አስፈፃሚ በትናንትናው እለት የጭነት ...
በቋራ ወረዳ ነብስ ገበያ ቁጥር 1 እና በመተማ ወረዳ ቱመት መንዶካ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች በሰላማዊ መንገድ ለመንግስት እጃቸውን ሰጡ። ሻለቃ ...