Forward from: አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ
#በሥላሴ እናምናለን #ለሥላሴ እንገዛለን #ለሥላሴ እንሰግዳለን ፤ ከነፋስ ከእሳት ፣ ከውኃና ከመሬት ባሕርያት ፈጥረውናልና የቸርነት ባለቤት የኾነው #የቅድስት_ሥላሴ በረከት እንዲያድርብን የአብ ሰላም ፣ የወልድ ፍቅር የመንፈስ ቅዱስ ሃይማኖት በመካከላችሁ ይደር ! የሰላም አምላክ ከእኛ ጋር ይኑር ።
ቅድመ ዓለም በነበረ በአንዱ በእግዚአብሔር አብ እናምናለን እናመልካለን አብን በጌትነት በሚመስለው በሚተካከለው በእግዚአብሔር ወልድ እናምናለን እናመልካለን በዓለም ምሉዕ በሆነው በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ እናምናለን እናመልካለን #ቅድስት_ሥላሴ የአምልኮታችን ማዕከል ናቸውና የሚሠዋው መሥዋዕት የሚታጠነው ዕጣን የሚቀርበው ቁርባን ሁሉ የሚያርገው ወደ #ቅድስት_ሥላሴ_ነው ።
ቅድመ ዓለም በነበረ በአንዱ በእግዚአብሔር አብ እናምናለን እናመልካለን አብን በጌትነት በሚመስለው በሚተካከለው በእግዚአብሔር ወልድ እናምናለን እናመልካለን በዓለም ምሉዕ በሆነው በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ እናምናለን እናመልካለን #ቅድስት_ሥላሴ የአምልኮታችን ማዕከል ናቸውና የሚሠዋው መሥዋዕት የሚታጠነው ዕጣን የሚቀርበው ቁርባን ሁሉ የሚያርገው ወደ #ቅድስት_ሥላሴ_ነው ።