"የኢትዮጵያ ብልጽግና ጉዞ አይቀሬ ነው"
የብልጽግና ፕሬዝዳንት ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በፓርቲው ሁለተኛው ጠቅላላ ጉባኤ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ብልጽግና ሀገር በቀል እሳቤ ነድፎ የመጣ የመጀመሪያው ፓርቲ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የአንድ ፓርቲ ዋና እስኳሉ ሃሳብ እንደሆነ በጉባኤው ላይ የተናገሩት የብልጽግና ፕሬዝዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ ሃሳብ ያለው ፓርቲ ለውጥ መፍጠርም መምራትም ይችላል ብለዋል።
በዘመቻ የጀመርናቸው ስራዎች ባህል መሆን አለባቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ፕሮጀክቶችን ጀምሮ መጨረስ እንዲሁ ባህል ልናደርገው ይገባል ሲሉ ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጵያ የፓርቲዎች ጉባኤ ታሪክ መላው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰብ ተወካይ ኖሮት የሚደረግ ጉባኤ የብልጽግና ፓርቲ ጉባኤ ብቻ ነው ሲሉም ተናግረዋል።
ብልፅግና በኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲ ልምምድ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ሀገር በቀል የሆነ እሳቤ ነድፎ የመጣ ፓርቲ መሆኑንም አመልክተዋል።
ብልፅግና ለኢትዮጵያ ፍቱን መድሀኒቱ መደመር ነው ብሎ ሲመጣ ላለፉት ስድስት አመታት ብልፅግናን መክሰስ እንጂ ማንም አማራጭ ሃሳብ ይዞ አለመምጣቱ የሚያሳዝን ነው ብለዋል።
ይህም ሆኖ በተቀዱ ሃሳቦች ላለፉት በርካታ አመታት የገጠሙንን ችግሮች ስለምናውቅ የኢትዮጵያን ተፎካካሪ ፓርቲዎች አማራጭ ሀገር በቀል ሃሳብ ቢያቀርቡ ብልፅግና ለመማር ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል።
ሃሳብ የነጠፈበት አካባቢ ማፍረስ ቢቀልም መልሶ መገንባት ግን መከራ ይሆናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለዚህም አማራጭ የፖለቲካ ሃሳብ ቢፈጠር ለመማር ዝግጁ ነን ብለዋል።
#prosperity
የብልጽግና ፕሬዝዳንት ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በፓርቲው ሁለተኛው ጠቅላላ ጉባኤ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ብልጽግና ሀገር በቀል እሳቤ ነድፎ የመጣ የመጀመሪያው ፓርቲ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የአንድ ፓርቲ ዋና እስኳሉ ሃሳብ እንደሆነ በጉባኤው ላይ የተናገሩት የብልጽግና ፕሬዝዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ ሃሳብ ያለው ፓርቲ ለውጥ መፍጠርም መምራትም ይችላል ብለዋል።
በዘመቻ የጀመርናቸው ስራዎች ባህል መሆን አለባቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ፕሮጀክቶችን ጀምሮ መጨረስ እንዲሁ ባህል ልናደርገው ይገባል ሲሉ ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጵያ የፓርቲዎች ጉባኤ ታሪክ መላው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰብ ተወካይ ኖሮት የሚደረግ ጉባኤ የብልጽግና ፓርቲ ጉባኤ ብቻ ነው ሲሉም ተናግረዋል።
ብልፅግና በኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲ ልምምድ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ሀገር በቀል የሆነ እሳቤ ነድፎ የመጣ ፓርቲ መሆኑንም አመልክተዋል።
ብልፅግና ለኢትዮጵያ ፍቱን መድሀኒቱ መደመር ነው ብሎ ሲመጣ ላለፉት ስድስት አመታት ብልፅግናን መክሰስ እንጂ ማንም አማራጭ ሃሳብ ይዞ አለመምጣቱ የሚያሳዝን ነው ብለዋል።
ይህም ሆኖ በተቀዱ ሃሳቦች ላለፉት በርካታ አመታት የገጠሙንን ችግሮች ስለምናውቅ የኢትዮጵያን ተፎካካሪ ፓርቲዎች አማራጭ ሀገር በቀል ሃሳብ ቢያቀርቡ ብልፅግና ለመማር ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል።
ሃሳብ የነጠፈበት አካባቢ ማፍረስ ቢቀልም መልሶ መገንባት ግን መከራ ይሆናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለዚህም አማራጭ የፖለቲካ ሃሳብ ቢፈጠር ለመማር ዝግጁ ነን ብለዋል።
#prosperity