ስለ-ሕግ ⚖️ ABOUT-LAW


Channel's geo and language: Ethiopia, English
Category: Law


ABOUT-LAW is a premier e-legal service platform established in October 2020. Whether you need legal advice, legal documents, , or any other legal assistance, we are here to help.
Contact us @AshenafiFisha
Vist our legal database via- @aboutethiopialaw_bot

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, English
Category
Law
Statistics
Posts filter


Essay Competition for Young Researchers in Intellectual Property sponsored by FICPI, the International Federation of Intellectual Property Attorneys. 
 
The Essay Competition is open for authors no older than 35 years of age as of December 31, 2024. ATRIP President may waive the age requirement in certain special situations, in particular in the case of maternity or paternity leave. 
 
Papers may be submitted in French or English. Entries should be submitted to 
admin@atrip.org no later than February 21, 2025. 
 
The authors of the top three placed papers will be announced on the ATRIP website and the papers uploaded to the essays section. There is also the opportunity to publish the papers in the Journal of World Intellectual Property Law or in IIC – International Review of Intellectual Property and Competition Law (subject to review). 
 
The author of the first-placed paper will be invited to give a presentation as a speaker at the 2025 ATRIP international annual conference to be held from June 22 to June 25, 2025, at the University of Copenhagen, Denmark. The Executive Committee reserves the right not to proclaim any or all winners should the quality of the papers be considered insufficient. 

More details on the Essay Competition, including the full requirements and the evaluation process of the submissions by ATRIP’s Executive Committee, can be found here. https://atrip.org/scholarship-opportunities-ukraine/


አቶ ብርሃኑ አዴሎ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነርነት  ዕጩ ሆነው ቀረቡ።

በቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ዘመነ መንግስት የሚኒስትሮች ካቢኔ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ብርሃኑ አዴሎ ገብረማርያም ለኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ኮሚሽነርነት ለመሰየም ዛሬ ጥር 22 ቀን 2017 ዓ/ም  ፓርላማ ቀርበዋል።

ሌሎች አራት ዕጩዎችም መቅረባቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

አቶ ብርሃኑ ከዚህ ቀደም በተለያዩ መንግሥታዊ ኃላፊነቶች ላይ የሠሩት ሲሆን የመጨረሻ መንግሥታዊ ኃላፊነታቸው የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተርነት ነበር።

ከኃላፊነታቸው የተነሱት " በቀረበባቸው ቅሬታ " መሆኑን ሪፖርተር ጋዜጣ ከ10 ዓመታት በፊት ዘግቧል።

" ከሠራተኞች እና ከተቋሙ ደንበኞች ቅሬታዎች ይቀርቡባቸው እንደነበር " ጋዜጣው በወቅቱ ዘግቧል።

የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ አቶ ብርሃኑን ከዚህ ኃላፊነት ማንሳታቸውም የሪፖርተር ዘገባ ያሳያል።

አቶ ብርሃኑ የአዕምሯዊ ንብረት ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬከተር ሆነው ከመሾማቸው በፊት የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ሆነው ከ1996 እስከ 2002 ዓ.ም. ለ6 ዓመታት አገልግለዋል።

በሪፖርተር ጋዜጣ ዘገባ መሠረት አቶ ብርሃኑ ከዚህ ኃላፊነታቸው የተነሱትም በቀረበባቸው ቅሬታ ምክንያት ነው።

ከተወለዱበት ካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች አዲስ አበባ ድረስ በመምጣት በአቶ ብርሃኑ ላይ የተፈራረሙትን ቅሬታ በጊዜው ጠቅላይ ሚኒስትር ለነበሩት አቶ መለስ ዜናዊ ማቅረባቸውን የሪፖርተር ዘገባ ያስታውሳል።

ይህን ተከትሎ " በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር የተቋቋመ አጣሪ ኮሚቴ ባቀረበባቸው ሪፖርት ከካቢኔ ጉዳይ ሚኒስትርነታቸው እና ከኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነታቸው እንዲነሱ " መደረጉን ሪፖርተር ከ10 ዓመታት በፊት በሠራው ዘገባ ጠቅሷል።

አቶ ብርሃኑ በመንግሥታዊ ተቋማት ከነበራቸው ኃላፊነት በተጨማሪ አወዛጋውን የ1997 ምርጫ ተከትሎ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ነበሩ።

የትምህርት ሁኔታቸው ምን ይመስላል ?

ከሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በሕግ የመጀመሪያ ዲግሪ አላቸው። በዓለም አቀፍ ሰብዓዊ መብቶች ከሕንድ አገር የማስተርስ ዲግሪያቸውን ተቀብለዋል።

የስራ ህይወታቸው ምን ይመስላል ?

- ከመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት እስከ ዩኒቨርሲቲ አስተምረዋል።

- በዞን ፋይናንስ መምሪያ የህግ አማካሪ ሆነው አገልግለዋል።

- የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ባገኙበት የሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የህግ ፋካልቲ ለ3 ዓመታት አስተምረዋል።

- በቀድሞው ደቡብ ክልል የፍትህ ቢሮ ኃላፊነት ላይ ሰርተዋል። ከዛ በመቀጠልም በቀረበባቸው ቅሬታዎች ከስልጣን ወደተነሱባቸው የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር እና የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ጽህፈት ቤት አቅንተዋል።

- ከመንግስታዊ የሥራ ኃላፊ ከተነሱ በኋላ ላለፉት 10 ዓመታት በጥብቅና እና በህግ ማማከር ስራ ላይ መሰማራታቸውን ለፓርላማ አባላት የቀረበው የስራ ልምድ ያሳያል።

Source - tikvahethiopia




Collateral Crisis a Pressing Challenge for Ethiopian Banks

As the Ethiopian government initiates a new corridor development plan, banks find themselves at the epicentre of a collateral crisis. However, it’s important to note that the banking sector in Ethiopia has shown remarkable resilience in the face of these challenges. Recent studies by the National Bank of Ethiopia (NBE) reveal that the industry heavily relies on securing immovable properties as collateral for loans. With the prevailing lending practice and the concentration of collaterals along main roads, banks often prioritize these properties for security.

Read more: https://lnkd.in/eRgM45k9


Call for Applications
Nuremberg Summer Academy for Young Professionals 2025 – Anglophone Edition
The International Nuremberg Principles Academy is pleased to announce that applications for the eighth edition of its Nuremberg Summer Academy are now open.


Young lawyers, prosecutors, judges and academics are invited to apply to the 2025 anglophone edition which will be held online from 4 to 15 August 2025.

The programme will be held online. The programme will be divided into two parts: (1) live lectures and (2) guided self-study time via Moodle, including daily quizzes and assignments. The live sessions will comprise twelve lectures, as well as group assignments, followed by interactive discussions.


Eligibility Criteria

Applicants should be young professionals with a minimum of three years of professional experience as prosecutors, judges, lawyers, other legal professionals or academics at accredited universities working in disciplines related to international criminal law (e.g. human rights, criminal law, public international law and international humanitarian law);
Applicants should have an undergraduate degree in law to be eligible. A Master’s degree in a discipline related to international criminal law is an added advantage;
Applicants should possess a basic understanding of international criminal law and/or international humanitarian law;
Applicants should have a demonstrated interest in applying or disseminating international criminal law in their professional life;
Applicants should be proficient in spoken and written English;
Applicants should be able to participate full time and should be available for the entire duration of the programme.

Please Note

The Nuremberg Academy holds two editions of its Summer Academy: the Nuremberg Summer Academy in English and l’Académie d’été de Nuremberg in French. For the francophone edition, please find more details on the application process here.

Applicants can only apply to one Nuremberg Summer Academy, either the anglophone edition or the francophone edition.

Priority will be given to young professionals directly involved in (or likely to be directly involved in) the investigation or prosecution of core international crimes and to young professionals from conflict and post-conflict states. Due consideration will be given to gender balance and equitable geographic representation.

Female candidates are strongly encouraged to apply.


How to Apply

Interested applicants are kindly requested to fill in the online application form by 31 January 2025 – midnight CET.

All applicants will be informed about the outcome of their application by the end of February 2024. Shortlisted applicants will be called for an interview between March and April 2025.


Fees and Scholarships

Participants are not required to pay any course fees.

As the Nuremberg Summer Academy 2025 will be held entirely online, there is no scholarship available. The Nuremberg Academy will provide financial help for the selected participants and support the purchase of technical equipment (stable internet connection, camera, microphone, etc.) for the purpose of the programme.


Certificate

Certificates of attendance will be awarded to participants on the last day of the programme. Full time attendance during the entire programme is required in order to receive a certificate.

Apply via- https://www.nurembergacademy.org/capacity-strengthening/nuremberg-summer-academy/nuremberg-summer-academy-2025/application-nuremberg-summer-academy-2025


Exciting Opportunity for Students!
ELSA is thrilled to announce the Second National Essay Competition! This year’s theme is: "Assessing the Impact of Technological Advancement on Legal Education in Ethiopia.”
Don’t miss the chance to showcase your ideas and win exciting prizes!
Check out the poster and guidelines for more details.

Telegram- https://telegram.me/ethiolawblog
Facebook-
https://m.facebook.com/aboutlawlegalservice
LinkedIn-
https://www.linkedin.com/company/aboutethiopian-law
TikTok-
https://www.tiktok.com/@aboutethiopianlaw1?_t=8qe3Ip7153m&_r=1


እየፀደቁ ያሉ አዋጆች ለሕዝብና ለአገር የሚኖራቸው ፋይዳ ይታሰብበት!


ሪፓርተር

መንግሥት በስኬት አገር ለማስተዳደር ሕጎችን ሲያወጣም ሆነ ፖሊሲ ሲነድፍ፣ የሚቀርቡለትን ምክረ ሐሳቦች በአግባቡ ማስተናገድ ይጠቅመዋል እንጂ አይጎዳውም፡፡ ቀደም ሲል በነበሩ ዓመታት የተለያዩ ሕጎች ተረቀው ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሲቀርቡ የሕዝብ አስተያየት እንዲሰጥባቸው ዕድሉ ቢኖርም፣ ነገር ግን በምክር ቤት አባላትም ሆነ በሌሎች ተሳታፊዎች የሚሰጡ ሐሳቦች ወደ ጎን ተገፍተው ብዙ ችግሮች መፈጠራቸው አይዘነጋም፡፡ በአንድ ወቅት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሳይቀር ጥራት የሌላቸው ሕጎች እየወጡ እንደገና ማሻሻያ ረቂቆች ሲቀርቡ ትችቶች መሰንዘራቸው ይታወሳል፡፡ ከምርጫ 97 በኋላ አፋኝ የተባሉት የሚዲያ፣ የፀረ ሽብርተኝነትና የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት አዋጆች አገር እንደሚጎዱ ብዙዎች በልመና ሳይቀር ተማፅነው አሻፈረኝ ተብሎ ያደረሱት በደል የሚረሳ አይደለም፡፡ የለውጡ መንግሥት ወደ ሥልጣን ሲመጣ በቅድሚያ እነዚህን አፋኝ አዋጆች የመለወጡ ምክንያትም ይታወቃል፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተከታታይ የተለያዩ ሕጎች እየተረቀቁ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቢቀርቡምና የሕዝብ አስተያየት መድረኮች ቢዘጋጁም፣ አሁንም በግብዓትነት የሚቀርቡ የሕዝብ አስተያየቶች በአግባቡ ባለመደመጣቸውና በቂ ክርክሮች ባለመደረጋቸው ቅሬታዎች እየተሰሙ ነው፡፡ ሰሞኑን ለፀደቁት የንብረት ታክስና የንብረት ማስመለስ አዋጆች ቀደም ሲል በተከታታይ በተደረጉ ሕዝባዊ ውይይቶችም ሆኑ የምክር ቤት ውሎዎች በርካታ ግብዓቶች ቢሰባሰቡም፣ እንደ ወረዱ ነው የፀደቁት ተብሎ የተቃውሞ ድምፆች እየተሰሙ ነው፡፡ እዚህ ላይ ልብ ሊባል የሚገባው ማንም ጤነኛ አዕምሮ ያለው ሰው በሕገወጥ መንገድ የተፈራ ንብረት ጥያቄ ሊነሳበት ይገባል እንደማይል ነው፡፡ ነገር ግን አንድ ንብረት ወደኋላ አሥር ዓመት ተሂዶ ጥያቄ ለምን እንደሚነሳበት በቂ ማብራሪያ ያስፈልገዋል፡፡ ንብረቱ ላይ ትኩረት ተደርጎ የወንጀል ተጠያቂነት አለመኖሩም ሌላው የሚነሳ ነጥብ ነው፡፡ አፈጻጸም ላይ የማጥቂያ መሣሪያ እንዳይሆን ጥያቄ ሲነሳ በቂ ምላሽ ይፈልጋል፡፡ የንብረት ታክሱም ጉዳይ ቢሆን ኑሮ እንደሚያከብድ አያጠራጥርም፡፡
ነገ ተነገ ወዲያም እንደ ሚዲያ ነፃነት የመሳሰሉ ሕጎች በባለድርሻ አካላት የቀረቡባቸው ጠቃሚ ግብዓቶች ተካተው ካልቀረቡ፣ የሕዝብ አስተያየቶችም ሆኑ የሕዝብ ውክልና ያላቸው የምክር ቤት አባላት ድምፅ አለመደመጥ ተጨማሪ ችግሮች ከመጥራት የዘለለ ፋይዳ አይኖራቸውም፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ሕግ አውጭው፣ ሕግ ተርጓሚውና አስፈጻሚው አካል ሚዛናዊ የእርስ በርስ ቁጥጥር እያደረጉ ካልሠሩ ዞሮ ዞሮ የምትጎዳው አገር ናት፡፡ ትናንት ሲፈጸሙ የነበሩ ስህተቶች አንዳችም ለውጥ ሳያደርጉ ዛሬም የሚደገሙ ከሆኑ፣ በብሔራዊ ጉዳዮች ላይ እንኳንስ ተነጋግሮ ለመግባባት ዓይን ለዓይን መተያየት ያዳግታል፡፡ መንግሥት የሚያወጣቸው ሕጎችም ሆኑ የሚነድፋቸው ፖሊሲዎች ለሕዝብ አስተያየት ከመቅረባቸው በፊት ግራና ቀኙን በሚገባ ያማተሩ ሊሆኑ ይገባል፡፡ ለዚህ ይረዳ ዘንድም በሁሉም መስኮች ካሉ በዕውቀትና በልምድ ከዳበሩ ባለሙያዎች ጋር መመካከር ብዙ ችግሮችን በቀላሉ ይቀርፋል፡፡
ዜጎች በአገራቸው ደስተኛ ሆነው እንዲኖሩ መንግሥት ከማንም የበለጠ ኃላፊነት አለበት፡፡ ሕጎች ሲወጡ ከምንም ነገር በላይ የዜጎችን አማካይ ፍላጎት መጠበቅ ይኖርባቸዋል፡፡ ሕጎች ጥቂቶችን ተጠቃሚ እያደረጉ ብዙኃኑን እንዳያስከፉ መንግሥት መጠንቀቅ አለበት፡፡ በዜጎች መካከል ልዩነት እንዳይፈጠርና በእኩልነት ላይ የተመሠረተ ግንኙነት እንዲኖር፣ ሕጎች ሚዛናዊና የሁሉንም ወገኖች ፍላጎት ያካተቱ እንዲሆኑ ጥረት ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ሕጎች ከማንኛውም ዓይነት የፖለቲካ ጫና ነፃ ሆነው ሲወጡ አተገባበራቸው አስቸጋሪ አይሆንም፡፡ የፖለቲካ ጫና ሲበረታ ግን ከሕግነት ይልቅ የጉልበት አጀንዳ አስፈጻሚ ይሆናሉ፡፡ ከዚህ ቀደም አወዛጋቢ የነበሩ ሕጎች ያስከተሉት ጥፋትና ጉዳት እየታሰበ፣ እንደገና ወደ እዚያ ዓይነቱ መራር ትውስታ ላለመመለስ ይታሰብበት፡፡ በሕግና በሥርዓት መተዳደር ለአገር ህልውናም ሆነ ለሕዝብ ደኅንነት በጣም ጠቃሚ ስለሆነ፣ ሕግ የማጥቂያ መሣሪያ እንዳይሆን ለሚለው ሥጋት ሲባል ጥንቃቄ ይደረግ፡፡
ከሕግ አወጣጥና ከፖሊሲ ቀረፃ በተጨማሪ መንግሥት በፖለቲካ፣ በዲፕሎማሲ፣ በኢኮኖሚና በሌሎች ማኅበራዊ ጉዳዮች የተለያዩ ውሳኔዎችን ሲያስተላልፍም ሆነ ዕርምጃ ሲወስድ በሚገባ የተጠኑ ቢሆኑ ይመረጣል፡፡ በውሳኔዎቹ ወይም በዕርምጃዎቹ ላይ የተለያዩ አስተያየቶች ሲሰጡ በሰከነ መንገድ መመርመር ተገቢ ነው፡፡ ድጋፍ ሲገኝ በደስታ መቀበል እንዳለ ሁሉ ተቃውሞ ሲሰማም ሥርዓት ባለው መንገድ ማስተናገድ የመንግሥት አንዱ ኃላፊነት ነው፡፡ ለምሳሌ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ተደርጎ ከተለያዩ አቅጣጫዎች ጉርምርምታ ሲሰማ የጠላት ወይም የከሃዲ ድምፅ ማስመሰል ተገቢ አይደለም፡፡ መንግሥትን መልካም ሥራ አከናውነሃል በማለት ተደስተው የሚያመሠግኑትን ያህል፣ በተከናወነው ሥራ ወይም በተላለፈው ውሳኔ ደስተኛ ያልሆኑ የተቃውሞ ድምፅ ቢያሰሙ ሊገርም አይገባም፡፡ ይልቁንም ለምክንያታዊ የሐሳብ ልውውጥ የሚረዱ መድረኮችን ማመቻቸት ይጠቅማል፡፡ ከፋይዳ ቢስ ጭብጨባ ይልቅ ምክንያታዊነት ላይ የተመረኮዘ ትችት ማስተናገድ ያስከብራል፡፡
ባለፉት ስድስት ዓመታት ኢትዮጵያ እያለፈችባቸው ያሉ ከባድ ችግሮች ጥለዋቸው የሚያልፉ ጉዳቶች ይታወቃሉ፡፡ በትግራይ፣ በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች የተካሄዱና እየተካሄዱ ያሉ አውዳሚ ጦርነቶች በአገርና በሕዝብ ላይ ያደረሱት ጉዳት ይታወቃል፡፡ ከዚህ ቀደም በተለያዩ አካባቢዎች በተፈጸሙ ጥቃቶችና ውጊያዎች የተፈጠሩ ጉዳቶች የፈጠሩት ቁርሾ የሚዘነጋ አይደለም፡፡ እነዚህ ሁሉ መከራዎች በደረሱባት አገር ውስጥ ለዘለቄታዊ ሰላም የሚያግዙ ንግግሮች እንዲደረጉ መድረኩን ማመቻቸት፣ እንዲሁም በውጊያ ውስጥ ካሉና በተለያዩ ምክንያቶች ካኮረፉ ወገኖች ጋር ተቀራርቦ ለመወያየት የሚያስችሉ አማራጮች ላይ ትኩረት አልተደረገም፡፡ ይልቁንም ከዛሬ ነገ የተሻለ ነገር የሚጠብቁ ወገኖችን ጭምር ለአመፅ የሚጋብዙ ድርጊቶች ሲስተዋሉ ቆም ብሎ ማሰብ ይገባል፡፡ ሕጎች ሲረቀቁ ከሥጋትና ከጥርጣሬ ይልቅ ተስፋ ይጫሩ፡፡ ለሕግ አወጣጥም ሆነ ለፖሊሲ የሚጠቅሙ ሐሳቦችም ይደመጡ፡፡ በተለይ እየፀደቁ ያሉ አዋጆች ለሕዝብ ጥቅምና ለአገር ህልውና የሚኖራቸው ፋይዳ ይታሰብበት!


እርስዎስ ምን ይላሉ?


🎓 Children’s Rights Scholarship 2 🎓

Are you passionate about children's rights and eager to advance your legal studies? The Children’s Rights Scholarship 2 offers a unique opportunity for students from Ethiopia, Kenya, Uganda, and Malawi to pursue a Master of Laws in Advanced Studies in International Children’s Rights at Leiden University.

Eligibility Criteria:

🌍 Nationality: Ethiopia, Kenya, Uganda, or Malawi

💶 Amount: €44,432 (covers tuition, travel, living expenses, and accommodation)

Application Process:

Apply online for the Master of Laws: Advanced Studies in International Children’s Rights and pay the €100 application fee.
- Upload a motivation letter detailing:
- Your student number

📧 Email ICRscholarships@law.leidenuniv.nl with:
Your scholarship motivation letter
A 2-minute video introducing yourself

Deadline: 🗓 February 1, 2025

Official Source- 🔗

Telegram- https://telegram.me/ethiolawblog
Facebook- https://m.facebook.com/aboutlawlegalservice


Vacancy Alert!

Human Rights Officer, Monitoring and Investigation
Samara, Ethiopia

Human Rights Officer, Human Rights Education
Addis Ababa, Ethiopia

Project Development & Resource Mobilization Officer
Addis Ababa, Ethiopia



Apply via - https://ehrc.org/jobs/


file number 29 1512.08 Meseret Taye.pdf
26.1Mb
አካለ መጠን ባልደረሰ ልጅ ስም የተመዘገበ የማይንቀሳቀስ ንብረት በህፃኑ በሕጋዊ መንገድ የተፈራ ንብረት ስለመሆኑ ግምት ሊወሰድ ይገባል፡፡ ፍርድ ቤቶች ህፃኑ ንብረቱን ከራሱ የሃብት ምንጭ ወጪ አድርጎ ስለመግዛቱ አላስረዳም በሚል ምክንያት ንብረቱን ባልና ሚስት በጋብቻ ውስጥ ያፈሩት አንጂ የህፃኑ አይደለም በማለት ወስነዋል፡፡ ባልና ሚስቱ ንብረቱን በራሳቸው ፈቃድ ከጋራ ንብረታቸው ወጪ በማድረግ አካለ መጠን ባልደረሰ ልጅ ስም ገዝተዋል፡፡ አንዲህ ዓይነት ህፃናትን የሚመለከቱ ጉዳዮች የህፃናትን ደህንነትና ጥቅም በቀደምትነት መታሰብ ያለበት እና ለህፃኑ ጥቅም ተብሎ አንደተገዛ (እንደተፈራ) ንብረት ተደርጎ ሊወሰን የሚገባው ነው በማለት ምክር ቤቱ ውሳኔ ተሰጥቷል፡፡
(የፌ/ም/ቤት መዝገብ ቁጥር 41/10)

Credit- Yadeta G.


Calling all legal enthusiasts and scholars!

The African Legal Studies Blog is a platform for exploring African legal developments through diverse and interdisciplinary perspectives. We invite you to contribute your expertise and engage with a global audience on topics like human rights, environmental law, and regional integration law.

Submit your contributions or inquiries to martin.mitschker@uni-bayreuth.de.


የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ.መ.ቁ 211028 ጥር 27 ቀን 2014 ዓ.ም በዋለው ችሎት ከተጨማሪ እሴት ታክስ ደረሰኝ አለመስጠት ጋር በተገናኘ የአንድ ድርጅት ሥራ አስኪያጅ በወንጀል ተጠያቂ የሚሆነው እሱ የሚመራው ድርጅት የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ ሆኖ ያለተጨማሪ እሴት ታክስ ደረሰኝ ግብይት ማከናወኑ ሲረጋገጥ እንደሆነ: የድርጅቱ ሀላፊነት ከተረጋገጠ የስራ አስኪያጁ ሀላፊነት የሕግ ግምት የሚወሰድበት ስለመሆኑ: ሆኖም የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ የድርጅቱን አስተዳደር በሚመለከት በውክልና ለሌላ ሰው ያስተላለፈ መሆኑ እና ተወካዩም በተቀበለው ውክልና መሠረት ሥራውን የሚያከናውን መሆኑ በተረጋገጠ ጊዜ ተጠያቂ የሚሆነው ውክልናውን ተቀብሎ ሥራውን በውክልና የሚያስተዳድረው ሰው እንጂ ስራ አስኪያጁ ወይም የድርጅቱ ባለቤት ሊሆን አይገባም በማለት ወስኗል።

Credit- Etmet Assefa (Consultant and attorney at Law Former Judge at federal supreme court of Ethiopia )


ውድ የስለ ህግ ቤተሰቦች በያላችሁበት ከፍ ያለ  ሰላምታየን እያቀረብኩ ከዚህ በታች ባለው ሊንክ በመግባት ከ april 3-6 በ ሀገረ አሜሪካ በሚካሄደው የ Future diplomats Forum ለመሳተፍ የሚያስፈልገኝን የህዝብ ድጋፍ (Endorsement) ማንኛውንም አስተያየት በመስጠት እና ላይክ በማድረግ እነድተባበሩኝ  ስል በታላቅ አክብሮት በትህትና እጠይቃለሁ።

Amsalu Lemlemu


Link- https://www.facebook.com/100009452407948/posts/pfbid0uaCfB5XGMxHHgyaFmsjt4PWFnScosBg1b9kzQ232Cii43X7QYq1BGiX7DHg8vPwEl/?app=fbl2


Concern worldwide #Vacancy
For Legal experts
https://hawassajobs.com/concern-worldwide-vacancy-2025/


Internship Program (Remote) under Adv. Param Bhamra
Are you a law student eager to gain hands-on experience in the dynamic field of law, with a special focus on Alternative Dispute Resolution (ADR), Arbitration, and Mediation? Here's your chance to work closely with Adv. Param Bhamra, an experienced professional and Founding Partner at MediateGuru, with expertise in International Arbitration and ADR.

This internship program offers:

Practical Exposure: Work on live projects, research assignments, and case studies.
Skill Development: Enhance your legal drafting, research, and analytical skills.
Mentorship: Receive personalized guidance and insights from an experienced mentor.
Networking Opportunities: Connect with industry professionals and expand your professional network.
Eligibility Criteria:

Current law students (3rd, 4th, or 5th year of a 5-year program OR 2nd/3rd year of a 3-year program).
Strong interest in ADR, Arbitration, and Mediation.
Demonstrated academic and extracurricular achievements (preferred).
Application Process:

Interested candidates are required to fill out the Google Form below.
Shortlisted candidates will be contacted for further rounds
Deadline: 22nd Jan 2025 (for Feb month)
Contact: For any queries, please email at advparambhamra@gmail.com

16k 1 150 2 19

Video is unavailable for watching
Show in Telegram
Lawyers walking back into the office after the holidays be like😃

Telegram- https://telegram.me/ethiolawblog
Facebook- https://m.facebook.com/aboutlawlegalservice
LinkedIn- https://www.linkedin.com/company/aboutethiopian-law
TikTok- https://www.tiktok.com/@aboutethiopianlaw1?_t=8qe3Ip7153m&_r=1


17th ANRS Justice Training Call (ABOUT-LAW).pdf
2.0Mb
Amhara  Regional State 17th Judicial Training Vacancy

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የፍትሕ ባለሙያዎች ማሠልጠኛና የሕግ ምርምር ኢንስቲትዩት በክልሉ ሥር በሚገኙ ወረዳዎች ዳኛ ወይም ዐቃቤ-ሕግ ሆኖ ለመሥራት ለሚፈልጉ ተወዳዳሪዎች የሥራ ውድድር ማስታወቂያ አውጥቷል።
ብዛት፡- 300
የመመዝገቢያ ጊዜ፡- ከታኅሳስ 30 እስከ ጥር 13 ቀን 2017 ዓ.ም

Telegram- https://telegram.me/ethiolawblog
Facebook- https://m.facebook.com/aboutlawlegalservice
LinkedIn- https://www.linkedin.com/company/aboutethiopian-law
TikTok- https://www.tiktok.com/@aboutethiopianlaw1?_t=8qe3Ip7153m&_r=1


Our graphic designer, Yonas A. who is an architect and assistant lecturer in architecture at Bahir Dar University, has developed our brand guidelines and logo. So, this will serve as the new logo for ስለ-ህግ ABOUT-LAW from now on.😊


Core International Human Rights Treaties.pdf
3.1Mb
📕 The Core International Human Rights Treaties

BY: United Nations Human Rights Office of the High Commissioner.

🔗 t.me/ethiolawblog



20 last posts shown.