🇸🇾 ሶሪያ : ልብ የሚሰበር ክስተት
#Ethiopia | አሳዛኝ እውነት፤ ማንም ሰው መሸከም ከሚችለው በላይ መከራ የወረደበት አባት
አንድ እግሩን በአደጋ በማጣቱ በሁለት ክራንች ( የብረት ድጋፍ) እየታገዘ ይራመዳል ።
ከስደት ወደ ትውልድ ቄዬው ከነልጁ እየተመለሰ ነው።
የስድስት ዓመቱ ኡመር ተልሃ የአባቱን ሰዉ ሰራሽ እግር በሁለት እጆቹ አቅፎ ፈጠን እየለ ለመሄድ በማሰብ ይወተረተራል ። አባቱ አይኑን ከልጁ አልነቀለም ።
የተሸከመው ሰው ሰራሽ እግር እይታውን ጋርዶት እንዳይወድቅ ስጋት ገብቶታል ።
ኡመር አንድ የቀረው ብቸኛው የአይኑ ማረፊያ ነው።
በባዕድ ሀገር በስደት ዓለም ሆስፒታል እግሩ ተቆርጦ ከአጠገቡ ሳይለይ ያስታመመው ትንሹ ኡመር በህይወት ያለው ብቸኛው ልጁ ነው ።
እንደ ዛሬው ሁለቱ ብቻ ሳይቀሩ የዛሬ 11 አመት ጦርነት ሸሽተው አገራቸውን ሶሪያን ጥለው ሲሰደዱ አምስት ነበሩ።
ቆይቶ እዚያው የተወለደው ኡመር ደግሞ 6ኛ የቤተሰቡ አባል ሆኖ ተቀላቀለ ።
በወቅቱ ሰውን ከሚበላው የጦርነት አቶን እሳት መሃል ሙሉ አካላቸውን እና የቤተሰብ ቁጥራቸው ሳይጐድል ቱርክ መግባታቸውን እንደ ትልቅ ዕድል ቆጥረውትም ነበር ።
ከ11 ዓመታት የስደት ኑሮ በኋላ ለ61 ዓመታት ሶሪያን ረግጦ የገዛው የባዝ ፓርቲ ሲሸነፍ የቱርክ ድንበርን አቋርጠው ሁለቱ ፤ አባትና ልጅ ብቻ ወደ መንደራቸው እየተመለሱ ነው ።
6 አመቱ ኡመር የተወለደው ቱርክ ቢሆንም ያጣውን የእናት ናፍቆት ሶሪያ ባላቸው አክስቱ ፍቅር ሊያስታግስ ጉዞውን ለመጨረስ ጓጉቷል ።
ባለ ክራንቹ መሐመድ እና የአባቱን ሰው ሰራሽ እግር የተሸከመው ከስደት ተመላሽ ኡመርን ያየው የአናዶሉ ዘጋቢ ጠጋ ብሎ ወደ ሀገር መመለስ የሚፈጥረውን ስሜት አባቱን ጠየቀ ።
የመሐመድ ዓይኖች በእንባ ተሞሉ ያሳለፈው መከራ ከፊቱ ተደቀነ ።
የህይወት ታሪኩን ውጣ ውረድና የዕጣ ፋንታን አይቀሬነት ዘርዝሮ ነገረው ።
የዛሬ 11 አመት ባለቤቴንና የዚህን ልጅ ታላቅ ወንድም አለ መሐመድ ወደ ኡመር በእጁ እየጠቆመ ፣ የልጆቼን ወንድ እያት እና የሴት አያትን ይዥ ነበር ቱርክ የገባሁት ።
በዚሁ አገር ደቡባዊ ቱርክ ሃታይ ግዛት የካቲት 6 ቀን 2023 የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ሰለባ ሆነን እንጂ አለ በትካዜ።
የመሬት መንቀጥቀጡ የበርካቶችን ህይወት ቀጥፎ ከፍተኛ የአካል ጉዳትና ንብረት አውድሟል፡፡
ከአምስት ቀን ፍለጋ በኋላ በነፍስ አድን ሠራተኞች ከፍርስራሽ ስር እኔና የስድስት ዓመት ልጄ ዑመር ብቻ ተረፈን ወጣን ሲል ዘረዘረ።
በደረሰብኝ ጉዳት ምክንያት አንድ እግሬ ተቆረጠ ።
ታድያ ይህንን እንዴት ብዬ ስሜቱን ልንገርህ ሲል ከእንባው ጋር እየታገለ ገለጸ ።
እኔ የናፍቀኝ የትውልድ ሀገሬ ሶሪያ ስመለስ ልጄ ከአክስቱ ይገናኛል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ በቃ ይኸው ነው ።
ከመሬት መንቀጥቀጥ አደጋው በኋላ በቱርክ ዜጐች የተደረገልኝ ድጋፍ ከምናገረው በላይ ነው ።
ከህዝቡ በተጨማሪ የቱርክ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጠይብ ኤርዶጋንን ማመስገን እፈልጋለሁ በብዙ አግዘውኛል ሲል ተናግሯል ።
የሀገሬ ሰው "ለመከራ የጣፈው ፤ ቢነግድ አያተርፈው" የሚለው ይሄኔ ነው ።
ምስጋናው ሀይሉ
#Ethiopia | አሳዛኝ እውነት፤ ማንም ሰው መሸከም ከሚችለው በላይ መከራ የወረደበት አባት
አንድ እግሩን በአደጋ በማጣቱ በሁለት ክራንች ( የብረት ድጋፍ) እየታገዘ ይራመዳል ።
ከስደት ወደ ትውልድ ቄዬው ከነልጁ እየተመለሰ ነው።
የስድስት ዓመቱ ኡመር ተልሃ የአባቱን ሰዉ ሰራሽ እግር በሁለት እጆቹ አቅፎ ፈጠን እየለ ለመሄድ በማሰብ ይወተረተራል ። አባቱ አይኑን ከልጁ አልነቀለም ።
የተሸከመው ሰው ሰራሽ እግር እይታውን ጋርዶት እንዳይወድቅ ስጋት ገብቶታል ።
ኡመር አንድ የቀረው ብቸኛው የአይኑ ማረፊያ ነው።
በባዕድ ሀገር በስደት ዓለም ሆስፒታል እግሩ ተቆርጦ ከአጠገቡ ሳይለይ ያስታመመው ትንሹ ኡመር በህይወት ያለው ብቸኛው ልጁ ነው ።
እንደ ዛሬው ሁለቱ ብቻ ሳይቀሩ የዛሬ 11 አመት ጦርነት ሸሽተው አገራቸውን ሶሪያን ጥለው ሲሰደዱ አምስት ነበሩ።
ቆይቶ እዚያው የተወለደው ኡመር ደግሞ 6ኛ የቤተሰቡ አባል ሆኖ ተቀላቀለ ።
በወቅቱ ሰውን ከሚበላው የጦርነት አቶን እሳት መሃል ሙሉ አካላቸውን እና የቤተሰብ ቁጥራቸው ሳይጐድል ቱርክ መግባታቸውን እንደ ትልቅ ዕድል ቆጥረውትም ነበር ።
ከ11 ዓመታት የስደት ኑሮ በኋላ ለ61 ዓመታት ሶሪያን ረግጦ የገዛው የባዝ ፓርቲ ሲሸነፍ የቱርክ ድንበርን አቋርጠው ሁለቱ ፤ አባትና ልጅ ብቻ ወደ መንደራቸው እየተመለሱ ነው ።
6 አመቱ ኡመር የተወለደው ቱርክ ቢሆንም ያጣውን የእናት ናፍቆት ሶሪያ ባላቸው አክስቱ ፍቅር ሊያስታግስ ጉዞውን ለመጨረስ ጓጉቷል ።
ባለ ክራንቹ መሐመድ እና የአባቱን ሰው ሰራሽ እግር የተሸከመው ከስደት ተመላሽ ኡመርን ያየው የአናዶሉ ዘጋቢ ጠጋ ብሎ ወደ ሀገር መመለስ የሚፈጥረውን ስሜት አባቱን ጠየቀ ።
የመሐመድ ዓይኖች በእንባ ተሞሉ ያሳለፈው መከራ ከፊቱ ተደቀነ ።
የህይወት ታሪኩን ውጣ ውረድና የዕጣ ፋንታን አይቀሬነት ዘርዝሮ ነገረው ።
የዛሬ 11 አመት ባለቤቴንና የዚህን ልጅ ታላቅ ወንድም አለ መሐመድ ወደ ኡመር በእጁ እየጠቆመ ፣ የልጆቼን ወንድ እያት እና የሴት አያትን ይዥ ነበር ቱርክ የገባሁት ።
በዚሁ አገር ደቡባዊ ቱርክ ሃታይ ግዛት የካቲት 6 ቀን 2023 የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ሰለባ ሆነን እንጂ አለ በትካዜ።
የመሬት መንቀጥቀጡ የበርካቶችን ህይወት ቀጥፎ ከፍተኛ የአካል ጉዳትና ንብረት አውድሟል፡፡
ከአምስት ቀን ፍለጋ በኋላ በነፍስ አድን ሠራተኞች ከፍርስራሽ ስር እኔና የስድስት ዓመት ልጄ ዑመር ብቻ ተረፈን ወጣን ሲል ዘረዘረ።
በደረሰብኝ ጉዳት ምክንያት አንድ እግሬ ተቆረጠ ።
ታድያ ይህንን እንዴት ብዬ ስሜቱን ልንገርህ ሲል ከእንባው ጋር እየታገለ ገለጸ ።
እኔ የናፍቀኝ የትውልድ ሀገሬ ሶሪያ ስመለስ ልጄ ከአክስቱ ይገናኛል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ በቃ ይኸው ነው ።
ከመሬት መንቀጥቀጥ አደጋው በኋላ በቱርክ ዜጐች የተደረገልኝ ድጋፍ ከምናገረው በላይ ነው ።
ከህዝቡ በተጨማሪ የቱርክ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጠይብ ኤርዶጋንን ማመስገን እፈልጋለሁ በብዙ አግዘውኛል ሲል ተናግሯል ።
የሀገሬ ሰው "ለመከራ የጣፈው ፤ ቢነግድ አያተርፈው" የሚለው ይሄኔ ነው ።
ምስጋናው ሀይሉ