የሲዳማ ሴቶች ባህላዊ አለባበስ ባጠቃላይ በ3 ይከፈላል።
የሲዳማ ሴቶች ባህላዊ አልባሳታቸውን እና ጌጣ ጌጦቻቸውን በጥንቃቄ በመያዝ ልምዳቸው ይታወቃል።
ልብሶቻቸው እና ጌጣ ጌጦቻቸው ጥሩ መዓዛ እንዲኖራቸው የተለያዩ የዛፍ ሥራ ሥሮች ፣ቅጠላ ቅጠሎች እና ቅርፊቶች በማደባለቅ የተቀመመ ንጥረ ነገር ያዘጋጃሉ።
የሲዳማ ሕፃናት ሴት ልጆች የሚለብሱት ከበግ ቆዳ ተለፍቶ የሚዘጋጅ ለምድ (Lande) ይሰኛል።
ወጣት ልጃገረዶች ደግሞ ከውስጥ ቆሎ (Qolo) የሚባል ልብስ የሚለብሱ ሲሆን ከላይ ከጥጃ ቆዳ ተለፍቶ የሚዘጋጅ ለምድ (Qonxolo) ይደርባሉ፡፡
የልጃገረዶች ቆሎ የተሰኘው ልብስ ከጥጥ የሚሠራ ሆኖ ከላይ እስከ ታች ተደርጎ የሚሰፋ የተለያዩ ቀለማት ባላቸው አዝራሮች፣ ጨሌዎችና ፈትሎች እንዲያሸበርቅን ይደረጋል፡፡
ዕድሜያቸው ለትዳር የደረሱ የሲዳማ ሴቶች ዱቤ (Dubbe) የሚባል ከቆዳ የሚሠራ ልብስ ይለብሳሉ፡፡
ላገባች ሴት ባሏ ዎዳሬ (Woodare) ይገዛላታል፡፡
ዎዳሬ ከበሬ ቆዳ የሚሠራ ሲሆን ቆዳው እጅግ የለሰለሰ ነው፡፡ አለባበሱም በሁለት በማጠፍና በወገብ ላይ በቆዳ የሚሠራ መቀነት በቁኔ (Qu’ne) በማሠር እጥፋቱ ወደ ታች በመልቀቅ ነው፡፡
ለጋብቻ የደረሰች ልጃገረድ ስታገባ ከእናቷ በስጦታ መልክ የሚሰጣትን ዎዳሬ ታጥቃ በልዩ ጌጣ ጌጦች ያሽቆጠቆጠ ለምድ ደርባና ተሞሽራ ስትወጣ በተለየ ሁኔታ የተጌጠ ቆሎና ቆንጦሎ ደርባ ነው፡፡
የሲዳማ ሴቶች ጎርፋ (Gorfa)፣ ቱባ (Tuba)፣ ዱዳ (Dudda)፣ ቦኬ (Boke) የሚባሉ ከቆዳ የሚሠሩ አልባሳትን ይለብሳሉ፡፡
ቦኬ፣ ወዳሬ የክት ልብሶች ሲሆኑ ቱባና ዲዳ በአዘቦት ቀናትና በሥራ ቀናት ጊዜ የሚለበሱ አልባሳት ናቸው፡፡
ከጎርፋ በስተቀር ከላይ የተጠቀሱ አልባሳት ከወገብ በታች የሚታጠቋቸው ሲሆን ጎርፉ በተለያየ ጨሌዎች ያጌጠና ሴቶች ወደ አደባባይ ሲወጡ ከላይ የሚደርቡት ካባ ነው፡፡
ሁለት ቆንጦሎ ከፊትና ከኋላ በማጠፍ መልበስ በሲዳማ ሴቶች ዘንድ የድሎት ወይም የቅንጦት ምልክት ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
በዚህ አለባበስ የሚታወቁ አበዛኞቹ ሴቶች “La’ma Lamu Landite” ተብለው ይወደሳሉ ትርጉሙም በሁለት ለምድ የተቀማጠለች መሆኗን የሚገልጽ ነው፡፡
(አዲስ1879)
(VOA)
እርስዎ የሚያውቁትን ባህላዊ አለባበስ ቢያጋሩን!
የሲዳማ ሴቶች ባህላዊ አልባሳታቸውን እና ጌጣ ጌጦቻቸውን በጥንቃቄ በመያዝ ልምዳቸው ይታወቃል።
ልብሶቻቸው እና ጌጣ ጌጦቻቸው ጥሩ መዓዛ እንዲኖራቸው የተለያዩ የዛፍ ሥራ ሥሮች ፣ቅጠላ ቅጠሎች እና ቅርፊቶች በማደባለቅ የተቀመመ ንጥረ ነገር ያዘጋጃሉ።
የሲዳማ ሕፃናት ሴት ልጆች የሚለብሱት ከበግ ቆዳ ተለፍቶ የሚዘጋጅ ለምድ (Lande) ይሰኛል።
ወጣት ልጃገረዶች ደግሞ ከውስጥ ቆሎ (Qolo) የሚባል ልብስ የሚለብሱ ሲሆን ከላይ ከጥጃ ቆዳ ተለፍቶ የሚዘጋጅ ለምድ (Qonxolo) ይደርባሉ፡፡
የልጃገረዶች ቆሎ የተሰኘው ልብስ ከጥጥ የሚሠራ ሆኖ ከላይ እስከ ታች ተደርጎ የሚሰፋ የተለያዩ ቀለማት ባላቸው አዝራሮች፣ ጨሌዎችና ፈትሎች እንዲያሸበርቅን ይደረጋል፡፡
ዕድሜያቸው ለትዳር የደረሱ የሲዳማ ሴቶች ዱቤ (Dubbe) የሚባል ከቆዳ የሚሠራ ልብስ ይለብሳሉ፡፡
ላገባች ሴት ባሏ ዎዳሬ (Woodare) ይገዛላታል፡፡
ዎዳሬ ከበሬ ቆዳ የሚሠራ ሲሆን ቆዳው እጅግ የለሰለሰ ነው፡፡ አለባበሱም በሁለት በማጠፍና በወገብ ላይ በቆዳ የሚሠራ መቀነት በቁኔ (Qu’ne) በማሠር እጥፋቱ ወደ ታች በመልቀቅ ነው፡፡
ለጋብቻ የደረሰች ልጃገረድ ስታገባ ከእናቷ በስጦታ መልክ የሚሰጣትን ዎዳሬ ታጥቃ በልዩ ጌጣ ጌጦች ያሽቆጠቆጠ ለምድ ደርባና ተሞሽራ ስትወጣ በተለየ ሁኔታ የተጌጠ ቆሎና ቆንጦሎ ደርባ ነው፡፡
የሲዳማ ሴቶች ጎርፋ (Gorfa)፣ ቱባ (Tuba)፣ ዱዳ (Dudda)፣ ቦኬ (Boke) የሚባሉ ከቆዳ የሚሠሩ አልባሳትን ይለብሳሉ፡፡
ቦኬ፣ ወዳሬ የክት ልብሶች ሲሆኑ ቱባና ዲዳ በአዘቦት ቀናትና በሥራ ቀናት ጊዜ የሚለበሱ አልባሳት ናቸው፡፡
ከጎርፋ በስተቀር ከላይ የተጠቀሱ አልባሳት ከወገብ በታች የሚታጠቋቸው ሲሆን ጎርፉ በተለያየ ጨሌዎች ያጌጠና ሴቶች ወደ አደባባይ ሲወጡ ከላይ የሚደርቡት ካባ ነው፡፡
ሁለት ቆንጦሎ ከፊትና ከኋላ በማጠፍ መልበስ በሲዳማ ሴቶች ዘንድ የድሎት ወይም የቅንጦት ምልክት ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
በዚህ አለባበስ የሚታወቁ አበዛኞቹ ሴቶች “La’ma Lamu Landite” ተብለው ይወደሳሉ ትርጉሙም በሁለት ለምድ የተቀማጠለች መሆኗን የሚገልጽ ነው፡፡
(አዲስ1879)
(VOA)
እርስዎ የሚያውቁትን ባህላዊ አለባበስ ቢያጋሩን!