ይህንም እንዳየች የኃጥአንንም መኖሪያ ያሳዩአት ዘንድ ወደ ኃጥአን ማደሪያም በወሰዷት ጊዜ የእነርሱን ሥቃይ አይታ እመቤታችን ርኅርኅተ ልብ ናትና ልጇ ከመከራ ያወጣቸው ዘንድ በጎልጎታ ስትጸልይ የካቲት ፲፮ ቀን ልጇ ወዳጇ የእናቱን ልመና ሰምቶ እልፍ አእላፋት መላእክትን አስከትሎ መጥቶ ሌላው ይቅርና ቀዝቃዛ ውኃ እንኳን በስማ የሰጠውን እንደሚምርላት ነግሯት ይህም የሰጣት ቃል ኪዳን እንዳይታበይ በራሱ ምሎላታል፡፡ (ሙሉ ሐሳቡን የካቲት ፲፮ ስንክሳር ላይ ይመልከቱ።)
የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጸሎቷ፣ አማላጅነቷና ተረዳኢነቷ አይለየን፤ አሜን!
የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጸሎቷ፣ አማላጅነቷና ተረዳኢነቷ አይለየን፤ አሜን!