" ይህ ተግባር ሕዝብን ለማስተዳደር ሥልጣን ላይ ካለ አካል የማይጠበቅ አስፀያፊ ተግባር መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን " - የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ፓርቲ
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) በላከው መግላጫ ፤ " ባለፉት ጥቂት ቀናት በአዲስ አበባ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች ላይ ወጣቶች በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች እየታፈኑ የት እንደገቡ ሳይታወቅ መሰወራቸውን ከቤተሰቦቻቸው እና ከተለያዩ አካላት ለመገንዘብ ችያለሁ " ሲል ገለጸ።
" ይኽን የመንግሥት ተግባር ይበልጥ አስከፊ የሚያደርገው እነዚህ ታፍነው የተወሰዱ ወጣቶች የት እንደሚገኙ አለመታወቅና ቤተሰቦቻቸውም በመንግሥት አካል የተያዘ ግለሰብ ሊገኙባቸው ይችላሉ የሚሏቸውን ቦታዎች ቢያስሱም ለማግኘት አለመቻላቸው ነው " ብሏል።
" በተጨማሪ አንዳንዶቹ ከተወሰኑ ቀናት መሰወር በኋላ በድንገት የት እንደነበሩ እንኳ መናገር በማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ ሆነው ወደቤታቸው መመለሳቸው ነው " ሲል ገልጿል።
ፓርቲው " ይሕ ሕጋዊ መንገድን ያልተከተለ የመንግሥትን ተግባር በሕግ ተጠያቂ መሆን ያለበትን አካል በቁጥጥር ሥር ማዋል ሳይሆን በወንበዴ የሚፈፀም አይነት አፈና እንደሆነ እና ይኽም ሕዝብን ለማስተዳደር ሥልጣን ላይ ካለ አካል የማይጠበቅ አስፀያፊ ተግባር መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን " ብሏል።
አሁንም በዚህ አይነት አፈና ውስጥ ያሉ ወጣቶች እንዳሉ ፓርቲው ማረጋገጡን ቤተሰቦቻቸውም በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ እንዳሉ ለማወቅ እንደቻለ አመልክቷል።
" ይህን አለማድረግ ግን ሥርዓት አልበኝነትን መጋበዝ፣ ለሕገወጥ ተግባራት ሽፋን መስጠት ብሎም ድጋፍ በማድረግ ቡራኬ እንደመስጠት እንቆጥራለን " ሲል ገልጿል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ጉዳዩን ተመልክቶ የሚመለከተውን አካል ተጠያቂ እንዲያደርግም ፓርቲው በመግለጫው ጥሪ አቅርቧል።
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) በላከው መግላጫ ፤ " ባለፉት ጥቂት ቀናት በአዲስ አበባ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች ላይ ወጣቶች በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች እየታፈኑ የት እንደገቡ ሳይታወቅ መሰወራቸውን ከቤተሰቦቻቸው እና ከተለያዩ አካላት ለመገንዘብ ችያለሁ " ሲል ገለጸ።
" ይኽን የመንግሥት ተግባር ይበልጥ አስከፊ የሚያደርገው እነዚህ ታፍነው የተወሰዱ ወጣቶች የት እንደሚገኙ አለመታወቅና ቤተሰቦቻቸውም በመንግሥት አካል የተያዘ ግለሰብ ሊገኙባቸው ይችላሉ የሚሏቸውን ቦታዎች ቢያስሱም ለማግኘት አለመቻላቸው ነው " ብሏል።
" በተጨማሪ አንዳንዶቹ ከተወሰኑ ቀናት መሰወር በኋላ በድንገት የት እንደነበሩ እንኳ መናገር በማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ ሆነው ወደቤታቸው መመለሳቸው ነው " ሲል ገልጿል።
ፓርቲው " ይሕ ሕጋዊ መንገድን ያልተከተለ የመንግሥትን ተግባር በሕግ ተጠያቂ መሆን ያለበትን አካል በቁጥጥር ሥር ማዋል ሳይሆን በወንበዴ የሚፈፀም አይነት አፈና እንደሆነ እና ይኽም ሕዝብን ለማስተዳደር ሥልጣን ላይ ካለ አካል የማይጠበቅ አስፀያፊ ተግባር መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን " ብሏል።
አሁንም በዚህ አይነት አፈና ውስጥ ያሉ ወጣቶች እንዳሉ ፓርቲው ማረጋገጡን ቤተሰቦቻቸውም በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ እንዳሉ ለማወቅ እንደቻለ አመልክቷል።
" ይህን አለማድረግ ግን ሥርዓት አልበኝነትን መጋበዝ፣ ለሕገወጥ ተግባራት ሽፋን መስጠት ብሎም ድጋፍ በማድረግ ቡራኬ እንደመስጠት እንቆጥራለን " ሲል ገልጿል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ጉዳዩን ተመልክቶ የሚመለከተውን አካል ተጠያቂ እንዲያደርግም ፓርቲው በመግለጫው ጥሪ አቅርቧል።