Posts filter


“ ዱባይ ስንሄድ እንነቃቃለን “ - ሚኬል አርቴታ

⏩ “ አስቸጋሪ ውድድር ነው “

የመድፈኞቹ ዋና አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ቡድናቸው ዛሬ ምሽት በመጀመሪያ ደቂቃዎች ያገኛቸውን እድሎች ባለመጠቀሙ ለሽንፈት መዳረጉን ገልጸዋል።

“ በመጀመሪያው ያገኘናቸውን እድሎች መጠቀም ነበረብን ነገርግን ያንን አላደረግንም “ ያሉት አርቴታ በዚህ ምክንያት ጨዋታው ወደሌላ አቅጣጫ ተቀይሯል ብለዋል።

“ ቀጥሎ በረጅም ኳስ የመጀመሪያ ግብ ሲቆጠርብን በስነልቦና ወርደን ነበር ፤ ውጤቱን መቀየር እንደምንችል አስበን ነበር አልሆነም “ ሲሉ አርቴታ አስረድተዋል።

የካራባኦ ካፕን “ በጣም አስቸጋሪ ውድድር “ ሲሉ የገለፁት አርቴታ ለንደን ከተመዘገበው ውጤት በኋላ የሚጠብቀን ሥራ ከባድ እንደሆነ እናውቅ ነበር ብለዋል።

“ አሁን ይህንን ረስተን ወደፊት መመልከት አለብን ዱባይ ስንሄድ እንነቃቃለን በድጋሜ ሀይላችንን እንመልሳለን “ አርቴታ

አርሰናል በቀጣይ ቀናት ወደ ዱባይ በማምራት ልምምዱን በዱባይ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።

@Tikvahethsport    @kidusyoftahe


ማርቲኔሊ በነገው ዕለት ምርመራ ይደረግለታል !

ብራዚላዊው የአርሰናል የፊት መስመር ተጨዋች ጋብሬል ማርቲኔሊ በዛሬው የኒውካስል ዩናይትድ ጨዋታ ጉዳት አጋጥሞታል።

ተጨዋቹ በጉዳቱ ምክንያት ከእረፍት በፊት በኢታን ንዋኔሪ ተቀይሮ ለመውጣት መገደዱ አይዘነጋም።

አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ከጨዋታው በኋላ በሰጡት አስተያየት ጋብሬል ማርቲኔሊ “ ነገ ምርመራ ይደረግለታል “ብለዋል።

“ የጉዳት ስሜት ነበረው ጨዋታውን ለመቀጠል ምቾት አልተሰማውም ፤ የጉዳት መጠኑን ለመለየት ነገ የ " MRI " ምርመራ ያደርጋል “ ሲሉ ሚኬል አርቴታ ተናግረዋል።

@Tikvahethsport    @kidusyoftahe


ኒውካስል ዩናይትድ ለፍፃሜ ደርሰዋል !

በእንግሊዝ ካራባኦ ካፕ ግማሽ ፍፃሜ የመልስ ጨዋታ ኒውካስል ዩናይትድ ከአርሰናል ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2ለ0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።

የኒውካስል ዩናይትድን የማሸነፊያ ግቦች አንቶኒ ጎርደን እና ሙርፊ ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል።

ኒውካስል ዩናይትድ አርሰናልን በድምር ውጤት 4ለ0 በማሸነፍ ለካራባኦ ካፕ ፍፃሜ መድረሳቸውን አረጋግጠዋል።

መድፈኞቹ በበኩላቸው ከውድድሩ ውጪ ሆነዋል።

በፍፃሜው ኒውካስል ዩናይትድ የሊቨርፑል እና ቶተንሀምን አሸናፊ የሚገጥሙ ይሆናል።

@Tikvahethsport    @kidusyoftahe


ተጠናቀቀ | ሌጋኔስ 2-3 ሪያል ማድሪድ
  
            ⚽ ⚽ ክሩዝ            ⚽ ሞድሪች
                                            ⚽ ኤንድሪክ
                                             ⚽ ጋርሺያ


- ሎስ ብላንኮዎቹ ማሸነፋቸውን ተከትሎ ለስፔን ኮፓ ዴላሬ ግማሽ ፍፃሜ ማለፋቸውን አረጋግጠዋል።

@tikvahethsport      @kidusyoftahe


82 '

ኒውካስል ዩናይትድ 2 - 0 አርሰናል

⚽ ሙርፊ
⚽ ጎርደን

ድምር ውጤት :- 4-0

@tikvahethsport      @kidusyoftahe


65 '

ኒውካስል ዩናይትድ 2 - 0 አርሰናል

⚽ ሙርፊ
⚽ ጎርደን

ድምር ውጤት :- 4-0

@tikvahethsport      @kidusyoftahe


52 '

ኒውካስል ዩናይትድ 2 - 0 አርሰናል

⚽ ሙርፊ
⚽ ጎርደን

ድምር ውጤት :- 4-0

@tikvahethsport      @kidusyoftahe


#እረፍት

ኒውካስል ዩናይትድ 1 - 0 አርሰናል

⚽ ሙርፊ

ድምር ውጤት :- 3-0

- በጨዋታው የመድፈኞቹ የፊት መስመር ተጨዋች ጋብሬል ማርቲኔሊ የጡንቻ ጉዳት አጋጥሞት ተቀይሮ ለመውጣት ተገዷል።

@tikvahethsport      @kidusyoftahe


37 '

ኒውካስል ዩናይትድ 1 - 0 አርሰናል

⚽ ሙርፊ

ድምር ውጤት :- 3-0

@tikvahethsport      @kidusyoftahe


#TikvahGoal

በአሁን ሰዓት እየተካሄዱ በሚገኙ ጨዋታዎች የተቆጠሩ ግቦችን እና አጫጭር ቪዲዮችን በጎል ቻናላችን መከታተል ይችላሉ።

የጎል ቻናላችን 👉 https://t.me/+rbdEU4UaEdQxYWFk

@tikvahethsport            @kidusyoftahe


27 '

ኒውካስል ዩናይትድ 1 - 0 አርሰናል

⚽ ሙርፊ

ድምር ውጤት :- 3-0

@tikvahethsport      @kidusyoftahe


20 '

ኒውካስል ዩናይትድ 1 - 0 አርሰናል

ድምር ውጤት :- 3-0

@tikvahethsport      @kidusyoftahe


10 '

ኒውካስል ዩናይትድ 0 - 0 አርሰናል

- ኒውካስል ዩናይትድ በአይሳክ አማካኝነት ያስቆጠረው ግብ ከጨዋታ ውጪ በሚል በቫር ተሽሯል።

ድምር ውጤት :- 2-0

@tikvahethsport      @kidusyoftahe


ተጀመረ

ኒውካስል ዩናይትድ 0 - 0 አርሰናል

ድምር ውጤት :- 2-0

@tikvahethsport      @kidusyoftahe


“ መጀመሪያ ግብ ማግባት አለብን “ አርቴታ

የመድፈኞቹ ዋና አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ቡድናቸው መጀመሪያ ግብ በማስቆጠር የስነልቦና ጫና እንዲያደርግ አሳስበዋል።

“ ጨዋታው ብዙ ስሜቶች የሚታዩበት ነው መጀመሪያ ግብ አስቆጥረን እነሱን በስነልቦና ጫና ማሳደር አለብን “ ሲሉ አርቴታ ተናግረዋል።

የቡድኑ ግብ ጠባቂ ዴቪድ ራያ በበኩሉ “ በቡድን አጋሮቼ እምነት አለኝ ለፍፃሜ መድረስ እንችላለን " ሲል ተደምጧል።

በካራባኦ ካፕ ግማሽ ፍፃሜ ኒውካስል ዩናይትድ የመጀመሪያውን ጨዋታ 2ለ0 ማሸነፉ የሚታወስ ነው።

@tikvahethsport      @kidusyoftahe


የጨዋታ አሰላለፍ !

5:00 ኒውካስል ዩናይትድ ከ አርሰናል

@tikvahethsport      @kidusyoftahe

32k 0 10 58 165

የማድሪድ የወሩ ምርጥ ተጨዋች ታውቋል !

በአሰልጣኝ ካርሎ አንቾሎቲ የሚሰለጥነው የላሊጋው መሪ ሪያል ማድሪድ የወርሀ ጥር የወሩ ምርጥ ተጨዋቻቸውን ይፋ አድርገዋል።

በዚህም መሰረት ፈረንሳዊው የፊት መስመር ተጨዋች ኪሊያን ምባፔ የወርሀ ጥር የሪያል ማድሪድ ወሩ ምርጥ ተጨዋች በመሆን መመረጥ ችሏል።

ኪሊያን ምባፔ በወሩ ባደረጋቸው ዘጠኝ ጨዋታዎች ስምንት ግቦችን ማስቆጠር ችሏል።

@tikvahethsport              @kidusyoftahe


አፄዎቹ ተከታታይ ድላቸውን አሳክተዋል !

በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ አስራ ስምንተኛ ሳምንት መርሐግብር ፋሲል ከነማ ከኢትዮጵያ መድን ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 1ለ0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።

የአፄዎቹን የማሸነፊያ ግብ አንዋር ሙራድ ከመረብ ማሳረፍ ችሏል።

በአሰልጣኝ ገብረመድን ኃይሌ የሚመራው ኢትዮጵያ መድን ከስድስት ተከታታይ ድል በኋላ የመጀመሪያ ሽንፈታቸውን አስተናግደዋል።

ፋሲል ከነማ ተከታታይ ሁለተኛ ድላቸውን አሳክተዋል።

የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?

1️⃣ ኢትዮጵያ መድን :- 32 ነጥብ
8️⃣ ፋሲል ከነማ :- 23 ነጥብ

ቀጣይ ጨዋታቸው ምን ይመስላል ?

እሁድ - ባሕርዳር ከተማ ከ ፋሲል ከነማ

ሰኞ - ድሬዳዋ ከተማ ከ ኢትዮጵያ መድን

@Tikvahethsport    @kidusyoftahe


“ መጨረሻው እየቀረበ ነው “ ሮናልዶ

ፖርቹጋላዊው የአምስት ጊዜ ባሎን ዶር አሸናፊ ተጨዋች ክርስቲያኖ ሮናልዶ የእግርኳስ ህይወቱ መጨረሻ እየቀረበ መሆኑን አውቃለሁ በማለት ተናግሯል።

በእግርኳስ ደማቅ ታሪክ ከፃፉ ተጨዋቾች መካከል አንዱ የሆነው ፖርቹጋላዊ ኮከብ ክርስቲያኖ ሮናልዶ በዛሬው ዕለት 40ኛ ዓመት የልደት ክብረ በዓሉን አክብሯል።

ሮናልዶ በሰጠው አስተያየትም “ መጨረሻው እየቀረበ መሆኑን አውቃለሁ በህይወቴ ከእግርኳስ ውጪ አዲስ ምዕራፍ ይሆናል “ ሲል ተናግሯል።

ይሁን እንጂ በዚህ ጊዜ ጫማዬን እሰቅላለሁ የሚል ቀነገደብ ማስቀመጥ እንደማይፈልግ ሮናልዶ አያይዞ ገልጿል።

ሮናልዶ አክሎም “ ወደ ስፖርቲንግ ሊስበን እመለሳለሁ የሚል ሀሳብ የለኝም “ ሲል በቀጣይ በአል ነስር ጫማውን ለመስቀል ስለማሰቡ ፍንጭ ሰጥቷል።

የሳውዲ አረቢያው ክለብ አል ነስር ከዛሬ ልምምዳቸው በፊት የክርስቲያኖ ሮናልዶን ልደት አክብረዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


ሶስቱ አናብስት በሲቲ ግራውንድ ሊጫወቱ ነው !

የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን በቀጣይ ሰኔ ወር ከሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ጋር የወዳጅነት ጨዋታ ለማድረግ ግብዣ ማቅረቡ ተገልጿል።

ጨዋታው 30,400 ተመልካች መያዝ በሚችለው የኖቲንግሀም ፎረስት ስታዲየም ሲቲ ግራውንድ እንደሚደረግ ተገልጿል።

የኖቲንግሀም ፎረስቱ ስታዲየም ሲቲ ግራውንድ ከ 8️⃣0️⃣ አመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድንን ጨዋታ የሚያስተናግድ ይሆናል።

ሶስቱ አናብስት ከቴራንጋ አንበሶቹ የሚያደርጉት የወዳጅነት ጨዋታ ሰኔ 3/2017 ዓ.ም የሚደረግ ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe

20 last posts shown.