ግብፅና ዮርዳኖስ የጋዛ ተፈናቃዮችን የማይቀበሉ ከሆነ የሚያገኙትን እርዳታ አቆማለሁ - ትራምፕ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ወደ ዋይት ኃውስ እንደገቡ የጋዛ ፍርስራሽ እስኪጸዳ ድረስ ፍልስጤማውያን እንደ ግብጽ እና ዮርዳኖስ ባሉ ሀገራት እንዲጠለሉ ሃሳብ ማቅረባቸው ይታወሳል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ፍልስጤማውያንን ከጋዛ ወደ ጎረቤት ሀገራት ለማፈናቀል በያዙት እቅድ ላይ መጽናታቸውን በድጋሚ ያረጋገጡ ሲሆን፤ ለመቀበል ፍቃደኛ ያልሆኑ ሀገራትን ማስፈራታቸውን ቀጥለዋል።
ትራምፕ ከፎክስ ኒውስ ጋር በነበራቸው ቆይታ “ፍልስጤማውያን ከጋዛ በቋሚነት ይወገዳሉ” ሲሉ ተናግረዋል።
ፍሊስጤማውያን መቼ ወደ ጋዛ ይመለሳሉ ተብለው የተጠየቁት ትራምፕ፤ “አይ አይመለሱም፣ ምክንያቱም የተሻለ መኖሪያ ቤት ያገኛሉ፣ በሌላ አነጋገር እኔ የማወራው ለእነሱ ቋሚ መኖሪያ ቤት ስለመገንባት ነው” ብለዋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ አክለውም “በርካታ ፍሊስጤማውያንን አነጋግረናል፤ ሌላ የሚኖሩበትነን ስፍራ ካገኙ ጋዛን መልቀቅ እንደሚፈልጉ ነግረውናል” ሲሉም ገልጸዋል።
የጋዛ ተፈናቃይ ፍሊስጤማውያንን ለመቀበል ፍቃደኛ ያልሆኑ ሀገራትን በተመለከተም ዶናልድ ትራምፕ “እኛም ለእነሱ የምንሰጠውን እርዳታ እናቆማለን” ሲሉ ዝተዋል።
ግብፅ እና ዮርዳኖስ ፍሊስጤማውያንን ለመቀበል ፍቃደኛ ካልሆኑ ከአሜሪካ የሚያገኙት እርዳታን ሙሉ በሙሉ እንደሚያቋርጡም ነው ትራምፕ ያስታወቁት።
https://t.me/voa_amharic1https://t.me/voa_amharic1