The Home of all የሁሉም ቤት


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Edutainment


Well come to the home of all in this channel all things about human being life post every day
* Motivate for free
* learn for free
* earn more for free
Buy ads: https://telega.io/c/+LiBy-b_3bjIyMjk0
══════❁✿❁═════════

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Edutainment
Statistics
Posts filter


♥️ ተማሪዋ ♥️
🌹...ክፍል 17...🌹

"አንቺን ከማፍቀሬ ዉጪ ምንም የሆንኩት የለም አልኩሽ እኮ ቃልዬ!"
"ታድያ ፍቅር ድብርት ይለቃል እንዴ ኤፍዬ••••?"
"አንዳንዴ!" አልካት።
"አንዳንዴ ማለት ምን ማለት ነው•••?"
"እራሱን ፍቅርን ጠይቂው እኔ ምን አውቃለኩ!"
"እና በምን ምክንያት እንደደበረኽ አታውቅም•••?
እያለችኝ ከቦርሳዋ ውስጥ ስልኳ ጠራ ። እጇን ከአንገቴ ላይ  ልታነሳና ስልኳን ከቦርሳዋ ልታወጣ ስትል አንገቴ ላይ ያለውን እጇን ያዝ አደረኩት።
ግራ በተጋባ ስሜት ትክ ብላ ብላ ስታየኝ•••
"እቀፊኝ እኔ አወጣልሻለሁ !" ብያት ቦርሳዋን ብድግ ሳደርገው።"ኪኪኪኪ •••ኧረ የሴት ቦርሳ ማየት ነውር ነው ኤፍዬ!"
"ምንም አላይም እሄው እጄን ልኬ ሞባይልሽን ብቻ ማውጣት " እያልኳት አይን አይኗን እያየሁ ስልኳን ከቦርሳዋ ውስጥ አውጥቼ እንደጨረስዩ የቦርሳዋን ዚፕ ዘግቼ ፊት ለፊታችን ባለው  ጠረቤዛ ላይ አስቀመጥከትና ።
ስልኳን እኩል ተመለከትነው።
የደወለው ዛኪ ነው! •••ተፋጠጥን፣  እንደተለመደው ከኔ መቶ ሜትር ርቃ እንዳታናግረው እንዳትነሳ •••አንገቴ ላይ ያለውን እጇን በግራ እጄ ያዝኩትና ••••
"ዛኪ ነው ደዋይሽ እንቺ አናግሪው!" አልኳት በቀኝ እጄ የያዝኩትን ስልክ እንድትቀበለኝ ወደሷ ጠጋ እያደረኩ። አልተቀበለችኝም ። ስልኳ እየጠራ ነው ።
ጥያቄ ባዘሉ አይኖቿ አንገቷን ወደ ቀኝ ዘመም አድርጋ በዝምታ አየችኝ።  እንደትቀበለኝ በአይኔ ወደ ስልኩ እያመለከትኳት እኔም ዝም ብዬ አየኋት•••ምንም ቃል ካፏ ሳይወጣ ስሜቱ ከአስተያየቷ የተቀዳ የሚመስል የግርምት ፈገግታ ወደ ጎን ፈገግ አለችና  ስልኩን ተቀበለችኝ። ዘገም ብላ ወደ ጆሮዋ አስጠጋችው።
እሷም እያየችኝ እኔም አይን አይኗን እያየኋት ነው።
"ሄ. ሄሎ ዛክ"
"ወዬ አዎ ይሰማኛል"
"አይ አይደለሁም። ኖኖ ቤተመፅሀፍትም አይደለሁም። እቃ ለመግዛት  ወደ ከተማ ወጣ ብያለሁ። 'አረዲ ' እየመሸ ነው•••'ኤኒዌይስ' እደውልልሀለሁ"
"እሺ ቻው!"
ተዘጋ። በቃ ይህንን ብቻ ብላ ወሬኣቸው አብቅቶ ስልኩ ተዘጋ።  እኔን ያቀፈችበትን እጇን በቀስታ አውርዳ ቦርሳዋን አነሳችና ስልኩን ቦርሳዋ ውስጥ ከተተችው።  ከልጁ ጋር ያወራችው ነገር ምንም ፍንጭ የማይሰጥ ድፍንፍን ያለ ነገር ሆነብኝ። ምን እንደምል ስለቸገረኝ እሷው የሆነ ነገር እስክትለኝ መጠባበቅ ጀመርኩ።
ያደረኩት ነገር ትክክል ይሁን ስተት ለማወቅ ቃልዬ  ቀጣይ የምትለኝን መስማት እንጂ በራሴ ትክክል ነው አልያም ስተት ነው ብዬ ለመደምደም ተሳነኝ ፣ ምክንያቱም ቃልዬ እንዲህ ሳደርግ ምን ይሰማት ይሆን? በሚል የተብሰለሰለ ስሌት ሳይሆን  ዛኪዋ በደወለባት በዛች ቅፅበት አጠገቤ ሆና እንድታናግረው ማድረግ እንዳለብኝ ባዘዘኝ ስሜት ተመርቼ ነበር አጠገቤ ሆና እንድታናግረው የተጫንኳት።
ያንን ያደረኩት ስለማፈቅራት ነው። ይሄ ሰው በደወለ ቁጥር ለምን እና ምን ለማውራት ካኔ አጠረብ ዘወር እንደምትል ውስጥ ውስጤን ሲከነክነኝ ውሎ ማደሩን ባልክድም   ያለ ፍላጎቷ እኔው አጠገብ ተቀምጣ እንድታወራ አስገድዳታለሁ ብዬ ጭራሽ አላስብኩም ነበርና ከማድረጌ በፊት ሳይሆን ካደረኩት በኋላ ምን ይሰማት ይሆን በሚል ጭንቀት ውስጤ መናጥ የጀመረው ወድያው ነበር።
ምክንያቱም በዚህ ምክንያት በኔና በቃልዬ መካከል አለመግባባት ቢፈጠር ያንን ለማስተናገና እንደአመጣጡ ለመቀበል  ዝግጁ አልነበርኩም።

ስልኳን ቦርሳዋ ውስጥ ካስገባች በኋላ ወደኔ ዞራ አልተመለከተችም። ከጠረጴዛው ላይ አጋምሳ ያስቀመጠችውን ውሃ አንስታ ጠጣችና ባዶውን ብርጭቆ ጠረጴዛው ላይ አንዴ ወደ ግራ አንዴ ወደቀኝ በቀስታ እያሽከረከረች ዝም አለች።

በቃ ለሶስት ለአራት ደቂቃዎች ዝም አለች። ጨነቀኝ። አራቱ ደቂቃ የአርባ ደቂቃ ያህል ረዘመብኝ።
በዝምታዬ ለመዝለቅ ወኔ አጣሁ። አስባ አስባ ድንገት  ካጠገቤ ብድግ ብላ የምትሄድ መስለኝ።
እንዴ ወዴት ነው ? ምናምን  እያልኩ ክንዷን ይዤ ላስቆማት  ስሞክር•••  አትንካኝ ብላ የምትጮኽብኝ፣ ምን ሆንሽ  ቃልዬ ስላት •••አትጥራኝ ! እንዳትከተለኝ ብላኝ ስትሄድ በአይነ ህሊናዬ ታየኝና ከእንቅልፉ ውሃ ተረጭቶበት እንደነቃ ሰው ብትት አደረገኝ።
"ቃቃቃ •••ቃልዬ!" አልኳት በደነገጠ ድምፅ።"ወዬ ኤፊ !" አለችኝ አይኗን ከብርጭቆው ላይ ሳትነቅል። በረጅሙ ተነፈስኩና••••
"ምነው ዝም አልሽ?" አልኳት።
"አንተስ ምነው ዝም አልክ?"
"አንቺ ዝም ስትይ"
"እኔም እንደዛው"
"እንደዛው ማለት?•••ደበረሽ እንዴ?"
"ምኑ?"
"እኔ እንጃ!
" አንተስ ደበረህ እንዴ?"
"ምኑ ነው የሚደብረኝ ቃልዬ?"
"እኔ እንጃ"
በመካከለችኝ እንደድቅድቅ ጨለማ የሚያስፈራው ድቅድቅ ፀጥታ መልሶ ሰፈነ።
እኛ ጋር ብቻ ሳይሆን አለም ሁሉ ዝም፣ ጭጭ፣ ረጭ ያለ መሰለኝ። እንዴት ይጨንቃል!"
"ኧረ ቃልዬ!" አልኳት ክንዷን ያዝ አድርጌ።ዝም አለች።
"እእእ •••እኔኮ አቅፈሽኝ ስለነበር  በቃ ለማናገር እንዳትነሺና  እንደዛው አቅፈሽኝ እንድንቆይ ስለፈለኩ ነው።  ከዛ ቦርሳውን ከፍተሽ  ስልክሽን ለማውጣት ስለናይመችሽ  ብዬ ነው ያቀበልኩሽ፣   ምን መስሎሽ ነው ቃልዬ?"
"አዎ ገብቶኛል ኤፊ !
" እና እንደዛ ማድረጌ ደበረሽ ቃል?
"አልደበረኝም ! ለምን ይደብረኛል ፣ ቢደብረኝ ለምን አናገርኩት?"
አለችኝ።  በአነጋገሯ ብስጭት አልኩ በውስጤ። አንዴ ተነካክቻለሁ እንግዲህ  ቃልዬ መናደዷ ካልቀረ ልግፋበት አልኩና•••
"ቆይ ማነው ዛኪ?" አልኳት ፈርጠም ብዬ።ቆይ ማነው ዛኪ?" አልኳት ፈርጠም ብዬ።
"ለምን ማወቅ ፈለክ?"
"እንዴ ! ለምን ማወቅ ፈለክ ከማለት እገሌ ነው ማለት አይቀልም ቃል?"
"እሺ ዛኪ ነው!" ብላኝ እርፍ።
"ምን ማለትሽ ነው?"
"እንዴ እገሌ ነው በይኝ እላልክም ኤፊ ?ዛኪ ነዋ  ታድያ ማን ልበልህ?"
"ጥያቄዬ ስላልገባሽ ነው ወይስ እያላመጥሽ ቃል?"
"አልገባትም ብለህ ካሰብክ እስኪገባኝ አስረዳኛ ኤፊዬ!"
"እሺ ዛኪ የት ነው?"
"እህህህም ግቢ ነዋ ስናወራ ሰምተህ የለእንዴ?" አለችኝ የግርምት ፈገግታ ፈገግ ብላ በጨረፍታ አይታኝ ወደ ብርጭቆው እየተመለሰች።
"ገባኝ የግቢ ተማሪ ነው ፣ አንድ ላይ ነው የምትማሩት ማለት ነው?"
"አዎ ነው!" ብላኝ ዝም
20 ላይክ ቡኋላ ክፍል 18 ይለቀቃል🌹


♥️ ተማሪዋ ♥️
🌹...ክፍል 16
የቷ ቃል ኪዳን••••?!"
"አንቺ ነሽ ሌላ ቃልኪዳን የት አውቃለሁ እኔ !"
"ሂድ ወደዛ አቦ ••••ምንድን ነው ግራ የምታጋባኝ!"
"ግራ ገብቶኝ ነዋ ቃልዬ!"
"እብድ ነገር ነህ!"
"ስላሳበድሽኝ አመሰግናለሁ እሺ•••••? በፍቅር ማበድ ግን  እንዴት ደስ ይላል ቃልዬ ••••? !"
"ኧረ ባክህ •••••በል እራስህን ችለህ  ብቻህን እበድ ኪኪ•••! እሺ እንዲሁ ሳስበው በወሬኣችን መሀል  ስለትራፊክ ህግ የምታወራው ተያይዘን እንድናብድ ስለፈለክ ሳይሆን አይቀርም. ኪኪኪኪኪ " አለች ።
እንደምንም ስትደውል ባለማንሳቴ ምክንያት የደበራትን ቃሌን ፈገግ አሰኘኋት።ለቃልዬ እንደዛ ብላትም እኔ ግን እንደዛ  የሳቅኩበት ሌላም ምክንያት ነበረኝ።
ያ ገራዥ የሚሰራው አብሮኝ የሚኖረው ጓደኛዬ ገና ስራውን በጀመረ ሰሞን የጠበሳት ልጅ ወሬው ሀሉ ስለመፍቻና እና ስለመኪና መለዋወጫ ሆኖባት።
ገራዥ የምትሰራ ሴት ፈልገህ ጥበስ እኔ በቃኝ!" እንዳለችው ትዝ ብሎኝ ነው። ያንን ሁኔታ እያነሳሁ ለወራት ጓደኛዬን ለማብሸቅ ተጠቅሜበታለሁ። ዛሬ ቃልዬ እንዲህ ስትለኝ ትዝ ያለኝ እሱ ነበር ። ለካ ወዶ አይደለም ጓደኛዬ አልኩ በልቤ።
"እሺ ስልኩስ ምን ሆኖ ነው ከእጅህ ላይ የወደቀው•••?" አለች ቃል።
"እያወራሁሽ ምህረት የለሹ ትራፊክ ከፊቴ መጥቶ ነዋ!•••ትንሽ ስተት ካየ ከሩቅ ነው የቅጣት ደረሰኙን እንደባንዲራ  እያውለበለበ የሚመጣው! ልመና አይገባው ምህረት፣  በቃ እሱ ደረሰኙን እያውለበለበ ሲመጣ አንቺ ብርሽን እያውለበለብሽ መጠበቅ ብቻ ነው ያለሽ አመራጭ! ፣ በቃ እንዳየሁት ስልኩን ለቀኩት ያው ባጃጅ ውስጥ ስለሆንኩ ስልኬ ምንም አልሆነም ወንበሩ ላይ ነው የወደቀው!"ስላት
" ኤፊዬ በቃ ወሬህ ከትራፊክ እና ከትራፉክ ህግ ሲወጣ ደውልልኝ እሺ ቻው !" አለችኝ ። ቻው ማለት አልቻልኩም ስልኩን ላለመዝጋት ብቻ  ስቄ እስክጨርስ ጠበቀችኝና••••
"ቻው በቃ!"  ብላ ዘጋችው።

እህህህህ አይ ቃልዬ። ስልቹ ነገር ነች ግን ። አሁን እንደዚህ ስትማረር በተገናኘን ቁጥር ስለትራፊክ ህግ እያወራሁ ያሰለቸኋት አትምመስልም። ያንን ጓደኛዬን ይዘዝብሽ አቦ በመፍቻ እና በመኪና መለዋወጫ እቃ ወሬ እያደነቆረሽ በህልምሽ ሁላ ገረዥ ብቻ እንዲታይሽ ያደርግሽ ነበር። ወጣም ወረደ አምልጦኝ ስቀባጥር ከገባሁበት ወጥመድ አምልጫለሁ። ካሁን ወዲህ እውነቱን ማጥመድ ብቻ ነው የኔ ስራ!።  እያልኩ ትንሽ ዘወር ዘወር ብዬ ሰራሁና በግዜ ወደ ቤት ገባሁ።
ቃልዬ ቅዳሜ ነው የምንገናኘው ብትለኝም በኔ ውትወታ አርብ አመሻሹ ላይ ለመገናኘት ተስማምታለች። ሰአቱ እየደረሰ ነው ። ያው ትናት ስላየሁት ነገር ምንም ነገር ትንፍሽ ላልል ለራሴ ቃል ገብቼ ላገኛት እየሄድኩ ነው።
ተገናኝተን ትንሽ እንደቆየን ግን ••••
"ቃልዬ!"
"ወዬ ኤፊ"
"ስንት የቅርብ ጓደኞች አሉሽ•••?"
"የቅርብ ጋደኛ •••? እዚህ ነው ነው አዲስ አበባ ኤፍዬ•••?"
"አይ እዚህ"
"እዚህ የለኝም ! አሉኝ ግን ያው ያን ያህል ነው ፣ ያን ያህል ማለት ወሰን ወይም ድንበር ያለው ቅርርብ አለ አደል በጋራ ጉዳዬች እና በትምህርት ዙርያ እንጂ ከዛ ያለፈ የግል ሚስጥሬን የማካፍላት በተለየ ሀኔታ የምቀርባት ጋደኛ የለችኝም"
"የወንድስ•••?" ልላት ብዬ ፈርቼ ተውኩትና በረጅሙ ተንፍሼ ዝም አልኩ።
"ኪኪኪኪኪ እንዴ ምነው በሀይል ተነፈስክ•••? ቆይ ለምን ጠየቅከኝ•••?
" ለምንም እንዲሁ ለማወቅ!"
"ዛሬ ግን ፉትህ ላይ የሚታየው ስሜትም መድህም ልክ አይደለም ሌላ ሰው ሆንክብኝ በሰላም ነው ኤፊዬ•••?   እቤት ሰላም ናቸው አይደል••••?"
"ደና ናቸው ቃልዬ!"
ከፊት ለፊቴ ተነስታ አጠገቤ ከጎኔ ተቀመጠችና እቅፍ አድርጋኝ•••
"ምን ሆንክብኝ ኤፊዬ•••? ምንድን ነው የሆንከው•••? እስቲ ንገረኝ•••!"
"ምን ሆንኩ ቃል •••? ምንም አልሆንኩም እኮ!"
" ስሜትህ  እኮ ልክ አይደለም ታድያ•••!"
ዝም አልኳት። እንዳቀፈችኝ በፀጥታ  ቆየን።
ሌላ ነገር ማውራት ሌላ ነገር ማሰብ ተሳነኝ፣ ስሜቴን መደበቅ ለይስመላ መሳቅ መጫወት አቃተኝ።
ፊቴ ላይ ቶሎ ቶሎ የምትመጣብኝ አሁን ከኔ ጎን የተቀመጠችው ቃል ኪዳን ሳትሆን ከዚራ መንገድ ላይ በሌላ ወንድ እቅፍ እና ጉያ ውስጥ ሆና ስትሄድ ያየህኋት ቃል ኪዳን ነች።
እኔ ሳልሆን ፍቅር የማስበውን ፣  የምናገረውን ፣ የማሳየውን ስሜት እስከመወሰን ሙሉ በሙሉ እንደተቆጣጠረኝ  አምኖ ካለመቀበል የመጣ ስህተት መሆነን አሰብኩ።
ብዙ ነገሬች መራራም ጣፋጭም ጎን አላቸው፣ ፍቅርም እንደዛው።
ለኔ ግን ጣፋጭ ጎኑን ደብቆ   መረር ካለው ጎኑ እንድጀምር  ተሰማኝ። ፍቅርን ታዘብኩት።
የንን ምስል መርሳት ያንን መጥፎ ስሜት መደበቅ አልችል አልኩ። እንደፎከርኩት የውስጤን በውስጤ ይዤ እንደበፊቱ ኤፍሬም መሆን የማይሞከር እውነት የማይወጣ አቀበት ሆኖብኝ ።
ከሷ ጋር ቁጭ ብዬ ከራሴ ስሜት ጋር ትግል ገጠምኩ፣ ትግሉን ግን በአሸናፊነት መወጣት አልቻልኩም ወሬዬ ሁሉ ከጥያቄ ውጪ ሊሆን አልቻለም •••
"ቃልዬ !"
"ወዬ ኤፊ!"
"ከግቢ ውጪ •••ማለት እዚህ ተመድበሽ መማር ከጀመርሽ በኋላ የተዋወቅሽው እና የምትቀርቢው የድሬ ሰው አለ እንዴ••••?
" የድሬ ሰው ማለት•••?"
"፣የድሬ ልጆች ማለቴ ነዋ!
" ብዙ የድሬ ልጆች ግቢ ይማራሉ እኔ በመጠኑ የምቀራረበው ግን ከአንዲት ልጅ ጋር ብቻ ነው!"
እኔ መጠየቅ የምፈልገው ሌላ የምጠይቅበት መንገድ ሌላ። እሷም እንድትነግረኝ የምፈልገው ስለወንድ ጓደኞቿ  የምትነግረኝ ግን ስለሴት ጓደኞቿ ብቻ ። በግልፅ አለመጠየቄ ያመጣው ውጤት መደናቆር ብቻ ሆነ።
አሁንም••••"እሺ !!" ብቻ ብያት ዝም አልኩ። ቃልዬ ግራ ገባት።ዝም ስል ይጨንቃታል። ተጫወት ብላ ትወተውተኛለች። ወሬ የምጀምረውም የምጨርሰውም  በጥያቄ ብቻ ሆነ። በአንደበቷ ባትናገረውም በሆዷ ግን••••
"ይሄ ልጅ ባጃጅ ሹፌር ከመሆኑ በፊት ወይ መርማሪ ፖሊያስ ወይም ደሞ ጋዜጠኛ ነበር መሰለኝ!" ብላ ሳትደመድም አትቀርም።
ፍቅር ግን  ይገርማል!።  በዛ ሁኔታ ውስጥም ሆኜ ቃልዬ የደበረኝ ስለመሰላት ከሌላ ግዜው በተለየ ሁኔታ ስትጨነቅልኝ ፣ በተለየ ሀኔታ ስታየኝ እና ስታቅፈኝ ሰውነቴ በደስታ ስሜት ይግል ነበር።
• አንዴ አንገቴን አንዴ ጣጦቼን በጣቶቿ መሀል እያስገባች ስትደባብሰኝ   ነፍሴ ሀሴት ታደርግ ነበር ። በህመምም ውስጥ ደስታ ማለት ይህ ስሜት ይሆን እንዴ እላለሁ ለራሴ።ምን እንደሆንኩ ለማወቅ ደጋግማ ስትጠይቀኝ ምንም አልሆንኩም ስላት ቆየሁ። የሆነ የሆንኩት ነገር ኖሮ እየደበኳት እንደሆነ ታውቋት ይሁን•••• ስራዋን ስለምታውቅ ብቻ መጠየቋን መተው አልቻለችም።
"ቆይ ምን እንደሆንክ ለምን አትነግረኝም••••!?"
20 ላይክ ቡኋላ ክፍል 17 ይለቀቃል🌹


♥️ ተማሪዋ ♥️
🌹...ክፍል 15.
" ወጣ ብዬ ነበር ፣ አሁን ግቢ ገባሁ አንተ ግን ቅድም ባልተለመደ ሰአት የደወልከው በሰላም ነው•••?"
"ቤት በኩል  ገባሽ••••? •••••ደሞስ ያልተለመደ ማለት ምን ማለት ነው  ••••? " አልኳት። በዛች ቅፅበት  በመደወሏም  በጥያቄዋም ድንብርብሬ ወጥቶ ።
"ምን••••? ቤት በኩል ስትል ••••? አልገባኝም ኤፍዬ ምን ለማለት ፈልገህ ነው•••?"
"ቤት በኩል••••? የምን ቤት በኩል ••••? ቤት በኩል አልኩ  እንዴ ቃልዬ•••? ኧረ አላልኩም! "ስላት•••
"ኪኪኪኪኪኪኪኪ•••••!" ያንን ሳቋን ጆሮዬ ላይ ስትለቀው ይብስ ተደነባብሬ ስልኩ ከእጄ ላይ ወደቀ።
••••ቆይ ግን ሳቅ ሳቅ ያለው በምን ይስቃል••••• የሚል ተረት አልተረቱም እንዴ ሰዎቹ •••? ለበጎ ነው ። ስልኬ በወደቀበት ቅፅበር - ድንገት አዳልጦኝ ይሁን አምልጦኝ በጥየቋት ጥያቄ •••በምላሹ የተሰነዘረብኝን  አደናግር ጥያቄ  በምን መልኩ ማለፍ እንዳለብኝ ትንሽ ለማሰብ ግዜ አገኛለሁ••••እያልኩ ገናስልኬን ከወደቀበት ሳነሳው ደግማ ደወለች።
ለመጀመሪያ ግዜ የቃልዬን ስልክ ላለማንሳት መጨከን ቻልኩ። ጠርቶ ጠርቶ እንደዘጋ አፍታም ሳትቆይ አሁንም ደወለች፣
ምን እንደምላት እርግጠኛ ሳልሆን ማንሳት አልፈለኩም። አፍ ሲከዳ መጥፎ ነው። "ቤት በኩል አለፍሽ•••? የሚል ጥያቄ እንዴት ከአንደበቴ እንደወጣ ፈጣሪ ይወቀው። ይህን ግራ የገባው ጥያቄ አንስቼ " ቤት በኩል ገባሽ ስትል ምን ለማለት ፈልገህ ነው••••?" ስትለኝ
ምን ልበላት••••? እየተከታተልኳችሁ ስለነበር ቤት በኩል ሸውዳችሁኝ ወደ ግቢ እንዴሄዳችሁ ግራ ገብቶኝ ነው ።ወደ ግቢ የምትሄዱ ከሆነ ፣ ከነበራችሁበት ከከዚራ ወደላይ መኮረብ ለምን አስፈለጋችሁ•••?  ከዛው ቆማችሁበት ከነበረው ቦታላይ •••• ፊታችሁን ወደ ባቡር ጣብያው መልሳችሁ በለገሀር ወደ ነምበር ዋን ፣ ከነበርዋን በአዲሱ መንገድ ቀጥታ ወደ ግቢ መሄድ ትችሉ ነበር፣ በዛ መሄድ ካልፈለጋችሁ ደግሞ•••  ቀጥታ ወደ ዲፖ መጥታችሁ ሽቅብ ወደሳብያን በመውጣት ወደ ዩንቨርስቲው መሄድ ትችሉ ነበርኮለምንድን ነው ቀጥታ ወደላይ ወደ ኮኔል አልያም ወደ ሼል ወደሚወስደው መንገድ ወጥታችሁ እናንተም ዙርያጥምጥም ሄዳችሁ  እኔንም የሸወዳችሁኝ •••?  አልላት ነገር ተቸግሬ በማይታመን ሁኔታ ቤት በኩል ገባሽ የሚል ነገር አልተናገርኩም ብዬ ካድኳት።
በዛች ቅፅበት ቀላሉ እና ማሰብ ማሰላሰል የማያስፈልገው  መንገድ መካድ ብቻ ነበር። ምክንያቱም መካድ ምክንያትም ማስረዳትም አይጠይቅም። ብለህም ቢሆን በቃ አላልኩም ካልክ አላልኩም ነው ። አይተህም ቢሆን እአላየሁም ካልክ  አላየሁም ነው።  ነገር ግን መካድ ወይ በቀጣይ እንዳትታመን ያደርግሀል ፣ ወይ ጤንነትህ ጥያቄ ምልክት ውስጥ እንዲገባ ምክንያት ይሆናል።
በተናገርኩ በሰከንዶች ውስጥ አላልኩም ብዬ ስክዳት ምን ነካው ኤፊ ጤነኛ ነው ግን••?  ነው ፍቅር የሚናገረውንም አሳጥቶ ያስቀባጥረው ጀመር ብላ በማሰብ ይሆናል እንደዛ የሳቀችብኝ እንጂ መካዴ  ሳቅ የሚጭር  ሳይሆን ምናልባትም የሚያናድድ ነው።
ቆይ ፍቅር ግን ፍትሃዊ ነው•••? እሷን ከወንድ ጋር አየኋት እንጂ እኔን ከሴት ጋር አላየችኝ ታድያ መደናበር ፣መርበትበት የነበረባት እሷ እንጂ እኔ ነኝ እንዴ! እሷ እየሳቀች እኔ ማጣፊያው አጥሮኝ ግራ መጋባቴ ምን ይሉታል?
እርግጥ ነው እኔ የተደናበርኩት ከልጁ ጋር ተቃቅፋ ስትወዛወዝ እንዳየኋት እንድታውቅ ስላልፈለኩ ነው።
ስለዚህ ጉዳይ በተለይ አሁን ላይ እንድናወራ አልፈልግም። ከወንድ ጋር አየሁሽ! ልጁ  ማነው•••? ምንሽ ነው•••? ብዬ መጠየቅም የለብኝም።
እኔ በራሴ መንገድ እውነቱን ሳላጣራ እና ሳላውቅ አየሁሽ ገለመሌ ብሎ መጠየቅ •••በቀጣይ እንድትጠነቀቅ የማንቂያ ደውል ከመደወል ያለፈ ለኔ የሚፈይድልኝ ነገር አይኖርም።
ቃልዬን መጣላት እና ማጣት አልፈልግም።  ነገር ግን እንዳጣት የማልፈልገው እኔም የሷ ፣ እሷም የኔ ብቻ ከሆነች ብቻ ነው። ከዛ ዉጪ ያለው መንገድ ከደስታው ስቃዩ ያመዝናል።
ቃልዬ አታደርገውም እንጂ ምናልባት ከልጁ ጋር ሌላ ግኑኝነት ካላት አሁን ላይ ምንሽ ነው•••? ብዬ ብጠይቃት •••
"ምንም •••••! በቃ ምኔም አደለም! እንቀራረባለን አለቀ !". ትለኝና የኔን ጥያቄ ባጭሩ ቀጭታው እሷ በድብቅ አለሟን እንድትቀጭ ከማድረግ ያለፈ ሌላ ነገር ትለኛለች ብሎ ማሰብ መጃጃል ነው።
በሁለቱ መሀል ያለው ነገር ለኔ ጥሩም ይሁን መጥፎ ዜና ፣ እውነቱ ላይ መድረስ ያለብኝ በራሴ መንገድ እንጂ እሷን በማወጣጣት አይደለም።
ስለዚህ ምንም ፍንጭ ማሳየት የለብኝም። ቢሆንም ግን አልኩና ••••• " አፈቅራታለሁና በቃልዬ እና በኔ መካከል ችግር እንዲፈጠር አልፈልግም!" አልኩት ፈጣሪዬን ወደ ባጃጄ ጣራ ቀና ብዬ ።
ትንሽ ሄደት  እንዳልኩ ለቃልዬ ልደውልላት ስልኬን በእጄ እንደያዝኩ ከፊት ለፊቴ ምህርት የለሹን ትራፊክ ስላየሁር እሱን አለፍ ብዬ ባጃጄን ጥግ አስይዤ  አቆምኩና  ደወልኩላት።
ትራፊኩን ማየቴ ጥሩ ምክንያት ለጭንቅላቴ ስላቀበለው ምን እንደምላት እርግጠኛ ሆኜ ነበር የደወልኩት።
አንስታው ዝም አለችኝ።
"ሄሎ•••ቃልዬ •••ሄሎ ••••ቃል!"
"ለምን ደወልክ•••••?  መዝጋትህ ሲገርመኝ ጭራሽ ስደውል አለማንሳትህ •••አኩርፌሀለሁ እሺ ቆይ ምን ሆነህ ነው•••?
" አታኩርፊኝ ቃልዬ! ••• ዘግቼብሽ ሳይሆን ስልኩ ከእጄ ላይ ወድቆ ነው፣ ስትደውይ አለማንሳቴ ግን ግድ ነበር!"
"ግድ ነበር ማለት••••?"
"ሁለተኛውን የትራፊክ ህግ ለማክበር!"
"እየቀለድክ ነው ኤፊ••••?"
"ኧረ በጭራሽ ቃልዬ እየቀለድኩ አይደለም ከዚህ በፊት አንዱን አክብረናል ዛሬ ደሞ ሁለተኛውን ማክበር ስላለብን ነው ያላነሳሁት!"
"እህም ምን እያልክ ነው ከዚህ ቀደም እኔና አንተ ብቻ ያከበርነው የትራፊክ ህግ አለ እንዴ?"
"በደንብ እንጂ ቃልዬ ሁሉ ነገር ቢረሳ ያቺ ቀን ትረሳለች እንዴ•••? እኔና አንቺ በተዋወቅን ምሽት አብረን እንድናድር ያስገደደችን እኮ ከጠጡ አይንዱ የምትለው የትራፊክ ህግ ነች።  አሁን ደግሞ እየነዱ ስልክ አያናግሩ በተለይ ከፍቅር ጓደኛዎ ጋር እያወሩ መንዳት ያጋልጣል ለጉዳት ምክንያቱም ልቦ በፍቅረኛዎ ቃል ስለሚወሰድ ልብ ብሎ መንዳት አይቻልም ። ልብ ብለው ካልነዱ አይለይም ገደል እና መንገዱ !" ስላት ብሽቅ ብላ ቆይ አንተ ግን በቅርብ ነው እንዴ መንጃ ፍቃድ ያወጣኸው•••?"
"ማለት•••?" አልኳት።
"እኔ ምን አውቃለሁ የፍቅር እና የትራፊክ ህግ ተደበላልቆብሀልኮ ! ••አብረን ያደርነው የትራፊክ ህግ ለማክበር እእእእእ ስልኬን የማታነሳው የትራፉክ ህግ ለማክበር ••ቆይ የኔና ያንተ ፍቅር የሚመራው በትራፊክ ህግ ነው እንዴ!"
ስትለኝ የንግግሯ ቃና እና በንዴት እየተንተባተበች ቶሎ ቶሎ ቶሎመናገሯ ፣ ከተናገርችው ነገር ጋር ተደምሮ  ከነበርኩበት የመከፋት ስሜት ፈንቅሎ ከልቤ አሳቀኝ። በእርግጠኝነት ወላጆቼን ሞት ከነጠቀኝ በኋላ ለመጀመሩያ ግዜ ነበር እንደዚህ ከልቤ የሳቅኩት።"

20 ላይክ ቡኋላ ክፍል 16 ይለቀቃል🌹


GOOD MORNING
#ሕይወት_ምንድን_ነው ?
ህይወት በተሻለ መንገድ ለመረዳት ወደ 3 ቦታዎች መሄድ አለብህ:
         1. ሆስፒታል
         2. እስር ቤት
         3. መቃበር
#በሆስፒታሉ ውስጥ ከጤና በላይ ምንም ነገር እንደሌለ ትገነዘባለህ።
:
#በእስር ቤት ነፃነት በጣም ውድ ነገር እንደሆነ ትገነዘባለህ።
:
#በመቃብር ውስጥ ሕይወት ምንም ዋጋ እንደሌለው ትገነዘባለህ።
:
የዛሬ የምንሄደው መንገድ የነገ የሕይወታችን መሰረት ነው። ስለዚህ ትሁት እና አመስጋኝ ሁን። ስለ ሁሉም ነገር እግዚአብሔር ይመስገን!
              ❤️ መልካም ቀን ❤️


♥️ ተማሪዋ ♥️ ...
           .
           .
🌹...ክፍል 14...🌹
አዎ  ተደብቄ ከምከታተላት ይልቅ ቀጥ ብዬ  ሄጄ ድንገት እንዳየኋት ሆኜ በራሷ አንደበት ከማን ጋር ምን እየሰራች ፣ ወዴት ልትሄድ?   ማንን እየጠበቀች?  እንደሆነ ብትነግረኝ ነው  የሚሻለሁ። ግን እኮ የምከታተላት ሊመስላት ይችላል።
ያኔ ኤፍሬም ተጠራጣሪ ነው ብላ ልትጠላኝም ትችላለች።
ምናልባት እኔ እንዳስብኩት ካልሆነና እሷ የሰራችው ስተት ከለል እራሴው ላይ ነጥብ አስቆጥሬ ። እንዲሁም ጨቅጫቃ ሳልሆን ጨቅጫቃ መስያታለሁ ጭራሽ ከጀርባ የምከታተላት ተጠራጣሪ ወንድ እመስላትና ይለይላታል።
አዋ ! አሁን ደውላ አናግራኝ የለ እንዴ! በደቂቃዎች ልዩነት ድንገት ስራ  ላይ እያለሁ በዚህ በኩል ሳልፍ አይቼሽ ነው ብላት በጭራሽ አታምነኝም። በዛ ላይ እሷ የምታውቀው ቀን ቀን ሳይሆን ማታ ማታ እንደምሰራ ነው። ቀን እሷን ለማግኘት ስል ከሷ ጋር ቀጠሮ ሲኖረኝ ብቻ እንደምወጣ እንጂ ስራዬን ወደ ቀን እንዳዞርኩት እስካሁን አልነገርኳትም። ስለዚህ ትናንት ነገ አይመቸኝም ስላለችኝ  ሆን ብዬ እሷን ለመከታተል ግቢ በር ላይ አድፍጬ የጠበኳት ነው የሚመስላት ።
አቦ ፍቅር የስራህን ይስጥህ እሺ ሌላ ምንም አልልህም።
ገና ያየሁትን ያየሁት እኔ እያለሁ ይመስላታል አይመስላትም እያልኩ ለሷ ልጨነቅ ወይኔ ኤፍሬም !፣ የምከታተላት ቢመስላትም ይምሰላታ በቃ!  ካሁን ቡሃላስ ቢሆን ይቀርላታል እንዴ !? እቺ ሀሙስ ቀንማ ሚስጥሯ መታወቅ አለበት። ይሄ አብሯት ያለው ልጅ የግቢ ልጅ ይሁን አይሁን?፣ ከሷ ጋር ምን አይነት ግኑኝነት እንዳለው? ፣ ትውውቃቸው ከመቼ ጀምሮ እንደሆነማ ማጣራቴ የማይቀር ጉዳይ ነው" አልኩ ለራሴ።
"አይ ኤፊ አሁን እጅህ ላይ ያላውን አጣርተህ ሳጨርስ ••• ለወደፊት እንዴት እንደምታጣራ እቅድ ታወጣለህ እንዴ ? ይላል ያ የቃል ጠበቃ  ውስጤ ተዘፍዝፎ ።  እንዳልሰማሁ ሆኜ አለፍኩት።
አልፌኣቸው ከቆምኩ ከሀያ ደቂቃ በላይ  እኔም እነሱን እነሱም የሚጠብቁትን እየጠበቁ ስንጠባበቅ ከቆየን በኋላ አንዲት ባለ አንቴና ባጃጅ ስትክለፈለፍ መጣችና እነሱ ከቆሙበት መደብር ፊት ለፉት ስትደርስ ቀጥ አለች። እኔም ልቤ ቀጥ እንዳለች ቀጣይ የሚሆነውን ለማየት አፍጥጫለሁ።
ከባጃጇ ውስጥ አንዲት ሺቲዋን  ሙታንታዋ ውስጥ የሰቀሰቀች ረጅም ወጣት ሴት ወረደችና እጆቿን ተራ በተራ እያወናጨፈችና   እየተመናቀረች ወደነ  ቃልዬ ተጠጋች።
ቃልዬን እና ልጁን በየተራ እየሳመች ሰላም አለቻቸውና እንደዛው እጇን እያወናጨፈች ማውራቷን ቀጠለች ቃልዬና ልጁ እሷንም እርስ በርስም  እየተያዩ  ይስቃሉ።
"እቺ ልጅ በየሄደችበት መሳቅ ነው እንዴ ስራዋ!"አልኩ በውስጤ።
ወድያው ሶስቱም. ተከታትለው  ልጅቷን ወዳመጣቻት ባጃጅ ውስጥ ገቡ። የባጃጄን ሞተር  አስነሳሁ። በጎን መስታወት( 'በስፖኪዬ')እያየኋቸው  በቀስታ ወደፊት መሄድ ጀመርኩ። ባጃጇ ቀጥ ብላ በኔ አቅጣጫ መምጣት ስትጀምር ሄደን ሄደን መውጫው ላይ ከላይ ከሼል፣ አልያም ከታች ከሳፕያን መስመር የሚመጡ ባጃጆችን ለማሳለፍ ቆም ካልኩ ደርሰውብኝ መተያየታችን ነው ስለዚህ መፍጠን አለብኝ ፣አልኩና ፍጥነቴን ጨምሬ ወደፊት እየገሰገስኩ አየት ሳደርግ•••• እነቃልኪዳን ያሉባት ባጃጅ ጭራሽ ወዳልጠበኩት አቅጣጫ ተኮረበች።
  ወይኔ ተሸወድክ ኤፊ ! እያልኩ  አመቺ ሁኔታ ጠብቄ ዞርኩና ወደሄዱበት አቅጣጫ ተምዘገዘኩ።  ውስጥ ለውስጥ በርሬ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስትያን ፊት ለፊት  ላይ ስወጣ •••ከየጣጫው ከሚርመሰመሱት ባጃጆች  መሀል እነ ቃልዬ ያሉባትን መለየት ከባድ ሆነብኝ፣  ድንገት አርቄ ወደ ፊት ለፊት አቅጣጫ  ሳማትር ወደ ድል ጮሮ ሀስፒታል በሚወስደው መንገድ ላይ የምትከንፍ አንዲት ባለ አንቴና ባጃጅ ተመለከትኩ።
"እራሷ ነች ፣ ባላንቴናዋ እራሷ ነች!  እያልኩ በሄደችበት አቅጣጫ እየበረርኩ መከተል ጀመርኩ።
እኔ ሆስፒታሉ በር ላይ ስደርስ እነሱ ያልቧት ባለ አንቴና ባጃጅ  አደባባዩን ተሻግራ ወደ ገንደ ቆሬ መስመር  እየበረረች ነው። አፈጣጠኗ አጃኢብ ነው። እየተከተልኳቸው መሆኑን አውቀው••••  "መጣኮ ! ኧረ ንዳው!  ንዳው እንጂ ! አፍጥነው!"  እያሉ ሲንጫጩበት በአይነ ህሊናዬ  ታየኝ።
ዋናውን የገንደቆሬ መንገድ ይዘው በካራማራ ሆቴል ፊት ለፊት  አልፈው  ቁልቁል ወደ ዲፖ መስመር በረሩ። እኔም ከጀርባቸው ሆኜ በረርኩ። በመካከላችን ያለው ርቀት ወደ ሁለት መቶ ሜትር ተጠጋ። ፀሀይ ሆቴል ከመድረሳቸው በፊት ወደ ቀኝ ታጠፉ። ረገብ አድርጌ ተጠጋሁ።  ወደታጠፉበት ሳልታጠፍ በዝግታ እያለፍኩ አየት ሳደርግ  ከዋናው አስፖልት ገባ ብሎ በተሰራ የመኝታ  አገልግሎት ብቻ በሚሰጥ በአንድ  'ፔንስዬን'  በር ላይ ተጠግተው ቆሙ።
እልህ ይሁን ንዴት፣ ቃልዬን የማጣት ፍርሀት ይሁን ቅናት  ብቻ የሆነ ስሜት ተናነቀኝ ••••
"ቃልዬ••••!  አይኔ እያየማ እዚህ ቤት ውስጥ ይዞሽ አይገባም !" አልኩ።

ልቤም እየደለቀች ትንፋሼም ሲሮጥ እንደመጣ ሰው ቁርጥ ቁርጥ እያለብኝ  እስኪወርዱ መጠባበቅ ጀመርኩ።
ከባጇጇ የወረዱት እድሚያቸው የገፋ ጠና ጠና ያሉ  ሴትና ወንድ  መሆናቸውን ስመለከት ክው አልኩ።
ባለአንተና ባጃጅ በሞላበት አገር አንድ ባላንቴና ባጃጅ ስከተል መበላቴን ፣ መሸወዴን ማመን አቅቶኝ ••• የወረዱትን ሰዎች ሂሳብ ከፍለው መልሳቸውን ተቀብለው እስኪገቡ  ድረስ በተናደደ አይን በደንብ አየኋቸው •••ሴትየዋ እድሚያቸው ወደ ሀምሳ ይጠጋል ፣ ግን ሞንደል ያለ ደባና ቀጠን ያለ ወገብ አላቸው።አለባበሳቸውም እንቢ አላረጅም ፣ ቶሎ እግላለሁ ማገዶ አልፈጅም እንደሚሉት አንዳንድ ባልቴቶች  ነገር ናቸው።ወንድየው ወደ ስልሳ አመቱ ሳይጠጋጋ አይቀርም።
የነዚህ በዚህ እድሚያቸው አልጋ ቤት ለአልጋ ቤት መርመጥመጥ ነው እንጂ የሚገርመው፣ ደሞኮ ፍጥነታቸው፣ በእርግጠኝነት ከሚስት እና ከባላቸው የፎረፉ ናቸው ፣ አዋ ናቸዋ! ምን ጥያቄ አለው።
እኔ በቅርብ ግዜ የባጃጅ ስራ ጀምሬ እንካን ስንቱን የነሱን ቢጤ ፎራፊ ነው  ስንት አልጋ ቤት አደረስኩ። ምን ይመስላሉ በፈጣሪ!
ባለአንቴና ባጃጅ ውስጥ ሆነው ሲንቀዥቀዡ እነ ቃልዬ መሰሉኛ እኔ ምን ላድርግ ቀዥቃዦች !" አያልኩ ••• እነቃልን እነሱ ያስመለጡኝ  ይመስል  እስኪገቡ ድረስ ቆሜ ስወርድባቸው ቆየሁ። እነሱም ገቡ ባለባጃጁም እዛው በቆምኩበት አልፎኝ ሄደ።
ወዴት እንደምሄድ ግራ ግብት አለኝ ።
ባጃጄን አስነስቼ በመዞር በመጣሁበት መንገድ ቀስ እያልኩ ሳዘግም ስልኬ ጠራ።
ከኪሴ ውስጥ አውጥቼ ስመለከተው ቃልዬ ነች የደወለችው። በፍጥነት ወደ ጆሮዬ ላኩትና •••
"ሄሎ ቃሌ የት ነሽ•••?
.
.
20 ላይክ ቡኋላ ክፍል 15 ይለቀቃል🌹


#ዛሬ April 1 ነው... April the fool...

ዛሬ የምሰሙትን ዜና ሁሉ እንዳታምኑ መጀመሪያ አረጋግጡ! በሀገራችን ደሞ አከባበሩ ስግጥና ስለሚበዛው የሰማቹት መጥፎ ዜና ሳትደናገጡ መጀመሪያ አረጋግጡ! አፕሪል 1 ማለት የውሸት ቀን እንደ ማለት ነው!


Good morning

ዛሬ አዲስ ቀን ነው ትላንት አልፏል በዛሬ ግን ነገን ማስተካከል ይቻላል።

የተኛችሁ ተነሱ ዛሬን ኑሩ

የስኬት ቀን ይሁንልን🙏


#መጋቤ_ሀዲስ_እሽቱ_አለማየሁ

✔️ቁንጅና ለትዳር ዋስትና አይሆንም!
✔️መታመም ማለት ትሞታለህ ማለት አይደለም!
✔️ሃብታም መሆን የጥሩ እድል ትርጉም አይደለም!
✔️ጥሩ ቤት ውስጥ መኖር የድሎት ምንጭ አይሆንም!
✔️ጥሩ መኪና መንዳት ለምትደርስበት ቦታ ዋስትና አይሰጥህም !
✔️ለቤተሰብህ ዶክተር ብትቀጥር ቋሚ የጤና ዋስትና አይኖርህም!
✔️ብዙ መማር ጥበበኛ አያደርግህም!
ሃብታም ማግባት ለደስተኛ ለህይወት ማረጋገጫ አይሆንም!
✔️ክርክር ማሸነፍ ትክክል መሆን አይደለም !
***
🔴ገነት የማያሸልም ምንም ነገር ብትሰራ ጊዜያዊ እና ውሸት ነው ። ያለ አምላክ የሚራመድ ሰው በድን ነው፣አንተ በራስህ ላይ ስልጣን የለህም አንተ ሰውነትህን ታያለህ እሱ ደምስርህን ያያል ። ሁሉም
ነገር ለርሱ ይቻላል በሁሉም ነገር ውስጥ አምላክህን ጣልቃ አስገባ።

🙏🙏ፈታ ያለ ቀን ይሁንልን🙏🙏


ቤተሰብ የምር vote የተደረገው መጀመርያ ያን ነበር ቆይቶ ነው የጨመረው ለዚሁ ደግሞ ሽልማት ጨምሬ ለ 8 ሰው የነበረው ለ 16 ሰው እሸልማለሁ ቃሌ ነው ካልተገበርኩት ጠይቁኝ በሌላ ቀን አስደስታቾኋለሁ👌


ውድ የሁሉም ቤት ተከታታዮች ብችልና ለ ሁላችሁም ብሸልማችሁ ደስታዬ ነበር ሆኖም ለዛሬ በዚሁ እናብቃ ለሁላችሁም ባልሸልምም ለሁላችሁም ማሳቅ ማዝናናት እሞክራለሁ

አሸናፊዎች ሽልማታችሁ በ
@algiti ውሰዱ

ይመቻችሁ👍


@Over_act winner 🌯🌯🌯


ኢትዮጵያ ብለን ብር ካልን ኤርትራ ብለን__ እንላላን?


ready....


ሁለተኛ ጥያቄ loading...


@Yoni_Ng the winner


በዓለማችን 99% መሬቷ በርሃ የሆነችውን ሀገር ማን ናት

prize 100 ብር


Ready....


1


2


3

20 last posts shown.