ዶ/ር ምህረት ደበበ እና ዶ/ር እዮብ ማሞ


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Blogs


👉የዶ/ር ምህረት ደበበ ፣ የዶ/ር እዮብ ማሞ እና የሌሎችም ፦፦፦፦፦፦፦፦
📖አነቃቂና አስተማሪ የሆኑ ወጎች
👉ስለ አመራር
👉አመለካከት(እይታ)
👉mindset
👉ስለ እድገት.......በስፋት እንዳስሳለን
📚 መፅሐፍት pdf
🎙የመፅሐፍ ትረካ
📖 አስተማሪ የሆኑ ፅሁፎች
👉👉👉contact us @Ay_ayche
@Fbg64


Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Blogs
Statistics
Posts filter


Enjoy The Day!!!

የዛሬዋ ቀን እንደገና ደግማ የማትመለስ ውብ የሆነች ቀን ነች! Enjoy it!

በምንም ሁኔታም ሆነ በማንም ሰው ምክንያት በድብርት አታሳልፏት! ደስተኛ ለመሆን ወስኑ፡፡

በምንም ሁኔታም ሆነ በማንም ሰው ምክንያት መራራ በመሆን አታባክኗት! የቀኑ መልካም ጎን ላይ በማተኮር አጣጥሟት!

በምንም ሁኔታም ሆነ በማንም ሰው ምክንያት ተስፋ ቆርጣችሁ አትለፍባችሁ! ተስፋችሁን በፈጣሪ ላይ አድርጉና ቀና ብላችሁ ዋሉ! 

መልካም ቀን ለሁላችሁም!


አልመህ ተኩስ!

አንድ ንጉስ ከአጃቢዎቹ ጋር በአንድ ጫካ ውስጥ ሲዘዋወር አንድ ዛፍ ላይ ያየው ነገር ትኩረቱን ሳበው፡፡ በዚህ ትልቅ ዛፍ ላይ የተለያዩ ክብ ቅርጽ ያላቸው ኢላማዎች ተስለዋል፡፡ የገረመው ነገር፣ እያንዳንዳቸው ኢላማዎች መካከል ምንም ሳይስቱ ኢላማቸውን በትክክል የመቱ ቀስቶች ተሰክተው ይገኛሉ፡፡ ንጉሱ በጣም ተገረመና፣ “እነዚህን ኢላማዎች ሁሉ በትክክል አነጣጥሮ የመታውን ሰው ለሰራዊቴ አለቃነት እፈልገዋለሁና ፈልጋችሁ አግኙልኝ” አለ፡፡

ልክ ይህንን ተናግሮ እንደጨረሰ አንድ ወጣት ልጅ ብዙ ቀስቶችን ተሸክሞ እየገሰገሰ ንጉሱ ጋር ደረሰ፡፡ ንጉሱ፣ እነዚህን ሁሉ ኢላማዎች በትክክል የመታው ሰው እሱ መሆኑን ጠይቆ የአዎንታ መልስ ካገኘ በኋላ እንዴት እንደዚህ አነጣጣሪ ሊሆን እንደቻለ ጠየቀው፡፡ የልጁ መልስ አጭርና ግልጽ ነበር፣ “በመጀመሪያ ቀስቴን ወጥሬ በዛፉ ላይ እሰካዋለሁ፡፡ ከዚያም ወደ ዛፉ በመሄድ በተሰካው ቀስት ዙሪያ የክብ ምልክትን አስቀምጥበታለሁ” በማለት እንደዚያ አነጣጣሪ ያስመሰለውን እውነት ፍርጥ አደረገና ነገረው፡፡

ይህ መሰረታዊና ቀላል አፈ-ታሪክ የብዙ ሰዎችን የሕይወት ዘይቤ ያንጸባርቃል፡፡ ይህ ወጣት በመጀመሪያ ዓላማን አድርጎ አልነበረም ያንን ዓላማ ለመምታት ጥረት ያደረገው፡፡ በቅድሚያ ወዳሻው ቀስቱን ከለጠጠና ከሰነዘረ በኋላ ቀስቱ ያረፈበትን ስፍራ ነው እንደዓላማ በመቁጠርና ልክ ዓላማውን እንደመታ ለማስመሰል በዙሪያው ክብን ያበጀለት፡፡ አንዳንድ ሰዎች እንዲሁ ናቸው፡፡

በመጀመሪያ ዒላማንና ግብን አቅደው በዚያ ባቀዱት መሰረት ሊተኩሲ ሲገባቸው ከተኩሱ በኋላ ቀስቱ ያረፈበትን ነው እንደግብ የሚቆጥሩት፡፡ በሌላ አባባል፣ ያገኘነውን፣ የመሰለንንና የቀለለንን ነገር ካደረግን በኋላ በዚያ ባደረግነው ተግባር ዙሪያ ዓላማን ለመፍጠር መሞከር የሞኝነት ሁሉ ሞኝነት ነው፡፡ ዓላማ ከሌለን የምንሄድበትን አናውቅም፡፡ ግብም ከሌለን ተኩሰን የመታነው ነገር ሁሉ እንደ ግብ ስለሚቆጠር ይህንና ያንን ስናደርግ ጊዜያችን ይባክናል፡፡ ለዚህ ነው በዓላማና በግብ የምንመራ ሰዎች መሆን ያለብን፡፡

አንድ በር ተከፍቶ ስላገኘህ ብቻ ከገባህ በኋላ የገባህበትን ዓላማ ለማግኘት አትሯሯጥ፤ በመጀመሪያ በዚያ በር የመግባትህ ጉዳይ ከሕይወትህ ዓላማ ጋር መስማማቱን አረጋግጥ፡፡

አንድ ሃገር የመሄድ እድል ስለተገኘ ብቻ ከሄድክ በኋላ ዓላማ ለመፍጠር አትሂድ፤ በመጀመሪያ ወደዚያ ሃገር የመሄድህ ጉዳይ ከሕይወትህ ዓላማህ ጋር አለመጣረሱን አረጋግጥ፡፡

አንድ ሰው ትኩረትና የመፈቀር ስሜት ስለሰጠህ ብቻ ሁለንታንህ በመስጠት ግንኙነት ውስጥ ከገባህ በኋላ ዓላማ ለመፍጠር አትታገል፤ ጓደኛንም ሆነ ፍቅረኛን ከዓላማህ አንጻር ምረጥ፡፡

ስራህንም እንደዚያው! ትምህርትህንም እንዲዚያው! የሕይወትህን ዋና ዋና ክፍሎችም እንደዚያ!

ከዓላማ ተነሳ እንጂ ተነስተህ ከተጓስክ በኋላ ዓላማህን ለማግኘት አትባክን፡፡ ዓልመህ ተኩስ እንጂ የተኮስከው ነገር የመታውን ነገር ሁሉ ዓላማህ እንደሆነ በማሰብ ራስህን በማታለል ዘመንህን አታባክን፡፡

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


ለአንድ ግለሰብም ሆነ ኅብረተሰብ፣ ቤተሰብም ሆነ አገር የዕድገትም ሆነ የውድቀት ቁልፉ መሬቱ ሳይሆን አዕምሮ ላይ ነው። መሬቱ የሚቆለፈው የሰው አዕምሮ ሲቆለፍ ነው። አንድ ሰው አዕምሮው ሲከፈትለት ሁሉ ነገር ይከፈትለታል። የአንድ ሀገር ሕዝብ አዕምሮው ሲቆለፍ፣ ሁሉ እያለው ምንም እንደሌለው ሁሉም ነገር ይዘጋጋል። … ለምሳሌ አፍሪቃን ውሰጂ…ሁሉም ነገር አላት። ግን ደግሞ ምንም ነገር የላትም። ያላትም ቢሆን እያጨራረሰን ነው እንጂ እየረዳን አይደለም። እይው መንገድ ላይ የወደቀውን ለማኝ፣ እስር ቤት የተከማቸውን እስረኛ፣ ሌሊት መንገድ ላይ ተደርድረው የምታያቸውን ቆንጅዬ ሴተኛ አዳሪዎች…እነሱ ሁሉ አዕምሮአቸው ተቆልፎባቸው የሐብታም ደኃ የሆኑ ድንቅ ፍጥረቶች ናቸው። ሌብነት ብትይ ሙስና፣ አምባገነንነት ብትይ ጦርነት፣ ዘረኝነት ብትይ የሐይማኖት ግጭት፣ ሁሉም የአዕምሮ መቆለፍ ምልክት ናቸው። ስለዚህ አሁን አንገብጋቢውና ትልቁ ቁም ነገር መንገድ መሥራት ወይም ሕንጻ መገንባት ሳይሆን ይህንኑ ማድረግም ሆነ በተሰራው በቅጡ መጠቀም የሚቻለው የሰው አዕምሮ ሲከፈትና ከተኛበት የዘመናት እንቅልፍ ሲነቃ ብቻ መሆኑ ላይ ነው።" 

"የሰው አዕምሮ በትክክል የሚዋኝበት ቢገኝ ከውቅያኖስ የጠለቀ … ከሠማይ የራቀ … ከሐሳብ የረቀቀ … በዋጋው ከሁሉ የላቀ … ተቆፍሮ ያልተደረሰበት ውድ ሐብት ነው። ግን የተቆለፈበት ቁልፍ ነውና ቁልፉን ለማግኘት ቁልፉ የተቆለፈበትን ደጃፍ ለመክፈት የሚያስችለውን ቁልፍ እስክናገኝ ተስፋ መቁረጥ የለብንም። ከቁልፉ ብዙ የራቅን አይመስለኝም!" 


ምንጭ:- "የተቆለፈበት ቁልፍ" በምሕረት ደበበ (ዶ/ር)

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


#አዕምሮህ_ማግኔት_ነው!

ሁልጊዜም አእምሮህ ማግኔት መሆኑን አስታውስ፡፡ አንተን የተቆጣጠሩህን ሃሳቦች እና በውስጥ የሰረፁትን እምነቶች የሚያምኑ እና የሚያስቡ ሌሎች ሰዎች ወዳንተ እንደሚያቀርብም ልብ በል፡፡

በትክክለኛ መንገድ የስበት ህግ (law of attraction) ብለን የምንጠራው አንድ ህግ አለ፡፡ ውሃ ከፍታውን የሚፈልግበት፣ በህዋ ውስጥ ያሉ ነገሮች ሁሉ የየራሳቸውን አምሳያ የሚፈልጉበት ህግ፡፡ ፕላኔቶችን በትክክለኛ ቦታቸው ጠብቆ እንደሚያቆየው የስበት ህግ፡፡

ይህ ህግ የሚለዋወጥ ቢሆን ኖሮ የማንጎ ፍሬ ከአበባው ውስጥ በርራ በፓፓያ አበባ ውስጥ በመግባት በከፊል ማንጎ፣ በከፊል ደግሞ ፓፓያ የሆነ ዛፍ ይፈጥሩ ነበር፡፡ እንዲህ አይነት ነገር ግን ሰምተን አናውቅም፡፡ ይሄንን የስበት ህግ ትንሽ በመከተል በሴቶች እና በወንዶች መካከል እንዴት እንደሚሰራ ማየት እንችላለን፡፡

ውጤታማና ሃብታም ወንዶች የሚፈልጓት ሴት የእነሱኑ አይነት ሴት እንደሆነ እናውቃለን፡፡ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ያለ ወንድም እንደዚያው፡፡ ይህ የሚሆነው በተፈጥሮ ነው - ልክ ውሃ ወደ ታች እንደሚፈሰው፡፡

“ሁሉም አምሳያውን ይስባል” የሚለው አባባል የማይገሰስ ሀቅ ነው፡፡ አንድ ወንድ የሚፈልጋት ሴት በብዙ መልኩ እሱን የምትመስለውን ሴት መሆኑ እውነት ከሆነ፣ የምትፈልጋቸውን ሰዎች ለማሰብ የእነዚህን ሰዎች ሀሳቦች እና እምነቶች በመቆጣጠር እና በማዳበር ማግኔት የመስራትን ጥቅም ማየት አትችልም?

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


ዛሬን መኖር !

ሁልጊዜ ስለሮጥክ ስለተጨነክ ስለነገ ስላሰብክ ብቻ ሁሉ ነገር ላይ አሪፍ ትሆናለህ ማለት አይደለም ዛሬ የምትባል ውድ ስጦታ እንዳለችም እንዳትዘነጋ ፤ ለራስህም ጊዜ መሥጠት ፣ እረፍት መውሰድ ፣ ቆም ብለህ ያለህን መመልከት በራሱ እንዴት ደስ የሚል ስጦታ ነው ። ወደፊት ለመሄድም በተለየ መንገድ እንድታስብ የሚያረግህ ይሄ ነው ።

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


ምንም አይነት የትምህርት ደረጃ እና ልምድ የማያስፈልገው ሲሆን  ማንኛውም የስራ ፍላጎት ያለው ሰው ስለ ስራው አጭር ገለፃ(Presentation) በመውሰድ ወዲያው ሊሰሩ የሚችሉት እጅግ በጣም አዋጭ የፕሮሞሽን ስራ ሲሆን ሂወትን መቀየር የሚፈልግ ማንኛውም ሰው ሊሰራው የሚችል ትርፋማ ስራ ነው።
       -በየትኛውም የትምህርት ደረጃ ላይ ያላችሁ
       -በየትኛውም አከባቢ የምትኖሩ
       -ሌላ ስራ እየሰራችሁ ተጨማሪ ስራ ለምትፈልጉ
       -ከትምህርታችሁ ጋር ማስኬድ ስምትችሉ አብራችሁ መስራት ትችላላቹ።
መረጃውን ባስቀመጥንላቹ ስልክ ማግኘት ትችላላቹ!!

👉@Ay_ayche
👉+251941731143


#የምታስበውን_አይደለህም

ወደ ማህደረ ትውስታህ የምትገባ ከሆነ ድግግሞሽ ይከሰታል፤ ሁሉንም በትኩረት መከታተል ግን ነገሮችን የመመልከት ችሎታህን ይለውጣል።

ብዙ ሰዎች በጭንቅላታቸው ውስጥ የሚያልፈውን ሃሳብ ሁሉ የነገሩን እውነት እንደሚወክል  የማይካድ እና የማያሻማ አድርገው በማመን በቁም ነገር ይወስዱታል። ነገር ግን ሃሳቦች እውነታዎች አይደሉም። 

የምታስበው ነገር እንደምታስበው አይደለም።

ሀሳቦች ሀሳቦች ብቻ ናቸው። ሀሳብ ስላለህ ብቻ ያ ሀሳብ እውነት ነው ማለት አይደለም። በአማካይ ሰው በቀን ከ50,000 በላይ ሃሳቦች አሉት። ታዲያ አንተስ ከምንም ነገር ጋር ምንም ግንኙነት የሌላቸው ስንት ሙሉ በሙሉ የዘፈቀደ ሀሳቦች አሉህ?

ስለዚህ አንተ አእምሮህን በቁም ነገር ሳትወስደው መመልከት በመማር ለራስህ ውለታ ዋልለት። በጭንቅላትህ ውስጥ የሚያልፉትን ሁሉንም ሃሳቦች ሳታምን ዝም ብለህ ተመልከታቸው። እንደ ሰማይ ደመና ወይም እንደ ውቅያኖስ ማዕበል በፍጥነት መጥተው በፍጥነት የሚጠፉ አድርገህ እያቸው።

እንዲሁም፣ አንተ የአስተሳሰብ ሂደትህ ኃላፊ እንዳልሆንክ እና ስለምታስበው ነገር ምንም ማለት እንደማትችል ተገንዘብ። ያንን ካደረግክ ከክፉ እና ከአሉታዊ ሀሳቦች ይልቅ አዎንታዊ እና ደስተኛ ሀሳቦችን ብቻ ታስባለህ። እንደ እውነቱ ከሆነ ስለ አእምሮህ ወይም ስለ ሃሳቦችህ ወይም መንስኤዎቻቸው፥ ከየት እንደመጡ፥ የሚቀጥለው ሀሳብህ ምን እንደሚሆን፥ ወይም ከምትፈልገው ይልቅ ለምን የማትፈልገውን ሀሳብ እንደምታስብ አታውቅም።

ይህን የማታምን ከሆነ፥ የሚቀጥለው ሀሳብህ ምን እንደሆነ፥ ከሌላ ሀሳብ ይልቅ አሁን አእምሮህ ውስጥ ያለውን ሀሳብ ለምን እንደምታስብ፥ አሁን ስላለውና አስፈላጊ ስለሆነው ነገር በማሰብ ፋንታ ከሁለት ሳምንት በፊት ወይም ከአመታት በፊት ስለተከሰት ነገር የምታስበው ለምን እንደሆነ እንዲሁም ምንም ነገር አለማሰብ ትችል እንደሆነ ራስህን ጠይቅ።

አንተ አእምሮህ ወይም ሃሳብህ እንዳልሆንክ እና ከእነሱ የተለየህ መሆንህን ማወቅ አንድ ሰው በህይወቱ ውስጥ ሊያደርጋቸው ከሚችላቸው ጥልቅ እና ከፍተኛ ግኝቶች አንዱ መሆኑን ተገንዘብ።

የሕይወት_ኬሚስትሪ መጽሐፍ

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


#ነገ_የሚባል_ቀን_የለም!

የአንተን ሕይወት የሚመለከት ነገር ስታነብና ሲነካህ ያነበብከውን ነገር ተቀብለህ ወዲያውኑ ተግብረው፡፡ ወዲያውኑ ወደ ተግባር ግባ፡፡ በቃ ጊዜ አትፍጅ፡፡ ሲጋራህን ጣል፤ ቢራ ተው፤ ጂም ግባ፤ ይቅርታ ጠይቅ… ወዘተ፡፡

ከእንደነዚህ አይነት ነገሮች ውስጥ አንዳንዶቹ ከሌሎቹ የበለጠ ከባድ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ የትኞቹም ቀላል ናቸው እያልኩኝ ግን አይደለም፡፡ እንደዚያ እንዳልሆነ አውቃለሁ፤ ግን ይቻላል - ለእኔም ለአንተም፡፡ እናም አሁን አድርገው፤ ነገን አትጠብቅ፡፡

ቁጭ ብለህ እያሰብክ ነገን አትጠብቅ፡፡ ሲጀመርም ነገ ስለመኖሩ ምንም ማረጋገጫ የለህም፡፡ ነገ ሚባል ቀን እንደሌለ አውቀህ ዛሬን ኑር፡፡ አእምሮህ ስለ ነገ እያሰበ ሰፊውን ጊዜህን እንዲወስድብህ እድል አትስጠው፡፡ ያለ እረፍት በአእምሮህ ውስጥ እየተንቀዋለለ የሚረብሽህ ነገር ካለ የማትወስንና የተወዛገብክ እንድትሆን ያደርግሃል፡፡  

አእምሮህ ለምን ስለ ለውጥ መጨነቅ እንደሌለብህ፣ ለምን እንደማይሰራልህና እንዴት ከባድ እንደሆነ እየነገረ ወደ ኋላ ሊጎትትህ ይሞክራል። አንተ ግን አታዳምጠው። አሁን ጊዜው የሕይወት ውጥንቅጦችን መልክ መልክ የማስያዣ ጊዜ ነው!

ዛሬን በአግባቡ ኑረው፡፡

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


ራዕይ የሌለው ልፋት!

በሕይወታቸን ስኬታማ ለመሆን በጥምረት ልንይዛቸው የሚያስልጉን ሁለት ልምምዶች አለ፡- 1) ራእይን ማወቅና መያዝ፣ 2) ጠንካራ ሰራተኛ መሆን፡፡

1) ራእይ ኖሮን ጠንካራ ስራ ከጎደለን የምኞትና የቀን-ሕልመኞች (Day dreamers) ከመሆን አናመልጥም፡፡

2) በተቃራኒው፣ ጠንካራ ሰራተኞች ሆነን ምንም ብንለፋም ራእይ ከሌለን የተበታተነ ውጤትና ማንነት ስለሚኖረን ምንም የምንገነባው ነገር አይኖረንም፡፡

ጠንካራ ስራ መልካም ውጤት የሚያመጣው ግልጽ ከሆነ ራእይ ጋር ሲያዝ ብቻ ነው፡፡

ራእያችሁ ምድን ነው?
የጠንካራ ሰራተኛነት ልምምዳችሁስ ምን ደረጃ ላይ ነው?

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


ልክ እንደ ወንዝ!

“ወንዝ ሲፈስ አነስተኛ የመቋቋም ብቃት ወዳለው አቅጣጫ እየተጣጠፈ ነው የሚዘልቀው” ይባላል፡፡ አቅሙ የሚፈቅድለት ቁልቁለቱ እያለለት ወንዝ ከአቅሙ በላይ ወደሆነው ወደዳገቱ አይፈስም፡፡ እንደ አቅሙ የሆነው እያለለት ወንዝ ከአቅሙ በላይ የሆነውን፣ “ለምን አያሳልፈኝም” እያለ አይታገልም፡፡ አሁን ስለቀለለው ወደቀኝ ታጥፎ፣ ወዲያው ሲከብደው ወደግራ ሊታጠፍ ይችላል፡፡ በዚህ የፍሰት ባህሪይው የወንዝ መጨረሻው ቀጥ ብሎ ከመሄድ ይልቅ እየተጣመሙ መኖርና የአካባቢው ዝቅተኛው ስፍራ ላይ መውረድ ነው፡፡

የወንዝ ባህሪይ ግን ከላይ የተገለጸው ብቻ አይደለም፡፡ አንዳንድ ጊዜ እኮ ወንዝ ወደከፍታም የሚፈስበት ጊዜ አለ፡፡  ወንዝ አቅሙን ሲያጠራቅም፣ ሲበረታና ኃይል ሲኖረው በፊቱ ያለውን ከፍ ያለ ነገርም ቢሆን ሞልቶና አልፎ ይሄዳል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ወንዝ ሲበረታ ከፍተኛውን ስፍራ እስኪሞላ ድረስ “ወደ ላይ ይፈስሳል”፡፡

ከወንዝ እንማር! ከአቅምህ በላይ የሆኑ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙህ ለምን መንገድ አይለቁም ብለህ እስክትደማ አትታገል፣ ወይም ደግሞ ወደኋለ አትመለስ፡፡ ብልሃት ፈልገህ ዘወር ብለህ እለፍ፡፡ ሆኖም ያንን እያደረክ ሳለህ፣ አቅምህን አጠራቅም፡፡ አቅም በጨመርክ ቁጥር መንገድ እየቀየርክና ጠመዝማዛ ጎዳናን በመጓዝ መድከምህ ያበቃና ቀጥ ብለህና በፊትህ የሚቆመውን እየገረሰስክ ማለፍ ትጀምራለህ፡፡

•  የስሜት ጽንአት አቅምህን አጠራቅም፣ እስከዚያ ግን የወቅቱን የስሜት ጽንአት ባገናዘበ ሁኔታ ተራመድ፡፡

•  የገንዘብ አቅምህን አጠራቅም፣ ለጊዜው ግን ኑሮህን ካለህ የገንዘብ አቅም ጋር በማገናዝ ተንቀሳቀስ፡፡

•  የግንኙነት መረብህ (Network) አቅምህን አጠራቅም፣ እስከዚያው ግን አጠገብህ የሚገኙ ሰዎች በሚደግፉህ ደረጃ ተራመድ፡፡

•  የእውቀት አቅምህን አጠራቅም፣ እስከዚያው ግን ባለህ እውቀት የምትችለውን ስራ በመስራት ኑሮህን ግፋ፡፡

ልክ እንደወንዝ!
D.R EYOB MAMO

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


#ካለህበት_ቦታ_ጀምር!

የምታልመውን አይነት ሕይወት ለመፍጠር እርምጃ መውሰድ ያለብህ አንተና አንተ ብቻ ነህ።

ሌላ ማንም ሊያደርግልህ አይችልም!!

አሁን ለመጀመር ተሰጥኦውም ሆነ የምትፈልጋቸው ነገሮች አሉህ።

ወዳጄ… የትኛውንም የምትፈልገውን ነገር መፍጠር የሚያስችል አቅም እንዳለህ አውቃለሁ። አንተም እንደምትችል ታውቃለህ ... ስለዚህ ውጣና አድርገው!

ሁሉም ነገር በጣም ጠንክሮ መስራት የሚጠይቅ ቢሆንም፣ በጣም ደግሞ ደስ የሚልም ነው። በምትሄድበት በማንኛውም መንገድ መደሰት እንዳለብህ አስታውስ።

ሪቻርድ ፖል እንዳለው አሁን ያሉበት ቦታ የደረሱ ሁሉ ከነበሩበት ቦታ መጀመር ነበረባቸው፡፡

#እናም_ወዳጄ_እነሆ_ወዳጃዊ_ምክር-  ካለህበት ቦታ አሁኑኑ ጀምር!!

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


''አድዋ የነፃነት ሳይሆን የድል ቀናችን ነው''

አድዋ ማለት አባቶቻችን በሀይማኖት እና ዘር ሳይከፋፈሉ ለሀገር አንድነት ከጫፍ እስከጫፍ ተነስተው ጣሊያንን አሸንፋዋል ውድ ህይወታቸውን መስዕዋት አድርገዋል ይህ ትልቅ ዋጋ ያለው የድል ቀን የሱጠበት ነው አድዋ

ይህን የድል ቀን ባይኖር ሀይማኖታችን ማንነታችን እንዲሁም ኢትዮጵያዊ ቀለማችን ጠፍቶ ውብ እና ድንቅ የሆኑ ባህሎቻችን ጠፍተው ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት እንደሆኑት እንሆን ነበር ባህል,ቋንቋ እንዲሁ ሀይማኖት የቆየው በአባቶቻችን ነው

🔥1888 ታላቁ ድል የተገኘበት ቀን ነው🔥

እነሱ ደማቸውን አፍሰው የሰጡንን የድል ቀን እንደ በሬ ቅርጫ አንከፋፍለው የጋራ ነገር ሁሌም የማረ ነው ድሉ የመላው ኢትዮጵያዊያን ነው!✊

   💐ክብር ለጀግኖች ለአባቶቻችን💐

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


ለነገ የማስተላለፍ ችግር (Procrastination)

ትልቁ ጀምሮ የመጨረስ ጠንቅ!

አንድን ነገር ስለመጀመር በማውጣትና በማውረድ በሃሳብ መጋለብ፣ ልናደርግ ስላቀድነው ነገር ለሰዎች መንገርና አንዳንዴም እቅድ እስከማውጣት መድረስ ከዚያም ነገሩን ለነገ ማስተላለፍ የብዙ ሰዎች ልማድ ነው፡፡

አንድን መጀመር ያለባችሁን ነገር ለነገ በማስተላለፍ የማሳደር ችግር ካለባችሁ ይህ ትምህርት ለእናንተ ነው፡፡ መተግበር ያለብንን  ነገር በወቅቱ የመተግበርን ልማድ ለማዳበር በቅድሚያ ነገሮችን ለነገ እንድናስተላልፍ የሚያደርጉንን እንቅፋቶች ለይተን ማወቅ አለብን፡፡

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


አንብቡ! ተንቀሳቀሱ!

ሁለት እውነታዎች አሉ፡- 1) ማወቅ የሚገባችሁን ሁሉ አላወቃችሁም፣ 2) መድረስ የሚገባችሁ ደረጃ ላይ አልደረሳችሁም፡፡

በእነዚህ በሁለት እውነታዎች ካመናችሁና ከተስማማችሁ ሁለት ልምምዶች ሊታዩባችሁ ይገባል፡-

1.  ካለማቋረጥ ማንበብ!
በዚህ ሳምንት ምን አነበባችሁ? በዚህ ሳምንት ካነበባችኋቸው ነገሮች ምን አዲስ እውቀት ገበያችሁ? ከእነዚህ ካገኛችኋቸው አዳዲስ እውቀቶች መካከል የትኞቹን ለመተግበር ሞከራችሁ?

2.  ካለማቋረጥ ወደ ፊት መራመድ!
በዚህ ሳምንት በዓላማችሁ አቅጣጫ ምን አይነት እንቅስቃሴ አደረጋችሁ? በዚህ ሳምንት ምን አዲስ ነገር ጀመራችሁ? ከእነዚህ ካደረጋችኋቸው እንቅስቃሴዎችና ጅማሬዎች መካከለት የትኞቹ ውጤትን ሰጧችሁ?

አንብቡ! ተንቀሳቀሱ!

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


ዛሬ ይጀመር!

ምናልባት ይህንን አባባል ከዚህ በፊት ሰምታችሁት ካላወቃችሁ ላሰማችሁ፣ ካወቃችሁት ደግሞ ላስታውሳችሁ፡-

“ዛፍን የመትከያው ትክክለኛውና ከሁሉም የተሻለው ጊዜ የዛሬ ሃያ አመት ነበር፤ ከዚያ ቀጥሎ የተሻለው ጊዜ ደግሞ ዛሬ ነው”፡፡

“ምነው የዛሬ ዓመት፣ አምስት ዓመት ወይም አስር ዓመት ጀምሬው ቢሆን” ኖሮ የምትሉት ነገር ካለና ያንን ባለማድረጋችሁ የምትጸጸቱ ከሆነ፣ የተጠቀሰውን አባባል ምክር በመስማት ወሳኝ እርማት ማድረግ ትችላላችሁ፡፡ ያን ጊዜ ብትጀምሩት የተሸለ የመሆኑ እውነታ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ የሚቀጥለው ትክክለኛ ጊዜ ዛሬ መጀመር እንደሆነ ላስታውሳችሁ፡፡

ምንም ነገር ለመጀመር ጊዜው አልረፈደምና ተነሱና ዛሬ ጀምሩ! 

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


💪💯 ውድቀትህ ብርታትህ ነው!

💪💯 በህይወትህ ለመጀመሪያ ጊዜ በሞከርክ ሰዓት የሆነ ቦታ ላይ ሚዛንህን ትስታለህ ፤ እራስህን ችለህ መቆም ያቅትሃል ፤ ትንገዳገዳለህ ፤ አቅም ያንስሃል ፤ ትዳከማለህ ፤ በስተመጨረሻም ትወድቃለህ ። ውድቀትህ የሙከራህ ማሳያ ነውና ወድቀህ ግን አትቀርም፤ ዳግም እራስህን ገንብተህ ፣ ጠንክረህ ፣ በርትተህ ትመለሳለህ ። አንዴ ወድቄያለሁ ብለህ ተስፋ አትቆርጥም ፤ ሁለቴ ወድቄያለሁ ብለህ በእራስህ አታዝንም ፤ ሰዎች ስቀውብኛል ፣ በውድቀቴ ተሳልቀውብኛል ብለህ በዛው አፍረህ አትጠፋም ። ሃሳብህ ትልቅ ነውና እርሱን ለማሳካት መውደቅ ያለብህን ያክል ወድቀህም ቢሆን ፣ ሊደርስብህ የሚገባው ሁሉ ደርሶብህም ቢሆን ሃሳብህን ከዳር ከማድረስ ወደኋላ አትልም ፤ ያቀድከውን ከማድረግ አትመለስም ፤ ግብህን ሳትመታ አትቀርም ።

💪💯 አዎ! ጀግናዬ..! ውድቀትህ ብርታትህ ነው ፤ ስህተትህ የጥበብ በርህ ነው ፤ ስብራትህ የእውነተኛው ጥንካሬህ ማንቂያ ደውል ነው ። ብዙ ቀላል መንገድ ነበረህ ነገር ግን አልተጓዝክበትም ፤ ብዙዎችን ያዋጣቸውን ታውቀዋለህ ነገር ግን አልመረጥከውም ። ቢከብድህም ፣ ስቃይ ቢኖረውም ፣ ቢያታግልህም ፣ ለውድቀት ቢያጋልጥህም ፣ አደጋ ላይ ቢጥልህም ከባድ የተባለውን የህይወት ጉዞ ጀምረሃል ። ብቻህን ስትሆንም ይበልጥ ሊያስፈራህ ይችላል ፤ ያንን ፍረሃት ካልተሻገርክ ግን ፍረሃቱ እንደማይተውህ አስታውስ ። ቆራጥነትህ ውድቀትን ጥሎ ፣ ፍረሃትን ተሻግሮ ፣ ተስፋ መቁረጥን አስወግዶ ወደፊት የሚገፋህ ግሩም መሳሪያህ ነው ።

💪💯 አዎ! አትጠራጠር ፤ በመረጥከው ከባድ መንገድ መቼም አታፍርበትም ፤ በመጣህበት ፈታኝ ጉዞ አንገትህን አትደፋም ። ስትጀምር የምታዘቀዝቀው ፣ አንገትህን የምትደፋው ፣ ከእግር በታች ሆነህ የምታገለግለው ፣ ያለምንም ክፍያ ጊዜህን ፣ ጉልበትህን ፣ ስሜትህን የምትሰጠው ቦሃላ ቀና እንደምትል ስለምታውቅ ነው ። የበዛው ዝቅታህ የላቀው ከፍታህ ምክንያት ነው ። የዛሬ ውድቀትህ የነገ ታላቅነትህ ሚስጥር ነውና ብትወድቅም አትሸበር ፤ አትደናገጥ ፤ አትታወክ ። ዳግም ተመልሰህ ትመጣለህ ፤ እንደገና ታንሰራራለህ ፤ ነፍስን ትዘራለህ ፤ ወደቀድሞ ማንነትህም ትመለሳለህ ። ከምንም በላይ ለመጀመር የታገልከውን ትግል አስታውስ ፤ በእራስህና በሰዎች አሉታዊ አመለካከት የተፈተንክበትን ወቅት አስታውስ ፤ እንዴት ለዚህ ውሳኔ እንደበቃህ እንዳትረሳ ። አንተ አለህ ፤ ተስፋህ ይኖራል ። ህልምህ አለ ፤ ታላቅነትህም አብሮት አለ ። በእርግጥም ተመልሰህ ተመጣለህና ዛሬ ባለህበት ሁኔታ በፍፁም ተስፋ እንዳትቆርጥ ። በርታ!

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


ራስህ ላይ ስራ!

ጂም ሮን የተባለ ድንቅ መምህር "ስራህ ላይ ጠንክረህ ሰርተህ የምትዝናናው ቅንጡ ሆቴል ሊሆን ይችላል፤ ከስራህ በተጨማሪ ግን ራስህ ላይ ስትሰራ ግን ሆቴሉን ትገዛዋለህ" ይለናል።

ድርጅቶች የሚቀጥሩት ያንተን ዕውቀትና ልምድ ነው፤ አንተ በዕውቀትና በልምድ ካደክ ተፈላጊነትህ ሰማይ ይነካል። ራስህ ላይ መስራት ማለት በዕውቀት፣ በአመለካከት፣ በመንፈሳዊ ህይወት፣ በአካል፣ በስነልቦና በየቀኑ ማደግ ማለት ነው። ስራውን ወጥሮ የሚሰራ ገቢ ያገኛል፤ ከስራው በተጨማሪ ራሱ ላይ የሚሰራ ደግሞ ሀብት ይገነባል፤ ልዩነቱ ግልፅ ነው!

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


#ካንተ_የሚጠበቀው_ማለምና_ማሰብ_ነው!

ማንኛውም ሰው ሙሉ ቁጥጥር ያለው የሀሳብ ኃይል ላይ ነው፡፡ በዩኒቨርስ ውስጥ አምስት የታወቁ ነገሮች ሲኖሩ ከትናንሾቹ ኤሌክትሮንና ፕሩቶን እስከ ትላልቆቹ ፀሀዮች ያሉ ነገሮች የሚሠሩት ከእነዚሁ ነገሮች ነው፡፡

እንደ ጊዜ፣ ቦታ፣ ኃይል እና ቁስ፡፡ ያሉት አራቱ ነገሮች ያለ አምስተኛው ምሉዕ አይሆኑም፡፡ አምስተኛው ነገር ከሌለ ሁሉም ነገር ስርዓት አልባ ይሆን ነበር፡፡ እኔና እናንተም አንኖርም ነበር፡፡ ያ አምስተኛ ነገር ምን ይመስላችኋል?

ሁሉን አቀፍ እውቀት ነው፡፡

ይህ ሁሉን አቀፍ እውቀት በሁሉም ነገር ላይ ማለትም በሚበቅሉት ሳሮች፣ በኤሌክትሮንና ፕሩቶኖች፣ በጊዜና በቦታ ሆኖ በሚገኝ በሁሉም ነገር ላይ ራሱን ይገልጣል፡፡

በመሆኑም ሰው በጣም ስኬታማ የሚሆነው ይህንኑ ዕውቀት በአእምሮው አሰላስሎ በተግባር መደገፍ ሲችል ነው፡፡ እያንዳንዱ ሰው የሚፈቅደውን ያህል ሁሉን አቀፍ ዕውቀት የራሱ ማድረግ ይችላል፡፡ ከእርሱ የሚጠበቀው ማለምና ማመን ነው፡፡

#ወደ_ሀብት_ጉዞ መጽሐፍ- በናፖሊዮን ሂል

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


#ራስህን_ጠልፈህ_አትጣል!

#ሁልጊዜ_ሌሎችን_ለማስደሰት_መፈለግ፤ ይኼንንም ከሌሎች በሚገኝ ሙገሳ እና ምስጋና ለማረጋገጥ መሻት፡፡ እርግጥ እውቅናን ብንፈልግ ችግር የለውም፡፡ ነገር ግን ሁልጊዜ የሌሎችን ሙገሳ እና አድናቆት መስማት መፈለግ የለብንም፡፡ ‹ሌሎች እስካልነገሩኝ ድረስ ጥሩ አልሰራሁም ማለት ነው› ብሎ ማመንም ትልቅ ችግር ነው፡፡

#በማንኛውም_ጊዜ_ብርቱ_መስሎ_ለመታየት_መፈለግ፡፡ ይኼም ሲባል ደግሞ ተጋላጭነትን ላለማሳየት ብሎ የሌለ ጥንካሬ ማሳየት፡፡ ይህ ተገቢ አይደለም፡፡ ሁላችንም ድክመቶች አሉብን፡፡

#ሁልጊዜ_እየመሩ_መታየትን_መፈለግ፡፡ ቆጥረን የማንዘልቃቸው እና ስኬትን ያገኙ ሰዎች ገና ከመጀመሪያው ብቃት እና ለየት ያለ ችሎታ የለውጥ ጥበብ አላቸው ሲባል በጣም ብዙዎች ደግሞ አልሆኑም፡፡ ‹ወጣቱ ሚልየነር› ወይንም ‹ከ 30 ዓመት በታች እጅግ ስኬታማ የሆነ› ከሚባል ተርታ ለመመደብ ብሎ መነሳት ብዙዎች የሚገቡበት ራስን ጠልፎ የሚጥል መነሻ ነው፡፡

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


ፍቅር እስከ መቃብር

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book

20 last posts shown.