#ስሜቶችህ_አሻንጉሊት_የሆንክ_ያህል_ይጫወቱብሀል
“ሃሳቦችህን እንዲህ ሰድራቸው - አንተ ሽማግሌ ነህ፤ ከዚህም በኋላ ጥቂት እድሜ ብቻ ነው ያለህ - በእነዚህ ነገሮች ከዚህ በኋላ አትገዛም፤ እያንዳንዱ ስሜቶችህ እንደ አሻንጉሊት አይጎትቱህም፤ አሁን ላይ ስላለህ ሕይወት አታማርርም ወይም መጻኢ ቀናቶችህን በፍርሃት አትጠብቃቸውም”
#ማርከስ_አውሬሊየስ
ሰው መጥቶ እኛን ሊያዘን እና አለቃ ሊሆንብን ሲሞክር እንበሳጫለን። እንዴት እንደምለብስ አትነግረኝም፣ እንዴት እንደማስብ፣ ስራዬን እንዴት እንደምሰራ፣ እንዴት መኖር እንዳለብኝ… ይህም የሆነው እኛ ነጻ ሰው ነን ብለን ስለምናስብ ነው።
ለራሳችን እኛው ራሳችን በቂ ነን።
ይህንንም ነው ለራሳችን ስንነግረው የኖርነው።
ሆኖም የማንስማማበትን ሃሳብ የሆነ ሰው ካቀረበልን፣ ውስጣችን እንድንሞግተው ይነግረናል። የሆነ ሰው የማንወደውን ነገር ካደረገብን እንበሳጫለን። መጥፎ ሁነት ሲገጥመን እናዝናለን፤ ድባቴ ውስጥ እንገባለን ወይም እንጨነቃለን። ሆኖም ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ መልካም ነገር ከሆነልን በድንገት ደስተኛ፣ ተጫዋች እና ተጨማሪ ፈላጊዎች እንሆናለን።
ማንም ሰው ከስሜቶቻችን በላይ በእኛ ላይ አይጫወትም። ልክ አሻንጉሊት እንደሆንን ሁሉ ስሜቶቻችን ይጫወቱብናል፤ ይህን ማስተዋል ስንጀምር በስሜቶቻችን መመራት ማቆም እንዳለብን እንረዳለን።
ስሜቶቻችን ሳይሆኑ እኛ ነን አለቃ መሆን ያለብን፤ ምክንያቱም ለራሳችን እኛው ራሳችን በቂ እና ነጻ የሆንን ነንና።
#የለት_ፍልስፍና መጽሐፍ
join us...
@Ab_book
@Ab_book
@Ab_book
“ሃሳቦችህን እንዲህ ሰድራቸው - አንተ ሽማግሌ ነህ፤ ከዚህም በኋላ ጥቂት እድሜ ብቻ ነው ያለህ - በእነዚህ ነገሮች ከዚህ በኋላ አትገዛም፤ እያንዳንዱ ስሜቶችህ እንደ አሻንጉሊት አይጎትቱህም፤ አሁን ላይ ስላለህ ሕይወት አታማርርም ወይም መጻኢ ቀናቶችህን በፍርሃት አትጠብቃቸውም”
#ማርከስ_አውሬሊየስ
ሰው መጥቶ እኛን ሊያዘን እና አለቃ ሊሆንብን ሲሞክር እንበሳጫለን። እንዴት እንደምለብስ አትነግረኝም፣ እንዴት እንደማስብ፣ ስራዬን እንዴት እንደምሰራ፣ እንዴት መኖር እንዳለብኝ… ይህም የሆነው እኛ ነጻ ሰው ነን ብለን ስለምናስብ ነው።
ለራሳችን እኛው ራሳችን በቂ ነን።
ይህንንም ነው ለራሳችን ስንነግረው የኖርነው።
ሆኖም የማንስማማበትን ሃሳብ የሆነ ሰው ካቀረበልን፣ ውስጣችን እንድንሞግተው ይነግረናል። የሆነ ሰው የማንወደውን ነገር ካደረገብን እንበሳጫለን። መጥፎ ሁነት ሲገጥመን እናዝናለን፤ ድባቴ ውስጥ እንገባለን ወይም እንጨነቃለን። ሆኖም ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ መልካም ነገር ከሆነልን በድንገት ደስተኛ፣ ተጫዋች እና ተጨማሪ ፈላጊዎች እንሆናለን።
ማንም ሰው ከስሜቶቻችን በላይ በእኛ ላይ አይጫወትም። ልክ አሻንጉሊት እንደሆንን ሁሉ ስሜቶቻችን ይጫወቱብናል፤ ይህን ማስተዋል ስንጀምር በስሜቶቻችን መመራት ማቆም እንዳለብን እንረዳለን።
ስሜቶቻችን ሳይሆኑ እኛ ነን አለቃ መሆን ያለብን፤ ምክንያቱም ለራሳችን እኛው ራሳችን በቂ እና ነጻ የሆንን ነንና።
#የለት_ፍልስፍና መጽሐፍ
join us...
@Ab_book
@Ab_book
@Ab_book