ቤተ ሊባኖስ ₃


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Religion


የኢ/ ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን አስተምሮ ና ስርዓት የጠበቁ
👉 መንፈሳዊ መዝሙሮች
👉 መንፈሳዊ ትምህርቶች
👉 መንፈሳዊ ግጥሞች
👉 መንፈሳዊ ታሪኮች
👉 ምንፈሳዊ ምክር ነክ ፁፎች
👉 ንግሶች ስኖሩ እናሳዊቃለን
👉ለመናፍቃለ የተለያዩ መልሶችን እንሰጣለን
ግሩፕን ለመቀላቀል @zemariwochu3
ለተለያየ ጥያቄ ና @DA121922 ካላቹ አናግሩኝ

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Religion
Statistics
Posts filter


✝️እንኳን ደስ አላችሁ በዩቲዩብ የምናውቀው #ማኅቶት_ቲዩብ አሁን ደግሞ በቴሌግራም መጥታል ለመቀላቀል ከስር Join የሚለውን ንኩት።

https://t.me/+2ua4-eAbNTI1MTRk
https://t.me/+2ua4-eAbNTI1MTRk


🙋‍♂አንድጥያቄ

✞በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ሰው ሰውን መግደል የጀመረው በማን ነበር ⁉️✟

         


'https://t.me/addlist/2CQ3e4ZJYT9hZGNk' rel='nofollow'>💁‍♂ስለ ሀይማኖቴ ማወቅ ግዴታዬ ነው የሚል የማንኛውም ኦርቶዶክስ ሊቀላቀለው የሚገባ ቻናል።  ጥያቄ ይጠየቃል ምዕመኑም ይሳተፋል
ቻናሉን ለመቀላቀል ከስር ክፍት የሚለውን
መጫን በቂ ነው።
              'https://t.me/addlist/2CQ3e4ZJYT9hZGNk' rel='nofollow'> ክፈት        ክፈት               
               ክፈት        ክፈት               
                                                   
ክፈት        ክፈት        ክፈት        ክፈት
ክፈት        ክፈት        ክፈት        ክፈት
                                                    
                                                   
                                                    
                                                    
                                                     
               ክፈት         ክፈት              
               ክፈት         ክፈት


⛪️ ዝጎራ# ፀሐፊ አለማየሁ ዋሴ እሸቴ

🌿#ተራኪ #እዮብ #ዮናስ ክፍል4⃣

🌺#አዳምጡ መልካም ቆይታ

https://t.me/Abalibabos333
ይቀጥላል


አንድ ዓሣ አጥማጅ ገና ሳይነጋ በጠዋቱ ወደባህር ዳርቻ ሄደ ነገርግን ይህ ሰው የደረሰበት ሰዓት ጨለማ ነበር በወቅቱም ለሥራው ስላልተመቸው እስኪነጋ ቁጭ ብሎ መጠበቅ ጀመረ ከባህር ዳርቻውም አጠገብ በድንጋይ ጠጠሮች የተሞላ ጆንያ አጋጠመው።

🌚ዓሣ አጥማጁም ከጆንያው ውስጥ ያለውን አንድ ጠጠር አውጥቶ ወደባህሩ ሲወረውረው እንቦጭ የሚል ድምፅ ሰማ። ይህም ድምፅ ስላስደስተው ወድያውኑ ሌሎች ጠጠሮች በየተራ እየወረወረ እንቦጭ እንቦጭ እየደረገ እየተደሰተ መወርወሩን ቀጠለ…

ይህ ዓሣ አጥማጅ በጆንያ ውስጥ የነበሩትን ጠጠሮች ወርውሮ አንዲት ጠጠር ብቻ በቀረው ሰዓት የብርሃን ወገግታ መምጣቱን አስተዋለ።

አጥማጁም የያዛውን ጠጠር ለመወርወር ከመቀመጫው ብድግ ሲል በእጁ የያዛውን ጠጠር በደንብ አገላብጡ ተመለከተ በድንጋጤም ሲያስተውለው ጠጠር ሳይሆን አልማዝ(💎) መሆኑን ተረዳ።

ዓሣ አጥማጁም በንዴት ሲቃ ተናነቀው ምክንያቱም እስኪነጋ ድረስ ሲወረውር የነበረው በጆንያ ሙሉ ጠጠር ሳይሆን አልማዝ መሆኑን አስተዋል።

ብዙ ሰዎች በህይወታቸው እንዲህ ናቸው። በእጃቸው ያለው ጊዜ አልማዝ መሆኑን ሳይረዱ እንቦጭ እንቦጭ የሚል ድምፅ ለመስማት ሲሉ ጊዜያቸውን በእንቅልፍ፣ በምንም፣ በፊልም፣ በማህበራዊ ድህረ-ገፅ፣ በወሬ፣  በክርክር እና በብስጭት ወደ ማይመልሰው ባህር ይወረውሩታል ጥቂቶች እንደ ዓሣ አጥማጁ በመጨረሻ ሰዓት ጊዜያቸው አልማዝ እንደሆነ ሲረዱ አብዛኞቹ ግን ጊዜ ምንም እንዳልሆነ ሳያውቁ በዚያው ይበቃል።

የሰው ልጅ በምድር ላይ የተሰጠው ጊዜ ውስን ነው። ይህን ውስን ጊዜ በወቅቱና በሰዓቱ ካልተጠቀመበት እድሉ ላይመለስ ይወሰድበታል።  ምንም ቢለፋ፣ ቢያለቅስ እና ቢፀፀት ተመልሶ አያገኘውም። ይልቁንም በጊዜው የዘራውን መልካም ይሁን ክፉ በጊዜው ያጭዳል።

https://t.me/Abalibanos333
ምክር ነክ ፁሑፍ..


⛪️ ዝጎራ# ፀሐፊ አለማየሁ ዋሴ እሸቴ

#ተራኪ #እዮብ #ዮናስ ክፍል3⃣

#አዳምጡ መልካም ቆይታ

https://t.me/Abalibanos333
ይቀጥላል


⛪️ ዝጎራ# ፀሐፊ አለማየሁ ዋሴ እሸቴ

#ተራኪ #እዮብ #ዮናስ ክፍል2⃣

#አዳምጡ መልካም ቆይታ

https://t.me/Abalibanos333

ይቀጥላል..


⛪️ ዝጎራ# ፀሐፊ አለማየሁ ዋሴ እሸቴ

🌿#ተራኪ #እዮብ #ዮናስ ክፍል1⃣

🌺#አዳምጡ መልካም ቆይታ

@Abalibanos333
ይቀጥላል


የተወደዳችሁ ውድ  የቤተ ሊባኖስ ቻናል ተከታታይ ቤተስቦች  ወንድሞችና እህቶች እንደምን ከረማችሁ አምላካችን እግዚአብሔር እስከዚች ዕለት ስላደረሰን ስሙ የተመሰገነ ይሁን በቀጣይ ጊዜያት የአለማየሁ ዋሴ እሸቴ ዝጎራ የተሰኘዉን ተወዳጅ መጽሐፍ በተራኪ መልክ በክፍል በክፍል አዘጋጅተን ወደ እናተ በዚህ ሳምንት የምናደርሰ ይሆናል



enatem ezi channl lay sew bemegabez edketatelu adrigu https://t.me/zemsriwochu3

    


ክርስቶስ ሊቀ ካህን ሲባል
መሀሪነቱን ነው የሚገልጸው?
ወይስ አማላጅነትን?

🎙ዮሐንስ🎙

የተሐድሶዎች እና ፕሮቴስታንቶች የዕብራውያን
2 : 17 ን ቃል በቸልታ
ሳይገነዘቡ ማለፍ አደጋ ላይ
ጥሏቸዋል!!!


ጾታዊ ፍቅር.pdf
227.8Kb
ጾታዊ ፍቅር
በ voice ማዳመጥ ያለተመቻችዉ
በpdf

@Abalibanos333


🥀ጾታዊ ፍቅር🥀

🎙አቡ(ወንዴ)🎙
ክፍል 5

፦ጾታዊ ፍቅር ከማን ጋር?
፦ጾታዊ ፍቅር ከማን ጋር ቢሆን አምላክ ይፈቅዳል?ከማንስ ጋር ቢሆን አይፈቅድም?

https://t.me/Abalibanos333


#ጾታዊ ፍቅር

🎙አቡ(ወንዴ)🎙
ክፍል 4

፦እኛ ወጣቶች(ፍቅረኛሞች) ጥምረታችን ምን መምሰል አለበት?
፦ጾታዊ ፍቅር መቼ እንጀምር?
፦ጾታዊ ፍቅር ከእግዚአብሔር ጋር

https://t.me/zemariwochu3
ይቀጥላል.


🌹ጾታዊ ፍቅር🌹

🎙አቡ(ወንዴ)🎙
ክፍል 3

፦የዘመኑ ጥምረት
፦ፍቅረኛ አለህ/ሽ? ምን አይነት ነው ጥምረታችሁ?
፦ፍቅረኛ ልትይዝ ልትጠይቃት ነው? ምክንያትህ ምንድነው? እርግጠኛ ነህ አፍቅረሀት ነው?

https://t.me/zemariwochu3


🌹ጾታዊ ፍቅር🌹

🎙አቡ(ወንዴ)🎙
ክፍል2

፦የመጀመሪያ ፍቅር ሲይዘን ታስታውሳላችሁ?

https://t.me/Abalibanos333

ይቀጥላል


🌹ጾታዊ ፍቅር🌹

🎙አቡ(ወንዴ)🎙
ክፍል 1

ፍቅር ምንድነው?ለምንድነው የምናፈቅረው?በምንድነው የምናፈቅረው?ለምንድነው ስናፈቅር ልባችን ታምቡር ሚመታው?አንደበታችን ሚቆላለፈው?እጃችን የሚያልበው?...

https://t.me/Abalibanos333

ይቀጥላል


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን

📖መጽሐፍ ቅዱሳን እንዴት ላንብብ📖
ክፍል ፯

#መጽሐፍ_ቅዱስን_በጊዜና_በሰአት_ከፋፍሎ_የማንበብ_ስልት

ሰዓትና ጊዜ የሁሉም ፍጡራን እኩል ስጦታዎች ናቸው። የሰዓትና የጊዜ ጥቅም ጎልቶ የሚታወቀው በሚሰራ ሰው ህሊና ውስጥ ነው። ቀድሞ ሰዓትና ጊዜን ውድ ከሆነው ወርቅ ጋር ሲነፃፀር ነበር። አሁን ግን ሰዓት ሰዓት ነው ጊዜም ጊዜ ነው። እግዚአብሔር ለሁሉም እኩል ነው ሰዓትና ጊዜን የሰጠው። ለሁሉም ፍጡራን ሐፕት ላለውም ድሀ ለሆነውም እኩል ይነጋል ይመሻል። በዚህ ጊዜ ውስጥ ሰው ሕይወቱን በትክክለኛ አቅጣጫ መርቶ ዘመኑን በምስጋና በሽልማት መቋጨት ከፈለገ የመጽሐፍ ቅዱስ ወዳጅ እና አንባቢ ሊሆን ይገባል። መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ዕለት ዕለት እራስንና እግዚአብሔርን ወደማወቅ ደረጃ ከፍ ማለት ነው። ጊዜና ሰዓትን በቀጥታ ከማየታችን በፊት የመጽሐፍ ቅዱስን አከፋፈል በምዕራፉ ብዛት እንመልከትና እንዴት ማንበብ እንዳለብን እንይ። ወደ ኋላ መለስ ብለን የመጽሐፍ ቅዱስን አከፋፈል (ክፍል ፪) ካስታወስን መጽሐፍ ቅዱስ ብሉይ ኪዳንና ሐዲስ ኪዳን ተብሎ በሁለት እንደሚከፈል ተመልክተናል። በዚህ አከፋፈል ውስጥ ያሉትን ምዕራፎች ነው የምናየው

#በብሉይ_ኪዳን
የህግ መጻሕፍት፦
ከኦሪት ዘፍጥረት - ኦሪት ዘዳግም ያሉ 5 መጻሕፍት ሲሆኑ በውስጣቸው 187 ምዕራፎች ይገኛሉ።
የታሪክ ክፍል፦
ከመጽሐፈ ኢያሱ - መጽሐፈ አስቴር ያሉት 12 መጻሕፍት ሲሆኑ 249 ምዕራፎች ይዘዋል።
የመዝሙርና የቅኔ ክፍል፦
ከመጽሐፈ ኢዮብ - ማኃልየ ማኃልይ ዘሰለሞን ድረስ ያሉት 5 መጻሕፍት ሲሆኑ በውስጣቸው 243 ምዕራፎች ይዘዋል።
የትንቢት ክፍል፦
ከትንቢተ ኢሳይያስ - ትንቢተ ሚልኪያስ ድረስ ያሉ 17 የትንቢት መጻሕፍት ሲሆኑ በውስጣቸው 250 ምዕራፎች ይገኛሉ።
በአጠቃላይ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት 929 ምዕራፎች አሉት።

#በሐዲስ_ኪዳን
የወንጌል ክፍል፦
ከማቴዎስ ወንጌል - ዮሐንስ ወንጌል ያሉት 4 ወንጌላት ሲሆኑ በመጻሕፍቱ ውስጥ 89 ምዕራፎች ይገኛሉ።
የታሪክ ክፍል፦
የሐዋርያት ሥራ ብቻ ሲሆን 28 ምዕራፎች አሉት።
የመልዕክት ክፍል፦
ከሮሜ መልዕክት - ይሁዳ መልዕክት ያሉት 21 መጻሕፍት ሲሆኑ 121 ምዕራፎች ይዘዋል።
የትንቢት ክፍል፦
የዮሐንስ ራዕይ ብቻ ሲሆን 22 ምዕራፎች አሉት።
የሐዲስ ኪዳን አጠቃላይ ምዕራፎች 260 ናቸው።

የብሉይ ኪዳንና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት ምዕራፎች አጠቃላይ ድምር 1189 (አንድ ሺህ አንድ መቶ ሰማንያ ዘጠኝ) ነው። በዚህ መጽሐፍ ቅዱሳዊ አከፋፈል ውስጥ የምዕራፎቹ ቁጥር የሚያሳየው የ66ቱን መጽሐፍት ብቻ ነው። ከላይ የመጽሐፍ ቅዱስን የምዕራፍ ብዛት ካየን በዓመት መጽሐፍ ቅዱስን አንብቦ ለመጨረስ ምን ማድረግ አለብን? የሚለውን እንመልከት። መጽሐፍ ቅዱስን በአከፋፈሉ ከተረዳነው ግን ለንባብ በጣም ይቀለናል። የብሉይ ኪዳንና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት ሲደመሩ 1189 ናቸው።

እንዚህን የመጽሐፍ ቅዱስ ምዕራፎች በዓመት ውስጥ አንብቦ ለመጨረስ በጊዜና በሰዓት መከፋፈል ያስፈልጋል። 1189 ሲካፈል ለ365 ቀናት = 4 ቀን ይደርሳል። ይህ ማለት በቀን 4 ምዕራፍ እናነባለን። ጠዋት 2 ማታ 2 ወደ ወር ስንቀይረው 120 ምዕራፎች ማለት ነው።

በቀን ውስጥ ለማንበብ የምንሰጠው ደቂቃ ጠዋት 10 ደቂቃ ማታ 10 ደቂቃ በድምሩ 20 ደቂቃ ነው። በወር ውስጥ 600 ደቂቃዎች ነው የምንጠቀመው።
እንግዲህ እንደ ንባብ ያለ ሕይወትን የሚሰጥ ታላቅ ነገር የለምና ከላይ በተቀናበረ መልኩ በተዘጋጀው ዘዴ በመጠቀም እንድናነብና የእግዚአብሔርን ቃል እንድናውቅ አምላካችን እግዚአብሔር ይርዳን።

ተፈጸመ

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!

https://t.me/Abalibanos333


" በፈጣሪ ልጄን አድኑልኝ😭😭😭"     #አበት

ይህ ቆንጅዬ ህፃን #አሚር የሱፍ  ይባላል!በተወለደ 4ኛ ወሩ ህመም ሲያሰቃየውና እንቅልፍ ሲከለክለው እናትና አባት ወደ ጥቁርአንበሳ ሆስፒታል ይዘውት ይሄዳሉ!
ህፃን አሚር አንድ ወር አልጋ ይዞ ክትትል ካደረገ በኋላ ዶክተሮች "የልብ ክፍተት  ችግር አለበት፣ አስቸኳይ ቀዶ ጥገና ያስፈልገዋል"ተባሉ!

ልጁን ለማሳከም የተጠየቁት 1500000 ብር ነው ከአቅም በላይ ስለሆነ ልጃቸውን ለማዳን እናንተን እየተማፀኑ ነው😭 እባካችሁ #እንድረስላቸው🙏  #በዱአ #ሼር እናግዛቸው🙏
                "ለመልካም ስራ ረፍዶ አያውቅም"
#አካውንት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000304310937-ዩሱፍ ሀምደለ (አባት)
#ስልክ
0705740135

☞አድራሻ ካራ ቆሬ ወታደር ሰፈር

☞ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን

📖መጽሐፍ ቅዱስን እንዴት ላንብብ📖
ክፍል ፮

#የመጽሐፍ #ቅዱስ #ዘይቤ

ዘይቤ ማለት የአነጋገር ስልት ማለት ነው።መጽሐፍ ቅዱስ ራሱን የቻለ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ዘይቤ አለው።ዘይቤያዊ አነጋገር እና አገላለጹ የሚመጣውን እንዳለፈ ያለፈውን እንደሚመጣ በማድረግ ይገላጻል። ዘይቤያዊ አነጋገርና አገላለጽን ማወቅ በመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ ውስጥ ትልቅ ሚና አለው።

1. #የሚመጣውን #እንዳለፈ #መናገር
የሚመጣውን ነገር እንደሚመጣ ሲናገር ይህ ትንቢት ይባላል። በመጽሐፍ ቅዱስ አገላለጽ ግን የሚመጣውን እንደሚመጣ በመግለጽ እና ያልተፈጸመውን ትንቢት ሲገልጽ እንመለከታለን።ይህ የመጽሐፍ ቅዱስ ዘይቤ ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ በቀራንዮ እጆቹና እግሮቹ በመስቀሉ ላይ ከመቸንከራቸው አስቀድሞ በ900 ዓመተ ዓለም የተናገረውን ትንቢት ስንመለከት "እጆቼንና እግሮቼን ቸነከሩኝ አጥንቶቼ ሁሉ ተቆጠሩ...ልብሴን ለራሳቸው ተከፋፍለው በቀሚሴ ላይ ዕጣ ተጣጣሉ" መዝ 21፡17 በመዝሙረ ዳዊት የተጠቀሰውን የትንቢት ቃል ስንመለከት ቀጥታ ነገሩ እንደተፈጸመ ያመለክታል። ትንቢቱ ግን በብሉይ ኪዳን ተነግሮ በሐዲስ ኪዳን መፈጸሙን ማቴ 27፡1 ጀምሮ ማንበብ እንችላለን። ይህንን የመሰሉ ሌሎች ጥቅሶችም አሉ፦ መዝ 68፡21፣ ት. ኢሳ 53፡4፣ ት. ኢሳ 9፡6 ገና ሊሆን ያለውን ትንቢት በመግለጽ መጽሐፍ ቅዱስ የሚመጣውን እንዳለፈ(እንደመጣ) በመናገር ሲገልጽ እንመለከታለን።

2. #ያለፈውን #እንደሚመጣ #መናገር
መጽሐፍ ቅዱስ የሚመጣውን እንዳለፈ አድርጎ የመናገር ዘይቤ እንዳለው ሁሉ በቀራንዮ ያለፈውን፣የሆነውን ወይም የተፈጸመውን ገና እንደሚመጣ አርጎ የመናገር ዘይቤ አለው። በይሁዳ መልዕክት 1÷7 "እንዲሁም እንደእነርሱ ዝሙትን ያደረጉና ሌላ ስጋ የተከተሉ ሰዶምና ገሞራ በዙሪያቸው የነበሩ ከተሞች በዘላለም እሳት እየተቀጡ ምሳሌ ሆነዋል"
ይህ በይሁዳ የተነገረውን ረጋ ብለን ስናጤነው ድርጊቱ ከተፈጸመ ብዙ ሺህ አመታትን አስቆጥሯል። አነጋገሩ ግን አሁንም ወደፊት እየተደረገ እንዳለ ይመስላል። ይህ ከተከናወነ ግን 2000 ዓመታት አልፈውታል። "እየተቀጡ" የሚለው ቃል የመጽሐፍ ቅዱስን ያለፈውን እንደሚመጣ አድርጎ የመናገር ዘይቤ ያስተምራል። በዕብ 7፡25 "ስለ እነርሱ ሊያማልድ (ሊያስታርቅ) ዘወትር በሕይወት ይኖራል" ቅዱስ ጳውሎስ የተናገረው ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። የአገላለፁ ዘይቤ ግን ያለፈውን እንደሚመጣ በማድረግ ነው። የተገለጸው ግን ፍፃሜ ያገኘው በዕለተ ዓርብ በቀራንዮ አደባባይ ነው። በዕብ 9፡28 "ሁለተኛ ጊዜ ያለ ኃጢአት ይታያቸዋል" የቅዱስ ጳውሎስን አገላለጽ ስንመለከት ቃሉ ስለሰዎች ኃጢአት ዳግመኛ መከራ ሊቀበል ይመጣል ማለቱ ሳይሆን በዳግም ምፅዓት በእርሱ ሕይወት ላገኙት ይገለጥላቸዋል ማለቱ ነው። አብዛኛውን ጊዜ ስህተቶች የሚመጡት መጽሐፍ ቅዱስን እንዴት ማንበብ እንዳለብን ካለማወቅ ነው። መጽሐፍ ቅዱስን ለማንበብ መሪ ያስፈልጋል የሐዋ 8፡30 "ፊሊጶስም ሮጦ የነቢዩን የኢሳይያስን መጽሐፍ ሲያነብ ሰማና በውኑ የምታነበውን ታስተውላለህን አለው። እርሱም የሚመራኝ ሳይኖር እንዴት ይቻላል? አለው" በውስጡ ያሉትን ነጠላ ትርጉም፣ምሳሌያዊ ትርጉም፣ምስጢራዊ ትርጉም፣የሕይወት ትርጉም ዘይቤያዊ አነጋገርን ማወቅ የግድ ነው።

በቀጣይ
📖መጽሐፍ ቅዱስን በጊዜና በሰዓት ከፋፍሎ የማንበብ ስልት እናያለን

የመጨረሻዉ ክፍል ይቀጥላል


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን።

📖መጽሐፍ ቅዱስን እንዴት ላንብብ📖
ክፍል ፭(5)

#የመጽሐፍ #ቅዱስ #አተረጓጎም

ዛሬ የመጽሐፍ ቅዱስን አተረጓጎም እናያለን።
የምናነበው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል በየትኛው የአተረጓጎም ስልት እንደተጻፈ ካላወቅን የምናነበውን ንባብ ላንገነዘበው እንችላለን።መጽሐፍ ቅዱስን ስናጠና አራት የትርጉም ዓይነቶች አሉት፦
፩. የነጠላ ትርጉም
፪. ምሳሌያዊ ትርጉም
፫. ምስጢራዊ ትርጉም
፬. ሕይወት ተኮር ትርጉም ናቸው
ሁሉንም እስኪ በተራ እንያቸው

፩. #ነጠላ #ትርጉም
ነጠላ ትርጉም የምንለው ንባቡን በቀጥታ ወስደን ያለምንም ዝርዝር የምንጠቀምበትን ነው! ለምሳሌ፦

፩. "እግዚአብሔር በመጀመርያ ሰማይና ምድርን ፈጠረ" ኦ. ዘፍ ፩፡፩
፪. "ወደፈተና እንዳትገቡ ትጉና ፀልዩ" ማቴ ፳፮፡፵፩

፪. #ምሳሌያዊ #ትርጉም
ምሳሌ በዕብራይስጥ "ማሻል" ይባላል።ምሳሌያዊ ትርጉም አንድ ነገርን የበለጠ ለመግለፅ ይረዳል።ለምሳሌ፦

፩. "እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ" ዮሐ ፩፡፳፱ ኢየሱስ ክርስቶስ በበግ መመሰሉን እንመለከታለን
፪. እስራኤላውያን በወይን ቦታ እንደተመሰሉ በ ት. ኢሳ ፭፡፩-፪ የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለት መመሰል ት. ዳን ፪፡፴፬

፫. #ምስጢራዊ #ትርጉም
ምስጢራዊ ትርጉም የተሰወረ የተደበቀ ነገር የያዘ ላይ በላይ የማይታይ ማለት ነው።መጽሐፍ ቅዱስን በማንበብ ሂደት ውስጥ ምስጢሩን ማግኘት ወይም መረዳት ካልተቻለ መልዕክቱን መጨበጥ አይቻልም።ምስጢራዊ ትርጉም ጥሬ ዘሩን ወይም ንባቡን ብቻ ሳይከተል ንባቡን ሳይጠብቅ ምስጢሩን በዋናነት ጠብቆ የሚተረጎም ነው።
"በበሰሉት መካከል ጥበብን እንናገራለን ተሰውሮ የነበረውን የእግዚአብሔርን ጥበብ በምስጢር እንናገራለን" ፩ቆሮ ፪፡፮-፯
በምስጢራዊ ትርጉም ውስጥ ሊገለጡ የሚችሉ ምስጢራት፣ያልተገለጡ ምስጢራት፣ ወደፊት የሚገለጡ ምስጢራት፣ምንም ሊገለጡ የማይችሉ ምስጢራት እንዳሉ ማወቅ አለብን። በመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ ውስጥ ሲነበብ ይህንን መረዳት አለብን።

፬. #የሕይወት #ትርጓሜ
የሕይወት ትርጓሜ የምንለው መጽሐፍ ቅዱስን የሚያነብ ሰው በሕይወቱ ውስጥ የሚሰጠው ትርጉም ነው። መጽሐፍ ቅዱስን በማንበብ የምናገኘውን የሕይወት ለውጥ ትህትና፣ሰላም፣ደስታ፣ፍቅር፣ርህራሄ...ያጠቃልላል።

ቃሉን በሕይወታችን እንድንተገብር የርሱ መልካም ፍቃድ ይሁን

በቀጣይ
📖የመጽሐፍ ቅዱስ ዘይቤና
📖መጽሐፍ ቅዱስን በጊዜና በሰዓት ከፋፍሎ የማንበብ ስልት እናያለን

https://t.me/Abalibanos333

ይቀጥላል

20 last posts shown.