#ስግደት
እና #ክብር
#ስግደት
በፈጣሪ እና በፍጡር፣ #በግዢ
እና በተገዢ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚገልጡበት #የመገዛት
ምልክት ነው፡፡
👉#ስግደት ራስን ዝቅ አድርጐ በመንበርከክ በተሰበረ ልቡና ይቀርባል፡፡
📌የስግደት
ዓይነቶች
#ስግደት #ሁለት ዐይነት ነው።
📌1ኛ፦#የባሕርይ (የአምልኮት ስግደት።
🌿ይህ ስግደት የሚገባው #ለፈጣሪ ብቻ ነው፡፡አምላክነቱን አምኖና ተረድቶ የሚፈጸም #የአምልኮት ስግደት ሲ
ሆን ለሌ
ላ አይሰጥም፡፡
📖ዘፀ፦20፥1-6 👈ይነበብ
📖መዝ፦81፥9👈ይነበብ
📖መዝ፦135፥
15-18👈ይነበብ
📌2ኛ፦#የጸጋ (#የአክብሮት ስግደት)
🌸ይህ ስግደት ደግሞ ለእግዚአብሔር #ቅዱሳን፣ አገልጋዮቹ #ፍጡራን(የአክብሮት ስግደት) የሚሰጥ ነው፡
፡
👉ይኸውም #ለእግዚአብሔር
ማደሪያ #ለእመቤታችን፣ #ለመላእክት፣ #ለቅዱሳን ሰዎች ጌታ ተሰቅሎ ክ
ቡር ደሙን ላፈሰሰበት ቅዱስ #መስቀል የሚፈጸው ከአክብሮት ጋር የጸጋ ስግደት ነው፡፡
📖ኢያ፦5፥13👈ይነበብ
📖ኢሳ፦49፥23👈ይነበብ
📖ዳን፦2፥46 👈ይነበብ
📖ራእይ፦3፥8👈ይነበብ
📌ክብር ማለት ምን ማለት ነው?
🎍#ክብር፦ማለት ጌትነት፣ ታላቅነት፣ ከፍተኛነትን የሚገልጽ ነው፡፡ከሁሉም ነገር በላይ ክብር ያለው አምላካችን ልዑል #እግዚአብሔር ነው፡፡
📖ዘፀ፦16፥7👈ይነበብ
📖መዝ፦18፥1👈ይነበብ
📖1ኛ፦ነገ፦8፥11👈ይነበብ
📖ኢሳ፦6፥3👈ይነበብ
👉ስለዚህም #ለእግዚአብሔር ልዩ ክብር መስጠት ይገባል፡፡
📖ይሁዳ፦2፥5👈ይነበብ
✍እግዚአብሔር #ክብሩን በሚፈቅደው ምሳሌ ይገልጻል እንጂ ሰው የእግዚአብሔርን #ክብር #ሊያይ አይችልም፡፡
📖ዘፀ፦33፥17👈ይነበብ
📖ዮሐ፦1፥14👈ይነበብ
📖ማቴ፦17፥1👈ይነበብ
📖ዕብ፦1፥3👈ይነበብ
👉የጌታ ክብር በዳግም ምጽአትም ይገለጻል፡፡
📖ማር፦8፥38👈ይነበብ
📖ማቴ፦24፥36👈ይነበብ
🙏እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እሳተ #መለኮትን በማኅፀኗ የተሸከመች የአሽናፊው የእግዚአብሔር ወልድ #ማደሪያ ናትና #ክብርት እናት ነች።
📖ሉቃ፦1፥30-37👈ይነበብ
📖ሉቃ፦1፥48👈ይነበብ
👉አገልጋዮቹ ቅዱሳን #መላእክትና፣ ቅዱሳን #ሰዎችም ክብር አላቸው።
📖ሉቃ፦2፥9👈ይነበብ
📖1ኛቆሮ፦11፥7👈ይነበብ
📖1ቆሮ 15፥41👈ይነበብ
https://t.me/Abalibanos333👉#ክብር ለሚገባቸው ቅዱሳን የአምላክ አገልጋዮች ክብር መስጠት ይገባል።"ክብር ለሚገባው ክብር ስጡ፡፡"
📚ሮሜ፦13፥7👈ይነበብ
✝️ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ይቆየን✝️🙏