ቤተ ሊባኖስ ₃


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Religion


የኢ/ ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን አስተምሮ ና ስርዓት የጠበቁ
👉 መንፈሳዊ መዝሙሮች
👉 መንፈሳዊ ትምህርቶች
👉 መንፈሳዊ ግጥሞች
👉 መንፈሳዊ ታሪኮች
👉 ምንፈሳዊ ምክር ነክ ፁፎች
👉 ንግሶች ስኖሩ እናሳዊቃለን
👉ለመናፍቃለ የተለያዩ መልሶችን እንሰጣለን
ግሩፕን ለመቀላቀል @zemariwochu3
ለተለያየ ጥያቄ ና @DA121922 ካላቹ አናግሩኝ

Related channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Religion
Statistics
Posts filter


Forward from: ✞ ኦርቶዶክስ መዝሙር ✞
ምኵራብ
    ✍
ምኵራብ ማለት ታላቅ ሕንፃ ተራራ ኮረብታ የሚያክል መስገጃ ቤተጣዖት የአይሁድ ቤተመቅደስ ቤተጸሎት የአይሁድ ጉባኤያቸው እና ማህበራቸው ምኲራብ ተብሎ ይጠራል ። ቀደም ሲል የአይሁድ አምልኮ በኢየሩሳሌም በነበረው ቤተመቅደስና በሥርዓቱ የተመሠረተ ነበር
አይሁድ ስግደትና መስዋዕት በኢየሩሳሌም ብቻ ነው ብለው ቢያምኑም ነገርግን በእየተበተኑበት ቦታ ሁሉ ምኲራብ ሰርተው ሕግና ነቢያትን እየተማሩ ሃይማኖታቸውን ያጸኑ ነበር ይህ በእንዲ እያለ ከጊዜ በኋላም የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ቤተመቅደሱን አፍርሶ ሕዝቡን ወደ ባቢሎን ካፈለሰው በኋላ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አይሁድ በሚገኙባቸው ሀገሮች (ስፍራዎች)ሁሉ ለጸሎት ለአምልኮ ለማኅበርተኛነት ልዩ ቤት ሊሠሩ እንደጀመሩ ይነገራል በክርስቶስ ጊዜ ግን በእስራኤል ሀገር በእየቦታው በኢየሩሳሌምም ሳይቀር ብዙ ምኲራቦች ነበሩ ኢየሱስም በምኲራቦቻቸው እያስተማረ ...በገሊላ ሁሉ ይዞር ነበር ማቴ.4፥23  ምኲራብ ለአምልኮ ሥርዓት ለጸሎት ለትምህርት በአጠቃላይ ለሕዝቡ መገልገያ ይውል ነበር ማቴ.6፥2-5 በእየሰንበቱ ሕዝቡ ሁሉ በምኲራብ ይሰበሰቡ ነበር ሉቃ.4፥16


የዐቢይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት ምን በመባል ይጠራል?


📍ᴡᴀᴠᴇ Ғᴏʟᴅᴇʀ መግባት የምትፈልጉ
ቻናላችሁ ከ 10ᴋ በላይ የሆናችሁ ብቻ

አናግሩኝ ➛ @Naolviva


'                   📌 ትጾማለህን?

➯ትጾማለህን? እንግዲያውስ በሥራህ አረጋግጥልኝ!
➯በምን ዓይነት ሥራ ካልከኝ?
➯ ደሃውን ካየህ እዘንለት (ቸርነትን አድርግለት)!
➯የተጣላኸውን ካየህ ታረቀው!
➯ጓደኛህ ክብርን ሲያገኝ ካየህ አትቅናበት!
➯መልከኛ ሴት ካየህ እለፋት!

➯አፍህ ብቻ ከምግብ አይከልከል፤ አይንህም፣ ጆሮህም፣ እግርህም፣ እጆችህም፣ ሁሉም  የሰውነትህ ክፍሎች ይጹሙ።
➯እጆችህ ከንጥቂያና ስግብግብነት (ንፉግነት) ይጹሙ።
➯እግሮችህ የማይገቡ ትእይንቶችን ለመመልከት ከመንደርደር ይጹሙ።

➯ዐይኖችህ ውብ መልኮች ላይ ያልተገቡ እይታዎችን መቼም መች ከማሳረፍ መከልከልን ይማሩ እና ቁንጅና ላይ ከመጠመድ ይጹሙ፤ ማየት ለዐይን ምግብ ስለሆነ ያልተገባ እና የተከለከለን እይታ ካደረግህ ጾምህን ያፈርሰዋል፣ የነፍስህንም ሙሉ ደህንነት ያነዋውጣል፤ ነገር ግን የተገባና ጥንቁቅ ከሆነ ጾምህን ያስጌጣታል።

➯የተከለከለውን በዓይን እየነካህ ነገር ግን በጾም ምክንያት ከማያረክስ ምግብ መጾሙ ከንቱ ከሆኑ ነገሮች መካከል ይቆጠራል፤ ሥጋን አትበላም አይደል? ስለዚህ በዐይኖችህ አማካኝነት ፍትወትን አትመገብ።

➯ጆሮም ይጹም የጆሮ ጾም ክፉ ወሬን እና ሐሜትን አለመቀበልን ያካትታል።
✍️“ሐሰተኛ ወሬ አትቀበል” እንዲል።
📚ዘፀ፦23፥1

➯አፍም እንዲሁ ከመጥፎ እና ከጥላቻ ንግግሮች ይጹም  ከአዕዋፋትና አሳዎች ብንከለከል ነገር ግን ወንድማችንን ብንበላው ምን ይጠቅመናል? ክፉ ተናጋሪ የወንድሙን ሥጋ ይበላል የባልንጀራውንም ሰውነት ይነክሳልና።

📌 ምንጭ
✍️በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

https://t.me/Abalibanos333


#ስግደት እና #ክብር

#ስግደት በፈጣሪ እና በፍጡር፣ #በግዢ እና በተገዢ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚገልጡበት #የመገዛት ምልክት ነው፡፡
👉
#ስግደት ራስን ዝቅ አድርጐ በመንበርከክ በተሰበረ ልቡና ይቀርባል፡፡

📌የስግደት
ዓይነቶች

#ስግደት #ሁለት ዐይነት ነው።

📌1ኛ፦#የባሕርይ (የአምልኮት ስግደት።

🌿ይህ ስግደት የሚገባው #ለፈጣሪ ብቻ ነው፡፡አምላክነቱን አምኖና ተረድቶ የሚፈጸም #
የአምልኮት ስግደት ሲን ለሌላ አይሰጥም፡፡
📖ዘፀ፦2
0፥1-6 👈ይነበብ
📖መ
ዝ፦81፥9👈ይነበብ
📖መ
ዝ፦135፥15-18👈ይነበብ

📌2ኛ፦#የጸጋ (#የአክብሮት
ስግደት)

🌸ይህ ስግደት ደግሞ ለእግዚአብሔር #ቅዱሳን፣ አገልጋዮቹ #ፍጡራን(የአክብሮት ስግደት)
የሚሰጥ ነው

👉ይኸውም #ለእግዚአብሔር
ማደሪያ #ለእመቤታ
ችን፣ #ለመላእክት፣ #ለቅዱሳን ሰዎች ጌታ ተሰቅሎ ክቡር ደሙን ላፈሰሰበት ቅዱስ #መስቀል የሚፈጸው ከአክብሮት ጋር የጸጋ ስግደት ነው፡፡
📖ኢያ፦5፥13👈ይነበብ
📖ኢሳ፦49፥23👈ይነበብ
📖ዳን፦2፥46 👈ይነበብ
📖ራእይ፦3፥8👈ይነበብ

📌ክብር ማለት ምን ማለት ነው?

🎍#ክብር፦ማለት ጌትነት፣ ታላቅነት፣ ከፍተኛነትን የሚገልጽ ነው፡፡ከሁሉም ነገር በላይ ክብር ያለው አምላካችን ልዑል #እግዚአብሔር ነው፡፡
📖ዘፀ፦16፥7👈ይነበብ
📖መዝ፦18፥1👈ይነበብ
📖1ኛ፦ነገ፦8፥11👈ይነበብ
📖ኢሳ፦6፥3👈ይነበብ

👉ስለዚህም #ለእግዚአብሔር ልዩ ክብር መስጠት ይገባል፡፡
📖ይሁዳ፦2፥5👈ይነበብ

✍እግዚአብሔር #ክብሩን በሚፈቅደው ምሳሌ ይገልጻል እንጂ ሰው የእግዚአብሔርን #ክብር #ሊያይ አይችልም፡፡
📖ዘፀ፦33፥17👈ይነበብ
📖ዮሐ፦1፥14👈ይነበብ
📖ማቴ፦17፥1👈ይነበብ
📖ዕብ፦1፥3👈ይነበብ

👉የጌታ ክብር በዳግም ምጽአትም ይገለጻል፡፡
📖ማር፦8፥38👈ይነበብ
📖ማቴ፦24፥36👈ይነበብ

🙏እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እሳተ #መለኮትን በማኅፀኗ የተሸከመች የአሽናፊው የእግዚአብሔር ወልድ #ማደሪያ ናትና #ክብርት እናት ነች።
📖ሉቃ፦1፥30-37👈ይነበብ
📖ሉቃ፦1፥48👈ይነበብ

👉አገልጋዮቹ ቅዱሳን #መላእክትና፣ ቅዱሳን #ሰዎችም ክብር አላቸው።
📖ሉቃ፦2፥9👈ይነበብ
📖1ኛቆሮ፦11፥7👈ይነበብ
📖1ቆሮ 15፥41👈ይነበብ
https://t.me/Abalibanos333

👉#ክብር ለሚገባቸው ቅዱሳን የአምላክ አገልጋዮች ክብር መስጠት ይገባል።"ክብር ለሚገባው ክብር ስጡ፡፡"
📚ሮሜ፦13፥7👈ይነበብ

✝️ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ይቆየን✝️🙏


🌿ወዳጄ ፆም ምንድነው? ታውቅ ይሆን?🌿

                    📌1.1፦ፆም

🌿ፆም በመንፈሳዊ ሕይወት የማደጊያና ልብላ ልጠጣ የሚለውን የሰውነት መሻትና ፍላጎት ለእግዚአብሔር
መሥዋዕት አድርጎ ማቅረቢያ መንገድ ነው።ፆም ማለት ከሆነ ነገር መከልከል ማለት በመሆኑ ፆም ለአዳም
የተሰጠው የመጀመሪያው ትእዛዝ ነው፡፡
✍️“ነገር ግን መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ፣
ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና” ብሎ ያዘዘው ትእዛዝ ይህ ነውና፡፡
📚ዘፍ፦2፥17 👈ይነበብ

🌿አዳም ማድረግ ይችል
የነበረውን ነገር (ከዚያ ዛፍ መብላትን) ስለ እግዚአብሔር ፍቅር ብሎ እንዲተው ነበር የታዘዘው፡፡ፆምም አንድ ሰው ለማድረግ መብት እያለው ነገር ግን ከዚያ በላይ ፈጣሪውን አስቦ ያን ነገር በመተው ከፈቃዱ መሥዋዕት አድርጎ የሚያቀርብበት መንገድ ነው፡፡አባታችን ዳዊት፦
✍️“ዘእምፈቃድየ እሠውእ ለከ - ከፈቃዴ እሠዋልሃለሁ" ያለው ይህን ነው፡፡
📚መዝ፦53፥6 👈ይነበብ

📌1.1.1፦ፆም በመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት

🌿የእግዚአብሔር ቅዱስ ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ ስለ ፆም አስፈላጊነትና ጠቀሜታ አበክሮ ይናገራል፣ያስተምራል፡፡በመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ፆም የሚከተሉት ጠቀሜታዎች አሉት፡፡እነርሱም፦

📌1.1.1.1 የፆም አስፈላጊነትና ጠቀሜታ

1ኛ፦ፆም እግዚአብሔርን የመፍራትና ፊትን ወደ እርሱ የማዞር ምልክትና የእግዚአብሔርን ገጸ ምሕረት
መለመኛ መንገድ ነው፡፡

🌿ኢዮሣፍጥ የተባለው የእሥራኤል ንጉሥ ከኃጢአት ወደ ጽድቅ፣ እግዚአብሔርን ከመተው እርሱን ወደ
ማምለክ ፊቱን ባቀና ጊዜ ይህን መልካም የሆነ መንፈሳዊ ጉዞውን የጀመረው በጾም ነበር፤
✍️“ኢዮሣፍጥም
ፈራ፣ እግዚአብሔርንም ሊፈልግ ፊቱን አቀና፣ በይሁዳም ሁሉ ጾም አወጀ” እንዲል።
📚2ኛ፦ዜና፦20፥3 👈ይነበብ

🌿እንዲሁም ካህኑ ዕዝራ እስራኤላውያን በኃጢአታቸው ምክንያት ተማርከው ባቢሎን ወርደው ሰባ ዓመት በኖሩበት ዘመን ሲናገር እንዲህ ይላል፡-
✍️“በአምላካችን ፊት ራሳችንን እናዋርድ ዘንድ፣ ከእርሱም የቀናውን መንገድ
ለእኛና ለልጆቻችን ለንብረታችንም ሁሉ እንለምን ዘንድ በዚያ በአኅዋ ወንዝ አጠገብ ጾም አወጅሁ።"
📚ዕዝ፦8፥21👈ይነበብ

🌿በዚያ በፆማቸው ስላገኙት ጥቅም ሲናገር ደግሞ፦
✍️“ስለዚህም ነገር ፆምን፣ ወደ እግዚአብሔርም ለመንን፡ እርሱም ተለመነን" በማለት ፆም እግዚአብሔርን መለመኛና ጸሎታችን እንዲሰማ የሚያደርግ መልካም መሣሪያ መሆኑን በተግባር ካገኙት ነገር በመነሣት ይመሰክራል፡፡
📚ዕዝ፦8፥23  👈ይነበብ

ክፍል ፪ ይቀጥላል..


✝️ጌታችን ዲያብሎስን በተዋሐደው ሥጋ ሳይሆን በመለኮቱ ኃይል ብቻ ድል እንዳደረገው አስመስለው የሚናገሩ ጌታችን በተዋሐደው ሥጋ ዲያብሎስን ድል ማድረጉን የሚክዱትን መናፍቃን በገሰጸበት ትምህርቱ ቅዱስ ሳዊሮስም የደገኛውን የጎርጎርዮስን ትምህርት ጠቅሶ እንዲህ አለ፡ “ሰይጣን በገዳመ ቆሮንቶስ በተፈታተነው ጊዜ ታገሠ፤ ግን ፈተናውን ሽቶ አይደለም፤ የሚፈታተን የዲያብሎስን ጦሩን ያጠፋ ዘንድ ነው እንጂ፡፡

➡ዳግመኛ በመለኮቱ ኃይል ዲያብሎስን አልተዋጋውም፤ በሚታመም በሚሞት ሥጋ ድል አደረገው እንጂ፤ ዳግመኛም በዚህ ሥጋ ኃጢአት ወደዚህ ዓለም እንዳይመጣ በኃጢአት ምክንያት በሁሉ ላይ ሞት ተፈርዶአልና፤ በዚህ ሥጋም የኃጢአት ፍዳ ጠፋ፣ ይህ ሥጋም ኃጢአትን ያለማ ዲያብሎስን ድል ነሳው አለ፡፡” (ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ሳዊሮስ ምዕራፍ 85፡16-17)

🍃የመጀመሪያው ፈተና በዚያው በገዳመ ቆሮንቶስ ሲሆን ፈተናውም ስስት ነበር፡፡ ዲያብሎስ ሥጋን የተዋሐደውን አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስን ተርቦ ቢያየው ‹‹የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ እነዚህ ድንጋዮች ዳቦ እንዲሆኑ እዘዝ›› በማለት ፈትኖታል፡፡ ሁለተኛው ፈተና ደግሞ በቤተመቅደስ ሲሆን ፈተናውም ትዕቢት ነበር፡፡ ‹‹መላእክት ያነሱኃል ተብሎ ተጽፏልና ራስህን ከመቅደስ ጫፍ ወርውር›› (መዝ 90፡11) ይህ ፈተና ከመጻሕፍት ጥቅስ ጠቅሶ የፈተነበት ነው፡፡

➡ሦስተኛው ፈተና ደግሞ በተራራ ጫፍ (በሰገነት) ሲሆን ፈተናውም የፍቅረ ንዋይ ነበር፡፡ ‹‹ወድቀህ ብትሰግድልኝ የዓለምን መንግስታት ከብራቸውንም ሁሉ እሰጥሀለሁ›› በማለት ፈትኖታል፡፡ እነዚህ ፈተናዎች ዛሬም በክርስትና ያሉ ዐበይት ፈተናዎች ናቸው፡፡ እኛም ጌታችንን አብነት አድርገን ሰይጣን በትዕቢት ቢፈትነን በትህትና፣ በስስት ቢፈትነን በትዕግስት፣ በፍቅረ ንዋይ (ገንዘብን በመውደድ) ቢፈትነን በጸሊአ ንዋይ (ገንዘብን ባለመውደድ) ልናሸንፈው ይገባል፡፡

🍃የተፈተኑት እሴቶች ምንድን ናቸው?🍃

🍃ለገዳማውያን አብነት ለመሆን የተፈተነው ፈተና የጽናት ፈተና ነው፡፡ የገዳማውያን ጾራቸው ስስት (መሳሳት) ነውና በመጽናት ላይ ለሚመጣባቸው ፈተና አብነት ሊሆን ተፈተነ፡፡ ገዳማውያን እምነትን፣ እውቀትን፣ ጽናትን እንዲያሟሉ ይጠበቅባቸዋልና፡፡ በቤተመቅደስ ለሚኖሩ ካህናት/በምዕመናን አገልጋዮች በብዛት የሚፈተኑ በትጋታቸው/እውቀታቸው ነው፡፡ እውቀት ያስታብያል ፍቅር ግን ያንጻል እንደተባለ ክርስትናን ተምረናል አውቀናል በማለት መታበይ ስላለ የካህናት ጾራቸው ትዕቢት ነው፡፡

➡ከዚህም የተነሳ መጽሐፍ ተጠቅሶ ፈተናው ይመጣልና ዲያብሎስም ከመጽሐፍ ጠቅሶ ፈተነው፡፡ በባለስልጣናት ዘንድ የሚፈተነው ደግሞ እምነት ነው፡፡ ጾራቸውም ፍቅረ ንዋይ ነውና፡፡ ወድቃችሁ ብታመልኩኝ በሀብት ላይ ሀብት፣ በስልጣን ላይ ስልጣን እጨምርላችኋላሁ ብሎ ይፈትናል፡፡ የሀሰት አባት ነውና የሌለውን የራሱ አድርጎ ይፈትንበታል፡፡ ስለዚህም ጌታችን ለሦስቱም አብነት ለመሆን ተፈተነ፡፡

🍃የፈተናዎቹ መፍትሔስ ምን ነበር?🍃

🍃ሁሉን የሚያውቅ ሁሉን የሚችል አምላክ በተለያየ መንገድ የመጡትን ሦስቱን ፈተናዎች እንደየአመጣጣቸው መለሳቸው፡፡ በስስት የመጣውን በትዕግስት ድል ነሳው፡፡ ‹‹ይህንን ድንጋይ ዳቦ አድርግ›› በማለት የመጣውን ፈተና ‹‹ሰው በእንጀራ ብቻ አይኖርም፣ በእግዚአብሔር ቃል እንጂ›› ብሎ መለሰለት (ዘዳ 8፡3)፡፡ ይህም ሰው ለሥጋ በሚመገበው እንጀራ ብቻ ሳይሆን ለነፍስ ምግብ በሚሆነው ቃለ እግዚአብሔርን በመስማትም ጭምር ነው የሚኖረው ማለቱ ነው፡፡ በትዕቢት የመጣውን ፈተና ደግሞ በትህትና ድል ነሳው፡፡ ‹‹መላእክቱ በእጃቸው ያነሱሃል›› ተብሎ ተጽፏልና ራስህን ወርውር ቢለው ‹‹ጌታ አምላክህን አትፈታተነው ተብሎ ተጽፏልና›› (ዘዳ 6፡16) በማለት አሳፈረው፡፡ በዚህም አእምሮአችን ረቂቅ፣ ማዕረጋችን ምጡቅ እያሉ በስጦታ በተሰጣቸው ስልጣን ለሚታበዩ የቤተመቅደስ ሰዎች ትህትናን አስተማረ፡፡

➡በፍቅረ ንዋይ የመጣውን በጸሊዐ ንዋይ ድል ነሳው፡፡ ‹‹ሂድ አንተ ሰይጣን ለጌታ ለአምላክህ ስገድ እርሱንም ብቻ አምልክ ተብሎ ተጽፏልና›› (ዘዳ 6፡13) በማለት መልሶታል፡፡ ነገስታት/ባለስልጣናት ቤታቸውን በከፍታ/በሰገነት ሠርተው ለሀብትና ለሥልጣን ሲሮጡ በባዕድ አምልኮ ይፈተናሉና ይህንን ድል መንሻ ሠራላቸው፡፡

✝️ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገዳመ ቆሮንቶስ ከተፈተነባቸው ሦስት ፈተናዎች የምንገነዘበው ፈታኝ የሚፈትነው በደካማ ጎን በመግባት መሆኑን ነው፡፡ የተራበውን በምግብ፣ ያወቀ የሚመስለውን በእውቀቱ፣ ሀብት/ስልጣን የሚወደውን ደግሞ በሀብት/በስልጣን ገብቶ ይፈትነዋል፡፡ በደካማ ጎን ለሚመጡት ፈተናዎች ድል መንሻ የእግዚአብሔር ቃል መሆኑን ጌታችን ዲያብሎስን ካሳፈረባቸው ሦስት መንገዶች እናስተውላለን፡፡ ሦስቱንም ፈተናዎች በመጻሕፍት ያለውን እውነት በመግለጥ ዲያብሎስን አሳፍሮታልና፡፡

➡ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ  ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዲያብሎስን ድል ከነሳው በኋላ ፈታኙ እንደራቀው መላእክቱም መጥተው እንዳገለገሉት ሲናገር ‹‹ያን ጊዜ ዲያብሎስ ተወው፡፡ እነሆ መላእክት ቀርበው ያገለግሉት ነበር›› (ማቴ 4፡11) ብሏል፡፡ እኛም ፈተናን ድል ስንነሳ ዲያብሎስ (ፈታኝ) ይርቃል፤ መላእክት (ተራዳኢዎች) ይቀርቡናል፡፡

➡በመጨረሻም ጌታችን በዲያብሎስ ከተፈተነበት ፈተና የምንማረው ፈተናን ድል ለመንሳት ጾምና ጸሎት መቅደም እንዳለበት ነው፡፡ የእምነት ጥሩር የእግዚአብሔር ዕቃ ጦር ይህ ነውና፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹የመዳን ራስ ቁር፣ እምነት ጋሻ፣ የመንፈስም ሰይፍ የእግዚአብሔር ቃል ነው›› (ኤፌ 6፡10-18) እንዳለው ከዲያብሎስ የሚመጣውን ፈተና ድል ለመንሳት ጽኑ እምነት፣ ጾም፣ ጸሎት፣ ስግደትና ምጽዋት ያስፈልጋል፡፡

➡ፈታኝ ዲያብሎስን በገዳመ ቆሮንቶስ ድል ያደረገ፣ ለቅዱሳን ሁሉ ዲያብሎስን የሚያሸንፉበት ኀይል የሰጠ አምላካችን እግዚአብሔር ለእኛም በጾማችን ወራት ከክፋት ሁሉ መራቅን እንዲያስችለን፣ የዲያብሎስንም ፈተና ድል የምናደርግበትን ጥበብ መንፈሳዊ፣ ኀይል መንፈሳዊ ያድለን ዘንድ ቅዱስ ፈቃዱ ይሁንልን።
https://t.me/Abalibanos33

✝️ወስብሐት ለእግዚአብሔር
✝️ወለወላዲቱ ድንግል
✝️ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን።
(ምንጭ- አስተምሕሮ.com)


✨ፆመ ኢየሱስ/ዐቢይ ጾም✨

✨ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በ30 ዓመቱ በማየ ዮርዳኖስ በዕደ ዮሐንስ ከተጠመቀ በኋላ ሳይውል ሳያድር ወደ ገዳመ ቆሮንቶስ ሄደ፡፡ በዚያም አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾመ፡፡ ይህም ጌታችን የጾመው ጾም ልዩ ልዩ መጠሪያዎች አሉት። እንደ ነቢያት ስርዓት አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ስለጾመ ጾመ አርብዓ (አርባ ጾም) ይባላል። ስሙ መድኀኒት የሆነ ጌታ የነፍስ ቁስል የሆኑ ሦስቱን ዐበይት ኃጢአቶች (ስስት፣ ትዕቢትና ፍቅረ ንዋይ) ድል ያደረገበት በመሆኑ የድል ጾም፣ ጾመ ኢየሱስ በመባል ይታወቃል።

➡የፍጥረት ሁሉ ጌታ፣ ልዑለ ባሕርይ፣ ሰው የሆነ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመው በመሆኑ ከሌሎች አጽዋማት ተለይቶ ዐቢይ (ታላቅ፣ ዋና) ጾም ይባላል። ለረዥም ጊዜ የሚጾም፣ ብዙ መንፈሳዊ በረከት የሚገኝበት ጾም በመሆኑ ብዙ ምርት ከሚያስገኝ ሰፊ እርሻ ጋር በማመሳሰል ጾመ ሁዳዴ ይባላል።

✨ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ ስለዚህ የጌታ ጾም ሲጽፍ ‹‹ከዚያ ወዲያ ኢየሱስ ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው፥ አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም ከጦመ በኋላ ተራበ›› በማለት ገልጾታል፡፡ ከዚህ በኋላ ነው ፈታኝ ወደ እርሱ የቀረበው፡፡ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያናችን ይህንን የጌታችንን በዲያብሎስ መፈተንን ሊቃውንት አባቶች ያመሰጠሩትን በመተንተን ታስተምራለች፡፡ እኛም በዚህች የአስተምህሮ ጦማር ይህንን የሊቃውንትን ትምህርት መሠረት በማድረግ የጌታችን በዲያብሎስ መፈተንና ድል ማድረጉ ለእኛ ያለውን መንፈሳዊ ትርጉም እንዳስሳለን፡፡ ይህንንም በሰባት ጥያቄዎች ሥር አቅርበነዋል፡፡

🍃ፈታኙ ማነው?🍃

✨ጌታችንን ለመፈተን ፈታኝ ሆኖ የቀረበው ጥንተ ጠላት ዲያብሎስ ነው፡፡ ይህ ፈታኝ በመጀመሪያ ራሱ ተፈትኖ የወደቀ ስለሆነ የሰውን ልጅ መፈተን የባሕርዩ ነው፡፡ አዳምን ፈትኖ ያሳተው፣ ኢዮብንና ሌሎችን አባቶች የፈተነው፣ በበርካታ ቅዱሳን ዜና ሕይወት በፈታኝነቱ የተገለጠው፣ ዛሬም መልካም የሚሠሩትን የሚፈትነው፣ ቅድስት ቤተክርስቲያንንም በየዘመናቱ የሚፈታተናት ይህ ፈታኝ ነው፡፡

✞በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አገላለፅ በቤተክርስቲያን ላይ ዝናሩን የጨረሰው ነገር ግን ያላጠፋት ዲያብሎስ ነው ክርስቶስን የፈተነው፡፡ ዛሬም በክርስቶስ የምናምን ክርስቲያኖችን በልዩ ልዩ መንገድ ይፈትነናል፡፡ ጌታችን በጾሙ ወራት ዲያብሎስን ድል ማድረጉን ያሳየን እኛም ኃይለ አጋንንትን የምናሸንፍበት ኃይል ጾም፣ ጸሎት እና ስግደት መሆናቸውን ሲያስተምረን ነው፡፡ ፈታኙን ድል ነሥቶ ድል የማድረጊያ ኀይል የሚሆኑንን ጾምን፣ ጸሎትንና ስግደትን ባርኮልናል።

✞ጌታችን ለምን ተፈተነ?

🍃በገዳመ ቆሮንቶስ የተፈተነው የሰውን ልጅ ለማዳን ሰው ሆኖ የመጣው ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ “አቤቱ ወደ ፈተና አታግባን” ብለን እንድንጸልይ ያስተማረን፣ ወደ ፈተና በገባን ጊዜም በቅዱስ ስሙ፣ በህያው ቃልኪዳኑ ተማምነን “አባታችን ሆይ በሰማያት የምትኖር” ብለን ስንጠራው የሚመልስልን ሰው የሆነ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ለምን ተፈተነ? የጌታችን መፈተን እንደሌሎች ቅዱሳን በፈተና በመጽናት ጸጋን ገንዘብ ለማድረግ አይደለም፤ እርሱ የጸጋ ሁሉ ምንጭ (አስገኝ፣ ሰጭ) ነውና፡፡ ይልቁንስ የሰው ልጅ በዚህ ምድር ላይ በሥጋ ሲኖር ፈተና እንዳለበት ሊያስተምር እርሱ ተፈተነ፡፡ በባሕርዩ መፈተን የሌለበት አምላክ የሰውን ልጅ ፈተና ሰው ሆኖ ተፈተነ፡፡

➡በዚህም በሕይወታችን መፈተን እንዳለብን አስተማረን፡፡ እርሱ በፈጠረው ፍጡር (በዲያብሎስ) የፈጠረውን ፍጡር (አዳምን) ለማዳን ተፈተነ፡፡ ጌታችን የተፈተነበት ዓላማ የሰው ልጅ የዲያብሎስን ፈተና እንዴት ድል እንደሚያደርግ አብነት፣ አርአያ ሊሆን ነው፡፡ ፈጣሪ በፍጡር ለፍጡራኑ አብነት ሊሆነን በፈቃዱ ተፈተነ፡፡ እርሱ እጸድቅ አይል ጻድቅ፣ እቀደስ አይል ቅዱስ፣ እከብር አይል ክቡር ሲሆን ለሰው ልጅ አርአያ ሊሆን በተለየ አካሉ ባሕርያችንን ባሕርይው አድርጎ በማስመሰል ሳይሆን በእውነት በዲያብሎስ ተፈተነ፡፡

✨ጌታችን መቼ ተፈተነ?

✞በዮርዳኖስ ወንዝ በዮሐንስ እጅ ተጠምቆ፣ በገዳመ ቆሮንቶስ 40 ቀንና 40 ሌሊት ከጾመ በኋላ በተራበበት ወቅት ተፈተነ፡፡ እንዲሁ በሰው ልጅ ላይም ፈተና የሚመጣው አምኖ ተጠምቆ በጎ ምግባራትን መሥራት ሲጀምር ነውና ይህንን ለማጠየቅ በዚህ ወቅት ተፈተነ፡፡ ክርስትና ከፈተና የምናመልጥበት (ሳንፈተን የምናሸንፍበት) መንገድ ሳይሆን በፈተና ውስጥ አልፈን፣ ድል በማድረግ ከሥጋ ሞት በኋላ የዘለዓለም ሕይወትና ክብር የምናገኝበት ፍኖተ ጽድቅ (የእውነት መንገድ) ነው።  ክርስቲያኖች ምግባር ትሩፋትን (ጾም፣ ጸሎት፣ ምጽዋት፣ ስግደት) መስራት ሲጀምሩ ነው ፈተና የሚበዛባቸው፡፡

✞ከቅዱሳን አባቶቻችንና እናቶቻችን ዜና ሕይወት (ገድል) እንደምንማረው ብዙዎቹ ቅዱሳን በገድል በትሩፋት እያደጉ በሄዱ ጊዜ የዲያብሎስ ፈተና ዓይነትና ብዛት ይጨምርባቸዋል። ምንም ዲያብሎስ ፈተናውን ቢያበዛ በገድል በትሩፋት የጸኑት በመስቀሉ ኀይል፣ በእግዚአብሔር ቸርነት ፈታኛቸውን ድል ይነሱታል። መፈተን የማደግ እንጂ የመውደቅ ምልክት አይደለምና። በዚህ ወቅት የሥጋንና የዲያብሎስን ፈተና ለማለፍ ተግተው ልንጸልይ ይገባል፡፡ ወደ ፈተና እንዳትገቡ ተግታችሁ ጸልዩ ተብሎ ተጽፏልና፡፡

      ✞ጌታችን በየት ተፈተነ?

✞ሦስቱን ፈተናዎች በሦስት ቦታዎች ተፈተነ፡፡ አንዱን በገዳም፣ ሁለተኛውን በቤተመቅደስ፣ ሦስተኛውን ደግሞ በተራራ (በቤተመንግስት) ተፈተነ፡፡ በገዳም ለሚኖሩ ባሕታውያን (መነኮሳት) አብነት ሊሆናቸው በገዳም ተፈተነ፡፡ በቤተመቅደስ ለሚያገለግሉና ለሚገለገሉ ካህናትና ምዕመናን አብነት ሊሆናቸው በቤተመቅደስ ተፈተነ፡፡ በተራራ (በዓለም) ለሚኖሩ አብነት ሊሆናቸው በተራራ ተፈተነ፡፡

➡በገዳም ሆነው በጾም በጸሎት የጸኑ ባሕታውያን ለመብቃት (ወደ ፍጹም መንፈሳዊነት ለማደግ) ሲተጉ ይፈተናሉና ለእነርሱ አብነት ሊሆን በገዳም ተፈተነ፡፡ በቤተመቅደስ በእምነት ጸንተው የሚኖሩ ካህናትና ምዕመናን ትሩፋትን ለመሥራት ሲተጉ ይፈተናሉና በቤተመቅደስም ተፈተነ፡፡ በቤተመንግስት (በከፍታ) የሚኖሩ ባለስልጣናትና ዓለማውያን ለማመን፣ በጎ ምግባራትን ለመሥራት  ሲተጉ በዲያብሎስ ይፈተናሉና በዚያም ተፈተነ፡፡

🍃ፈተናዎቹስ ምን ነበሩ?🍃

✞ጌታችን ሦስት ታላላቅ ፈተናዎችን ተፈተነ፡፡ ሦስቱንም እንደየአመጣጣቸው በትዕግስት ድል አደረጋቸው፡፡ የእስክንድሪያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ አባታችን ቴዎዶስዮስ ለአንጾኪያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ሳዊሮስ በጻፈው ጦማር እንደተናገረው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተዋሐደው ሥጋ ዲያብሎስን ድል ስለነሳው የእኛ ባሕርይም ከእርሱ የተነሳ በዲያብሎስ ላይ መሰልጠን የሚችል ሆነ፡፡ “ጌታ ሰይጣንን ድል ቢነሣው የሚደነቅ ሥራ አይደለም፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቀድሞ ድል ተነሥቶ የነበረ ሥጋን የተዋሐደ ባይሆን በባሕርይ ከእኛ ጋር አንድ በሚሆን ሥጋ እዳ በደል ያልተገኘበት እርሱ በሥጋ መከራን የተቀበለ ባይሆን ኖሮስ መከራ መቀበሉ ባልተደነቀም ነበር፤ ሞትንም በሥጋው ያጠፋው ባይሆን ኖሮ ሞትን የሚያሰለጥን ኃጢአት ባልጠፋም ነበር፤ የሞት ሥልጣንም ባልተሻረም ነበር፡፡” እንዲል (ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ቴዎዶስዮስ 82፡7)










የወጣቶች ሕይወት ከጋብቻ በፊት ክፍል 5 (Part Five) በዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ Deacon Henoke Hail

https://t.me/zemariwochu3


የወጣቶች_ሕይወት_ከጋብቻ_በፊት_ክፍል_4_(Part_Four)_በዲያቆን_ሄኖክ_ኃይሌ


https://t.me/Abalibanos333


#የመጨረሻዉ ክፍል 5 ይቀጥላል


የወጣቶች ሕይወት ከጋብቻ በፊት ክፍል 3 (Part Three) በዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ Deacon Henoke Haile


https://t.me/Abalibanos333

ክፍል አራት ይቀጥላል


የወጣቶች ሕይወት ከጋብቻ በፊት ክፍል 2 (Part Two) በዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ Deacon Henoke Haile



https://t.me/Abalibanos333

ክፍል 3 ይቀጥላል


ያዳምጡት በጣም ይጠቅሞታል!

📌 የወጣቶች ህይወት ከጋብቻ በፊት ምን መምሰል አለበት❓

📌 እንዴት ብቸኝነትን እናሳልፍ ❓

📌 እና የተለያዩ ጠቃሚ ሀሳቦች ይነሱበታል

በዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ

ክፍል ሁለት ይቀጥላል....

https://t.me/Abalibanos333






የንስሐ ሕይወት ክፍል 15 በአቤል ተፈራ
https://t.me/Abalibanos333
የመጨረሻ ክፍል ነገ ይቀጥላል

20 last posts shown.