ያሳዝናል‼
የሀገሪቱ ወርቅ በባእዳን እየተዘረፈ ነው።
ከኢትዮጵያ እስከ ዱባይ የተዘረጋው የወንጀል ሰንሰለት ውስጥ መሪ ተዋንያኑ የቻይና ተወላጆች መሆናቸውን ጥናቱ ያሳያል ። እነዚህ ዘራፊዎች በተለይ በጋምቤላ እና በቤን ሻንጉል ጉሙዝ የተከማቸውን የወርቅ ማዕድን ያለ ከልካይ እያፈሱ በጎረቤት ሀገራት በኩል በማዉጣት የዱባይ፣ የህንድ እና የቻይና የወርቅ ገበያን መቆጣጠራቸው የአደባባይ ምስጢር ሆኗል።
በቤን ሻንጉል ጉምዝ የዘረፋው ቡድን አለቃ ሱዛን ትባላለች። ሴትየዋ የክልሉን መንግሰት የማዘዝ ስልጣን እንዳላት የአይን እማኞች ይናገራሉ። የራስዋን ሀይል በማደራጀት ህጋዊ ፈቃድ ያላቸውን የወርቅ አምራቾችን ጭምር ከአካባቢው ማባረርዋን የሚኒሰቴሩ ምንጮች መስክረዋል። ይህች የቻይና ተወላጅ የክልሉን መንግስት በጉልበት አልያም በጥቅም በመያዝ አቅም አልባ እንዲሆን አድርጋ የሀገሪቱን የወርቅ ክምችት እያሟጠጠችው ትገኛለች።
በጋምቤላ የተሰማራችው ደግሞ ቼሪ (በፎቶ ያለችው) ትባላለች። ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ወንጀል ሶስት አመት ተፈርዶባት ከእስር የተለቀቀች ፍርደኛ ናት። የክልሉን የጸጥታ ሀይል የግልዋ እስኪመስል የማዘዝ ስልጣን አግኝታ ወርቁን ቀን እና ሌሊት በማፈስ ላይ እንደምትገኝ የአይን እማኞች ይመሰክራሉ።
በጋምቤላ ክልል የዲማ ወረዳ ማዕድን ጽ/ቤት ኃላፊና የወረዳው ኮማንድ ፖስት ምክትል ሰብሳቢ አቶ ኡቦንግ ኡቶው ባለፈው ሳምንት ለዶይቼ ቬሌ ሲናገሩ የተሰጣቸውን ፈቃድ ለህገወጥ ተግባር አውለዋል የተባሉና በወርቅ ማውጣት ሥራ ተሰማርተው የነበሩ አካላት ፈቃዳቸው መሰረዙን ገልፀዉ ነበር፡፡
እንደ አቶ ኡቦንግ በወረዳው ከነበሩ 47 አነስተኛ የወርቅ አምራቾች ውስጥ 36ቱ የተሰጣቸው ፈቃድ ተሰርዞ ከስራ እንዲሰናበቱ መደረጉን፣በወርቅ ግብይት ማእከል ከተሰማሩት 34 ማዕከላት መካከል 33 በህገወጥ ስራ ተሰማርተው በመገኘታቸው ፈቃዳቸው መሰረዙንም አስረድተዋል፡፡ ይህ ገለፃ ግን ለሜዲያ ፍጆታ ካልሆነ በስተቀር በተግባር የሚታየው ግን ሌላ ነው።
ፍቃዳቸውን ከተነጠቁት ከነዚህ ሀገወጥ የወርቅ አምራች እና ነጋዴዊች ውስጥ ቼሪ አንድዋ ብትሆንም ፈቃድዋ ተሰርዞም ስራዋን አላቆመችም። የአካባቢው ነዋሪዎች እንደሚሉት በክልሉ ሀይል ጥበቃ እየተደረገላት የዲማን ወርቅ በተጠናከረ መልክ እየዘረፈች ትገኛለች ( ዘሀበሻ)።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የሀገሪቱ ወርቅ በባእዳን እየተዘረፈ ነው።
ከኢትዮጵያ እስከ ዱባይ የተዘረጋው የወንጀል ሰንሰለት ውስጥ መሪ ተዋንያኑ የቻይና ተወላጆች መሆናቸውን ጥናቱ ያሳያል ። እነዚህ ዘራፊዎች በተለይ በጋምቤላ እና በቤን ሻንጉል ጉሙዝ የተከማቸውን የወርቅ ማዕድን ያለ ከልካይ እያፈሱ በጎረቤት ሀገራት በኩል በማዉጣት የዱባይ፣ የህንድ እና የቻይና የወርቅ ገበያን መቆጣጠራቸው የአደባባይ ምስጢር ሆኗል።
በቤን ሻንጉል ጉምዝ የዘረፋው ቡድን አለቃ ሱዛን ትባላለች። ሴትየዋ የክልሉን መንግሰት የማዘዝ ስልጣን እንዳላት የአይን እማኞች ይናገራሉ። የራስዋን ሀይል በማደራጀት ህጋዊ ፈቃድ ያላቸውን የወርቅ አምራቾችን ጭምር ከአካባቢው ማባረርዋን የሚኒሰቴሩ ምንጮች መስክረዋል። ይህች የቻይና ተወላጅ የክልሉን መንግስት በጉልበት አልያም በጥቅም በመያዝ አቅም አልባ እንዲሆን አድርጋ የሀገሪቱን የወርቅ ክምችት እያሟጠጠችው ትገኛለች።
በጋምቤላ የተሰማራችው ደግሞ ቼሪ (በፎቶ ያለችው) ትባላለች። ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ወንጀል ሶስት አመት ተፈርዶባት ከእስር የተለቀቀች ፍርደኛ ናት። የክልሉን የጸጥታ ሀይል የግልዋ እስኪመስል የማዘዝ ስልጣን አግኝታ ወርቁን ቀን እና ሌሊት በማፈስ ላይ እንደምትገኝ የአይን እማኞች ይመሰክራሉ።
በጋምቤላ ክልል የዲማ ወረዳ ማዕድን ጽ/ቤት ኃላፊና የወረዳው ኮማንድ ፖስት ምክትል ሰብሳቢ አቶ ኡቦንግ ኡቶው ባለፈው ሳምንት ለዶይቼ ቬሌ ሲናገሩ የተሰጣቸውን ፈቃድ ለህገወጥ ተግባር አውለዋል የተባሉና በወርቅ ማውጣት ሥራ ተሰማርተው የነበሩ አካላት ፈቃዳቸው መሰረዙን ገልፀዉ ነበር፡፡
እንደ አቶ ኡቦንግ በወረዳው ከነበሩ 47 አነስተኛ የወርቅ አምራቾች ውስጥ 36ቱ የተሰጣቸው ፈቃድ ተሰርዞ ከስራ እንዲሰናበቱ መደረጉን፣በወርቅ ግብይት ማእከል ከተሰማሩት 34 ማዕከላት መካከል 33 በህገወጥ ስራ ተሰማርተው በመገኘታቸው ፈቃዳቸው መሰረዙንም አስረድተዋል፡፡ ይህ ገለፃ ግን ለሜዲያ ፍጆታ ካልሆነ በስተቀር በተግባር የሚታየው ግን ሌላ ነው።
ፍቃዳቸውን ከተነጠቁት ከነዚህ ሀገወጥ የወርቅ አምራች እና ነጋዴዊች ውስጥ ቼሪ አንድዋ ብትሆንም ፈቃድዋ ተሰርዞም ስራዋን አላቆመችም። የአካባቢው ነዋሪዎች እንደሚሉት በክልሉ ሀይል ጥበቃ እየተደረገላት የዲማን ወርቅ በተጠናከረ መልክ እየዘረፈች ትገኛለች ( ዘሀበሻ)።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter