አዲስ ሚዲያ


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Education


አዲስ ሚዲያ ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ 🇪🇹
Share and Support us


Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Education
Statistics
Posts filter


36 የህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ተፈተዋል።

በወንጀል ተጠርጥረው ክሥ ቀርቦባቸው የነበሩ የህወሓት ሲቪል እና ወታደራዊ አመራሮችን ክሥ ማቋረጡን የፍትሕ ሚኒስቴር ከአስታወቀ በኋላ እነ ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም፣ ዶ/ር አዲስአለም ባሌማ፣ ዶ/ር አብርሃም ተከስተን ጨምሮ 36 ከፍተኛ አመራሮች ዛሬ ሃሙስ መጋቢት 21 ቀን 2015 ዓ.ም ከእስር ተለቀዋል።

ከጠበቆቻቸው አንዱ የሆኑት አቶ ሀፍቶም ከሠተ ለአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ በሰጡት ቃል ፤ ከእስር ተፈቺዎቹ፣ በማረሚያ ቤት መኪኖች፥ ሳሪስ፣ ፒያሳ እንዲሁም ሲኤምሲ ወደሚገኙ ቤተሰቦቻቸው እንደተሸኙና ቤተሰቦቻቸውም አቀባበል እንዳደረጉላቸው ገልጸዋል፡፡

በዛሬው ዕለት ከእስር የተፈቱት 16ቱ የህወሓት የሲቪል እና ወታደራዊ ባለሥልጣናት፣ ላለፉት ሁለት ዓመታት በዶ/ር ደብረጽዮን ገብረ ሚካኤል የክሥ መዝገብ ሥር እንደነበሩ ጠበቃው ገልጸዋል።

በሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ የክሥ መዝገብ ሥር ጉዳያቸው በፍርድ ቤት ሲታይ የቆየው 20 ተከሣሾች እንደሆኑም ጠበቃው ለሬድዮ ጣቢያው ጠቅሰዋል።
@Adis_Media
@Adis_Media


የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች ምዝገባ ነገ መጋቢት 20/2015 ዓ.ም ይጀመራል፡፡

የመልቀቂያ ፈተናውን ለመውሰድ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች እንደሚመዘገቡ ይጠበቃል፡፡

በበይነ መረብ አማካይነት በሚደረገው ምዝገባ፤ ከመንግስት ትምህርት ቤቶች 850 ሺህ የሚጠጉ እንዲሁም በግል 200 ሺህ የሚጠጉ ተማሪዎች እንደሚመዘገቡ ይጠበቃል፡፡

የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች ምዝገባ ከመጋቢት 20/2015 ዓ.ም እስከ ሚያዚያ 15/2015 ዓ.ም እንደሚከናወን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለጹ ይታወቃል።
@Adis_Media
@Adis_Media


አዲስ አበባ📍

የትግራይ ክልል ግዚያዊ ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ

ምሽቱን በአዲስ አበባ 😄
@Adis_Media
@Adis_Media


Addis Lisan (1).pdf
2.5Mb
የ4ኛ ዙር የ40/60 የጋራ መኖሪያ ንግድ ቤቶች ጨረታ አንደኛ እና ሁለተኛ የወጡ ተጫራቾችን ስም ዝርዝር በአዲስ ልሳን ጋዜጣ ታትሞ ተሰራጭቷል።

(2.5 MB የሆነውን ፋይል አውርደው ስሞትን ይፈልጉ)
@Adis_Media
@Adis_Media


በመላው ዓለም ላይ የሚታወቁት የዝምባብዌ ዜግነት ያላቸው የእስልምና መሁር ሙፍቲ  ኢስማኤል ሜንክ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት ስለ ቅዱሱ የረመዷን ወር እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል ፦

ሙፍቲ  ኢስማኤል ሜንክ (ዶ/ር) ፦

" ረመዷን ምንድን ነው ? ሰዎች እየፆምን ነው ይላሉ ይህ ግን የረመዷን አንዱ ክፍል ብቻ ነው።

ረመዷን ፦
🤲 #የሰላም ወር ነው፤
🤲 #የመረጋጋት ወር ነው፤
🤲 #የመፈወሻ ወር ነው፤
🤲 #የቸርነት ወር ነው፤
🤲 #የምህረት ወር ነው፤
🤲 #የይቅርታ ወር ነው፤
🤲 #ጀነትን የምናገኝበት ወር ነው፤
🤲 ይህ ወር #ሙስሊም መሆናችንን የምናከብረበት ነው ፤ ሙስሊም በመሆናችን #ራስን_መግዛትን የምንለማመድበት የፈለግነውን ብቻ ሳይሆን ሁሉን ቻይ የሆነው አላህ የወሰነውን የምናደርግበት ወር ነው ፤  ሱብሃንአላህ ! ስለዚህ ለአላህ ቃል ጥረት ማድረግ ግዴታችን ነው። "

መልካም #የረመዷን_ጾም ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንዲሆን እንመኛለን።
@Adis_Media
@Adis_Media


250 ሺህ ለሚጠጉ የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

በመጪው ሐምሌ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ለሚመረቁ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት እየተጠናቀቅ እንደሚገኝ በሚኒስቴሩ የከፍተኛ ትምህርት ጥራትና ብቃት ማሻሻያ ዴስክ ኃላፊ ሰይድ መሐመድ ለኢፕድ ተናግረዋል፡፡

ሚኒስቴሩ የመውጫ ፈተናውን በተሳካ ሁኔታ ለመስጠት ከመንግሥት እና ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በቅርበት እየሠራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

የመውጫ ፈተናውን ወስደው ማለፍ ያልቻሉ ተማሪዎች ደጋግመው መፈተን የሚችሉበት ዕድል መኖሩን ኃላፊው አመልክተዋል።

ፈተናውን በተደጋጋሚ ወስዶ ማለፍ ያልቻለ ተማሪ ከዲግሪ በታች ባሉ ደረጃዎች ምዘና እንዲወስድ የሚያደርግ የብቃት ማረጋገጫ ማዕቀፍ በትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን በመዘጋጀት ላይ ይገኛል ብለዋል።

ይሁን እንጂ ተፈታኙ ለዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ዝግጁ ነኝ ብሎ ባሰበ ጊዜ ፈተናውን መውሰድና ማለፍ ከቻለ የዲግሪ ማረጋገጫ ማግኘት እንደሚችል ገልጸዋል።

የመውጫ ፈተናው በኦንላይን እንደሚሰጥ ያመለከቱት ኃላፊው፤ ተማሪዎች ዋናውን ፈተና ከመፈተናቸው በፊት ሞዴል ፈተናዎች እንደሚወስዱ ጠቅሰዋል፡፡ 
@Adis_media
@Adis_media


የረመዷን ወር መግቢያ ጨረቃ ዛሬ ባለመታየቷ ምክንያት ታላቁ የረመዷን ጾም ሀሙስ መጋቢት 14 ይጀምራል።

እንኳን ለታላቁ የረመዷን ጾም በሰላም አድረሳችሁ።

ረመዷን የፍቅር፣ የአንድነት፣ የሰላም፣ የመተሳሰብ እና የአብሮነት ወር እንዲሆንልን ከልብ እንመኛለን።
@Adis_Media
@Adis_Media


ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) አረፉ።

በቀድሞ ስማቸው አባ ኃይለማርያም መለሰ (ዶ/ር) በጵጵስና ስማቸው ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት እና የውጪ ግንኙነት መምሪያ የበላይ ኃላፊ የድሬዳዋና የጅቡቲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።

ብፁዕ አቡነ አረጋዊ ሐምሌ 9 ቀን 2009 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት አንብሮተ ዕድ የሾሙት ጳጳሳት 14 ኤጲስ ቆጶሳት መካከል አንዱ ነበሩ።

ብፁዕነታቸው ለረጅም ጊዜ ከሀገር ውጪ እና በሀገር ውስጥ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ሊሻላቸው ሳይችል ቀርቶ ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ  ተለይተዋል።

ምንጭ፦ EOTC TV
@Adis_Media
@Adis_Media


" የአራቱም ሰዎች አስከሬን ተገኝቷል " - የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን

በአዲስ አበባ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ ከተማ ወረዳ 12 በተለምዶ " ማንጎ ሰፈር " እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ ትላንት ቅዳሜ መጋቢት 9 ቀን 2015 ዓ.ም በደረሰዉ የጎርፍ አደጋ #እናት እና #ልጅን ጨምሮ 4 ሰዎች በጎርፍ መወሰዳቸዉን ተከትሎ የአስክሬን ፍለጋ ሲደረግ ውሏል።

በዚህም የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የዋናተኛ ቡድን የአራቱንም ሰዎች አስከሬን ማግኘት እንደቻለ ኮሚሽኑ አሳውቋል።

የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የሟቾቹን አስከሬን ለማግኘት በተደረገዉ ጥረት ለአካባቢዉ ማህበረሰብና ለጸጥታ ሀይሎች ምስጋናዉን አቅርቧል።

#ሰሞኑን_እየጣለ_ባለዉ_ዝናብ ተመሳሳይ አደጋ እንዳያጋጥም ህብረተሰቡ አስፈላጊዉን ጥንቃቄ እንዲያደርግ ኮሚሽን መ/ቤቱ አሳስቧል።

ምንጭ፦ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን
@Adis_Media
@Adis_Media


" እናት እና ልጅን ጨምሮ አራት ሰዎች በጎርፍ ተወስደዋል "

በአዲስ አበባ ትናንት ምሽት በጣለው ዝናብ እናት እና ልጆችን ጨምሮ አራት ሰዎች በጎርፍ መወሰዳቸውን የእሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አሳውቋል።

ትናንት ምሽት የጣለውን ዝናብ ተከትሎ ከምሽቱ 12:05 ሰዓት በንፋስስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ማንጎ ሰፈር ወንዝ ዳርቻ ላይ በሚገኙ መኖሪያ ቤቶች ውስጥ ጎርፍ ገብቶ እንደነበር ኮሚሽኑ ገልጿል።

በዚህም እናትና ልጆችን ጨምሮ አራት ሰዎች በጎርፍ ተወስደዋል ብሏል።

ኮሚሽኑ እንዳስታወቀው ፥ በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ የነበሩ የ3፣ የ13፣ የ15 እና የ46 ዓመት ሴት ናቸው በጎርፉ የተወሰዱት።

የ46 ዓመቷ ሴት በጎርፍ የተወሰዱት የ13 እና የ15 ታዳጊዎች ወላጅ እናት መሆናቸውን ኮሚሽኑ ገልጿል።
@Adis_Media
@Adis_Media


የአንቶኒ ብሊንከን ጉብኝት የኢትዮጵያና አሜሪካ ወዳጅነት ወደ አዲስ የትብብር ምዕራፍ ለመሸጋገሩ ማሳያ ነው - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን የኢትዮጵያ ጉብኝት የኢትዮጵያና የአሜሪካ ወዳጅነት ወደ አዲስ የትብብር ምዕራፍ ለመሸጋገሩ ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ አለም ዛሬ በሰጡት መግለጫ÷የሚኒስትሩ የኢትዮጵያ ጉብኝት የሀገራቱን ትብብርና ወዳጅነት ወደ ተሻለ እና አዲስ ትብብር እየተሸጋገረ መሆኑን ያሳየ ነው ብለዋል፡፡

ሚኒስትሩ በቆይታቸው÷ በቀጠናዊና የሀገራቱን ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን አንስተዋል፡፡

በተጨማሪም አንቶኒ ቢሊንከን 331 ሚሊየን ዶላር የሰብዓዊ ድጋፍ ይፋ ማድረጋቸውን ቃል አቀባዩ ተናግረዋል፡፡

የሰላም ሒደቱ ዘላቂ እንዲሆን የአሜሪካ መንግስት ሁለገብ ድጋፍ ማድረግ እንደሚፈልግ መግለጻቸውንም ጠቁመዋል፡፡
@Adis_Media
@Adis_Media


የተለያዬ ነገሮችን ለማሰራት ከፈለጉ በስልክ ደውለው ማውራት ይቻላል
1.ለሀብት 
2.ለገበያ
3.ለብልት
4.ለትምህርት
5.ለመስተፋቅር
6. ለህመም
7.ለዓይነ ጥላ
8. ለበረከት
9. ለግርማ ሞገስ
10. ለትዳር
11. ለታሰረ ሰው እንዲፈታ ለማድረግ
12.ለጠላት(ጠላት እንዳይጎዳ ለማድረግ)
13. ለ ኤች አይ ቪ ኤዲስ
እና ለተለያዩ ነገሮችን ለማሰራት ደውለው ማናገር ይቻላል በኣካል መቅረብ ካለባችሁ መቅረብ ያስፈልጋል
መለወጥ መፈለግ ብልሀት ነው
መዝ: 23-፷፮፰
https://t.me/+w1Wd50CMnr8yNTk8
📞0923861426
📞0923861426


የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ፓርቲ ( #አብን )የፌዴራል መንግስቱ/ገዢው ብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ከንቲባን ከስልጣን እንዲያስነሳ እና ለፍርድ እንዲያቀርብ ጠየቀ።

አብን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ዛሬ ለምክር ቤት ያቀረቡትን ሪፖርት አጥብቆ አውግዟል።

ፓርቲው ከንቲባ አዳነች አበቤ ዛሬ ለአዲስ አበባ ከተማ ም/ ቤት ባቀረቡት ሪፖርት " ከአንዳንድ ክልሎች የሚደረገው ከፍተኛ ፍልሰት መንግስትን በመጣል በኃይል ስልጣን ለመቆጣጠር ያለመ ነው " ሲሉ ሪፖርት ማቅረባቸውን ከተለያዩ ሚዲያ ዘገባዎች እና ከውስጥ ምንጮቻችን አረጋግጠናል ብሏል።

ከንቲባዋ በሪፖርታቸው ይህን ማለታቸው አደገኛ ከፋፋይ እና የዘር ማጥፋት ወንጀል ቅስቀሳ ነው ያለ ሲሆን ይህም አገረ መንግስቱን አደጋ ላይ የሚጥል እና በማናቸውም መመዘኛ ተቀባይነት የሌለው የዓለም አቀፍ ወንጀል ጥሪ ነው ሲል ገልጾታል።

አብን ፤ ዜጎች በነፃነት ተዘዋውረው የመስራት እና የመኖር ሰብዓዊ መብት ያላቸው መሆኑ ኢትዮጵያ በፈረመቻቸው ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ሥምምነቶች ድንጋጌዎች እና በሥራ ላይ ባለው ሕገ-መንግስት ጭምር የተረጋገጡ ተፈጥሯዊ መብቶች ናቸው ብሏል።

ፓርቲው በመግለጫው ፤ ከንቲባዋ " የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትዎርክ " እየተባለ በሚጠራው ጽንፈኛ እና በአንድ ወቅት መንግስት ራሱ " የሽብርተኞች መጠቀሚያ ነው " ብሎ በፈረጀው ሚዲያ በተከታታይ የወጡ ቅስቀሳዎች ቅጥያ የሆነ አደገኛ የወንጀል ቅስቀሳ አድርገዋል ሲል ከሷል።

" ዓለም አቀፍ ከተማን በከንቲባነት እመራለሁ ከሚል የመንግስት ባለስልጣን እንዲህ ዓይነት አደገኛ ቅስቀሳ በሪፖርትነት መሰማቱ እስካሁን ሲፈፀሙ ለነበሩ በሰብዓዊነት ላይ የተፈፀሙ ወንጀሎች እና እየታወጀ ላለው የዘር ማጥፋት ወንጀል ከለላ የሚሆን አደገኛ የወንጀል ድርጊት ጥሪ ነው " ሲል ፓርቲው ገልጿል።

አብን በመግለጫው ፤ " ሁሉም አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን እና የዓለም አቀፍ ማኅበረሰቡ ይኼንን አደገኛ የዘር ማጥፋት ወንጀል ቅስቀሳ ትኩረት በመስጠት አስቀድሞ ተገቢውን እርምጃ እንዲወስዱ ታሪካዊ ጥሪ እያደረግን፤ በተለይ የዓለም አቀፉ ማኅበረሰቡ ይኼንን ባያደርግ በሩዋንዳ የፈፀመውን ታሪካዊ ስህተት የሚደግመው መሆኑን ማስረገጥ እንሻለን " ብሏል።

በሌላ በኩል ፥ የፌደራል መንግስቱ ሆነ ገዥው የብልጽግና ፓርቲ ይኼንን አደገኛ የዘር ማጥፋት ወንጀል ቅስቀሳ ያደረጉትን ግለሰብ ከስልጣን እንዲያነሳና ለፍርድ እንዲያቀርብ ጥሪ እናቀርባለን ያለ ሲሆን " መሰል ድርጊት በድጋሚ እንዳይፈፀም መንግስታዊ ማረጋገጫ ጭምር እንዲሰጥ ጥሪ እናቀርባለን " ብሏል።
@Adis_Media
@Adis_Media




psiphon-214.apk
8.8Mb
Psiphon VPN

በኢትዮጵያ የማህበራዊ መገናኛዎች ላይ ገደብ ከተገደረገባቸው አንድ ወር ከ4 ቀን ይዟል።

ቴሌግራምን ጨምሮ ሌሎች የማህበራዊ መገናኛዎች ምክንያቱ በግልፅ ወይም በይፋ ባልተነገረበት ሁኔታ ገደብ ከተደረገባቸው ሰነባብቷል። እንደሚታወቀው ፍጥነቱ ተቀንሶም ቢሆን #በVPN እየተገለገልን እንገኛለን።

ለእርስዎ #ምርጡ የምንለው Psiphone VPN መተግበሪያ ከላይ አያይዘናል ፣ አውርደው ይጠቀሙ

Tiktalk, Facebook, AppStore, Browsers, Vidmate, Instagram... አልሰራ ላላችሁ በዚ VPN ተጠቀሙ።

Share @Adis_Media
@Adis_Media


በ2015 ዓ.ም የቅድመ ምረቃ መደበኛ እና የአቅም ማሻሻያ ሪሚዲያል የመግቢያ ቀን ያሳወቁ ዩኒቨርሲቲዎች

¤ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ - መጋቢት 11 እና 12

¤ ደብረ ብርሀን ዩኒቨርሲቲ መጋቢት 16 እና 17

¤ አምቦ ዩኒቨረሲቲ መጋቢት 7 እና 8

¤ መቅደላ አምባ ዩኒቨረሲቲ መጋቢት 7 እና 8

¤ ቡሌ ሆራ ዩኒቨረሲቲ መጋቢት 4 እና 5

¤ ጂንካ ዩኒቨረሲቲ መጋቢት 4 እና 5

¤ መዳ ወላቡ ዩኒቨረሲቲ መጋቢት 7 እና 8

¤ ወለጋ ዩኒቨረሲቲ መጋቢት 7 እና 8

¤ ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨረሲቲ መጋቢት 4 እና 5

¤ ኢንጂባራ ዩኒቨረሲቲ መጋቢት 4 እና 5

¤ ደባርቅ ዩኒቨረሲቲ መጋቢት 5 እና 6

¤ አሶሳ ዩኒቨረሲቲ መጋቢት 11 እና 12

¤ ወሎ ዩኒቨረሲቲ መጋቢት 4 እና 5

¤ ቦረና ዩኒቨረሲቲ መጋቢት 11 እና 12

¤ ሚዛን ቴፒ ዩኒቨረሲቲ መጋቢት 8 እና 9

Share @Adis_Media
@Adis_Media


ባጃጆች እንዳይሰሩ መታገዳቸው በርካታ ችግሮችን እንዳስከተለ ተነገረ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በድንገት በከተማዋ ውስጥ የባጃጅ ትራንስፖርትን ላልተወሰነ ጊዜ በማገዱ ምክንያት ችግሮች ማጋጠማቸውን ለአዲስ ማለዳ ቃላቸውን የሰጡ ቅሬታ አቅራቢዎች ተናግረዋል፡፡

የባጃጅ ትራንስፖርት መታገዱን ተከትሎ አዲስ ማለዳ ቅኝት ባደረገችባቸው ባጃጆች ይንቀሳቀሱባቸው በነበሩ የጉዞ መስመሮች የትራንስፖርት አቅርቦት ችግር መኖሩን ተመልክታለች፡፡

በዚህም የተጓዦች ረዥም ሰልፎች የተስተዋሉ ሲሆን፣ የትራንስፖርት ፍላጎቱን ለማሟላት በጋማ እንስሳት የሚንቀሳቀሱ ጋሪዎች ጥቅም ላይ የዋሉባቸው አካባቢዎች እንዳሉም ተስተውሏል፡፡

የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጥ አስተያየቱን ለአዲስ ማለዳ የሠጠ ወጣት፣ በከተማ አስተዳደሩ በድንገት የተወሰነው እግድ በሕይወቱ ላይ ስጋት እንደፈጠረበት ተናግሯል፡፡ 5 የቤተሰብ አባላቱን በሚሰራው ሥራ እንደሚያስተዳድር የተናገረው ወጣቱ፣ የገቢ ምንጬ ሙሉ በሙሉ ተቋርጧል ብሏል፡፡ የከፋ ችግር ከፊቴ ተደቅኖ ይታየኛል የከተማ አስተዳደሩ በውሳኔው ጫና የደረሰባቸውን የባጃጅ አሽከርካሪዎችና ባለንብረቶችን ጉዳይ መመልከት አለበት ሲልም ተናግሯል፡፡

“የከተማ አስተዳደሩ አካሂዳለሁ ያለውን ጥናት ባጃጆች በዚህ መልኩ ሳይታገዱ ማካሄድ ይችል ነበር።” ያሉ አዲስ ማለዳ ያነጋገረቻቸው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጠቃሚዎች ደግሞ፣ ከከተማዋ የትራንስፖርት ችግር አንጻር ውሳኔው በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ነው ብለዋል፡፡
@Adis_Media
@Adis_Media


" ተጥሎ የነበረው የመሬትና መሬት ነክ አገልግሎት እግድ ተነስቷል " - ዶ/ር ቀንኣ ያደታ

በአዲስ አበባ ከተማ ተጥሎ የነበረው የመሬትና መሬት ነክ  አገልግሎት እግድ መነሳቱን የከተማዋ የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ማስታወቁን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።

የቢሮው ኃላፊ ዶ/ር ቀንአ ያደታ ፤ የመሬትና መሬት ነክ መረጃዎችን ለማጥራት ሲባል በጊዜያዊነት ተጥሎት የነበረው የአገልግሎት እግድ ተነስቷል ብለዋል።

እግዱ በሁሉም ክፍለ ከተሞች ከትናትን የካቲት 29 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ መነሳቱን ሃላፊው ተናግረዋል።

የመሬትና መሬት ነክ አገልግሎት ማግኘት የሚፈልጉ ባለጉዳዮችም አስፈላጊ መረጃዎችን በመያዝ ከሚመለከተው አካል አገልግሎት ማግኘት እንደሚችሉ ጠቁመዋል፡፡

በመዲናዋ የመሬት ወረራንና ሕገወጥ ድርጊቶችን ለመከላከልና የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ሲባል የመሬትና መሬት ነክ አገልግሎት ከጥር 24 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በጊዜያዊነት ታግዶ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ 
@Adis_Media
@Adis_Media


ማርች 8 የሴቶች ቀን! ለመሆኑ ዕለቱ ለምን ይከበራል?

✔• ከ3 ሴቶች አንዷ በህይወት ዘመኗ ተደፍራለች (UN)
✔• በአለማችን ዕድሜቸው ከ15 እስከ 44 የሆኑ ሴቶች ከካንሰር፣ ከጦርነት፣ ከመኪና አደጋና የወባ በሽታ ይልቅ አስገድዶ የመደፈር ስጋት ያሳስባቸዋል (UN)
✔• 603 ሚሊዮን ሴቶች ጾታዊ ጥቃት ወንጀል ባልሆነባቸው አገራት ውስጥ ይኖራሉ (UN)
✔• በአሁኑ ወቅት በአለማችን 700 ሚሊዮን ያህል ሴቶች ዕድሜያቸው 18 ዓመት በታች ሆነው ያገቡ ሲሆን 250 ሚሊዮን ሴቶች ደግሞ ዕድሜያቸው 15 ዓመት በታች ሆነው ያገቡ ናቸው (UNICEF)
✔• በየአመቱ በአለም ላይ ከ600-800 ሺህ ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውሮች ይካሄዳሉ፡፡ ከሚካሄደው የህገ ወጥ ሰዎች ዝውውር ከአምስት አራቱ ሴቶች ነው፡፡ (Trafficking.org)
✔• በየአመቱ 62 ሚሊዮን ሴቶች የትምህርት ዕድል አያገኙም (Makers)
✔• የአለማችን116 ሚሊዮን ሴት ተማሪዎች (25 በመቶ ያህሉን የሴት ተማሪዎችን ቁጥር ይዛል) አንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አያጠናቅቁም፡፡
✔• በአለማች ለሴቶች የሚከፈለው ክፍያ ከወንዶች አንጻር ከ60-75 በመቶ ያነሰ ነው (PBS)
✔• 155 አገራት ሴቶችን ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የሚገድብ ህጎች ሲኖራቸው 100 አገራት ደግሞ ሴቶች የሚሰሩትን የስራ አይነት ገድበዋል (The Guardian)
✔• በየደቂቃው አንድ እናት በወሊድ ምክንያት ትሞታለች (UN)
✔• በአለማች 200 ሚሊዮን ሴቶች በግዳጅ ይገረዛሉ (World Health Organization)

መለካም የሴቶች ቀን❣
@Adis_Media
@Adis_Media


ኢትዮጵያ በኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጥ ብቻ 146 ሚሊየን ዶላር ማጣቷ ተነገረ።

ቶፕ 10 ቪፒኤን የቴክኖሎጂ ኩባንያ እንዳስታወቀው፣ በትግራይ ክልል የነበረውን ጦርነት ተከትሎ ለአንድ አመት ሙሉ የኢንተርኔት አገልግሎት በመዘጋቱ ሃገሪቱ 146 ሚሊዮን ዶላር ማጣቷን አስታውቋል።

አሁንም ቢሆንም በመላው ሀገሪቱ ኢንተርኔት በመቋረጡ ሚሊዮን ዶላሮችን እያጣች ትገኛለች ብሏል። ኢንተርኔት ከተዘጋ ዛሬ 28ኛ ቀኑን ይዟል።
©capital
@Adis_Media
@Adis_Media

20 last posts shown.