አማራ ባንክ የፋይናንስ ሴክተሩ ለሴቶች ምቹነቱ እንዲረጋገጥ በሚያበረታታ መርሃ-ግብር ላይ ተሳተፈ፡፡
አማራ ባንክ መጋቢት 19/2016 ዓ.ም በሸራተን አዲስ ሆቴል የፋይናንስ ሴክተሩ የሴቶችን አካታችነትና ተጠቃሚነት እንዲያረጋጥ በሚመክር ዓለም ባንክ ባዘጋጀው መርሃ-ግብር ላይ በመሳተፍ ለሴቶች በልዩነት የተዘጋጀውን እቴጌ የተሰኘ አገልግሎቱን አስተዋውቋል፡፡
እቴጌ የተሰኘው የአማራ ባንክ ልዩ የሴቶች ቁጠባ ሒሳብ እድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ ለሆኑ ሴቶች ፣ በአነስተኛ እና ጥቃቅን ንግድ ሥራ ላይ ለተሰማሩ ለድርጅት ባለቤቶች፣ ለሴት ተማሪዎች ፣ለዲያስፖራዎች እንዲሁም በተለያዩ ሙያዎች ለተሰማሩ ሴት ልሂቃን በተለየ ሁኔታ የተዘጋጀ አገልግሎት ነው፡፡
አማራ ባንክ
ከባንክ ባሻገር!
Website:
www.amharabank.com.et #አማራባንክ #AmharaBank