ከመጽሐፍት ዓለም!


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Books


Books only!
This channel is created for books sharing To widen your mind and to get books easily We have more than 2000 amharic and english books !
Join and share @Books_worldd
አስተያየት @BooksWorlddd_bot !
@books_worlddd መወያያ ግሩፕ
#share

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Books
Statistics
Posts filter


ኦሮማይ - Oromay (በዓሉ ግርማ).pdf
9.3Mb
ኦሮማይ
ድርሰት - በአሉ ግርማ
የመጀመሪያ ዕትም - ፲፱፻፸፭ 1975 ዓ.ም
የገፅ ብዛት - 375
@books_worldd


ዶክተር ዳዊት አሰፋ _የአእምሮ ሐኪም ናቸው_የአገር ውስጥ መፈናቀል ጦርነት መደፈር ወዘተ የፈጠረው ማሕበራዊ ድባቴ ይታከም ይሆን ?

#የልጆቻችን_ኢትዮጲያ!


ያዲሱ ዘመን አስተምሕሮት በአነቃቂዎች አንድምታና የመንግት ተቋማዊ አሰራር _በዶክተር ኤርሲዶና በኢንጅነር ጌታሁን ሔራሞ

@books_wOrldd #ሼር


የታላላቅ_ሰዎች_እውነተኛ_የፍቅር_ታሪክ_@OLDBOOKSPDF.pdf
15.6Mb
የፍቅር ጀርባው @OLDBOOKSPDF.pdf
58.1Mb
አንድ_ሺህ_አንድ_ሌሊት_ቅፅ_2_@OLDBOOKSPDF.pdf
19.7Mb
የታላላቅ ሰዎች እውነተኛ የፍቅር ታሪክ
ድርሰት - Unknown
ትረጉም - ሰለሞን ሀይለማርያም
ይዘት - ታሪክ
የመጀመሪያ ዕትም - 1990 ዓ.ም
የገፅ ብዛት - 173
@books_worldd #ሼር


ሰምና ወርቁ ተሰማ እሸቴ @OLDBOOKSPDF.pdf
15.3Mb
ሰምና ወርቁ ተሰማ እሸቴ
ድርሰት-ይድነቃቸው ተሰማ
ይዘት-ታሪክ
@books_worldd #ሼር




ኪም ኢል ሱንግ @OLDBOOKSPDF.pdf
38.0Mb
ኪም ኢል ሱንግ
ታላቁ የኮሬያ ህዝብ መሪ ኪም ኢል የሞቱበትን 5ኛ አመት መታሰቢያ በማድረግ!
@books_worldd #ሼር


የጣፈለግ @OLDBOOKSPDF.pdf
40.9Mb
የጣፈለግ
ሲድኒ ሸልደን
ልብወለድ
@books_worldd #ሼር




The_art_of_fearless_mindset,_John_Ward_$_@meet_book_storage.pdf
2.1Mb
ያለ አግባብ መፍርሃት ትልቁ እንቅፋታችን ነው ይላል የዚህ መፅሀፍ ፀሀፊ ጆን ዋርድ።

ለመለወጥ እንፈልጋለን አዲስ ነገር ለመሞከር እንፈራለን ።

በይሉኝታ በፍርሃት ብዙ ነገር እናደርጋለን ያ ደግሞ ሲጎዳን ይታያል ይላል ፀሀፊው።

የለውጥ ፍርሃትን እንዴት ማሸነፍ እንደሚቻል እና በመንገድዎ የሚመጡትን ሁሉንም አጋጣሚዎች እንዴት መያዝ እንዳለበዎት መፅሀፉ ያስተምራል።

ለምንድነው የማያውቁትን መፍራት አዳዲስ ጠቃሚ ልምዶችን ለመጋፈጥ ኋላ የሚያፈገፍጎት በማለት መፅሀፉ ይሞግታል ትችት እና መፍትሄ ሀሳቦች ያቀርባል።

@books_worldd #ሼር

44.2k 1 377 1 112









#መደመጥ ያለበት 🤔

ሰይፋ በኢቢኤስ ላይ ልጄን በትራስ አፍና ገደለችና በ3 ኛው ወር ተለቀቀች ስለተባለችው የቤት ሰራተኛ አቃቢ ሕግ የሰጠው ምላሽ  በሀኪም ምርመራ የተደገፈ ማስረጃ ነው ልጆቻችንን ምን ያሕል እናውቃቸዋለን? #የቸገረን_ነገር ከተሰኘ ፕሮግራም የተወሰደ ።

@books_worldd #ሼር


በመንገዳችን ላይ
(በእውቀቱ ስዩም)

በዚያ ሰሞን፥ በቦሌ መድሀኒያለም ጀርባ የተሰመረችውን ጎዳና ይዤ በእግሬ እወዘወዛለሁ፤ ብዙ ሳልርቅ፥ የእግረኞች መንገድ ላይ ሶስት የጎዳና አዳሪዎች ጎንለጎን ተደርድረው በጀርባቸው ተንዘራግተው እንቅልፍ ወስዷቸው ተመለከትኩ፤ አንድ በእድሜና በአካል የሚልቅ ብጢያቸው አጠገባቸው ቁጭ ብሏል፤ ሌላ አንድ ጎረምሳ ከ “ጽጌ” ሽሮ አቅጣጫ አንድ ፌስታል ሙሉ ፍርፋሪ ይዞ ደረሰ፤ ቁጢጥ ብሎ የፌስታሉን አፍ ለመክፈት ሲቃጣ ጠና ያለው ልጅ ወደ ተኙት ብላቴኖች በአገጩ እየጠቆመ እንዲህ ሲል አዘዘው፤

“ መጀመርያ እነሱን ቀስቅሳቸው !“

ደነቀኝ! ለምን ደነቀኝ? ሞልቶ ተርፎት ከማካፈል መድፋት የሚመርጥ ብዙ ሰው ያለበት አለም ውስጥ ነው እምንኖረው፤ ብዙዎቻችን በዚህ ጎረምሳ ቦታ ብንሆን ምንድነው የምናረገው? ነቅተው ሳይሻሙን እንበላ እንደምንል እገምታለሁ፤ ያንዳንድን ሰው ቸርነት እጦት እና ድሀነት አያከስመውም፤ በኔ ግምት ጠና ያለው ጎዳና አዳሪ ያንን ያደረገው ለታይታ አይደለም፤ የቲክቶክ ካሜራ እንዳላነጣጠረበት ያውቃል፤ ከተኙት ልጆች ደቃቃነት አንጻር ወጠምሻ እሚባል አይነት ነው፤ እና ብቻውን ቢበላ ፥ ቀጭም ሆነ ተቆጭ ያለበት አይመስልም፤ እንደመታደል ሆኖ፥ በመናመን ላይ ያለው የሰው ልጅ ህሊና እዚህ ልጅ ላይ ጨርሶ አልጠፋም፤ እንዲህ አይነቱ ትእይንት በሰው ልጅ ተስፋ እንዳትቆርጪ ያደርግሻል::


በአለማችን ሩህሩህ ሰዎች ብርቅ ናቸው፤ ርህራሄም ደረጃ አለው፤ ብዙ ሰው ፥ ለራሱ እና ለቤተሰቦቹ ብቻ ይራራል፤ ያንዳንዱ ሰው ደግነት ደግሞ ለጎረቤቱ ለወዳጆቹ ለዘመዶቹ ብቻ ተወስኖ ይቀራል ፤ ከሁሉ የላቀ መንፈስ ያላቸው ጥቂት ሰዎች ፥ ለሰው ዝርያ ብቻ ሳይሆን ለአራዊት አዋፋት ለነፍሳት ሳይቀር ቸርነታቸውን ያሳያሉ::

ሰዎች ሆድ የሚባል ጉድ የተገጠመልን ፍጡሮቸ ነን፤ ቢቸግረን ዶሮ ፥ በግ ፍየል በሬ አርደን እንበላለን፤ ግን ሳይቸግረን በእብሪት ወይም በግዴለሽነት ተነሳስተን የምናደርገው ጭካኔስ ምን ይባላል? ባለፈው እዚህ አክሱም ሆቴል ፊትለፊት ባለው መንገድ ላይ አንዱ አህያ እየነዳ ይሄዳል፤ አህያዋ በፍጥነት ትራመዳለች፤ ነጂው ግን በጎማ ዱላ እያከታተለ ይወግራታል፤ ለግማበት ነው እንዳልል በምትችለው አቅም እየተጣደፈች ነው፥ ሰውየው ከጭካኔ የተሻለ መዝናኛ ያለው አይመስልም፤ ወይም ደሀነቱ የፈጠረበትን ብስጭት እሚወጣው አገልጋዩን በመደብደብ ይሆናል፤ እስቲ ወደ ባለቤት አልባ ውሾች ተመልከቱ! አንድ አይኑ ያልጠፋ፥ ወይም እግሩ ያልተቀለጠመ ውሻ ማግኘት ይከብዳል!

ከሩቅ ምስራቃውያን የመነጨ አንድ ፍልስፍና ሀሳብ እንዲህ ይላል፤ እኛ ሰዎች በዚህ አለም መኖር የምንፈልገውን ያህል አራዊት አእዋፍ እና ነፍሳት መኖር ይፈልጋሉ፤ ስለዚህ ሌሎች ፍጡራን ያንተ ብጤ ናቸው፥ ባንተ ልክ ተንከባከባቸው!

ጋዜጠኛ ገነት አየለ ሸጋ አድርጋ፥ የተረጎመችውን የሚካኤል ዳባዲ ማስታወሻ ሳነብ ያገኘሁት አንድ ውብ አንቀጽ የድብርት መዳኒት ነው፤ ላጋራውና ልሰናበት፤

ደአባዲ የተባለ የፈረንሳይ አሳሽ የዛሬ ሁለት መቶ አመት ገደማ ጎጃም ሳርምድር ውስጥ አደን ለማደን ይሰማራል፤ ድንገት በለስ ቀንቶት አንድ አጋዘን ያይና አነጣጥሮ ሊኩስበት ሲዘጋጅ፥ በከፊል የተራቆተ ሰውየ ብቅ ይልና ተኩሱን ያደናቅፍበታል ፤ሰውየው በዳባዲ አጃቢዎች ተይዞ ሲመጣ በበረሀ የሚኖር ባህታዊ መሆኑ ይገለጣል፤ ባህታዊው አደኑን በማደናቀፉ ይቅርታ ከጠየቀ በሁዋላ እንዲህ አለ፤

“ይህ አጋዘን የከፋው(የተከፋ) እንስሳ ነው፤ በአቅራቢያ እያገሱ ያሉት ብዙ አንበሶች በጣም ያስጨንቁት ነበረ፤ ለኔ እንደ ባለንጀራየ ነው፤ አንዳንዴ በበረሀ አቁዋርጨ ስጓዝ ቀኑን ሙሉ እየተከተለኝ አብሮኝ ይሄዳል፤ አሁን በኔ ምክንያት ህይወቱ ድኖ ከሆነ ደስ ይለኛል “

ከ በእውቀቱ ስዩም የፌስቡክ ገጽ !
@books_worldd #ሼር


#Update

የዲቪ (DV) 2024 አሸናፊዎች ይፋ ተደረጉ።

ባሳለፍነው ጥቅምት እና ህዳር ወራት ላይ በበይነ መረብ አማካኝነት የተሞላው የ2024 ዲቪ (DV) ሎተሪ ይፋ ተደርጓል።

ለዲቪ /DV/ 2024 ማመልከቻ የሞሉ በ https://dvprogram.state.gov/ESC/Default.aspx ብቻ ውጤቱን / ማሸነፍ አለማሸነፋቸውን መመልከት ይችላሉ።

በአ/አ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ "የዲቪ (DV) ሎተሪ አሸንፋችኋል፣ ከአሜሪካ ኢምባሲ ነው እምንደውለው / ኢሜይል / ቴክስት የምንልከው"  በሚል #የሚያጭበረብሩ አካላት ስለሚኖሩ አመልካቾች እንዲጠነቀቁ አደራ ብሏል።

አሜሪካ በየዓመቱ ከአፍሪካ ፣ እስያ ፣ አውሮፓ፣ ሰሜን አሜሪካ፣ ደቡብ አሜሪካ እና አውስትራሊያ 50 ሺህ ሰዎችን በዲቪ (DV) ሎተሪ ወደ ሀገሯ ታስገባለች።

@books_worldd #ሼር


ነገሮችን በተደጋጋሚ ለ21 ቀናት ያክል ማድረግና መፈፀም ወደ ምንፈልገው ባህሪ ለመለወጥ ያግዘናል ይባላል።

21 ቀናት ያክል እኛ ህይወት ላይ የደጋገምነው ድርጊት ከኛ ባህሪ ጋር ተላምዶ እንዲቀር ያደርጋል።

እናንተም ከእነዚህ መካከል አንዱን ብቻ በመምረጥ ለተጠቀሰው ጊዜ ያክል በመፈፀም እውነት ይሄ ሀሳብ የእናንተ ባህሪ ላይ ለውጥ መኖር አለመኖሩን ተመልከቱ።

- ጠዋት መነሳት
- ስፖርት መስራት
- ማንበብ (መንፈሳዊም ሆነ አለማዊ መፅሀፎችን)
- 1 ሰዓት ያክል ብቻ ወሳኝ ለምትሉት ነገር መስጠት መቻል

አንዱን በመምረጥ ለ21 ቀናት ይደጋግሙት። መልካም ለውጥ በራሳችሁ ላይ ታያላችሁ ሲሉ ብዙዎች ይናገራሉ።

@books_worldd #ሼር


እ.ኤ.አ በ 1889 አንዳቸው የሌላውን ህይወት ስለታደጉት "መሀመድ እና ሰሚር" ስለተባሉት ጓደኛማቾች እናስተዋውቅዎ!

መሀመድ ዓይነ ስውር ቢሆንም በእምነቱ ደግሞ ጠንካራ ሙስሊም ነበር ፣ ሰሚር ደግሞ ሰውነቱ "ፓራላይዝ" የሆነ ሲሆን የክርስትና ሀይማኖትን ይከተላል።

በፎቶው ላይ እንደሚታዩት ህይወታቸውን ሲገፉ የነበሩት ሰሚር የመሐመድ አይን ፤ መሐመድ ደግሞ የሰሚር እግር በመሆን ነበር።

በህይወት ውስጥ እርስ በርስ ለመረዳዳት ሲሉ ሁኔታዎቻቸውንና እክሎቻቸውን አሸንፈዋል

ታሪካቸው የተለያዩ ባህሎች እና ሃይማኖቶች አንድ ላይ ሆነው እርስበርስ ሲረዳዱ ተአምር እንደሚፈጠር የሚያሳይ ድንቅ ምሳሌ ነው።

#ከታሪክ ማህደር !
@books_worldd #ሼር


#መራራ_እዉነት #ከሞት_በኋላ
ሰው ልጅ ከሞተ #በኋላ
በ3ኛ ቀን ጥፍሩ መነቃቀል ይጀምራል
በ4ኛ ቀን ጸጉሩ #ይራገፍና ጭንቅላቱ ባዶ ይቀራል
በ5ኛ ቀን አእምሮው እንደ #ቅቤ መቅለጥ ይጀምራል
በ6ኛ ቀን ቆዳው ጠቁሮ መላላጥ ይጀምራል,
በ7ኛ ቀን #የውስጥ አካሉ ሁሉ ይበሰብስና #እጅግ በጣም መሽተት ይጀምራል!
በ60ኛ ቀን ሥጋ ሁሉ ሸሽቶ ብዙ #አጥንቶች ብቻቸውን ይቀራሉ!!

#ይህንን መራራ እዉነት እያወቅን:-
ከኩራት
#ከስግብግብነት
ከክፋት
ከጥላቻ
#ከራስ ወዳድነት
#ከተንኮል ... ብንርቅ አይሻልምን?

#በነገሮች_ሁሉ_ትሁት_እንሁን! #በሰዎች_ሕይወት_በጎ_ተጽዕኖ_ለመፍጠር_እንትጋ!

#ይህቺ የምናያት ህይወት ከንቱ ናት። ይህቺ ዓለም ጊዜያዊ ድንኳን ናት። በዚህች ዓለም ሰዎች እርስ በርስ የሚተላለቁት ለ2 ነገሮች ብቻ ነዉ ፦ ለስልጣንና ለሀብት። ሰዎች ለስልጣንና ለሀብት #የንፁሐን ደም ያፈሳሉ። ሰዎች ለስልጣንና ለሀብት ከፈጣሪ ጋር ይጣላሉ። ሰዎች ለስልጣንና ለሀብት ኃጢአትና ፤ ወኝጀል ፤ ነዉር ይሰራሉ።

ነገር ግን ስልጣንና ሀብት ወደ ዘላለማዊ ሕይወት አያስገቡም። ከዚህ ዓለም ስንለይ ወደ ዘላለም ህይወት ወይም ወደ ዘላለም ሞት መሄድ ምርጫችን ነው! ደግሞም ይህ #እውነታ አይካድም።

#ፈጣሪን እንውደድ ፤ ፈጣሪን እንፍራ
✓እርስ በርሳችን እንዋደድ
#ለሌሎች መልካም እንሁን
✓አንቅና
#ሁሌም ደግ ደጉን እናድርግ፤ በጎ በጎዉን እናስብ!
የኛ ያልሆነውን ነገር ከሌሎች አንቀማ!
ይህንን #ስናደርግ አምላክ ይባርከናል!

#ከማህራዊ ሚዲያ ያገኘሁት ጠቃሚ ቁምነገር!

ማህራዊ ሚዲያን ለመማማር ፣ ለቁምነገርና ለመዝናኛ ዓላማ ብቻ እንጠቀም። ደግ ደጉን እናድርግ ፤ በጎ በጎዉን እናስብ። #ፈጣሪ በነገር ሁሉ ማስተዋልና #ጥበብ ይስጠን። አሜን።

@books_worldd #ሼር

20 last posts shown.