Development Bank of Ethiopia (DBE)


Channel's geo and language: Ethiopia, English
Category: Economics


The development bank of Ethiopia (DBE) is one of the financial institutions engaged in providing short, medium and long term development credits.

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, English
Category
Economics
Statistics
Posts filter


ባንኮች ለግሉ ዘርፍ የሚሰጡት የብድር መጠን አነስተኛ በመሆኑ መሻሻል እንደሚገባው ተጠቆመ፡፡

ይህ የተገለፀው የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ‹‹ የብድር አቅርቦት በግሉ ዘርፍ ላይ ያለውን ተፅዕኖ ›› የሚዳስስ የውይይት መድረክ ከሰሞኑ በቀረበበት ወቅት ነው፡፡

የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ወ/ሮ መሰንበት ሽንቁጤ መድረኩን ሲከፍቱ እንዳሉት የግሉ ዘርፍ ችግር ብሎ ካስቀመጣቸው መካካል የብድር አቅርቦት በሚፈለገው ደረጃ አለመኖር 40 በመቶ ድርሻ ይይዛል:: ፕሬዚዳንቷ አክለውም በፋይናንስ አቅርቦት ዙሪያ የሚስተዋሉ ችግሮች የግሉ ዘርፍ አዳዲስ ምርት ለማምረትና ተወዳዳሪ እንዳይሆን ማነቆ መሆኑንም ገልፀዋል ፡፡

በፓናል ውይይቱ ላይ ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ፣ ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ፣ ከአዋሽ ባንክ የተገኙ ኃላፊዎች የብድር አቅርቦት ላይ ያሉ ምቹ እና አሰቻይ ሁኔታዎች እንዲሁም ፈተናዎች በመዳሰስ በቀጣይ መሰራት በሚኖርባቸው ጉዳዮች ውይይት ተደርጓል፡፡

ከብሄራዊ ባንክ የተወከሉት አቶ በለጠ ፎላ የብድር አቅርቦት ለሁለንተናዊ አገር አድገት እድገት ያለውን ፋይዳና ከፖሊሲ አንጻር ያሉ ምቹ ሁኔታዎች አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ከብድር ጋር በተያየዘ ያለውን ፖለሲ ያብራሩት አቶ በለጠ ቀደም ሲል የብድር አሰጣጡ የማይንቀሳቀሱ ንብረቶችን ብቻ ዋስትና ያደረገ እንደነበር አውስተዋል ፡፡ ይህም በመሆኑ የሚያስይዙት ንብረት የሌላቸው ሰዎች ብድር እያገኙ አለመሆናቸውን ጠቅሰው ፤ አሁን ላይ ተንቀሳቃሽ ንብረቶች እንደ ብድር ዋስትና የሚታዩበት ሁኔታ መፍጠሩን ገልፀዋል ፡፡

ቀደም ሲል ከፍተኛውን የብድር መጠን የሚያቀርቡት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክና የፖሊሲ ባንክ የሆነው የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ብቻ ከፍተኛ መጠን ያለውን ብድር ያቀርቡ እንደነበር ተወካዩ አስታውሰዋል፡ምንም እንኳ የግሉ ዘርፍ የማበደር ድርሻ እያደገ የመጣ ቢሆንም የብድር ተደራሽነቱን በተመለከተ ሀገሪቱ ካላት 120 ሚሊዮን ህዝብ ውስጥ የብድር ተጠቃሚ መሆን የቻሉት 3 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብቻ ናቸው ብለዋል፡፡ ይህም የሚያሳየው የብድር ተደራሽነት በዝቅተኛ ደረጃ ላይ መሆኑን ነው ብለዋል አቶ በለጠ፡፡

ለብድር አቅርቦቱ ዝቅተኛ መሆን ፈተናው ከራሳቸው ከባንኮች አሰራርና ከደንበኞቹ ጋር የተያየዙ ችግሮች መኖር፤ ብድር ከወሰዱ በኋላ የመክፈል ፍላጎት መቀዛቀዝ፤ የብድር የወለድ መጠን እና የአገልግሎት ክፍያ ከፍተኛ መሆንና የውጭ ምንዛሬ እጥረት እንዳሉ አንስተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የብድር አቅርቦት ተደራሽነት ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች በሚል የባንኩ ተወካዮች አቶ ይልማ አበበ እና ወ/ሮ መዓዛ ወልዴ የባንኩን የብድር አስጣጥ በተመለከተ ማብራሪያ ስጥተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በአጭር፣ መካከለኛ እና ረጅም ጊዜ ብድር እንደሚሰጥ የጠቀሱት ወ/ሮ መዓዛ ባንኩ በፕሮጀክት እና በሊዝ ፋይናንስ ላይ በማተኮር ብድር መሰጠቱ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል፡፡ የኢትጵያ ልማት ባንክ ባለፉት አመታት ከነበረበት አስቸጋሪ ሁኔታ ወጥቶ አሁን ላይ ትርፋማ በመሆን በለውጥ መንገድ ላይ ይገኛል ብለዋል አቶ ይልማ፡፡

አሁን ላይ ፍትሃዊ አሰራርን በመከተል ታዳጊ ክልሎችን ጨምሮ በሁሉም ክልሎች ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝም ነው የገለፁት:: የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እንደ ፖሊሲ ባንክነቱ ሌሎች ባንኮች በማይገቡባቸው ዘርፎች ላይ ገብቶ ይሰራል ያሉት የባንኩ ቺፍ ኦፍ ስታፍ የኦፐሬሽን ፋሲሊቴሽን ዲቪዥን ኃላፊ ወ/ሮ መዓዛ በተለይ ለግብርና ዘርፍ ትኩረት ሰጥቶ መሰራቱ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል ፡፡ የባንኩ ቺፍ ኦፍ ስታፍ አቶ ይልማ አበበ በበኩላቸው ባንኩ 99 ነጥብ 9 በመቶ የሚሆነውን ፋይናንስ ለግሉን ዘርፍ እንደሚያቀርብ ገልፀዋል፡፡

ይሁንና ባንኩ ሰለሚሰጠው የሊዝ ፋይናንስ እና ፕሮጀክት ፋይናንስ አገልግሎት ደንበኞች ያላቸው ግንዛቤ አነሰተኛ መሆን፣ ሊዝ ፋይናንስ ብድር ሳይሆን ኪራይ መሆኑን ያለማወቅ፣ የማሽነሪዎችን አይነትና ጥራት አለማወቅ ጠቅሰዋል::

ለጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች የሚቀርብ ብድርን በተመለከተ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱን ጠቅሰው በቅርብ ጊዜያት ወደ ሙሉ ትግበራ ለመግባት እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡






የፋይናንስ አቅርቦት መስፋት ኢንቨስትመንትን በማበረታታት ኢኮኖሚያዊ እድገትን ለማፋጠን እና ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በተቃራኒው የፋይናንስ አቅርቦት አለመኖር ደግሞ (Access to Finance) በብዙ አገራት ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋት ማነቆ ሆኖ ሲቀርብ ይስተዋላል፡፡ በዚህም አገራት በሚያቀርቡት አሳማኝ ጥያቄ መሰረት ዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ሳይቀር ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ማጎልበቻ የሚሆን ገንዘብ በመለገስ ድጋፍ ሲያደርጉ ይስተዋላል፡፡

በቂ የፋይናንስ አቅርቦት ለኢንቨስትመንት መሳላጥ ወሳኝ በመሆኑ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በአገራችን በፋይናንስ አቅርቦት እና በቴክኒካል ድጋፍ ችግር ምክንያት የሚደናቀፍ የኢንቨስትመንት ፍሰት እንዳይኖር እየሰራ ይገኛል፡፡ ባንካችን ወደስራ የሚገቡ አዲስ ኢንዱስትሪዎችንም ሆነ በስራ ላይ ለሚገኙ ኢንዱስትሪዎች የማቋቋሚያ እና ማስፋፊያ ብድር በመስጠት የልማት አጋርነቱን እያሳየ ነው፡፡

መንግስት ቅድሚያ በሚሰጣው የማኑፋክቸሪንግ እና ግብርና ዘርፍ ላይ ለሚደረጉ ኢንቨስትመንቶች ትኩረት በመስጠት ፋይናንስ ያቀርባል፡፡ ባንካችን ኢንዱስትሪዎች የአገሪቱን የልማት ክፍተቶች የሚሞሉ እና አገራዊ ኢኮኖሚያዊ አቅማችንን የሚያጎለብቱ እንዲሆኑ ይፈልጋል፡፡ ባንኩ የፖሊሲ ባንክ እንደመሆኑ ባለፉት ዓመታት የፋይናንስ ድጋፍ የተደረገላቸው እና ወደገበያው የገቡ ኢንዱስትሪዎች በኢኮኖሚው ላይ ተጨባጭ ለውጦችን ማስመዝገብ ጀምረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፋይናንስ እያደረጋቸው ያሉ እና ሰፊ የሰው ኃይል መሸከም የሚችሉ እንዲሁም የወጪ ንግድን በማበረታታትና የገቢ ንግድን በመተካት የላቀ ፋይዳ ያላቸው ኢንዱስትሪዎችን በቀጣይነት ፋይናንስ የሚያደርግ ይሆናል፡፡ ባንካችን የፖሊሲ ባንክ እንደመሆኑ መንግስት የሚያወጣቸውን ሀገራዉ የልማት አቅጣጫዎችን የሚፈጽም በመሆኑ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸው ፕሮጀክቶችን በመደገፍ ለአገራዊ ልማት የራሱን አስተዋጽዖ ማበርከቱንም አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለመላው ሙስሊም ወገኖቻችን እንኳን ለ1445ኛ ኢድ አልፈጥር አደረሳችሁ እያለ መልካም በዓል እንዲሆንላችሁ ልባዊ ምኞቱን ይገልጻል፡፡

ዒድ ሙባረክ


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ልዩ የዒድ አልፈጥር ፕሮግራም ዝግጅት በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የዜና ቻናል ከቀኑ 8፡00 እስከ 10፡00 ይጠብቁን፡፡

ዒድ ሙባረክ!

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!


የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ ወገኖቻችን በሙሉ እንኳን ለ1445ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል አደረሳችሁ እያለ ልባዊ ምኞቱን ይገልጻል፡፡

ባንካችን የዲቢኢ-ተዐውን ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎትን በይፋ የጀመረበት ዓመት እንደ መሆኑ በሀብት ማሰባሰብ አገልግሎቱ፤ ሱኩክ ዋካላ፣ ሙዳራባህ፣ ወዲዓ የተንቀሳቃሽ ሒሳብ እና ወዲዓ የቁጠባ ሒሳብን እንዲሁም በፋይናንሲንግ አገልግሎቱ፤ኢጃራና ሙራበሐን ለሁሉም የአገልግሎቱ ፈላጊዎች ለማቅረብ እየተጋ መሆኑን ሲያረጋግጥ በታላቅ ደስታ ነው፡፡

ዒድ ሙባረክ!

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!


የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሚሰጣቸው ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎቶች
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!


የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ሰሞኑን በቢሾፍቱ ከተማ የሚገኘውን የብሄራዊ የእንስሳት ጤና ጥበቃ ኢንስቲትዩት ከመንግስት የልማት ድርጅት ይዞታና አስተዳደር ጋር በጋራ በመሆን ጎብኝቷል፡፡

ኢትዮጵያ ከሰሃራ በታች ከሚገኙ እና በእንስሳት ሃብት በተለይ በቁም እንስሳት ሃብታቸው ከሚታወቁ አገራት መካከል ኢትዮጵያ ተጠቃሽ ናት፡፡ ይሁንና ያላትን እምቅ አቅም የሚመጠን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ከዘርፉ እንዳላገኘች በተለያየ ጊዜ ሲነገር ይደመጣል፡፡

የእንስሳት በሽታ የዘርፉን ኢኮኖሚያዊ አስዋጽዖ ከሚያቀጭጩ መንስኤዎች ይጠቀሳል፡፡ በመሆኑም የእንስሳት ጤና ላይ መስራት አገሪቱ በእንስሳት ሃብት የሚገባትን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እንድታገኝ የሚያስችል መሆኑ አያጠያይቅም፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ከግብርና ዘርፍ ልማት አንዱ የሆነው የእንስሳት ሃብት ልማትን አየደገፈ የሚገኝ ሲሆን በዘርፉ ያለውን የኢንቨስትመንት ተሳትፎ ለማሳደግ እንደ አንድ የፋይናንስ ተቋም ስራዎችን እየሰራ ይገኛል፡፡ በመሆኑም ባንኩ ከኢንስቲትቱ ጋር ያደረገው ውይይት በዘርፉ ያለውን እምቅ አቅም ተጠቀሞ ዘርፉ ኢኮኖሚያዊ አበርክቶዎን ለማሳደግ እድል የሚፈጥር ነው ማለት ይቻላል፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዮሐንስ አያሌው የብሄራዊ የእንስሳት ጤና ጥበቃ ኢንስቲትዩት ጋር በተደረገው ውይይት እንዳመላከቱት ባንኩ የፖሊሲ ባንክ እንደመሆኑ ሀገራችን ቅድሚያ ሰጥታ ለማልማት ከምትሰራባቸው ዘርፎች መካከል አንዱ የሆነውን የእንስሳት ሀብት በዘመናዊ መንገድ ጥቅም ላይ ለማዋል የብሄራዊ የእንስሳት ጤና ጥበቃ ኢንስቲትዩት እያደረገ ያለው አስተዋፅዖ የላቀ በመሆኑ በጋራ የሁለቱ ተቋሞች ቅንጅት ወሳኝ ነው።

የውይይቱ ተሳታፊ የነበሩት የመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ትግስቱ አምሳሉ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የግብርናውን ዘርፍ ለማዘመን ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው ከብሄራዊ የእንስሳት ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችለውን ውይይት ማድረጉ ሀገሪቱ ከዘርፉ የምታገኘውን ገቢ በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ እንደሚረዳ ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ቅድሚያ ሰጥቶ የፋይናንስ ድጋፍ ከሚያደርግባቸው ዘርፎች መካከል የእንሰሳት ዘርፍ አንዱ መሆኑን ያስታወሱት ዶ/ር ዮሃንስ ለተያዙት ፕሮጀክቶች የአዋጭነት ጥናት /feasibility study/ ኢንስቲትዩቱ በማቅረብ በጥናቱ መሰረት እገዛ ለማድረግ ባንኩ ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ አክለውም ይህን የሀገር ሀብት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ በጋራ መስራታቸው አስፈላጊና ጊዜ የሚሰጠው ጉዳይ አለመሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ከመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ጋር በመሆን የኢንስቲትዩቱን አጠቃላይ የስራ እንቅስቃሴ መጎብኝታቸው ኢትዮጵያ ከቫይረስና ከባክቴሪያ የሚመጡ የእንስሳት በሽታዎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችሉ የእንስሳት ክትባቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት ለሀገር ውስጥ ገበያ እየቀረበ መሆኑን የሚያስገነዝብ ነው፡፡

የኢንስቲትዩቱ የኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር በሬቻ ባይሳ የኢንስቲትቱ የምርምር ስራዎች፣ የክትባት ማምረቻ ላቦራቶሪዎች ያሉበትን ደረጃና የመድሃኒት ማቀነባበሪያ ፋብሪካን በተመለከተ ለጎብኚዎቹ ገለጻ ያደረጉ ሲሆን የአገር ውስጥ የእንስሳት ክትባት ፍላጎትን ሙሉ ለሙሉ በመሸፈን ለክትባት ግዢ ይወጣ የነበረን የውጭ ምንዛሪ ኢንስቲትዩቱ ማስቀረቱን አብራርተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የኮርፖሬት ግብርና ዘርፍ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ዋቄ በበኩላቸው ባንኩ በልዩ ትኩረት ግብርናውን ለማዘመን እየሰራ በመሆኑና በርካታ በዘርፉ የሚሰማሩ ኢንቨስተሮች ወደ ባንኩ እየመጡ በመሆናቸው ለእንስሳት ጤና የሚሆነውን ክትባት በቅርበት እንዲያገኙ እና የዘርፉን ቢዝነስ ለማሳደግ ከኢንስቲትዩቱ ጋር መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።

ብሄራዊ የእንስሳት ጤና ኢንስቲትዩት በአሁኑ ጊዜ 23 ዓይነት የእንስሳት በሽታ መከላከያ ክትባቶችን እያመረተ ይገኛል፡፡ በዚህም የሚያመርታቸውን ክትባቶች ወደ ጎረቤትና ሌሎች የአፍሪካ አገራት በመላክ የውጭ ምንዛሬ ገቢ ማግኘት መቻሉን፤ እንዲሁም በቀጣይ የእንሰሳት መኖ ማቀነባበሪያ፣ ተቋሙ ሲመሰረት የተገነቡ ላቦራቶሪዎችን በዘመናዊ የአመራረት ዘዴ /GMP/ የመቀየር፣ የእንስሳት መመርመሪያ ኪት ለማምረት፣ መድሃኒቶችን ከእንክብል ይልቅ በመርፌ ወደሚሰጥ ለመለወጥ በእቅድ ላይ እንደሆነና እነዚህን ወደ ተግባር ለመለወጥ የታሰቡ ፕሮጀክቶችን ወደ ተግባር በመቀየር በኩል የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የፋይናንስ የብድር ስርዓቱን ተከትሎ እንዲያግዘው የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ታከለ አባይነህ ጠይቀዋል፡፡

ዋና ዳይሬከተሩ አክለውም ኢንስቲትዩቱ በእንስሳት ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር ድጋፍ የሚያደርግ ተቋም እንደመሆኑ ስትራቴጂ ተነድፎ የገበያ ዕድል ከመፍጠር አንጻርና ፕሮጀክቶቹን ተግባራዊ ለማድረግ ሙሉ አቅሙን በመጠቀም የአዋጭነት ጥናት ለኢትዮጵያ ልማት ባንክ ያቀርባል ብለዋል፡፡

የብሔራዊ የእንስሳት ጤና ጥበቃ ኢንስቲትዩት ከተመሰረተ ከ60 ዓመታ በላይ ብቸኛ በእንስሳት ጤና ላይ የሚሰራ የልማት ድርጅት ሲሆን፤ በአሁን ወቅት በዓመት ከ350 ሚሊዮን ዶዝ በላይ ክትባት እያመረተ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል፡፡


የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እና የብሄራዊ የእንስሳት ጤና ጥበቃ ኢንስቲትዩት አብሮ ለመስራት የሚያስችላቸውን ውይይት አደረጉ።

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እና የመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር  የብሄራዊ የእንስሳት ጤና ጥበቃ ኢንስቲትዩትን ጎብኝተዋል።

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የግብርናውን ዘርፍ ለማዘመን ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ በመሆኑ ከብሄራዊ የእስስሳት ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችለውን ውይይት ማድረጉ ሀገሪቱ ከዘርፉ የምታገኘውን ገቢ በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ እንደሚረዳ በውይይት ወቅት ተነስቷል።


ማኅበራዊ ኃላፊነት፣ የልማት ጉልላት

የተቋማት የብቃት ጥግ የሚለካው ለሠራተኞቻቸው በሚከፍሉት ደሞዝ፣ በሚጠቀሙት ዘመናዊ ቴክኖሎጂ፣ ባላቸው አሠራር ሥርዓት፣ በሚያስመዘግቡት የትርፍ ፈሰስ… ብቻ አይደልም፡፡ ተቋሙ ራሱን የሕዝብ፣ የአካባቢው ማኅብረሰብ አለኝታ የማድረጉ ጉዳይም ትልቁ ስኬት ነው፡፡ የገንዘብ ተቋማትም ሆኑ አጋር ሆነው የሚገደግፏቸው ኢንቨስትመንቶች ቀጣይነታቸው፣ ዘላቂነት ያለው ስኬታቸው፣ ዝናቸው፣ የሚያገኙት ከለላና ክብር ዐቢይ ሥራ ብለው ካሰቡት ያልተናነሰ ዋጋ ሰጥተው ከሚንቀሳቀሱብት ዐቢይ የኮርፖሬት ማኅበራዊ አገልግሎታቸው ይመነጫል፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በባንኩ ውስጥ እያካሄደ ካለው የሪፎርም ሥራዎቹ የተገኘው አንዱ ትሩፋት በየጊዜው እየጎለበተ የመጣው የማኅበራዊ ኃላፊነትን በጎላ በተረዳ መንገድ የመወጣት ተግባር ነው፡፡ ባንኩ በተለይ ባለፉት ተከታታይ ሦስት ዓመታት ካስመዘገበው አመርቂ ትርፍ በጀት መድቦ የተለያዩ ተቋማትንና ግለሰቦችን በዚህ አገልግሎቱ ተደራሽ አድርጓል፡፡

ባንኩ በዋናነት በሚሰጠው የሊዝና የፕሮጀክት ፋይናንሲንግ አገልግሎት ልማትን በማፋጠን እየተጫወተ ካለው ቁልፍ ሚና ባሻገር በችግር ውስጥ ወድቀው የነበሩ የሀገር ባለውለታዎችን ከችግር ታድጓል፤ ማኅበረሰቡን ከተለያዩ ማኅበራዊ ችግሮች ለመታደግ ቁልፍ ሚና ያላቸውን ተቋማት ደግፏል፤ ሀገራዊ ፋይዳቸው ለእያንዳንዱ ዜጋ ትርጉም የሚሰጡ ፕሮጀክቶች አጋር ሆኗል፡፡ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በቀጣይ ጊዜያትም የሕዝብ አለኝታ፣ የማኅበረሰብ ታዳጊ ለሆኑ ተቋማት በኮርፖሬት ማኅበራዊ ኃላፊነት ሥራዎቹ ውስጥ አጋርነቱን እያረጋገጠ ይጓዛል።


የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሚለቃቸውን ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ዌብሳይት፡- www.dbe.com.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/dbethiopia
ቴሌግራም፦ https://t.me/DBE1900
ትዊተር፡- https://twitter.com/DBE_Ethiopia
ሊንክድኢን፡- https://www.linkedin.com/in/dbe1900/
ዩቱብ:- @developmentbankofethiopia' rel='nofollow'>https://www.youtube.com/@developmentbankofethiopia

በመወዳጀት፣ ለሌሎች በማጋራትና ገንቢ አስተያየትዎን በመስጠት ቤተሰብ ይሁኑ፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!




የኢትዮዽያ ልማት ባንክ ክልሉን ለማገዝ እያደረገ ያለው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ
ባንኩ ከክልሉ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ስልጠና እየሰጠ ይገኛል፡፡
መንግስት ትኩረት በሰጣቸው የተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች የአጭር የመካከለኛና የረጅም ጊዜ ብድር በማቅረብና የቴክኒክ ድጋፍ በመስጠት የሀገሪቱን ልማት በማፋጠን ላይ የሚገኘው የኢትዮዽያ ልማት ባንክ በክልሉ ይህን መሰል ልዩ ስልጠና ከማዘጋጀቱም ባሻገር ተደራሽነቱን እያሰፋ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር የኢኮኖሚና የመሰረተ ልማት ዘርፍ አማካሪ ዶ/ር ኢ/ር ምትኩ በድሩ ገልጸዋል፡፡
ክልሉ አብዛኛውን አምራች የሰው ሃይልና እምቅ የተፈጥሮ ሀብት የያዘ ክልል በመሆኑ ባንኩ ይህን ሃብት ወደ ልማት ቀይሮ ለመጠቀም የሚያስችል ስልጠና ያዘጋጀ በመሆኑ ሰልጣኞች ስልጠናውን በአግባቡ በመከታተልና ከስልጠናው በሚያገኙት ዕውቀት ለክልላቸው ብልፅግና የበኩላቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል፡፡
የክልሉ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ግዛው ጋጊያብ በበኩላቸው የሀገራችንን ብልጽግና ዕውን ከማድረጉ አንጻር የአምራቹ ዘርፍ ሚና ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡
በመሆኑም በክልሉ በአጠቃላይ 7 መቶ 37 አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስተሪዎች እንደሚገኙ የጠቆሙት ሃላፊው እነዚህን በማገዝና በማብቃት የክልሉን ዕድገት ማረጋገጥ እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡
ለዚህም የልማት ባንኩ ድጋፍ ወሳኝ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡ በበቨርቿል የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢትዮዽያ ልማት ባንክ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አስፋው አበራ ስልጠናው በክልሉ በሚገኙ አነስተኛና መካከለኛ ባለሀብቶች ጥያቄ መዘጋጀቱ ቀደም ሲል ባንኩ ከሚሰጣቸው ስልጠናዎች ይሄኛውን ለየት እንደሚያደርገው ጠቅሰዋል።
የበለጸጉ ሀገራት መሰረቶች አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስተሪዎች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ እነዚህም የዓለማችንን 50 በመቶ ሀብት በማንቀሳቀስ ትልቅ ድርሻ ይይዛሉ ያሉት ምክትል ፕሬዝዳንቱ ባንኩ እነዚህን ኢንተርፕራይዞች ሚና ከግንዛቤ በማስገባት የሊዝ ብድር ማዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡
በመሆኑም ይህን ውጤታማ ለማድረግ ይህ ስልጠና መዘጋቱን ጠቅሰው ሰልጣኞቹ ይህን ዕድል በአግባቡ በመጠቀም ከራሳቸው አልፈው ለክልላቸው ዕድገት የበኩላቸውን መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
ባንኩ ለክልሉ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ አንቀሳቃሽ ባለሀብቶች የጀመራቸውን ድጋፎች አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ጠቁመዋል፡፡ ለ5 ተከታታይ ቀናት በሚቆየው በዚሁ ስልጠና ላይ ከክልሉ ሁሉም ዞኖች የተውጣጡ ከ6 መቶ 70 በላይ የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ባለቤቶች እየተሳተፉ ይገኛል ሲል ደሬቴድ ቦንጋ ቅርንጫፍ ዘግቧል፡፡
@Southwest Communications
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ





15 last posts shown.