ለአዲስ እና ነባር የማከካሻና የመደበኛ ተማሪዎች አቀባበል ተደረገ
==================
ደ.ማ.ዩ ፡- | መጋቢት 20/2016 ዓ.ም | ህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት| በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ/ም ለነባርና አዲስ የመደበኛና የማከካሻ ተማሪዎች አቀበባልና ልዩ ልዩ ስልጠናዎች ተሰጡ።
ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ.ም ለአንድ መንፈቀ ዓመት ያክል ሲማሩ ለነበሩ መደበኛ እና የማከካሻ ትምህርት ተጠቃሚ ተማሪዎች እንዲሁም በ2016 ዓ.ም የትምህርት ሚኒስቴርን የመግቢያ መስፈርት አሟልተው በአዲስ ለተመደቡ መደበኛ እና የማከካሻ ትምህርት እንዲወስዱ ለተመደቡ ተማሪዎች አጠቃላይ አቀባበልና ገለፃ እንዲሁም ልዩ ልዩ ስልጠናዎችን ሰጠ።
የአቀባበል መድረኩ በሁለት ተከፍሎ የተሰጠ ሲሆን በጥዋቱ መርሃ ግብር ነባር የአንደኛ አመትና ነባር የማከካሻ ትምህርት ተጠቃሚዎች ተሳትፈውበታል። በከስዓቱ መርሃ ግብር ደግሞ በ2016 ወደ ዩኒቨርሲቲያችን የተመደቡ አዲስ አንደኛ አመት እና አዲስ የማከካሻ ተጠቃሚ ተማሪዎች ተሳትፈዋል።
በመድረኮቹ ላይ የዩኒቨርሲቲያችን የአካደሚክ ጉዳዮች ም/ ፕሬዚደንት ዶ/ር ይሄይስ አረጉን ጨምሮ ሌሎችም ከፍተኛ አመራሮች እና ጉዳዩ የሚመለከታቸው የስራ ክፍል ኃላፊዎች እንዲሁም የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ህብረት ፕሬዚደንት ተገኝተዋል።
የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚደንት ይሄይስ አረጉ (ዶ/ር) ተማሪዎችን እንኳን ደህና መጣችሁ ካሉ በኋላ የዩንቨርሲቲ ተማሪ ሀብቱ ተስፋውና ጊዜው መሆኑን ገልፀው ተማሪዎች እስካሁን በባከነው ጊዜ ተስፋ ሳይቆርጡ አሁን በእጃቸው ላይ ያላቸውን ጊዜ ባግባቡ መጠቀም ለስኬታቸው ወሳኝነት እንዳለው አሳስበዋል፡፡
አካዳሚክ ጉዳዮች ኤክሲኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር በለጠ ያዕቆብ በጥዋቱ መድረክ ተገኝተው ለተማሪዎች ባስተላለፉት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት፣ በነበረው ከባቢያዊ ነባራዊ ሁኔታ የትምህርት ጊዜው የተጓተተ ቢሆንም ተማሪዎች ለመጡለት ዓላማ ብቻ ትኩረት ሰጥተው እርስ በርስ በመከባበር ፣ በመቻቻል፣ ማህበራዊ ግንኙነታቸውን በማዳበር እንዲሁም ደንብና ስርዓትን በተከተለ መንገድ ትምህርታቸውን መከታተል እንደሚገባቸው አሳስበዋል፡፡
በተደረገው የአቀባበል መርሃ ግብር ተማሪዎች ፦
- ማድረግ ስለሚጠበቅባቸውና ማድረግ ስለማይገባቸው ነገሮች፤
- ከቤተሰቦቻቸው ተለይተው በግቢ በሚቆዩበት ወቅት ሊከሰቱባቸው ስለሚችሉ የስነ ልቦና ችግሮችና መፍትሄዎች በተመለከተ፤
- እንዴት ማጥናትና ውጤታማ መሆን እንደሚችሉ፤
- በግቢ ውስጥና ከግቢ ውጭ እቅስቃሴያቸው ወቅት መከተል ስለሚገባቸው የስነ ምግባር መርሆዎችን በተመለከተ ሰፊ ማብራሪያና ገለፃ ተደርጎላቸዋል።
===============
ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ
የእውቀት አውድማ ከጮቄ ማማ!
ለተጨማሪ እና አዳዲስ መረጃዎች
👇👇
#ቴሌግራም፡
https://bit.ly/3HbDPCB#ፌስቡክ፡
https://bit.ly/3mYfnNW#ዩቱዩብ፡
https://bit.ly/3L73hu3#ዌብሳይት
www.dmu.edu.et