EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation)


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation) @etvafaanoromoo1
@ETVkidschannel
@EBCWORLD1

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


ማስታወቂያ
****
ሬስ ማይክሮ ፋይናንስ እና ሁድ ሁድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በመተባበር የተመቻቸ ብድር


በተጠባቂው ጨዋታ አርሰናል ሪያል ማድሪድን 3 ለ 0 አሸነፈ
******

በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የሩብ ፍፃሜ ጨዋታ ኤምሬትስ ላይ የውድድሩን ባለሪከርድ አሸናፊ ሪያል ማድሪድን ያስተናገዱት መድፈኞቹ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፈዋል።

100 ሚሊዮን ፓውንድ ወጥቶበት ሰሜን ለንደን የደረሰው ዴክላን ራይስ ያስቆጠራቸው ሁለት ድንቅ የቅጣት ምት ግቦች እንዲሁም ስፔናዊው አማካኝ ሚኬል ሞሪኖ ያከላት አንድ ግብ የአርሰናልን ድል 3 - 0 እንዲሆን አስችለዋል፡፡

ኪልያን ምባፔ ቪንሺየስ ጁንየርንና ጁድ ቤልንግሀምን የያዘው የማድሪድ ወርቃማ ስብስብ በእንግሊዝ ምድር አስደንጋጭ ሽንፈት አጋጥሞታል፡፡

በሃብተሚካኤል ክፍሉ




የመገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት የሚዲያ ባለሙያዎችን የመመዝገብም ሆነ የሙያ ማረጋገጫ የመስጠት ተግባርና ኃላፊነት አልተሰጠውም፦ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን
****************

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት፣ ለጋዜጠኞች የሙያ ማረጋገጫ ለመስጠት እና የጋዜጠኞች ምዝገባ ለማከናወን ውይይት እና እንቅስቃሴ መጀመሩን ተከትሎ፤ የተለያዩ የሚዲያ ተቋማት፣ ጋዜጠኞች እና የሙያ ማህበራት ጉዳዩን በተመለከተ የሕጋዊነት ጥያቄ እና ስጋቶቻቸውን በማቅረብ ላይ መሆናቸውን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን አስታውቋል።

አያይዞም፥ የመገናኛ ብዙኃን ምክር ቤቱ ጋዜጠኞችን ወይም የሚዲያ ባለሙያዎችን የመመዝገብም ሆነ የሙያ ማረጋገጫ የመስጠት ተግባርና ኃላፊነት በመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቁጥር 1238/2013 አልተሰጠውም ብሏል።

በመሆኑም የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ለዚህ የምክር ቤቱ ተግባር እውቅና የማይሰጥ መሆኑን ባለስልጣኑ ለኢቢሲ በላከው የፕሬስ መግለጫ አሳውቋል።


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የፕሬዚዳንትነት ርክክብ ሥነ ሥርዓት


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
ማስታወቂያ
******


አቶ ጌታቸው ረዳ ምን አሉ?

"የሁለት ዓመት የጊዜያዊ መስተዳድር ሀላፊነቴን በይፋ አስረክቤያለሁ።

የትግራይ ህዝብ ላሳየኝ ክብር እና ድጋፍ ላቅ ያለ ምስጋና አለኝ።

ህዝባችን ወደ ተሻለ ሁኔታ እንዲመለሰ ሁለንተናዊ ፍላጎቱ እንዲሟላለት የተቻለኝን ሁሉ አደርጋለሁ።

የሰላም እና የለውጥ ፍላጎት እንዳይሰናከል ትግላችንን እናጠናክር። ክብረት ይስጥልኝ!" ሲሉ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ አስፍረዋል::


የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት የፈረሙት የትግራይ ክልል አካታች ጊዜያዊ አስተዳደር የተልዕኮ አፈጻጸም፣ የቃል ኪዳን ሰነድ፦


ሌ/ጄኔራል ታደሰ ወረደ አቶ ጌታቸው ረዳን በመተካት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንትነትን ተረከቡ
*****************

"ባለፈው አንድ ወር ገደማ የኢትዮጵያን ሕገ መንግሥት፣ የፕሪቶርያን ስምምነት እና የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡን ምክር በማከል ሰፊ ውይይቶች ሲካሄዱ ቆይተዋል። የአቶ ጌታቸው የሥልጣን ዘመን በሕጉ መሠረት ሲያበቃ የሚቀሩ ቁልፍ ሥራዎችን የሚያከናውን አካል፣ ግዝያዊ መንግሥቱ መቀጠል አለበት የሚል ድምዳሜ ከተያዘ በኋላ፣ ይሄንን ሽግግር ማን መርቶ ከግብ ሊያደርስ ይችላል? የሚሉ ውይይቶችን ስናደርግ ቆይተናል።

ዛሬ በይፋ እና በሰላማዊ መንገድ በአዲስ ባህል የሥልጣን ሽግግሩን እና ቅብብሎሹን ለማካሄድ የተዘጋጀ ፕሮግራም አከናውነናል። ጄኔራል ታደሰ ባለፋት ሁለት ዓመታት የአቶ ጌታቸው ምክትል ሆነው ያገለገሉ ሰው ናችው። ባለፋት ሁለት ዓመታት የነበሩ ድካሞችን እና ጥንካሬዎችን በግልጽ የሚገነዘቡ ሰው ናቸው። አሁን ትግራይ ውስጥ ያለውን ክፍተት ሞልተው ወደ ፊት ሊወስዱ ይችላሉ የሚል እምነት በብዙ አካላት የታመነ ነው። የትግራይ ሕዝብ የጠማውን ሰላም እና ልማት፣ እንደ ሌሎች ወንድሞቹ ወጥቶ የመግባት መሻት ስናሳካ፣ ለኢትዮጵያም ለአፍሪካም እጅግ ጠቃሚ የሆነ ነገር ሠርቶ ለማለፍ ታሪክ የሰጣቸውን ዕድል እንደሚጠቀሙበት ተስፋ አደርጋለሁ።"

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)


ማስታወቂያ
****
ሬስ ማይክሮ ፋይናንስ እና ሁድ ሁድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በመተባበር የተመቻቸ ብድር


አስፈሪው ቡድን... አስደናቂው ድል...

የሃያሉ ክለብ ፕሬዝደንት ፍሎሬንቲኖ ፔሬዝ በመጀመርያው የስልጣን ዘመናቸው በሮናልዶ ሊዩስ ናዛሪዮ፣ ዚነዲ ዚዳን፣ ዴቪድ ቤክሀም እና ሮቤርቶ ካርሎስ የገነቡት ጋላክቲኮ ለየትኛውም ቡድን አስፈሪ ነው።

2005/2006 የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ምድብ ሁለትን አንድም ጨዋታ ሳይሸነፍ ያጠናቀቀው አርሰናል በጥሎ ማለፉ ከምድብ ስድስት ሁለተኛ ሆኖ ካጠናቀቀው ሪያል ማድሪድ ተገናኙ።

ሳንቲያጎ ቤርናባው ላይ ሊደረግ ቀጠሮ የተያዘለት የመጀመርያው ጨዋታ እለተ ማክሰኞ ምሽት በዋና ከተማው ማድሪድ ሊጀመር ነው።

በምድብ ጨዋታዎች ካደረጓቸው 6 ጨዋታዎች 5ቱን ያሸነፉት አሰልጠሰኝ አርሰን ቬንገር ከወሳኙ ፍልሚያ በፊት ላውረን እና ሶል ካምቤልን ጨምሮ 8 ተጫዋቾቻቸው ጉዳት ላይ መሆናቸው ሌላ መፍትሄ እንዲፈልጉ አድርጓቸዋል።

አስፈሪው ቡድን... አስደናቂው ድል...


የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሻርጃ ከተማ አዲስ በረራ ሊጀምር ነው
**************

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ሻርጃ ከተማ ከግንቦት 24 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ አዲስ የበረራ አገልግሎት የሚጀምር መሆኑን አስታውቋል።

ይህ አዲስ የበረራ አገልግሎት በሳምንት አራት ቀናት የሚደረግ መሆኑንም አየር መንገዱ አስተውቋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚጀምረው አዲስ የበረራ መስመር መንገደኞች በተቀላጠፈ የበረራ አማራጭ የደማቅ ባህል እና ሰፊ ኢኮኖሚያዊ እድሎች ባለቤት ወደ ሆነችው ሻርጃ ከተማ በቀላሉ እንዲጓዙ እንደሚስችልም አስታውቋል።

#etv #ebcdotstream #EBC #Ethiopia #Ethiopian #sharjah #ethiopianairlines


የልብ ሕመምን በሰከንዶች ውስጥ መለየት የሚችል መተግበሪያ የሠራው የ14 ዓመቱ አዳጊ
********
በአሜሪካዋ ቴክሳስ ግዛት ዳላስ የሚኖረው ሲዳርት ናንድያላ የተባለ የ14 ዓመት አዳጊ በሰው ሠራሽ አስተውሎት የሚታገዝ እና ድምፅን ብቻ በመጠቀም በ7 ሴኮንዶች ውስጥ የልብ ሕመምን መለየት የሚችል ‘ሲርካዲያን ኤአይ’ የተባለ የስልክ መተግበሪያ (አፕሊኬሽን) መሥራት ችሏል።

አዳጊው እንደ ሌሎቹ የዕድሜ እኩዮቹ አይደለም ያለው ኦዲቲ ሴንትራል፣ በዓለም ላይ ካሉት በዕድሜ ትንሹ የሰው ሠራሽ አስተውሎት አበልጻጊ ባለሙያ እንደሆነ እና ለዚህም ከኦራክል እና ከኤ.አር.ኤም የባለሙያነት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት እንዳገኘ ጠቁሟል።

እርሱ የሠራው ‘ሲርካዲያን ኤአይ’ መተግበሪያ በስልክ የተወሰደውን ድምፅ በአልጎሪዝም በመተንተን ታማሚ ሰው አፋጣኝ እገዛ እንዲያገኝ በማድረግ ለሕይወት አድን ሥራ እገዛ ያደርጋል።

መተግበሪያው እስካሁን ድረስ በአሜሪካ 15 ሺህ ያህል ሰዎች ላይ፣ በሕንድ ደግሞ 700 ሰዎች ላይ ተሞክሮ 96 በመቶ ትክክለኛ ምላሽ ሰጥቷል።

የልብ ሕመምን በሰከንዶች ውስጥ መለየት የሚችል መተግበሪያ የሠራው የ14 ዓመቱ አዳጊ


የኦሮሚያ ክልል 1 ሺህ 402 የእርሻ ትራክተሮችን ለአርሶአደሮች ሊያስረክብ ነው
*******************

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት 1 ሺህ 402 የእርሻ ትራክተሮችን ከነመገጣጠምያቸው ለአርሶ አደሮች፣ የህብረት ስራ ማህበራትና ዩኒየኖች በዛሬው እለት በሻሸመኔ ከተማ ሊያስረክብ ነው።

ትራክተሮቹን የሚረከቡት 143 አርሶ አደሮች፣ 12 የህብረት ስራ ማህበራት እና 42 ዩኒየኖች ለክልሉ መንግስት የይቅረብልን ጥያቄ ያቀረቡና ቀድመው የቆጠቡ መሆናቸውን ማወቅ ችለናል።

ትራክተሮቹ ኬኛ የግብርና መሳሪያዎች ማምረቻና ጠቅላላ ንግድ ሀላፊነቱ የተወሰነ ድርጅት በሀገር ውስጥ የተገጣጠሙ ናቸው።

ትራክተሮቹ የክልሉ መንግስት የግብርና ሜካናይዜሽንን ለማስፋፋት ለያዘው ውጥን ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖራቸዋል።

የትራክተሮቹ ርክክብ የኦሮምያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳን ጨምሮ ከፍተኛ የክልሉ የመንግስት ባለስልጣናት በተገኙበት የሚፈፀም ይሆናል።

በፍቃደአብ አለማየሁ

#etv #ebcdotstream #EBC #ኦሮሚያ #ትራክተር

https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02g5yfiC22ZrX1endsTehs26tc8ygjvFB7kFhqQzeKeJvJhq9CnTSEJjxDcWTwiTyul


ማስታወቂያ
****
ሬስ ማይክሮ ፋይናንስ እና ሁድ ሁድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በመተባበር የተመቻቸ ብድር


እጅጋየሁ ታዬ ሻምፒዮን ሆነች

በጃማይካ ኪንግስተን በተደረገው የ5 ሺህ ሜትር ረጅም ርቀት ግራንድ ስላም ትራክ አትሌት እጅጋየሁ ታዬ በበላይነት አጠናቃለች።

14 ደቂቃ 54.88 ሰከንድ እጅጋየሁ ርቀቱን ለማጠናቀቅ የወሰደባት ጊዜ ሆኗል።

ቀደም ብላ የ3 ሺህ ሜትር ረጅም ርቀትን በተመሳሳይ በአንደኝነት ያጠናቀቀችው አትሌቷ
ያገኝችውን ነጥብ 24 በማድረስ የርቀቱ ሻምፒዮን ሆናለች።

በመሆኑም በአዲሱ ውድድር የአለም ሻምፒዮና የነሀስ ሜዳልያ ባለቤቷ አትሌት እጅጋየሁ ታዬ የ100 ሺህ ዶላር ተሸላሚ ሆናለች።

ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ጽጌ ገብረሰላማ 3ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።

ጽጌ በ3 ሺህ ሜትር ረጅም ርቀት በተመሳሳይ 3ኛ ሆና ማጠናቀቋ የሚታወስ ሲሆን ያገኝችውን ነጥብ 12 በማድረስ የ30 ሺህ ዶላር ተሸላሚ ሆናለች።

ኬንያዊቷ አግነስ ኒጌቲች ደግሞ በአጠቃላይ የረጅም ርቀት ውጤት 2ኛ ወጥታለች።

በአንተነህ ሲሳይ


አብን ዶ/ር በለጠ ሞላን የፓርቲው ሊቀመንበር አድርጎ ሰየመ
*******

የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ /አብን/ 3ኛ መደበኛ ጉባኤውን በድምቀት በማካሄድ፤ ዶ/ር በለጠ ሞላን የፓርቲው ሊቀመንበር፣ አቶ መልካሙ ጸጋዬን ምክትል ሊቀመንበር አድርጎ ሰይሟል።

የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ /አብን/ ዛሬ መጋቢት 28 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ 3ኛ ድርጅታዊ ጉባኤውን ያካሄደ ሲሆን፤ ጉባኤውን በድምቀት በመጸፈም ልዩ ልዩ ውሳኔወችን አሳልፏል።

ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት የአብን ሊቀመንበር ዶ/ር በለጠ ሞላ ድርጅቱ ከምስረታው ጀምሮ ያጋጠሙትን ተግዳሮቶች፣ የተደረጉ ትግሎችን እና የተገኙ ድሎችን አውስተዋል።

በለጠ ሞላ (ዶ/ር)

https://t.me/EBCNEWSNOW



18 last posts shown.