አስፈሪው ቡድን... አስደናቂው ድል...
የሃያሉ ክለብ ፕሬዝደንት ፍሎሬንቲኖ ፔሬዝ በመጀመርያው የስልጣን ዘመናቸው በሮናልዶ ሊዩስ ናዛሪዮ፣ ዚነዲ ዚዳን፣ ዴቪድ ቤክሀም እና ሮቤርቶ ካርሎስ የገነቡት ጋላክቲኮ ለየትኛውም ቡድን አስፈሪ ነው።
2005/2006 የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ምድብ ሁለትን አንድም ጨዋታ ሳይሸነፍ ያጠናቀቀው አርሰናል በጥሎ ማለፉ ከምድብ ስድስት ሁለተኛ ሆኖ ካጠናቀቀው ሪያል ማድሪድ ተገናኙ።
ሳንቲያጎ ቤርናባው ላይ ሊደረግ ቀጠሮ የተያዘለት የመጀመርያው ጨዋታ እለተ ማክሰኞ ምሽት በዋና ከተማው ማድሪድ ሊጀመር ነው።
በምድብ ጨዋታዎች ካደረጓቸው 6 ጨዋታዎች 5ቱን ያሸነፉት አሰልጠሰኝ አርሰን ቬንገር ከወሳኙ ፍልሚያ በፊት ላውረን እና ሶል ካምቤልን ጨምሮ 8 ተጫዋቾቻቸው ጉዳት ላይ መሆናቸው ሌላ መፍትሄ እንዲፈልጉ አድርጓቸዋል።
አስፈሪው ቡድን... አስደናቂው ድል...