ESAT (ኢሳት🇪🇹)®


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot
🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


በሳዑዲ ዓረቢያና በኦማን በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 470 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ‼️

በዚህ ሳምንት ውስጥ 180 ወንዶች፣ 109 ሴቶች እና 13 ጨቅላ ህፃናት በድምሩ 302 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደ ሀገር የተመለሱ ሲሆኑ ከተመላሾች መካከል 56 እድሜያቸው ከአስራ ስምንት አመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች ይገኙበታል።

በተያያዘ ዜና በሳምንቱ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 157 ወንዶች 11 ሴቶች በድምሩ 168 ኢትዮጵያውያን ከኦማን ወደ ሀገራቸው የተመለሱ መሆኑ ታውቋል።

ለተመላሽ ዜጎች በአየር ማረፊያና በማቆያ ማዕከላት ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ የማድረግ እና ከቤተሰብ ጋር የማቀላቀል ስራም እየተሰራ ይገኛል፡፡

ከሚያዚያ 04 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ እየተከናወነ በሚገኘው ከሳዑዲ ዓረቢያ ዜጎችን የመመለስ ስራ እስካሁን 91 ሺህ 420 ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገር መመለስ ተችሏል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


እስራኤል የሙስሊም ረመዳን እና የአይሁዶች የፋሲካ በዓል እስኪያልፍ ድረስ በሚል ለቀጣይ ስድስት ሳምንታት የጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነትን በጊዜያዊነት ለማራዘም ወሰነች‼️

የጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ጽሕፈት ቤት ይህንን ያስታወቀው ቀደም ሲል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት የመጀመሪያ ምዕራፍ ቅዳሜ እኩለ ሌሊት ላይ ካበቃ በኋላ ብዙም ሳይዘገይ ነበር።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


#ቴምር ሪልስቴት

⚠️7ሳይቶችን ስርተን አስረክበናል አሁን ላይ ደግሞ ለሽያጭ ያወጣናቸው ቤቶቾ እና ሱቆች
‼️ፒያሳ (ሊሴ ገ/ማርያም ትምህርት ቤት) ጀርባ
         👉1 መኝታ 66ካሬ=
         10% ቅድመ ክፍያ 693,000ብር
         ሙሉ ክፍያ 6,930,000 ብር
         👉2መኝታ 71ካሬ
        10%ቅድመ ክፍያ 745,000ብር
        ሙሉ ክፍያ 7,455,000ብር
         👉2መኝታ 93ካሬ=
       10% ቅድመ ክፍያ 1,044,000ብር
       ሙሉ ክፍያ 10,044,000ብር
        👉3መኝታ 130ካሬ
      10%ቅድመ ክፍያ 1,365,000ብር
      ሙሉ ክፍያ 13,650,000ብር
        👉ቀሪውን 90% በ17ዙር ከፍለው         የሚጨርሱት
        👉30% እና ከዛ በላይ ለሚከፍል ከከፈሉት ላይ 25% ደረስ የሚደርስ ቅናሽ አዘጋጅተናል

ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
 ☎️📞👇👇👇👇👇👇

0901168027

0901179577

    


የመጋቢት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል‼️

የመጋቢት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በነዳጅ ውጤቶች ግብይት አዋጅ እና መመሪያ መሠረት መንግስታዊ ውሳኔውን ተግባራዊ እንዲያደርጉም ሚኒስቴሩ አሳስቧል፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ዓድዋ! 🇪🇹🇪🇹🇪🇹


የዓድዋ ድል ሚስጢር ኢትዮጵያውያን ስለሀገራቸው ክብር ያሳዩት ፍጹም አንድነት ነው‼️

የዓድዋ ድል ሚስጢር ኢትዮጵያውያን ስለሀገራቸው ክብር ያሳዩት ፍጹም አንድነት መሆኑን የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አበባው አያሌው ገልጸዋል፡፡ 

ድሉ የአፍሪካውያን የአርነት ትግልና የፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ እንዲፋፋም ትልቅ ጉልበት መሆኑንም አስታውቃል፡፡

“የዓድዋ ድል የ19ኛው ክፍለ ዘመን ታላቅ ጦርነት እና ድል ነው” ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ ፤ የዓድዋ ድል የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ያስከበረና የአሸናፊነት ሥነ-ልቦናን ያጎናጸፈ ድል እንደሆነም መናገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

129ኛ የዓድዋ ድል በዓል "ዓድዋ የጥቁር ህዝቦች ድል" በሚል መሪ ሀሳብ በዓድዋ ድል መታሰቢያ በመከበር ላይ ይገኛል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ፕሬዚዳንት ትራምፕ እንግሊዝኛን የሥራ ቋንቋ የሚያደርግ ትዕዛዝ ሊፈርሙ ነው‼️

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እንግሊዝኛን የአሜሪካ የሥራ ቋንቋ የሚያደርገውን ትዕዛዝ ሊፈርሙ ነው።

ምንም እንኳን አብዛኞቹ የአሜሪካ ግዛቶች እንግሊዝኛን እንደ መንግሥታዊ የሥራ ቋንቋቸው አድርገው ቢወስዱትም፤ በሀገሪቱ የ250 ዓመታት ታሪክ ውስጥ እንግሊዝኛን በይፋ የሥራ ቋንቋ ለማድረግ ሲታሰብ የመጀመሪያው እንደሆነ ታውቋል።

እንግሊዝኛ በይፋ እንደ የሥራ ቋንቋ የተወሰነ ባይሆንም፤ ከተለያዩ ሀገራት ወደ አሜሪካ የሚሄዱ ሰዎች ማሟላት ከሚገባው መስፈርቶች አንዱ እንግሊዝኛ ቋንቋን መቻል እንደሆነ የአሜሪካ ኢሚግሬሽን አገልግሎት መረጃዎች ያመላክታሉ።

ከሦስት አራተኛ በላይ የሚሆኑት አሜሪካውያን እንግሊዝኛን የሚጠቀሙ ቢሆንም፤ ሌሎች ከ350 በላይ በላይ ቋንቋዎች በሀገሪቱ እንደሚነገሩ ኤን.ቢ.ሲ የአሜሪካ የሕዝብ ቆጠራ ቢሮ መረጃን ጠቅሶ ዘግቧል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


🌙 ረመዳን ሙባረክ🌙

የረመዳን ወር መግቢያ ጨረቃ በመታየቷ ነገ ቅዳሜ የረመዳን የመጀመሪያው ቀን ይሆናል።

ዛሬ የተራዊህ ሶላት የሚጀመር ሲሆን ነገ የረመዷን ጾም ይጀምራል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ለ129ኛው የዓድዋ ድል መታሰቢያ በዓል ዝግ የሚሆኑ መንገዶች‼️

በቸርችል ጎዳና በቴዎድሮስ አደባባይ ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ የሚወስደው መንገድ ባንኮ ዲሮማ መብራት

ከአራት ኪሎ በራስ መኮንን ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ የሚወስደው መንገድ ራስ መኮንን ድልድይ

ከመነን አካባቢ እና የካቲት 12 ሆስፒታል በአፍንጮ በር ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ የሚወስደው መንገድ አፍንጮ በር

ከእሪ በከንቱ በኤሌክትሪክ ህንፃ ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ የሚወስደው መንገድ ደጎል አደባባይ

ከአዲሱ ገበያ በሰሜን ሆቴል ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ የሚወስደው መንገድ ሰሜን መብራት

ከመርካቶ በአቡነ ጴጥሮስ ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ የሚወስደው መንገድ ደጃዝማች ሀብተጊዮርጊስ ድልድይ

ከእንቁላል ፋብሪካ በቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ የሚወስደው መንገድ ዝግ ይሆናል።

ከየካቲት 22 ቀን 2017 ዓም ከምሽቱ 6፡00 ሠዓት ጀምሮ እስከ የካቲት 23 ቀን 2017 ዓም ከቀኑ 7፡00 ሠዓት ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ ስለሚሆኑ አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙና አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

ህብረተሰቡ ማንኛውም አጠራጣሪ ጉዳዮች ሲያጋጥሙ  011-1-11-01-11 ወይም በነፃ ስልክ መስመር 991 መጠቀም የሚቻል መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በአዲስ አበባ ተግባራዊ የሚደረግ የወንዞች ዳርቻ ልማትና ብክለት መከላከል ደንብ ይፋ ሆኗል‼️

የወንዞች ዳርቻ ልማትና ብክለት መከላከል ደንብን መተላለፍ የሚያስከትለው ቅጣት እንደሚከተለው ቀርቧል።

በባህሪው አደጋኝነት የሆነ ደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ በወንዝ ዳርቻ ያሰወገደ ድርጅት አንድ ሚሊዮን ብር ይቀጣል፣

ደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ ወንዝ ላይ የጣለ ግለሰብ 500 ሺህ ብር ይቀጣል

ፍቃድ የወሰዱም ሆነ ሳይወስዱ ፍሳሽን ቀጥታ በወንዞች ዳርቻ ሲያስወግዱ ቢገኙ 100 ሺህ ብር  ይቀጣሉ፣

በወንዝ ዳርቻና አካባቢ መጸዳዳት ሁለት ሺህ፤

የፈሳሽ ማጣሪያ ሳይኖር በወንዝ ዳርቻና አካባቢ ተሽከርካሪ ማጠብ 400ሺህ ብር፤

እንስሳትን ማሰማራት፣ ማስገባት ከተፈቀደው ውጪ ተሽከርካሪ ማሽከርከር 30 ሺህ ብር

ለመዝናኛ፣ ለመናፈሻና ለፖርክ ከተፈቀደ ውጪ ግንባታ መገንባት 200 ሺህ ብር፤

ከአምራችና አገልግሎት ሰጪ  ተቋማት ማንኛውም ያልታከመ ቆሻሻ መልቀቅ 300 ሺህ ብር ያስቀጣል፣

ኬሚካል ነክ ቆሻሻዎችን የማከሚያ ዘዴ ሳይጠቀም የለቀቀ ግለሰብ 50 ሺህ፤ ድርጅት 300 ሺህ ብር ይቀጣሉ፣

ማንኛውም በካይ ቆሻሻ ከተፈቀደ የፈሳሽ ማጠራቀሚያ ውጪ ያፈሰስ ግለስብ 50 ሺህ ድረጅት 400 ሺህ ብር፤

የአትክልትና ፍራፍሬ ተረፈ ምርቶችን በወንዝ ዳርቻ ማስወገድ ግለሰብ 20 ሺህ፣ ድርጅት 100 ሺህ፤

ዘይት፣ ጨዋማ ፈሳሽ፣የሞተር ዘይት፣ ነዳጅ ሳሙና ነክ ነገሮችን በወንዝ ዳርቻ ያስወገደ 400 ሺህ ብር ይቀጣል፣

ማንኛውም ያልተጣራ ቆሻሻ ወደ ወንዝ መልቀቅ ግለሰብ 150 ሺህ ድርጀት 300 ሺህ ይቀጣል፣

ፍቃድ ሳይሰጠው ያልታከመ ቆሻሻን ወደ ወንዝ ያስወገደ ግለሰብ 15 ሺህ ብር ድርጅት 40 ሺህ ብር ይቀጣል"ተብሏል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በአዲስ አበባ ሀብተጊዮርጊስ ድልድይ አካባቢ ተከስቶ የነበረው የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለጸ‼️

በአዲስ አበባ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ሀብተጊዮርጊስ ድልድይ አካባቢ ዛሬ ሌሊት 10:35 ሰዓት አካባቢ በመኖሪያና ንግድ ቤቶች ላይ ተከስቶ የነበረው የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር መዋሉን የከተማዋ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ።

በእሳት አደጋው በሰውና በንብረት ላይ የደረሰው ጉዳት እንዲሁም የአደጋው መንስዔ ተጣርቶ እንደሚገለጽ ኮሚሽኑ አስታውቋል።

አደጋ የደረሰበት ስፋራ በከተማ ደረጃ ለእሳት አደጋ ተጋላጭ ተብለው ከተለዩ የመኖሪያና የንግድ አካባቢዎች አንዱ መሆኑ ተጠቁሟል።

ቤቶቹ የተገነቡበት ግብዓት፣ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታው እንዲሁም ቦታው የአደጋ ጊዜ ተሽከርካሪዎችን ለማስገባት ምቹ አለመሆኑ የእሳት አደጋው እንዲሰፋ ምክንያት መሆኑን ኮሚሽኑ ጠቅሷል።

እሳቱን ለመቆጣጠር የኮሚሽኑ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች፣ የጸጥታ አካላት፣ የአካባቢው ማህበረሰብ እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ከፍተኛ ርብርብ ማድረጋቸውም ተገልጿል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በአዲስ አበባ ከተማ የአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት በሽታ መከሰቱን የጤና ባለሙያዎች ጠቆሙ ‼️

በመዲናዋ ውስጥ የአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት (አተት) በሽታ እንደተከሰተ የጤና ባለሙያዎች ለሚድያችን በሰጡት ቃል አሳወቁ።

የበሽታው መከሰትን ለመሠረት ሚድያ ያረጋገጡት እነዚህ በአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ስር ባሉ ጤና ጣቢያ የሚሰሩ የጤና ባለሙያዎች ስጋቱ ለህዝብ ይፋ ሆኖ የጥንቃቄ እርምጃዎችን በተመለከተ መልዕክት አለመተላለፉ የበለጠ ጉዳት እንዳያስከትል ስጋታቸውን ገልፀዋል።

"ሰሞኑ ከፍተኛ የአተት በሽታ ተከስቷል፣ ነገር ግን ምንም እየተባለ አይደለም። እኛም በየጤና ጣቢያ ሸራ ወጥራቹ ዝም ብላችሁ ስሩ እየተባልን ነው" ያለው አንድ የጤና ባለሙያ በአስደንጋጭ መልኩ 'vibrio cholerae' የተባለው የኮሌራ አምጪ ተህዋስም በምርመራ ወቅት በከተማው ውስጥ መገኘቱን ተናግሯል።

"እንደምናውቀው አተትም ሆነ ኮሌራ በጣም ተላላፊ ነው፣ ነገር ግን እየሆነ ያለው ነገር ፍፁም ተቃራኒ ነው" የሚሉት የጤና ባለሙያዎቹ ከ100 በላይ የበሽታው ተጠቂዎች አሁን ላይ ባሻ ወልዴ ተብሎ በሚጠራው የአራዳ ክፍለ ከተማ ጤና ማዕከል ገብተው እንደሚገኙ አረጋግጠዋል።

"አሁን በዚህ ሰአት በርካታ ታማሚዎችን ካለ በቂ መከላከያ እና መሸፈኛ እያከምን ነው፣ አስቸኳይ መፍትሄ እንሻለን" ያሉን ሌላኛው የጤና ባለሙያ ናቸው።

ከሰሞኑ በጋምቤላ ክልል ኑዌር ብሔረሰብ ዞን አራት ወረዳዎች የአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት በሽታ ተከስቶ የዘጠኝ ሰዎችን ሕይወት መንጠቁ ታውቋል።
©ለመሠረት ሚድያ

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ኢትዮጵያ እና የዓለም ባንክ የ60 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ስምምነት ተፈራረሙ‼️

የገንዘብ ሚኒስቴር እና የዓለም ባንክ  የተቀናጀ የሴቶች እና ልጃገረዶች ጤና ምላሽ ፕሮጀክትን ለማስተዋወቅ እና ለመተግበር የሚውል የ60 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ስምምነት ተፈራርመዋል።

ፕሮጀክቱ በአየር ንብረት ለውጥ እና ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች ለተለያዩ ጉዳቶች የተጋለጡ ሰዎችን የሚደግፍ ሲሆን፤ በዚህም መሰረት በአገር አቀፍ ደረጃ የጤና ዘርፉን በማጠናከር 15 ሚሊዮን ሴቶችን እና ልጃገረዶችን በቀጥታ ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሏል።

ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ እና በዓለም ባንክ የኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ ሱዳን እና ደቡብ ሱዳን ዲቪዥን ዳይሬክተር ማርያም ሳሊም ተፈራርመዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ሶማሊያ ገቡ‼️

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ሶማሊያ ገብተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሶማሊያ ሞቃዲሾ ሲደርሱ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሀመድ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በአዲስ አበባ ቢቂላ መናፈሻ በሚባለው አካባቢ የተከሰተው የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለጸ‼️

ዛሬ ከቀኑ 9:33 ሰዓት ላይ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ካራ ቆሬ ቢቂላ መናፈሻ በሚባለው አካባቢ ለፍራሽ መስሪያ የሚሆኑ ግብአቶች በተከማቹበት መጋዘን ላይ የተነሳው እሳት በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።

የእሳት አደጋውን ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር የአደጋ ጊዜ ሰራተኞችና የጸጥታ አካላት እንዲሁም የአካባቢው ህብረተሰብ ርብርብ ማድረጋቸው ተጠቁሟል።

በዚህም እሳቱ በአቅራቢያው ወዳለው መስኪድ እንዲሁም ሌሎች የመኖሪያና ንግድ ቤቶች  እንዳይዛመት ማድረግ  መቻሉን ኮሚሽኑ ገልጿል።

በእሳት አደጋው በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት አለመኖሩንም ኮሚሽኑ ባወጣው መረጃ አስታውቋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በአዲስ አበባ አገልጋዮች ሞባይል ስልክ ይዘው ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዳይገቡ ተከለከሉ‼️

በኢኦተቤ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አገልጋዮች በቅዳሴና ለሌሎች መንፈሳዊ አገልግሎት ሰዓት ሞባይል ስልክ ይዘው ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዳይገቡ መከልከሉን አስታውቋል።

ሀገረ ስብከቱ ለሁሉም ገዳማትና አድባራት በላከው የመመሪያ ደብዳቤ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሚከናወኑ  የጸሎተ ቅዳሴና ሌሎች መንፈሳዊ አገልግሎቶች የእጅ ሞባይል ስልክ ይዞ መግባት በጥብቅ መከልከሉን ይገልጻል።

የገዳማትና አድባራት አስደዳሪዎችና ሰበካ ጉባኤያት ጥብቅ ክትትል በማድረግ መመሪያውን እንዲያስፈጽሙ ታዘዋል።

መረጃው ከሀገረ ስብከቱ ሚዲያ ክፍል የተገኘ ነው።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ኢትዮጵያ 2,500 ወታደሮችን በሶማሊያ እንድታሰማራ ከስምምነት ላይ መደረሱ ተገለጸ‼️

የአፍሪካ ህበረት እና የሶማሊያ ፌዴራል መንግስት፤ ኢትዮጵያ 2,500 ወታደሮቿን በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት የድጋፍ ተልዕኮ (አውሶም) ውስጥ እንድታካትት ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተገለጸ።

የአፍሪካ ህበረት እና ሶማሊያ ለአዲሱ ተልዕኮ ወታደር አውጭ ሀገሮች የሚያዋጡት የወታደሮች ቁጥር ላይ  ባደረጉት ውይይት፤ ኢትዮጵያ 2,500፣ ዩጋንዳ 4,500፣ ጅቡቱ 1,520፣ ኬንያ 1,410 እና ግብጽ 1,091 ወታደሮችን በሶማሊያ እንደሚያሰማሩ ከስምምነት ለይ መድረሳቸውን የአሜሪካ ድምጽ ዘግቧል።

በተጨማሪም ከናይጄሪያ፣ ከሴራሊዮን እና ከግብጽ የተወጣጡ በመቶዎች የሚቆጠሩ የፖሊስ መኮንኖች በሞቃዲሾ፣ በጆዋር እና በቢዶዋ ውስጥ እንደሚመደቡ ተገልጿል።

በ ቡሩንዲ ወታደሮች ቁጥር ላይ አለመግባባት በመፈጠሩ እ.ኤ.አ ከ2007 ጀምሮ በሶማሊያ የሚገኙት የቡሩንዲ ወታደሮች ከሀገሪቱ እንደሚወጡ ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ የአፍሪካ ህብረት ባለስልጣን ለቪኦኤ ተናግረዋል።

ወታደሮች፣ ፖሊሶች እና ሲቪል ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞችን ጨምሮ 11,900 ሰራተኞች በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት የድጋፍ ተልዕኮ (አውሶም) ውስጥ የሚሳተፉ መሆኑን ሶማሊያ እና የአፍሪካ ህብረት ባለስልጣናት መግለጻቸውን ዘገባው አመላክቷል።

የኢትዮጵያ ኃይሎች ቀድሞውኑ በነበሩበት በሶማሊያ ጌዶ፣ ባይ፣ ባኮል እና ሂራን ክልሎች ውስጥ ይሰፍራሉ የተባለ ሲሆን  ኢትዮጵያ በተለየ የሁለትዮሽ ስምምነት መሠረት ተጨማሪ ወታደሮችን በሶማሊያ ውስጥ ታሰማራለች ተብሏል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ባለፉት አስር ቀናት ብቻ ከ80 ኪሎ ሜትር በላይ የኮንዳክተር ሽቦ ገመድ ለስርቆት ተዳርጓል‼️

🗣የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል

ባለፉት አስር ቀናት በአዋሽ - ወልዲያ - ሃራ ገበያ የባቡር የኃይል አቅርቦት ፕሮጀክት ከ80 ኪሎ ሜትር በላይ የኮንዳክተር ሽቦ ገመድ እና 25 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር የኦ.ፒ.ጂ ደብሊው ፋይበር መስመር ለስርቆት መዳረጋቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ።

በአዋሽ - ወልዲያ - ሃራ ገበያ የባቡር የኃይል አቅርቦት ፕሮጀክት የሳይት ሥራ አስኪያጅ የሆኑት ተክለወይን ብርሃነአሰፋ እንደተናገሩት ባለፉት አስር ቀናት ከመተሃራ እስከ ባቡር ትራክሽን ጣቢያ አንድ ድረስ በቡድን በተደራጀ ሁኔታ 78 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር የኮንዳክተር ሽቦ እና 25 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር የኦፕቲካል ፋይበር መስመር ዝርፊያ ተፈጽሟል።

ከባቡር ትራክሽን ጣቢያ አንድ እስከ ባቡር ትራክሽን ጣቢያ ሁለት ድረስ ደግሞ 2 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር የኮንዳክተር ሽቦ ገመድ በዘራፊዎች መወሰዱንም ነው የጠቆሙት።

በአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ በዱዱብ እና ዶሆ ቀበሌዎች ሁለት ጊዜ እንዲሁም በዱለሳ ወረዳ በቡሩቱሊ እና ኢስኪለሊ ቀበሌዎች አንድ ጊዜ በተፈፀመ የስርቆት ወንጀል ሳቢያ ከ758 ሺህ ዶላር በላይ እና በብር ከ6 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር በላይ ኪሳራ መድረሱንም ተናግረዋል።

የስርቆት ወንጀሉ የተፈፀመው የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ወደ ሥራ እስኪገባ ድረስ በ33 እና 15 ኪሎ ቮልት በጊዜያዊነት ኃይል ይዞ እንዲቆይ ለማድረግ ከሥራ ተቋራጩ ጋር ምክክሮች እየተደረጉ ባሉበት ወቅት መሆኑም ተገልጿል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ሩሲያ በዩክሬን ካርኪቭ ክልል የሚገኝ መንደር ተቆጣጠርኩ አለች‼️

ዩክሬን በተለያዩ ግንባሮች ከሩሲያ ጋር ከባድ ውጊያ ላይ መሆኗን አስታውቃለች።

3 ዓመት የሞላውን ጦርነት ለማቆም ጥረቶች እየተደረጉ ባሉበት ሰዓት ውጊያው ተባብሶ ቀጥሏል።

የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር የሀገሪቱ ጦር በዩክሬን ካርኪቭ ክልል የሚገኝ መንደር መቆጣጠሩን አስታውቋል።

በ24 ሰዓታ ውስጥም የሩሲያ ኃይሎች ከዩክሬን ጦር በተለያዩ አቅጣጫዎች የተከፈተበትን ጥቃቶች መመከቱን ነው ሚኒስቴሩ ያስታወቀው።
በዛሬው እለትም በዩክሬን ወታደራዊ አየር ማረፊያ ላይ ጥቃት መፈፀሙን የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋ።

በዚህም የዩክሬን ሰው አልባ አውሮፕላን ማምረቻዎች መመታቸውን እና 905 የሚደርሱ የየዩክሬን ጦር አባላት መሞታውን ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

የዩክሬን መከላከያ ሚኒስቴር በበኩሉ ውጊው አሁን በተለያዩ ግንባሮች ተጠናክሮ ንደቀጠለ አስታውቋ።

የዩክሬን ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም እንደተናገሩት በትናንትናው እለት ብቻ በ69 የተለያዩ በግንባሮች ውጊያዎች መካሄዳቸው አስታውቀዋል

@Esat_tv1
@Esat_tv1


አሜሪካ በተመድ በዩክሬን ጦርነት ጉዳይ የቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ በመቃወም ሳትጠበቅ ሩስያን ደገፈች‼️

አሜሪካ በዩክሬንና አውሮፓውያን የሚደገፈውን የውሳኔ ሀሳብ በመቃወም ከረጅም ጊዜ አጋሮቿ ጋር ሆድና ጀርባ ሆናለች።

አሜሪካ በተመድ ጠቅላላ ጉባኤ በትናንትናው እለት የቀረበውን ሩሲያ በዩክሬን ላይ የፈጸመችውን "ወረራ" የሚያወግዝ የውሳኔ ሀሳብ በመቃወም ባልተጠበቀ ሁኔታ ለሩሲያ ድጋፏን አሳይታለች።

አሜሪካ በዩክሬንና አውሮፓውያን የሚደገፈውን የውሳኔ ሀሳብ በመቃወም ከረጅም ጊዜ አጋሮቿ ጋር ሆድና ጀርባ ሆናለች።

ሩሲያ በዩክሬን ላይ ልዩ ያለችው ወታደራዊ ዘመቻ የከፈተችበት ሶስተኛ አመት በትናንትናው እለት ታስቧል።

አሜሪካ በተመሳሳይ ትናንት ምሽት ሩሲያን እንደ ወራሪ የማያየውንና ለዩክሬን የግዛት አንድነት እውቅና የማይሰጠውን በአሜሪካ ድጋፍ የተዘጋጀውን በተመድ የጸጥታው ምክር ቤት የቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ በመደገፍ ከሩሲያ ጋር አንድ አይነት አቋም አንጸባርቃለች።

@Esat_tv1
@Esat_tv1

20 last posts shown.

238 780

subscribers
Channel statistics
Popular in the channel

ዶናልድ ትራምፕ የአፍሪካ መሪዎች ሰው መሆናቸውን እጠራጠራለሁ አሉ‼️ ከ50 ዓመታት የአህጉሪቷ የነጻነት ጉዞ በኋላ፣ ለህዝባችው አስፈላጊውን መሠረተ ልማ...
ሳዑዲ ኔታንያሁ ፍልስጤማውያንን በማፈናቀል ዙሪያ የሰጡትን አስተያየት ውድቅ አደረገች‼️ ኔታያሁ “በሳዑዲ ግዛቷ ላይ የፍልስጤም መንግስት መመስረት ትችላ...
የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት እንደሚቀጥል ተገለጸ‼️ የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበ...
በመጨረሻው ዙር የእስረኞች ልውውጥ እስራኤል 369 ፍልስጤማውያንን ከእስር ለቀቀች‼️ በእስራኤል እና ሀማስ የተኩስ አቁም ስምምነት መሰረት በመጨረሻው ዙ...
የፕሪቶሪያውን ስምምነት በሚመለከት በአፍሪካ ሕብረት ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተካሄደ‼️ በትግራይ ክልል የነበረውን ግጭት ያስቆመው የፕሪቶሪያው የሰላም ስም...