ESAT (ኢሳት🇪🇹)®


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot
🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ የነዳጅ ማደያዎች እለታዊ የነዳጅ አቅርቦት መጠንን ከትላንት ጀምሮ ይፋ ማድረግ ጀምሯል‼️

አሁን ላይ በከተማዋ 123 ማደያዎች ግልጋሎት እየሰጡ ነው ተብሏል።

ቢሮው ፤ " በየዕለቱ የነዋጅ ማደያዎችን እለታዊ የነዳጅ አቅርቦት መጠን ይፋ ማድረግ የተጀመረው በአገልግሎቱ ሂደት እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ እንዲሁም የተገልጋች እንግልት ለመቀነስ ነው " ብሏል።

ነዳጅ ማደያዎች የት ቦታ እንደሚገኙ እና በእለቱ የተራገፈው ነዳጅ መጠን እንዲሁም የጥቆማ ስርዓቱ ከላይ ተያይዟል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


[CREATINE MONOHYADRATE ]

ጡንቻን ለመገንባት እና ጉልበት ለማግኘት፤ ለሰውነትዎ የሚያስፈልገውን ይስጡት!

በፆም ወቅት የሚወሰድ!

ጥንካሬ፣ብርታት እና ፈጣን የሰዉነት ጥገና ያስፈልገኛል ብለዉ ካሰቡ ክሬቲን ይገባዎታል
👨🏾‍⚕️የዘርፉ ባለሙያዎች ጥናት እንደሚያሳየዉ ክሬቲን የሚጠቀሙ አትሌቶች እና ስፓርተኞች 23 % የተሻለ አፈጻጸም እና ጥገና ያሳያሉ!🏃‍♂️

ለነፃ የምክር አገልግሎት እና የተሟላ መረጃ ወደ ጥሪ ማእከላችን ይደውሉልን
☎️9369 ☎️

አድራሻ📍 አዳማ - ፖስታ ቤት ሶሬቲ ህንፃ ፊትለፊት ጀርመን ሲቲ ሞል 1ኛ ፎቅ ሱቅ ቁጥር 110

☎️ +251966113766 ☎️

Join https://t.me/+RCaZ_Ka6SOrlz0u5


🌻50% ቅናሽለ10 እድለኞች
አዲስ አበባ : ኢትዮጵያ
#ከ DMC Real estate.
በመሀል ከተማ ለቡ 
  በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው  B4  ለሽያጭ አቅርበናል::

ግንባታው ሙሉ በሙሉ በ አሉሚኒየም ፎርም ወርክ በመገንባት ላይ የሚገኙ
50% ባንክ የተመቻቸላቸው

8% ብቻ በመክፈል ቤትወን ይምረጡ
ማለትም 
    
💝💝💝አንድ መኝታ
        69ካሬ  =431,918ብር
        77.6ካሬ=485,751
💝💝💝ሁለት መኝታ👇👇
            99ካሬ=>619,708ብር
             104ካሬ=651,000ብር
💝💝💝ሶስት መኝታ👇👇
    👉139ካሬ=870,000ብር
      👉147.6ካሬ=923,928ብር
ብቻ በመክፈል ቤትወን ዛሬውኑ  ይምረጡ
ለሱቅ ፈላጊወች  ከ20 ከካሬ
ለበለጠ  መረጃ  
💚በ+251918642895
@Gashawkefie


ዛሬ ጠዋት ከኢራን ፕሬዚዳንት መስዑድ ፔዥሺካን ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርጌያለሁ። በውይይታችን ወቅት ኢትዮጵያ የመካከለኛው ምስራቅ ውጥረቶች የሚረግቡበት ሁኔታ ለማገዝ ዝግጁ መሆኗን ገልጫለሁ‼️

🗣ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

@Esat_tv1
@Esat_tv1


እስራኤል አዲሱን የሂዝቦላህ መሪ ሀሽም ሳፊይዲንን መግደሏን አረጋገጠች‼️

የእስራኤል መከላከያ ሃይል እንዳስታወቀው÷ የቀድሞው የሂዝቦላህ መሪ ሀሰን ናስራላህ የአጎት ልጅ የሆነው ሀሽም ሳፊይዲን ከሶስት ሳምንት በፊት እስራኤል በደቡባዊ ሊባኖስ በወሰደችው የአየር ጥቃት ተገድሏል።

ከሀሽም ሳፊይዲን በተጨማሪ የሂዝቦላህ ኢንተለጀንስ ዳይሬክቶሬት ሃላፊ አሊ ሁሴን ሃዚማ እና የቡድኑ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦች በጥቃቱ ተገድለዋል ተብሏል፡፡

በጉዳዩ ላይ ሂዝቦላህ የሰጠው ምላሽ አለመኖሩ ተገልጿል።
ቀደም ሲል በፈረንጆቹ ጥቅምት 8 ቀን 2024 የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታኒያሁ የእስራኤል መከላከያ ሀይል ሀሰን ሳፊይዲንን ጨምሮ በሺዎች የሚቆጠሩ የሂዝቦላህ መሪዎችና ታጣቂዎች መገደላቸውን ተናግረው ነበር።

በወቅቱም ሀሰን ነስራላህን በመተካት ወደ ሂዝቦላህ መሪነት የመጣው ሀሽም ሳፊይዲን ሳይገደል እንዳልቀረ እየተነገረ ነበር።

ይሁን እንጂ በእስራኤል ጥቃት የመሪውን መገደል የእስራኤል መከላከያ ሃይል አዛዥ ሌተና ጄኔራል ሄርዚ ሃሌቪ በሰጡት መግለጫ አረጋግጠዋል

@Esat_tv1
@Esat_tv1


የሞሪንጋ (ሽፈራው) ተክል በሕጻነት ላይ የሚከሰተውን የመቀንጨር ችግር እንደሚከላከል በጥናት መረጋገጡ ተገለጸ‼️

በኢትዮጵያ 'ሽፈራው' እየተባለ የሚጠራው የሞሪንጋ ተክል በሕጻነት ላይ የሚከሰተውን የመቀንጨር ችግር እንደሚከላከል በጥናት መረጋገጡ ተገልጿል፡፡ጥናት እና ምርምሩ ተግባራዊ እንዲሆን የጣሊያን መንግሥት፣ የተባበሩት መንግሥታት የኢንዲስትሪ ልማት ድርጅት እንዲሁም የአርባ ምንጭ ዩንቨርስቲ በጋራ የሰሩትን ፕሮጀክት ይፋ አድርገዋል፡፡

በአርባ ምንጭ ዩንቨርስቲ በምግብ ቴክኖሎጂና ባዮቴክኖሎጂ ተባባሪ ፕሮፌሰር አዲሱ ፍቃዱ፤ የሞሪንጋ ወይም የሽፈራው ተክል በሕጻነት ላይ የሚከሰተውን የመቀንጨር ችግር ጨምሮ ብዙ የጤና ጠቀሜታ እንዳለው በጥናት እና ምርምር መረጋገጡን ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

በተክሉ ውስጥ የተለያዩ ንጥረ ነገሮች የሚገኝበት በመሆኑ ከሌሎች ምግቦች ጋር በመቀላቀል በመጠቀም እንደሚቻል አንስተው፤ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፍ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶችንም ማስቀረት እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡

ፕሮጀክቱ በዋናነት ተግባራዊ የተደረገው ተክሉ በስፋት የሚበቅልበት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አርባ ምንጭ ከተማ ዘይሴ ቀበሌ ሲሆን፤ የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ገብረመስቀል ጫላ ከተክሉ የተለያዩ ምርቶች እንደሚገኝበት እና ዘርፍ ብዙ ጠቀሜዎች እንዳሉት ተናግረዋል፡፡

በተገኘው ጥናት እና ምርምር መሰረት፤ ተክሉ በብዙ መልኩ የሚቀነባበርበት የፋብሪካ ግንባታ ተጠቀናቆ የተለያዩ ማሽኖችም መግባታቻውን አሐዱ ማረጋገጥ ችሏል፡፡የተጀመረው ፕሮጀክት ተግባራዊ እንዲሆን ያሉትን የመሰረተ ልማት ችግር ለመቅረፍ ምን እየተሰራ ነው? ሲል አሐዱ ለክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ላነሳው ጥያቄም፤ የመንገድ እና የኤሌትሪክ አገልግሎት ችግሮች እንደሚፈቱም ተናግረዋል፡፡

በተባበሩት መንግሥታት የኢንደስትሪ ልማት ድርጅት ተወካይ እና የፕሮጀክቱ ቴክኒካል አማካሪ ዶክተር ለምለም ሲሳይ በበኩላቸው፤ በገጠር ላሉ ሴቶች የኑሮ ማሻሻያ ያስፈልጋል በሚል ከመንግሥት በቀረበው ጥያቄ መሰረት ፕሮጀክቱ ተግባራዊ መደረጉን አንስተው ከክልሉ መንግሥት ጋር በጋራ እንደተሰራም አስረድተዋል፡፡የሞሪንጋ ወይም የሽፈራው ተክልን አብዛኛው የኢትዮጵያ የማህበረሰብ ክፍሎች የተለያዩ የካንሰር አይነቶችን እና ደምግፊትን ጨምሮ ሌሎች በሽታዎችን ለመከላከል እንደሚጠቀሙበት የሚታወቅ ነው፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1




በመርካቶ ሸማ ተራ አካባቢ የደረሰውን የእሳት አደጋ መንስኤ እየመረመረ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ‼️

የአደጋውን መንስኤ ለማጣራት የአዲስ አበባ ፖሊስ ከፌዴራል ፖሊስ የፎረንሲክ ምርመራ ቡድን ጋር በመቀናጀት ምርመራ መጀመሩን አስታውቋል።

አደጋውን ለመከላከል እና በአደጋው ምክንያት ሌላ ወንጀል እንዳይፈፀም እንዲሁም የአደጋ ተከላከይ ሰራተኞች ተግባራቸውን በአግባቡ መወጣት እንዲችሉ እና ተጨማሪ ጉዳት እንዳያጋጥም የፌዴራል እና የአዲስ አበባ ፖሊስ፣ የመከላከያ ሠራዊት፣ ሪፐብሊካን ጋርድ፣ ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት፣ የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች፣ የሠላምና ፀጥታ መዋቅር፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ሌሎች ተቋማትም ከፍተኛ ርብርብ በማድረግ አደጋው እንዳይባባስ ከፍተኛ ጥረት ተደርጓል።

አደጋውን እንደ ምቹ ሁኔታ በመጠቀም የስርቆት ወንጀል የፈፀሙ 33 ተጠርጣሪዎችን ይዞ ምርመራ እያጣራ መሆኑን እና ከአደጋው ጋር በተያያዘ በ7 ሰዎች ቀላል በ2ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት መድረሱን ፖሊስ አስታውቋል፡፡

አደጋውን ለመከለከል የፀጥታና ሌሎች ተቋማት እንዲሁም የአካባቢው ህብረተሰብ ላደረገው ድጋፍና ተባባሪነት ፖሊስ ምስጋናውን አቅርቧል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ በደረው የእሳት አደጋ የተሰማውን ሃዘን ገልፆ ወደፊት በምርመራ የደረሰበትን ውጤት ለህዝብ እንሚያሳውቅም አስታውቋል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በአዲስ አበባ እየተካሔደ የሚገኘው 46ኛው የካፍ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ‼️

@Esat_tv1
@Esat_tv1


🌻50% ቅናሽለ10 እድለኞች
አዲስ አበባ : ኢትዮጵያ
#ከ DMC Real estate.
በመሀል ከተማ ለቡ 
  በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው  B4  ለሽያጭ አቅርበናል::

ግንባታው ሙሉ በሙሉ በ አሉሚኒየም ፎርም ወርክ በመገንባት ላይ የሚገኙ
50% ባንክ የተመቻቸላቸው

8% ብቻ በመክፈል ቤትወን ይምረጡ
ማለትም 
    
💝💝💝አንድ መኝታ
        69ካሬ  =431,918ብር
        77.6ካሬ=485,751
💝💝💝ሁለት መኝታ👇👇
            99ካሬ=>619,708ብር
             104ካሬ=651,000ብር
💝💝💝ሶስት መኝታ👇👇
    👉139ካሬ=870,000ብር
      👉147.6ካሬ=923,928ብር
ብቻ በመክፈል ቤትወን ዛሬውኑ  ይምረጡ
ለሱቅ ፈላጊወች  ከ20 ከካሬ
ለበለጠ  መረጃ  
💚በ+251918642895
@Gashawkefie


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
መርካቶ አሁናዊ ገፅታ‼️

@Esat_tv1


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
በመርካቶ ሸማ ተራ አከባቢ የተከሰተው የእሳት አደጋ አሁንም መቆጣጠር አልተቻለም‼️

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በመርካቶ ሸማ ተራ አከባቢ በተከሰተው የእሳት አደጋ በንብረት ላይ ለደረሰው ጉዳት እጅግ አዝነናል‼️

🗣 ከንቲባ አዳነች አቤቤ

የተከሰተውን የእሳት አደጋ ለመቆጣጠር ከእሳት አደጋ  እና ስጋት መከላከል እንዲሁም  ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመሆን ርብርብ እየተደረገ  ሲሆን አደጋውን ቶሎ ለመቆጣጠር እየተደረገ ያለዉን ጥረት  አዳጋች ያደረገዉ የአካባቢው መንገድ የእሳት አደጋ መኪና በተሟላ ሁኔታ ለመንቀሳቀስ አስቸጋሪ በመሆኑ ምክንያት በሄሊኮፕተር ለመጠቀም እየጣርን  ነው።  ይህንን አደጋ ለመቀነስ ርብርብ እያደረጋችሁ ያላችሁ አካላት ሁላ ጥረታችሁን አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ አሳስባለሁ።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በአዲስ አበባ መርካቶ ሸማ ተራ የተከሰተውን የእሳት አደጋ ለመቆጣጠር እየተሰራ ነው‼️

በአዲስ አበባ አዲስ ክ/ከተማ መርካቶ በተለምዶ ሸማ ተራ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የተከሰተውን የእሳት አደጋ ለመቆጣጠር እየተሰራ መሆኑን የከተማዋ የእሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ እንዳሉት÷እሳቱን በቁጥጥር ስር ለማዋል የእሳት የአደጋ መከላከያ ተሽከርካሪዎችና ባለሞያዎች በስፍራው ተሰማርተዋል፡፡

የእሳት አደጋውን መንስዔና ያደረሰውን ጉዳት ምርመራ ከተጣራ በኋላ እንደሚያሳውቁም ባለሞያው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1

14 last posts shown.