ESAT (ኢሳት🇪🇹)®


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot
🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹


Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


የጎንደር ከተማ የጸጥታ ሁኔታን አስመልክቶ የሚናፈሰው መረጃ ከእውነት የራቀ ነው‼️

🗣 ብርጋዴር ጄኔራል ማርዬ በየነ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በጎንደር ከተማ ያለውን የጸጥታ ሁኔታ አስመልክቶ በማህበራዊ ሚዲያ የሚናፈሰው መረጃ ፈጽሞ ከእውነት የራቀ መሆኑን የጎንደር ከተማ ኮማንድ ፖስት ሰብሳቢ ብርጋዴር ጄኔራል ማርዬ በየነ ገለጹ፡፡

ኮማንድ ፖስቱ ጽንፈኛ ቡድኑ ላይ እየወሰደ ካለው እርምጃ ባሻገር የከተማዋን ነዋሪዎች በማወያየት ባከናወነው ስራ የከተማዋ የሰላም ሁኔታ መሻሻሉን ተናግረዋል።

ጽንፈኛ ቡድኑ የኢትዮጵያን ህልውናና ሰላም ከማይፈልጉ አካላት የሚላክለትን ፍርፋሪ በመጠቀም ሰላማዊ ዜጎች ላይ ጥቃት የሚፈጽም የህዝብ ጠላት መሆኑን አብራርተዋል፡፡

ኮማንድ ፖስቱ ከህዝብ ጋር ባደረገው ውይይትም ህብረተሰቡ የጽንፈኛ ቡድኑን እኩይ ድርጊት በግልጽ ማንሳቱን ጠቅሰዋል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ከ450 ሺሕ ብር በላይ የሚገመት የኮንትሮባንድ እቃ በቁጥጥር ሥር ዋለ‼️

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ጋር በመቀናጀት ከ450 ሺሕ ብር በላይ የሚገመት ዋጋ ያላቸውን የኮንትሮባንድ ልባሽ ጨርቆችን እና በጉዳዩ የተጠረጠሩ አምስት ግለሰቦችን ከሁለት ተሽከርካሪዎች ጋር በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራባቸው እንደሚገኝ ገልጿል።

ተጠርጣሪዎቹ ሊያዙ ያቻሉት መነሻቸውን ሻሸመኔ ከተማ በማድረግ ወደ አዲስ አበባ ከተማ በመጓዝ ላይ እያሉ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ጋር ባደረጉት ክትትል መሆኑ ተመላክቷል፡፡

በዚህም የሰሌዳ ቁጥራቸው አ.አ ኮድ 3- A84787 እና A31581 በሆኑ ሁለት የጭነት ተሽከርካሪዎች በርካታ ልባሽ ጨርቆችን በድንች ስር ደብቀው በመጫን ሲጓዙ ጦር ኃይሎች አካባቢ እንደደረሱ በተደረገባቸው ድንገተኛ ፍተሻ ከነ-ኤግዚቢቱ በቁጥጥር ስር ሊውሉ መቻላቸውን የፌዴራል ፖሊስ መረጃ አመላክቷል::

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ለደመራ በዓል ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን ይፋ ሆኑ‼️

በነገው ዕለት በመስቀል አደባባይ በሚከበረው የደመራ በዓል ምክንያት ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ይፋ አድርጓል፡፡

በዚሁ መሠረት ነገ ከረፋዱ 5:00 ጀምሮ እስከ በዓሉ ፍፃሜ ድረስ፡-

➡️ከኡራዐል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኡራኤል አደባባይ ላይ

➡️ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ

➡️ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ ላይ

➡️ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ አጠገብ እንዲሁም ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር ላይ)

➡️ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት ላይ

➡️ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ

➡️ከራስ ሆቴል ወደ ስታድየም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል ላይ

➡️ከሃራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት ላይ

➡️ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ

➡️ከዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ከዛንቺስ ሼል አጠገብ እንዲሁም

➡️ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወሰደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ፡፡

አሽከርካሪዎች ይህን ተገንዝበው አማራጭ መንገዶችን በመጠቀምና የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚያሳዩአቸው መንገድ በመጓዝ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪውን አቅርቧል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በትራኮን ሪል እስቴት ላይ የደረሰውን የእሳት አደጋ ለመቆጣጠር አስር ሰዓት ወስዷል‼️

በአዲስ አበባ ከተማ ትላንት መስከረም 14 ቀን 2016 ዓ.ም ምሽት 1:05 ሰዓት ላይ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ ሀጫሉ ሁንዴሳ መንገድ ትራኮን ሪል እስቴት እየገነባ ባለዉ አፓርታማ  5ኛና 6ኛ ፎቅ ላይ የተነሳዉ የእሳት አደጋ ለሊት 10 ሰዓት በቁጥጥር ስር መዋሉን አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።

የእሳት አደጋው በሁለት ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት ሲያደርስ በንብረት ላይ ከባድ ጉዳት አድርሷል ተብሏል።

አደጋዉ የደረሰባቸዉ ሁለቱም  የእሳት አደጋ ሰራተኞች ሲሆኑ  አንደኛዉ ሰራተኛ እሳቱን በማጥፋት ሂደት ከህንጻዉ ላይ ወድቆ ከባድ ጉዳት የደረሰበት ሲሆን በአሁን ሰዓት በአለርት ሆስፒታል ህክምና እየተደረገለት ይገኛል።

የእሳት አደጋዉ  በአካባቢዉ ባሉ  መኖሪያ ቤቶች ተዛምቶ ተጨማሪ ጉዳት ሳያደርስ በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን  እሳቱን ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር 9 ሰዓት መፍጀቱ ተነግሯል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ዛሬ ምሽት ትራኮን ሪል እስቴት እያስገነባው በሚገኘው ህንፃ ላይ የተከሰተውን ከባድ እሳት ለማስቆም ርብርብ እየተደረገ ይገኛል‼️

ዛሬ መስከረም 14  ቀን 2016 ዓ.ም ምሽት 1:05 ሰዓት ላይ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ ልዪ ቦታዉ ሀጫሉ ጎዳና እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ ትራኮን ሪል እስቴት እየገነባ ባለዉ አፓርታማ 6 ኛ ፎቅ ላይ የተነሳዉን እሳት ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የእሳትና የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።

እሳቱ ተዛምቶ ተጨማሪ ጉዳት ሊያደርስ የሚችልበት ዕድል ማስቀረት መቻሉን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለብስራት ሬዲዮና ቲቪ ተናግረዋል። በአደጋዉ በሰዉ ላይ የደረሰ ምንም ጉዳት የለም።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ለሞተር ብስክሌተኞች፣ ለባለ አራት እግርና ባለሶስት እግር ባጃጅ አሽከርካሪዎች በሙሉ‼️

በአዲስ አበባ የምትገኙ የሞተር ብስክሌተኞች፣ የባለ አራት እግርና ባለሶስት እግር ባጃጅ አሽከርካሪዎች በሙሉ ከዛሬ መስከረም 14/2016 ዓ.ም ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ እስከ ማክሰኞ መስከረም 29/2016ዓ.ም እስከ ጠዋቱ 12:00 ድረስ ሞተር ብስክሌትን፣ የባለ አራት እግርና የባለሶስት እግር ባጃጅ ማሽከርከር ፍጹም የተከለከለ መሆኑን ቢሮው ያሳውቃል፡፡

ክልከላው የፀጥታ እና የትራፊክ ቁጥጥር የሚሰሩ አካላትን የማያካትት ሲሆን፤ ባለንብረቶችም ሆኑ አሽከርካሪዎች እስከ ተጠቀሰው ቀን ድረስ በትዕግስት እንዲጠብቁ ቢሮው እየገለፀ፤ ይህንን መልእክት በሚተላለፉ አካላት ላይ ጥብቅ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑንም ቢሮው ያሳስባል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ከአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ መምሪያ ዕዝ የተሰጠ ወቅታዊ መረጃ‼️

መስከረም 16 እና 17 የሚከበሩት የመውሊድ፣ የደመራና የመስቀል በዓላት በአማራ ክልል የሃይማኖቶቹ ሥርዓት በሚፈቅዱት መንገድ እንዲከበሩ ኮማንድ ፖስቱ እየሠራ ነው።

የሕዝብ ስብሰባዎች በአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጁ መከልከላቸው ይታወቃል። ይሄም ጽንፈኛና ዘራፊ ኃይሎች በሕዝብ ላይ ሊያደርሱት የሚችሉትን ጉዳት ለመቀነስ ታስቦ የተደረገ ነው። መስከረም 16 እና 17 የሚከበሩት ሃይማኖታዊ በዓላት የአደባባይ በዓላት በመሆናቸው ለበዓላቱ ሥነ ሥርዓት ሲባል የአደባባይ መሰባሰብን መፍቀድ አስፈልጓል።

በመሆኑም የሚከተሉት ትእዛዛት እንዲፈጸሙ የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ መምሪያ ዕዝ ያስታውቃል፦

1. እነዚህ መሰባሰቦች ለሃይማኖታዊ የበዓል አከባበር ሥነ ሥርዓት ብቻ የሚውሉ ናቸው።

2. የአደባባይ መሰባሰቦች የበዓላቱ አከባበር ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ብቻ የሚከናወኑ ናቸው።

3. በእነዚህ አከባበሮች ወቅት ለሕዝብ ደኅንነት ሲባል ከጸጥታ አካላት ጋር መተባበር ግዴታ ነው።

መስከረም 14 ቀን 2016 ዓ.ም
የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ መምሪያ ዕዝ

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ባለስልጣኑ የጉራጌ ባሕላዊ እሴቶችን በዩኔስኮ ለማስመዝገብ እየተሰራ መሆኑን ገለጸ‼️

የባለስልጣኑ ምክትል ዳይሬክተር ኤሊያስ ሽኩር÷ የጉራጌ ዞን በርካታ ባህላዊ፣ ተፈጥሮሯዊና ሰው ሰራሽ ሃብቶች መገኛ መሆኑን አውስተዋል፡፡

በዞኑ የጉራጌ ክትፎ አዘገጃጀት፣ ባሕላዊ የቤት አሰራር፣ የጉራጌ የመንደር (ጀፎረ) አሰራር፣ ባህላዊ የዳኝነት ስርዓት (ቂጫ) እና ሌሎች እሴቶች መኖራቸውን ተናግረዋል፡፡

የጉራጌ ዞንም እነዚህ የጉራጌ ባህላዊ እሴቶችን በዩኔስኮ እንዲመዘገቡ ለባለስልጣኑ ጥያቄ ማቅረቡን ነው የገለጹት፡፡

የኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለስልጣንም ጥያቄውን ተቀብሎ ባህላዊ እሴቶች በዩኔስኮ እንዲመዘገቡ በትኩረት እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።

የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ በበኩላቸው÷ መስቀል ሃይማኖታዊ በዓል ቢሆንም ጉራጌ ባህላዊና ሃይማኖታዊ በዓል አድርጎ እንደሚያከብረው አስረድተዋል።

ማህበረሰቡ በበዓሉ ወቅት የተጣላ ካለ እርቅ የሚፈጽምበት፣ የተራራቀ የሚገናኝበት፣ ወላጆች ልጆቻቸው የሚመርቁበት፣ ደስታቸው የሚገልጹበትና ሌሎች መልካም ተግባራት የሚከውኑበት ነው ብለዋል።

የመስቀል በዓል የጉራጌ ብሔር የመቻቻል፣ የአብሮነትና ማንነቱን የሚገለጽበት በመሆኑ ትውልዱ ይህንን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ መናገራቸውንም የዞኑ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በመስቀል ደመራ በዓል ላይ የተከለከሉ ተግባራት‼️

➡️የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተክርስቲያን አርማ የሌለበትን የትኛውንም ባንዲራ ይዞ መግባት አይፈቀድም።

➡️በዓሉ ሃይማኖታዊ በዓል እንጂ የንግድ በዓል ባለመሆኑ የተፈቀደ የቲሸርት ህትመት የለም።

➡️ርችት የቤተክርስቲያን ቀኖና የማይፈቅድ በመሆኑ መተኮስ አይቻልም።

➡️ከተፈቀደላቸው 10 ሺሕ የሰንበት ተማሪዎች ማደራጃ መምሪያ ከታቀፉ ወጣቶች ውጭ እንደማንኛውም ምዕመናን መምጣት እንጂ ዩኒፎርም ለብሰው ከበሮ እና ፅናፅል ይዞ ወደ መስቀል አደባባይ መምጣት አይቻልም።

➡️በበዓሉ ላይ የሚገኝ ሁሉም ሰው ይፈተሻል።

➡️በመላው አዲስ አበባ 2304 ደመራዎች ይደመራሉ የተባለ ሲሆን ሌሎቹን በሚረብሽ መልኩ ደመራዎችን መደመር አይቻልም።

ይህንን ተላልፈው በሚገኙት ላይ በጸጥታ አካላት ብቻ ሳይሆን በቤተክርስቲያኒቱም እርምጃ ይወሰዳል ተብሏል።

ይህም የተገለጸው የመስቀል ደመራ በዓልን በሰላም ማክበር በሚቻልበት ሁኔታ ዙሪያ የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ከአዲስ አበባ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጋር በመተባበር ባዘጋጁት መድረክ ላይ ነው።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


👨🏾‍⚕️🐠የአሳ ዘይት(ኦሜጋ -3 ፋቲ አሲድ)

የኦሜጋ -3 ቅባቶች ጠቀሜታ ዘርፈ ብዙ ቢሆንም አብዛኛዎቻችን በምንከተለዉ የአመጋገብ ስርአት በቀን የሚያስፈልገንን መጠን ማግኘት አንችልም። ስለዚህ በሰውነት ላይ የሚፈጥሩትን ጥቅም መገንዘብ ተገቢ ነው።

🔸 ለልብ ጤንነትን (የኮለስትሮል መጠንን እና የደም ግፊትን ይቆጣጠራል)
🔸 የአእምሮ ጤናን ይጠብቃል(ጭንቀትን፣ ድብርትን.. ይከላከላል)
🔸 የአይን ጤንነትን ይጠብቃል
🔸 የበሽታ መከላከል አቅምን ይጨምራል
🔸 የቆዳ ጤንነትን ይጠብቃል
🔸 ለነፍሰጡር ሴቶች ጠቃሚ ነው (ኦሜጋ 3 የተባለ ንጥረ ነገር ስለያዘ ለፅንሱ እድገት ጤነኛ እንዲሆን ያደርጋል)
🔸 ለሚያጠቡ ሴቶች (የልጆች እድገት ጤናማ እንዲሆን ያደርጋል)
🔸 የጉበት ስብን ይቀንሳል
🔸 ልጆች ፈጣን የዐዕምሮ ዕድገት እንዲኖራቸው እና ንቁ እንዲሆኑ ያደርጋል
🔸 የአጥንት ጤናን ይጠብቃል

☎️ +251966113766 ☎️
☎️  9369 ላይ ይደውሉ ☎️

📍አድራሻ:-   አዳማ ፖስታ ቤት ሶሬቲ ህንፃ ፊትለፊት ጀርመን ሲቲ ሞል 1ኛ ፎቅ ሱቅ ቁጥር 110📍

Join  https://t.me/+RCaZ_Ka6SOrlz0u5


የድህረ ምረቃ ተፈታኞች የምዝገባ ጊዜ ተራዝሟል‼️

የድህረ ምረቃ ተፈታኞች አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ባዘጋጀው የGAT መመዝገቢያ ፖርታል https://portal.aau.edu.et ላይ ምዝገባ የሚያደርጉበት ጊዜ ተራዝሟል።

ትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ ለሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በላከው መልዕክት በGAT ፖርታሉ ላይ የተፈታኞች ምዝገባ የሚከናወነው ከመስከረም 21 እስከ 25/2016 ዓ.ም ድረስ በበይነ-መረብ መሆኑ ተገልጿል።

የመግቢያ ፈተና መስከረም 28 እና 29/2016 ዓ.ም በሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በበይነ-መረብ ይሰጣል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


የድህረ ምረቃ የመግቢያ ፈተና ከመስከረም 21 - መስከረም 23 ድረስ በኦንላይን እንደሚሰጥ ይታወቃል‼️

ትምህርት ሚኒስቴር ባስተላለፈው መመሪያ መሠረት በ2016 ትምህርት ዘመን የድኅረ ምረቃ ትምህርት ለመከታተል ተፈታኞች በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተዘጋጀው Graduate Admission Testing (GAT) የመመዝገቢያ ፖርታል https://portal.aau.edu.et ከዛሬ መስከረም 11 ጀምሮ እስከ መስከረም 20 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ማመልከት ይገባቸዋል።

ይህ ተከትሎ የመግቢያ ፈተና ከመስከረም 21 እስከ 23/2016 ዓ.ም በሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በበይነ-መረብ ይሰጣል።

የማለፊያው ነጥብ የሚወሰነው በትምህርት ሚኒስቴር ሲሆን ተፈታኞች ፈተናቸውን ሲጨርሱ ወዲያውኑ ማየት ይችላሉ።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ፈተናውን 98.6 በመቶ ተማሪዎች አልፈዋል‼️

በትግራይ የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች 98.6 ከመቶ ወደ ቀጣዩ ክፍል ማለፋቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታውቋል።

ኮሮና ተከትሎ በትግራይ በተካሄደው ጦርነት ተቋርጦ የነበረው የመማርና የማስተማር ሂደት ከሚያዝያ 2015 ዓ.ም ጀምሮ በተሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርት በመውሰድ የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና የተፈተኑ ተማሪዎች ውጤታቸዉ ይፋ ሆኗል።

በትግራይ ትምህርት ቢሮ የትምህርት ጥራትና ምዘና ኤጀንሲ ዳይሬክተር ዳይሬክቶሬት አቶ ክንፈ ፍስሃ  ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ከተፈታኞቹ 98.6 በመቶ ወደ ቀጣይ ክፍል ተሸጋገረዋል።  

የነበረውን ክፍተት ለሞምላት የተሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርት በቂ ባለመሆኑ በ2016 ዓ.ም ለ9ኛ ክፍል ተማሪዎች በሚሰጠው ትምህርት ፤ ሁሉም መምህራንና የሚመለከታቸው አካላት ልዩ ትኩረት በመስጠት ተማሪዎቹ ለማብቃት ጥረት ማድረግ አለባቸው ብለዋል ዳይሬክተሩ። 

በተያያዘ በክልሉ ትምህርት ቢሮና የፌደራል መንግስት ቅንጅት ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑንና አገር አቀፍ ፈተና ከመስከረም 29 እስከ ጥቅምት 2/2016 ዓ.ም እንደሚወስዱ ከትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ከ300 በላይ የአልሸባብ ታጣቂዎች ተደመሰሱ ‼️

ከ300 በላይ የአልሸባብ ታጣቂዎች ሲደመሰሱ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው አባላቱ መቁሰላቸውን የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት አስታወቀ።

በሶማሊያ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ሠላም አሥከባሪ ሃይል ለመቀየር ተልዕኮ ወደ ሚፈፀምበት ቦታ በተንቀሳቀሰው የኢትዮጵያ ሠራዊት ላይ ጠላት ቀድሞ ባገኘው መረጃ መሠረት ደፈጣ ይዞ ጥቃት ለመሠንዘር የሞከረው አልሸባብ ባላሠበው መልኩ ክፉኛ መመታቱ ተገልጿል።

በተሳሳተ ስሌት የኢትዮጵያ ሠላም አሥከባሪ ቅይይር ላይ ጥቃት ለማድረስ የሞከረው የአልሸባብ ሃይል ከ300 በላይ ታጣቂዎቹ ሲገደሉ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው አባላቱም ቆስለዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የ2016 የተማሪ ቅበላ በነባሩ ስርዓት እንደሚቀጥል ገለጸ‼️

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የ2016 የተማሪ ቅበላ በነባሩ ስርዓት የሚቀጥል መሆኑንና አዲስ አሰራሮች ከመጡ በየጊዜው እንደሚያሳውቅ የዩኒቨርሲቲው ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ገለጹ።

ዶክተር ሳሙኤል በዩኒቨርሲቲው እየተከናወኑ ያሉ የሪፎርም ስራዎችን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሀን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

በዚህም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝነት ታውጆ ወደ ስራ መገባቱንና፤ የሽግግሩን ሂደት የሚመሩ አመራሮች መመደባቸውንም ገልጸዋል።

አዲሱ አመራር ከመስከረም ሁለት ጀምሮ ወደ ስራ መግባቱን የገለጹት ዶክተር ሳሙኤል፤ በተደረጉ ጉብኝቶችና ውይይቶችም ብዙ ጉድለቶችን መመልከት መቻሉን አስረድተዋል።

በውይይቶቹም በአግባቡ ለመስራት ከስምምነት ላይ መደረሱን እና የሽግግር ሂደቱ የሚመራበት እቅድ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል።

የሽግግር ሂደቱ እስኪጠናቀቅ ድረስም ነባር አሰራሮች ባሉበት እየቀጠሉ የሚተኩ አሰራሮችን በየጊዜው የማሳወቅ ስራዎች ይሰራሉ ብለዋል።

በጊዜያዊነት የሽግግር ሂደቱን የሚመሩ አመራሮች ስራቸውን እንዳጠናቀቁ በዓለም አቀፍ መስፈርቶች ለሚመረጠው አመራር ኃላፊነታቸውን ያስረክባሉ ማለታቸውንም ኢዜአ ዘግቧል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በፀጥታ ችግር ምክንያት የተቋረጠውን ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች ወደ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ገቡ‼️

በፀጥታ ችግር ምክንያት የተቋረጠውን ፈተና የሚወስዱ ከ11 ሺህ 581 በላይ ተማሪዎችን በተረጋጋ መልኩ ለማስፈተን ዝግጅት ማድረጉን ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ገለጸ፡፡የጎንደር ከተማ አሥተዳደር ትምህርት መምሪያ ኀላፊ አቶ ዳንኤል ውበት 3 ሺህ 134 ፈተናውን የሚወስዱ ተማሪዎች መኖራቸውን ገልጸዋል። ለተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት ሲሰጥ መቆየቱን ተናግረዋል።

የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ትምህርት መምሪያ ኀላፊ አቶ ክንዱ ዘውዱ ተማሪዎች ዝግጅት እንዲያደርጉ ቀደም ብሎ መሠራቱን ገልጸዋል። ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ በሚጓዙበት ወቅት የመጓጓዣ ኹኔታ ምቹ እንዲኾን መሠራቱንም አመላክተዋል። በዞኑ 6 ሺህ 119 ተፈታኝ ተማሪዎች መኖራቸውን ኀላፊው አንስተዋል።

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የአሥተዳደር እና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ልጅዓለም ጋሻው በሶስት ዞኖችና በጎንደር ከተማ የሚገኙ ከ11 ሺህ 581 በላይ ተማሪዎች ፈተናቸውን እንዲያጠናቅቁ ዩኒቨርሲቲው በቂ ዝግጅት ማድረጉን ገልጸል ሲል አሚኮ ዘግቧል።ተፈታኝ ተማሪዎች በፀጥታ ችግር ምክንያት ፈተናቸውን ማጠናቀቅ አለመቻላቸውን በማስታወስ በአሁኑ ወቅት ፈተናውን ለመውሰድ ሙሉ ዝግጅት ማድረጋቸውን ተናግረዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በትግራይ ክልል ነገ መደበኛ ትምህርት ይጀመራል‼️

የ2016 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሂደት ነገ እንደሚጀመር የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አስታወቀ፡፡

የ2016 የትምህርት ዘመንን ነገ ለማስጀመር ለትምህርት ማሕበረሰቡ ሥልጠና መስጠትን ጨምሮ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን ነው ቢሮው ያስታወቀው፡፡

በዚህም ባለፉት 5 ቀናት ለመምህራን እና ለትምህርት ባለሙያዎች ሲሰጥ የቆየው ስልጠና መጠናቀቁን ነው የገለጸው፡፡

ስልጠናው እንዲሳካ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላትም ቢሮው ምስጋና አቅርቧል፡፡በትምህርት ቁሳቁስ እጥረት ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጭ እንዳይሆኑ በየአካባቢው የሚደረጉ ድጋፎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ቢሮው ጥሪ አቀርቧል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1


💪Ethio Fitness & Nutrition 💪

አላማችን ቢለያይም ለምንፈልገዉ ነገር ጠንክረን መስራታችን አንድ ያደርገናል። ጤናማ የአኗኗር ዘይቤ ለመከተል በሚያደርጉት ጉዞ እኛ ሁሌም ከጐንዎ ነን‼️

የሰውነት ክብደትን ጤናማ በሆነ መንገድ ለመጨመር እንዲሁም ለመቀነስ የሚረዱ።

👉Platinum Mass (1kg, 2.27kg, 4.54kg)
👉 Whey Core Protein(908gm, 2.27kg, 5Kg)
👉Creatine Monohydrate 300gm
👉 Hyperrush Pre-workout 380gm
👉 Omega 3(60, 120caps)
👉 Immune Shield 90 Caps
👉BCAA 504
g

🇪🇺 ሁሉም ምርቶቻችን ጥራታቸው ተጠብቆ በአውሮፓና በአሜሪካ የተመረቱ ናቸው  🇺🇸

☎️ +251966113766 ☎️
☎️  9369 ላይ ይደውሉ ☎️

📍አድራሻ:-   አዳማ ፖስታ ቤት ሶሬቲ ህንፃ ፊትለፊት ጀርመን ሲቲ ሞል 1ኛ ፎቅ ሱቅ ቁጥር 110📍

Join https://t.me/+RCaZ_Ka6SOrlz0u5


የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ በዩኔስኮ በዓለም ቅርስነት ተመዘገበ‼️

የዓለም ቅርስ ኮሚቴ በኦሮሚያ ክልል የሚገኘው የባሌ ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በዓለም ቅርስነት እንዲመዘገብ ውሳኔ አሳልፏል።

የባሌ ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ በቅርስነት የተመዘገበው በኢትዮጰያ ሁለተኛው ታላቅ የተፈጥሮ ቅርስ ሆኖ ሲሆን በዓለም ደግሞ 11ኛው ቅርስ በመሆን ነው።

45ኛው የአለም የቅርስ ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ ሁለት ታላለቅ የቱሪስት መዳረሻዎችን በአለም ቅርስነት ማስመዝገቧን የቱሪዝም ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በትግራይ ክልል ተቋርጦ የቆየው የ12ኛ ክፍል ፈተና ከመስከረም 29 ጀምሮ ይሰጣል‼️

በትግራይ ክልል ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ ተቋርጦ የቆየው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከፊታችን መስከረም 29 ቀን ጀምሮ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና የፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል፡፡

አገልግሎቱ የፈተና አሰጣጡን አስመልክቶ ከፌደራል ፖሊስ ሃላፊዎችና ከክልሉ የፈተና አስፈጻሚዎች ጋር ውይይት አካሂዷል፡፡

በክልሉ ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ ተቋርጦ የቆየውን የ12ኛ ክፍል ፈተና ለማስቀጠል በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን የአገልግሎቱ ም/ዋና ዳይሬክተር ይልቃል ወንድሜነህ ተናግረዋል፡፡

ፈተናውን በሶስት ዙር ለመስጠት መታቀዱን ጠቁመው÷የመጀመሪያው ዙር ፈተና (የ2012 ዓ.ም) ከመስከረም 29 እስከ ጥቅምት 2 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ገልጸዋል፡፡

የተፈታኝ ተማሪዎች ምዝገባ ከመስከረም 8 እስከ 12 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ባሉት ቀናት እንደሚከናወን መገለጹንም የአገልግሎቱ መረጃ ያመላክታል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1

20 last posts shown.