ESAT (ኢሳት🇪🇹)®


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot
🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


የብልፅግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳል‼️

የብልፅግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ከዛሬ ጀምሮ ለሦስት ቀናት ይካሄዳል፡፡

‘ከቃል እስከ ባህል’ በሚል መሪ ሐሳብ በሚካሄደው በዚህ ጉባኤ ላይ በርካታ ውሳኔዎች እና ወሳኝ አቅጣጫዎች እንደሚተላለፉ ይጠበቃል፡፡

በጉባኤው ላይ ከፓርቲው አባላት እና አመራሮች በተጨማሪ የጎረቤት እና የብሪክስ አባል ሀገራት እህት ፓርቲዎች እንደሚሳተፉም ተገልጿል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1


መኪና ለመግዛት ወይም ለመሸጥ ከፈለጉ ያለምንም ክፍያ
ይህንን የቴሌግራም መተግበሪያ ይቀላቀላሉ።

📌 📍.. THE EASIEST PLACE TO SELL AND BUY CARS

📌 📍.. VERY RELIABLE AGENT

📌 📍.. FULLY TRUSTWORTHY


📌.. ALL YOU NEED TO DO IS JOIN OUR TELEGRAM CHANNEL

https://t.me/Poppycarmarket

☎️ 0911407105   👈 ይደውሉልን


ቁርአንን ያቃጠለው ግለሰብ በስዊድን ተገደለ‼️

ቁርአንን ካቃጠለ በኋላ ከፍተኛ ተቃውሞ እንዲነሳ ያደረገው ስዊድን ግለሰብ በጥይት ተመትቶ መሞቱን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። የ38 ዓመቱ ሳልዋን ሞሚካ ረቡዕ ማምሻውን በሶደርትልጄ ስቶክሆልም ውስጥ ባለ አፓርታማ ውስጥ መገደሉ ተዘግቧል።

እ.ኤ.አ. በ2023 ሞሚካ የእስልምና ቅዱስ መጽሐፍን ከስቶክሆልም ማእከላዊ መስጊድ በራፍ ላይ ካቃጠለ በኋላ አለመረጋጋት ተፈጥሯል። የስቶክሆልም ፖሊስ ባወጣው መግለጫ በ40ዎቹ ዕድሜ ውስጥ የሚገኝ አንድ ሰው በፈፀሙው ጥቃት መገደሉን እና በጥይት ከግድያው ጋር በተያያዘ አምስት ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቋል።

ሞሚካ በተተኮሰበት ወቅት በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በቀጥታ ስርጭት ላይ እንደነበር የሀገር ውስጥ ሚዲያዎች ዘግበዋል። በስዊድን የሚኖረው እና የዘር ሀረጉ ከኢራቅ የሚመዘዘው ሞሚካ በ2023 ክረምት ለአራት ጊዜያት በአንድ ጎሳ ላይ ቅስቀሳ በማድረግ በነሀሴ ወር ክስ ቀርቦበታል። የስቶክሆልም አውራጃ ፍርድ ቤት ሀሙስ ሊሰጥ የነበረው ብይን "ከተከሳሾቹ አንዱ መሞቱ ከተረጋገጠ በኋላ ለሌላ ጊዜ ተላልፏል" ብሏል። ሞሚካ ተከታታይ ፀረ እስልምና ተቃውሞዎችን በማካሄድ በብዙ ሀገራት ቁጣ ቀስቅሷል።

በባግዳድ በሚገኘው የስዊድን ኤምባሲ ሁለት ጊዜ አለመረጋጋት የተፈጠረ ሲሆን የስዊድን አምባሳደር በዲፕሎማሲያዊ ውዝግብ ከከተማዋ ተባረዋል። የስዊድን ፖሊስ ሞሚካ ቅዱስ መጽሃፉን ያቃጠለበት የተቃውሞ ሰልፍ በሀገሪቱ በነጻ የመናገር ህግ መሰረት ነው ሲል ተጠያቂ አለማድረጉ ቁጣን አስከትሎ ነበር። መንግስት በኋላ በተወሰኑ ሁኔታዎች ላይ ቅዱስ መፅሃፍን ማቃጠልን የሚያካትቱ ተቃውሞዎችን ለማስወገድ ህጋዊ መንገዶችን ለመፈለግ ቃል ገብቶ ነበር።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ቀሲስ በላይ መኮንን በ5 ዓመት ጽኑ እስራትና በ10 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ተቀጡ‼️

የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በእነ ቀሲስ በላይ መኮንን መዝገብ ላይ የቀረቡ የግራ ቀኝ ማስረጃዎችን መርምሮ በዛሬው የችሎት ቀጠሮ በጽኑ እስራትና በገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወሰነ።

የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በተከሳሾች ቀሲስ በላይ መኮንን፣ በግብርና ኢንቨስትመንት ላይ የተሰማራው እያሱ እንዳለ፣ በኮሚሽን ስራ ላይ የተሰማራው በረከት ሙላቱ እና አለምገና ሳሙኤል እንዲሁም የኒሞና ንግድ ስራ ኃላ/የተ/የግል ማህበር ስራ አስኪያጅ አበራ መርጋ በተባሉ ተከሳሾች ላይ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ ቁጥር 32 ንዑስ ቁጥር 1 (ሀ) እና የሙስና ወንጀሎች ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 32 ንዑስ ቁጥር 2 እና ንዑስ ቁጥር 3 ስር የተመለከተውን ድንጋጌ እና በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ ቁጥር 382 ንዑስ ቁጥር 1 ስር የተመለከተውን ድንጋጌ መተላለፋቸውን ጠቅሶ ዝርዝር ክስ አቅርቦባቸው ነበር።

በዚህም ተከሳሾቹ ከአፍሪካ ህብረት ምንም አይነት የክፍያ ትዕዛዝ ባልተሰጠበት ሁኔታ ላይ ተከሳሾች በተለያየ መጠን ክፍያ እንዲፈጸምላቸው የሚል አጠቃላይ የ6 ሚሊየን 50 ሺህ ዶላር ሀሰተኛ የክፍያ ሰነድ በአንደኛ ተከሳሽ አማካኝነት ለባንኩ መቅረቡ ተጠቅሶ በሁሉም ተከሳሾች ላይ ከባድ የማታለል ሙስና ወንጀል ክስ ማቅረቡ ይታወሳል።

በዚህ መልኩ የቀረበውን ዝርዝር ክስ ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት ተከሳሾች ብቻ ችሎት ቀርበው የክስ ዝርዝሩ እንዲደርሳቸው የተደረገ ሲሆን 4ኛ እና 5ኛ ተከሳሾች በአድራሻቸው ባለመገኘታቸውና በተደጋጋሚ ቀጠሮ ባለመቅረባቸው ለጊዜው ክሳቸው እንዲቋረጥ ተደርጓል።

ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱ ተከሳሾች ክሱ እንዲሻሻልላቸው ያቀረቡት የመጀመሪያ ደረጃ ክስ መቃወሚያ ነጥቦችን ፍርድ ቤቱ መርምሮ ወደፊት በማስረጃ የሚጣራ መሆኑን ገልጾ መቃወሚያቸውን አልተቀበለውም።

ከዚህም በኋላ ተከሳሾቹ በክሱ ላይ የተጠቀሰውን የወንጀል ድርጊት አለመፈጸማቸውን ጠቅሰው የዕምነት ክህደት ቃል መስጠታቸውን ተከትሎ ዐቃቤ ሕግ አጠቃላይ ሶስት ምስክሮችን አቅርቦ ምስክርነታቸውን አሰምቶ ነበር።

ፍርድ ቤቱ የምስክሮችን ቃል መርምሮ በክሱ ዝርዝር የተጠቀሰው የወንጀል ድርጊት መፈጸሙን በዐቃቤ ሕግ በማስረጃ ማረጋገጡን ጠቅሶ በአንደኛው ክስ ብቻ እንዲከላከሉ በሙሉ ድምጽ ብይን ሰጥቶ ነበር።

ሁለተኛውን ክስ በሚመለከት በሐሰተኛ ሰነድ የተፈጸመ ድርጊት መሆኑ በአንደኛውን ክስ ላይ መገለጹን ተከትሎ በሰበር ሰሚ ችሎት ትርጉም የተሰጠባቸው በተደራራቢነት የቀረቡና ተጠቃልለው ሊያስቀጡ የሚችሉ ድንጋጌዎች መኖራቸውን ፍርድ ቤቱ አብራርቶ ሁለተኛውን ክስ ውድቅ በማድረግ በአንደኛው ክስ ብቻ በከባድ አታላይነት ሙስና ወንጀል እንዲከላከሉ ብይን ሰጥቷል።

ሆኖም ተከሳሾቹ እንዲከላከሉ በሰጠው ብይን የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በተገቢው ማስተባበል አለመቻላቸው ተጠቅሷል።

በዚህም 1ኛ ተከሳሽ ቀሲስ በላይ መኮንን በሙሉ ድምጽ የጥፋተኝነት ፍርድ የተሰጠባቸው ሲሆን፤ 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች በአንድ ዳኛ የሀሳብ ልዩነት በአብላጫ ድምጽ ጥፋተኛ ተብለዋል።

የሀሳብ ልዩነት ያቀረቡት አንደኛው ዳኛ 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾችን በሚመለከት የባንክ ሂሳባቸው በመገለጹ ብቻ የወንጀል ተግባሩ በስምምነት ተፈጽሟል ለማለት አያስችልም የሚል የሀሳብ ልዩነት እንዳላቸው ጠቅሰው ልዩነታቸውን አሳይተዋል።

ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየት መርምሮ ዐቃቤ ሕግ ወንጀሉ የተፈጸመው በትብብር መሆኑን ጠቅሶ ያቀረበውን የቅጣት ማክበጃ ይዟል።

በዚህም1ኛ ተከሳሽ ቀሲስ በላይ መኮንን ያቀረቡትን አራት የቅጣት ማቅለያ በመያዝ በዕርከን 21 መሰረት በ5 ዓመት ጽኑ እስራትና በ10 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወስኗል።

2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾችን በሚመለከት ደግሞ እያንዳንዳቸው አራት፣ አራት የቅጣት ማቅለያ አስተያየት በመያዝ በዕርከን 17 መሰረት በ3 ዓመት ከ3 ወር ጽኑ እስራትና በ3 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወስኗል።

በፍርድ ቤቱ በተከሳሾች ላይ የተወሰነውን የጽኑ እስራት ውሳኔን የአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት እጃቸው ከተያዘ ጀምሮ ታሳቢ በማድረግ እንዲያስፈጽም ታዟል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1




የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ከቀጣይ ዓመት ጀምሮ የተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምርጫ ውስጥ ይገባል‼️

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ከቀጣይ ዓመት ጀምሮ የተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምርጫ ውስጥ እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ገልጸዋል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር ዩኒቨርሲቲው እያከናወናቸው ለሚገኙ የለውጥ ሥራዎች ድጋፍ እንደሚደረግም ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ብርጋዲየር ጀኔራል ከበደ ረጋሣ በበኩላቸው ፤ ዩኒቨርሲቲው ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የሚመጥን በቂ ዕውቀት ያለው የሰው ኃይል ለማፍራት እየሰራ መሆኑን አንስተዋል፡፡

የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች በዩኒቨርሲቲው ጉብኝት ማድረጋቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በአማራ ክልል ወራት ያስቆጠረውን መንግሥት እያካሄደ ያለውን 'የዘፈቀደ የጅምላ እስር ዘመቻ' ለማስቆም ዓለም አቀፍ ጫና እንዲደረግ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቱ አምነስቲ ኢንተርናሽናል ጠየቀ‼️

ድርጅቱ መንግሥት እያካሄደው ያለው የዘፈቀደ የጅምላ እስር አራት ወራትን እንዳስቆጠረ በገለጸበት በጥር 20/ 2017 ዓ.ም. መግለጫው በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች በእስር ላይ እንዳሉ አስታውሷል።

"በአማራ ክልል በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በዘፈቀደ በጅምላ ታስረው ዓለም አቀፉ ዝምታን መምረጡ ከማሳፈር በላይ ነው።

የኢትዮጵያ የልማት አጋሮች እንዲሁም የአፍሪካ እና የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች በዘፈቀደ የታሰሩ ዜጎች በሙሉ እንዲፈቱ ያላቸውን ተጽዕኖ በመጠቀም በይፋ ጥሪ ሊያደርጉ ይገባል" ሲሉ የአምነስቲ የምሥራቅ እና የደቡብ አፍሪካ ቀጣና ዳይሬክተር ቲገሬ ቻጉታህ ጥሪ አቅርበዋል።

ዳይሬክተሩ አክለውም "የኢትዮጵያ መንግሥት የሕግ የበላይነትን እየተላለፈ ባለበት በዚህ ወቅት ዓለም አቀፉ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ ቀውስን በቸልታ ሊመለከተው አይገባም" ብለዋል።

ቻጉታህ አክለውም በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ያለ ክስ እና ያለ ፍርድ ቤት እውቅና ለወራት ታስረው መቆየታቸው ተቀባይነት እንደሌለው በዚሁ መግለጫቸው ጠቅሰዋል።

"በሺዎች የሚቆጠሩ ግለሰቦችን ክስ ሳይመሰረትባቸው እንዲሁም ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ለወራት አስሮ ማቆየት የፍትህ መጓደል እንዲሁም ግልጽ የሆነ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ነው" ሲሉ ዳይሬክተሩ ተችተዋል።

በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ያለምንም ሕጋዊ መሠረት መታሰራቸው ብቻ ሳይሆን ባለሥልጣናቱ በአማራ ክልል በዘፈቀደ የሚያደርጉትን እስር መቀጠላቸውንም አመልክተዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


መኪና ለመግዛት ወይም ለመሸጥ ከፈለጉ ያለምንም ክፍያ
ይህንን የቴሌግራም መተግበሪያ ይቀላቀላሉ።

📌 📍.. THE EASIEST PLACE TO SELL AND BUY CARS

📌 📍.. VERY RELIABLE AGENT

📌 📍.. FULLY TRUSTWORTHY


📌.. ALL YOU NEED TO DO IS JOIN OUR TELEGRAM CHANNEL

https://t.me/Poppycarmarket

☎️ 0911407105   👈 ይደውሉልን


በኢትዮ ጅቡቲ ባቡር መስመር ለመጓዝ ፋይዳ መታወቂያ ማቅረብ ግዴታ ሊሆን ነው‼️

የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር አክሲዮን ማህበር ከየካቲት 2017 አ.ም  ጀምሮ በኢትዮ ጅቡቲ ባቡር መስመር ለመጓዝ ተጓዦች ፋይዳ መታወቂያ ማቅረብ እንዳለባቸው አስታውቋል።

ዋና ስራ አስፈፃሚው ኢንጂነር ታከለ ኡማ ከየካቲት 2017 ጀምሮ በኦንላይን ቦታ በማስያዝ የህዝብ መንገደኞች ትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ነው የገለጹት።

በዚህም ጥራት ያለዉና እና ቀልጣፋ የጉዞ አገልግሎት  ለመስጠት፣ ትክክለኛ የመንገደኛ መረጃን ለማረጋገጥ እና ከችግር የጸዳ ጉዞን ለማመቻቸት እንዲሁም የሀገር ውስጥ ተሳፋሪዎች ቦታ ለመያዝም ሆነ ለመጓዝ ብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) ማቅረብ በመስፈርትነት መቀመጡን ነው ያስታወቁት።

በኢትዮ ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት ባለፉት 6 ወራት 165 ሺህ 639 መንገደኞችንና 934 ሺህ ቶን ጭነት ማጓጓዝ መቻሉን የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር መረጃ ያሳያል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


የአክሱም ከተማ ፍርድ ቤት፣ ሒጃብ በለበሱ ሴት ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ መከልከል ዙሪያ ካሁን ቀደም ያስተላለፈውን የእግድ ትዕዛዝ ያልተቀበሉ ትምህርት ቤቶች ርዕሰ መምህራን የካቲት 7 ቀን በፖሊስ ተይዘው እንዲቀርቡ ትናንት ማዘዣ ማውጣቱን የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ቢሮ አስታውቋል‼️

ፍርድ ቤቱ በፖሊስ ተይዘው እንዲቀርቡ ትዕዛዝ ያወጣባቸው፣ አምስት ትምህርት ቤቶች ናቸው። ፍርድ ቤቱ፣ የአክሱም ከተማ ትምህርት ቤቶች በሙስሊም ሴት ተማሪዎች ላይ ሒጃብ በመልበሳቸው ሳቢያ የጣሉትን እገዳ ቀደም ሲል ማገዱ ይታወሳል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ኢትዮጵያ ከጣሊያን መንግሥት የ585 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አገኘች‼️

ኢትዮጵያ ለጀመረችው የዲጂታል ሽግግርና ፈጠራን መሰረት ያደረገ የኢኮኖሚ እድገት ከጣሊያን መንግሥት የ585 ሚሊየን ብር ድጋፍ አገኘች።

የድጋፍ ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ እና የጣልያን የከፍተኛ ትምህርት እና ምርምር ሚኒስትር አና ማሪያ ፈርመውታል።

የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ የጣሊያን መንግሥት ያደረገው የገንዘብ ድጋፍ የኢትዮጵያን የዲጂታል አገልግሎት ለማጠናከር ያግዛል።

የድጋፍ ስምምነቱ የሁለቱን ሀገራት የቆየ ታሪካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል።

ድጋፉ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ግቦችን ከማሳካት ባለፈ የሁለቱን ሀገራት ትብብር የሚያሳድግ መሆኑንም መናገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

የጣሊያን የከፍተኛ ትምህርት እና ምርምር ሚኒስትር አና ማሪያ በበኩላቸው፥ ኢትዮጵያ የጣሊያን አጋር በመሆኗ ሁለቱ ሀገራት በጋራ እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

የውሀ አስተዳደር፣ የግብርና ቴክኖሎጂ፣ ሳይንስና ኢኖቬሽን ዘርፎች በትብብር የምንሰራባቸው የጋራ ራዕዮቻችን ናቸው ብለዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ የኤምባሲዎችን የመሬት ጥያቄን የሚመልስ ውሳኔ አሳልፊያለሁ ሲል ገለጸ‼️

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው የተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ማሳለፉን አስታወቀ።ካቢኔው ካሳለፋቸው ውሳኔዎች መካከልም የሀገሪቱን ዲፕሎማሲ ታሳቢ ያደረገ የኤምባሲዎች የመሬት ጥያቄን ማስተናገድ የሚለው እንደሚገኝበት አመላክቷል።

ካቢኔው የኤምባሲዎች የመሬት ጥያቄን የሚመልስ ውሳኔ አሳልፊያለሁ ቢልም መሬት የጠየቁትን ኤምባሲዎች በዝርዝር አላሳወቀም።ከኤምባሲዎች በተጨማሪም የዉጪ ምንዛሬ እያስገኙ ላሉ የአምራች ኢንዱስትሪዎች የማምረቻ ማስፋፊያ ቦታ ጥያቄዎችን ምላሽ የሚሰጥ ውሳኔ አሳልፊያለሁ ብሏል።

የከተማዋን የኢኮኖሚ እንቅቃሴ ለሚያጎለብቱ፣ ሰፊ የስራ እድል እየፈጠሩ ላሉ ተቋማትም መሬት ለመስጠት የሚያስችል ውሳኔ ማሳለፉን ከአስተዳደሩ የኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በእስክንድር ነጋ የሚመራዉ የፋኖ ሀየረል ከመንግስት ጋር የሚያደርገዉ ድርድር በአሜሪካ ወይም በአውሮፓ እንዲሆን ጠየቀ‼️

ከሰሞኑ ታዛቢዎች በተገኙበት ከመንግስት ጋር ውይይት እንዳደረገ እና ለድርድር ዝግጁ እንደሆነ የገለፀው በእስክንድር ነጋ የሚመራው የፋኖ ክንፍ ድርድሩ በውጭ ሀገራት እንዲሆን እየጠየቀ መሆኑ ታውቋል።

የመሠረት ሚድያ ምንጮች እንደተናገሩት ታጣቂ ክንፉ ድርድሩ በአውሮፓ አልያም በአሜሪካ እንዲደረግ ቅድመ ሁኔታ አስቀምጧል።

መንግስት በዋናነት በእስክንድር ከሚመራው የፋኖ ክንፍ  ጋር በቅርቡ በቴክኒክ ኮሚቴ ደረጃ እንደተወያየ እስክንድር ከኢትዮ 360 ጋር ባደረገው ቃለ መጠይቅ ገልፆ ነበር። አክሎም በድርድሩ ላይ የኢጋድ፣ የአውሮፓ ህብረት፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአሜሪካ ተወካዮች መገኘታቸውን ገልፆ ነበር።

በውይይቱ ላይ በፋኖ ክንፉ በኩል የተነሱ ነጥቦች መከላከያ አካባቢውን በግዜያዊነትም ቢሆን ለቆ መውጣት፣ ክልሉን ማስተዳደር፣ በፌደራል መንግስቱ በስልጣን መወከል፣ የድሮን ጥቃት ማቆም፣ ለተጎዳው ህዝብ ለህይወት ሳይቀር ካሳ መክፈል እና የመሳሰሉት ናቸው ተብሏል።

በመንግስት በኩል ደግሞ ትጥቅ በመፍታት ወደ ማሰልጠኛ መግባት፣ ጎጃም አካባቢ ላይ ያለውን ነገር ማስተካከል፣ በየከተማው ያለውን አደረጃጀት መረጃ መቀበል፣ ተጠያቂ የሚሆኑ አባላቱን አሳልፎ መስጠት እንዲሁም በምክክር ኮሚሽኑ ውስጥ መካተት ናቸው ተብሏል።

"በመንግስት ዝግ ስብሰባ ላይ ሲያጨቃጭቅ የነበረው የነእስክንድር ክንፍ አቅም ጉዳይ ሲሆን ግምገማውም በሀገር ውስጥና በውጭ ተቀባይነትን ለማግኘት መነጋገሩ እንደ  አማራጭ ተወስዷል" ያሉን ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቁ ምንጫችን ሸዋ ላይ ድርጅቱ የተሻለ አቅም እንዳለው፣ ነገር ግን ጎጃም ላይ የለም የሚባል ደረጃ ላይ እንደደረሰ መረጃ ቀርቦ ንግግር ተደርጎበታል ብለዋል።

"ቢያንስ ሸዋን ማቃለሉ እንደ ጥሩ እድል በመታየቱ እና የድርድር ዝርዝር መረጃም የሚቀበሉ አለም አቀፍ ተቋማትም በመንግስት የንግግሩ ቦታ ስለተጓጓዙ ውይይቱ ተደርጓል" በማለት ሂደቱን አስረድተዋል።

"ነገር ግን አሳሳቢው ጉዳይ አሁንም ልክ እንደነ ጃል ሰኒ እንዳይሆን ነው፣ ሙሉ ሰላም ለማምጣት የተወሰነ ቡድን ሳይሆን ሁሉንም አካታች መሆን አለበት" ያሉን ደግሞ በጉዳዩ ዙርያ አስተያየት የሰጡን ተንታኝ ናቸው።

"መንግስት ነገሮችን ያቀሉልኛል ብሎ እየሄደበት ያለው ይህ ነው። ሁሉም ወደ ንግግሩ መግባት አለበት፣ አልያ እንደ  ኦሮምያ አይነት ሁኔታ ይፈጠራል፣ ይባስ ብሎም በቀረው ፋኖ ታጣቂ እና በመንግስት መካከል የሚኖረው ሁኔታ ይባስ ሊካረር ይችላል" በማለት ለሚድያችን ተናግረዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነገ 1ኛ ልዩ ስብሰባውን ያካሂዳል‼️

6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ ልዩ ስብሰባ ነገ ይካሄዳል።

ምክር ቤቱ በስብሰባው የግብርና ሚኒስቴርን የ2017 በጀት አመት የ6 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት የሚያዳምጥ ሲሆን፤ ሁለት የብድር ስምምነቶችን መርምሮ እንደሚያጸድቅም ይጠበቃል።

የከተማ መሬት ይዞታ እና መሬት ነክ ንብረት ምዝገባ እንዲሁም የከተማ መሬትን በሊዝ ስለመያዝ የተዘጋጀ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ የከተማ መሰረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ አዋጁን እንደሚያፀድቅም ይጠበቃል።

በተጨማሪም የአጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ የሰው ሀብት ልማት፣ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ አዋጁን ያጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ከምክር ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በዛሬው ዕለት በመላው የትግራይ ከተሞች ሊባል በሚችል ደረጀ ሰልፎች እየተደረጉ ነው‼️

ስልፎቹ ገሚሶቹ ሰሞኑን "የትግራይ ሰራዊት የበላይ አመራሮች" ያስተላለፉትን ውሳኔ የሚቃወሙ ገሚሶቹ ደግሞ የሚደግፉ መሆናቸው ከማህበራዊ ትስስር ገፆች ለመመልከት ተችሏል።

መቐለ፣ተምቤን ዓብይ ዓዲ፣ ጣንቋ ምልሽ፣ ኮረም፣ ዓዲ ግራት፣ አኽሱም፣ ውቅሮና እንትጮ ሰላማዊ ሰልፍ ከተደረገባቸው ከተሞች መካከል ይጠቀሳሉ።

በሰልፎቹም በአንድ በኩል ከፍተኛ የጦር አመራሮቹ የወሰኑት ውሳኔ እንዲተገበርና ጊዝያዊ አስተዳደሩ እንደ አዲስ እንዲዋቀር የተጠየቀ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ የጦር አመራሮቹ ውሳኔን የሚቃወም ብሎም ትግራይ ላይ ዳግም ጦርነት እንዲነሳ አንፈልግም የሚሉ ድምፆች ተሰምተዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በትግራይ ክልል ዳግም ጦርነት እንዳይቀሰቀስ እንደሰጉ ነዋሪዎች ገለጹ‼️

በትግራይ ክልል የሚገኙ ወታደራዊ አመራሮች ትላንት በሰጡት መግለጫ በዶክተር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል ለሚመራው ህወሓት ቡድን ድጋፍ እንደሚሰጡ መግለጻቸውን ተከትሎ፣ ለአሜሪካ ድምፅ አስተያየት የሰጡ የመቐለ ከተማ ነዋሪዎች፣ ትግራይ ክልል ዳግም ወደ ጦርነት እንዳትገባ የሚል ስጋት እንዳላቸው ተናገሩ። ሁለቱም ወገኖች ጉዳዩን ወደ ሕዝብ አቅርበው “ይዳኙ” ብለዋል።

በሌላ በኩል ሦስት የክልሉ ፓርቲዎች በሰጡት መግለጫ፣ የወታደራዊ አመራርን በፖለቲካዊ ጉዳዮች ጣልቃ መግባት እንደሚቃወሙ በመግለጽ፣ “ወታደራዊ አዛዦቹ ከኤርትራ መንግሥት ድጋፍ ያላቸው ናቸው" በማለት ወንጅለዋል።

ከከፍተኛ ወታደራዊ ጄነራሎች አንዱ፣ ኮልኔል ገብረ ገብረ ጻድቃን፣ “የትግራይ የፀጥታ ሁኔታ ከትግራይ ሕዝብ እና የፀጥታ አካል ውጭ ባለመኾኑ የውጭ ኃይል አንሻም" ሲሉ ውንጀላውን አጣጥለዋል። አክለውም "ጉዳዩ ስም ማጥፋት ነው” ብለዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ባለቤቱን ገድሎ ስጋዋን ከትፎ መጸዳጃ ቤት ዉስጥ የከተተዉ ተከሳሽ በሞት እንዲቀጣ ተወሰነበት‼️

ፀሃዬ ቦጋለ በየነ የተባለ ተከሳሽ ከነሐሴ 27 ቀን 2014 ዓ.ም በግምት ከቀኑ 5፡00 እስከ ነሐሴ 28 ቀን 2014 ዓ.ም ከምሽቱ 12፡30 ድረስ ባለው ጊዜ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 አርሴማ ፀበል አከባቢ ባለቤቱ የነበረችውን ሟች ወንበር ላይ ተቀምጣ እያለ ሳታየው ከኋላዋ በመምጣት በሊጥ ማዳመጫ ዱላ ማጅራትዋን በመምታት እራሷን እንድትስት ካደረገ በኋላ እዛው ትቷት ከቤት ወጥቶ በመሄድና ከተወሰነ ሰዓታት በኋላ ተመልሶ በመምጣት ሟች እራሷን ስታ ከወደቀችበት መሬት ለመሬት በመጎተት እቤት ውስጥ ወደሚገኘው መታጠቢያ ቤት በማስገባት አንድ እግሯን ከዳሌዋ ጀምሮ በመቁረጥና ሙሉ የእግሯን ስጋ አጥንቷ ባዶ እስኪሆን ድረስ መልምሎ በማውጣት ስጋዋን አድቅቆ በመክተፍና በመቆራረጥ ሽንት ቤት ውስጥ በመጨመር የቆረጠውን እግሯ ለሁለት በመስበርና በፌስታል በመቋጠር ፀጉሯን በመቀስ በመቁረጥ ቀሪ አስከሬንዋ ላይ ጨርቅና የተለያየ መዘፍዘፊያ በመጫን እዛው መታጠቢያ ቤት ውስጥ በማስቀመጥ እስከ 30/12/2014 ዓ.ም ድረስ ምንም እንዳልተፈጠረ እቤት ውስጥ እያደረ ከቆየ በኋላ ከ1/13/2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 16/1/2015 ዓ.ም ድረስ ቤቱን ዘግቶ በመሰወሩ ምክንያት በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምርመራ ተጣርቶ በፍትህ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ በሴቶችና ህጻናት ላይ ሚፈፀሙ ወንጀሎች ዐቃቤ ሕግ ዳይሬክቶሬት በወ/ሕ/አ539/1/ሀ/ መሰረት በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ የሰው ግድያና ከባድ ውንብድና ወንጀል ችሎት ክስ ቀርቦበት ክርክር ሲደረግ ቆይቷል፡፡

በክርክሩ ሒደትም የዐቃቤ ሕግ ማስረጃ ከተሰማ በኋላ ተከሳሽ እንዲከላከል ብይን ቢሰጥም የመከላከያ ማስረጃ አቅርቦ የቀረበበትን ክስ ሊከላከል ባለመቻሉ ፍ/ቤቱ በተከሳሽ ላይ የጥፋተኛነት ፍርድ በመስጠት በዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጣ የወሰነ የነበረ ቢሆንም ዐቃቤ ሕግ ባቀረበው ይግባኝ መሰረት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት የወሰነውን የእድሜ ልክ ጽኑ እስራት ውሳኔ በመሻር ተከሳሹ በሞት እንዲቀጣ ወስኖበታል፡፡

©ከፍትህ ሚኒስቴር የተገኘ መረጃ

@Esat_tv1
@Esat_tv1




"የትግራይ ሐይል አዛዦች" መንግሥትና ምርጫ ቦርድ ህወሓትን ለማፍረስ አመራሩን ለመበተን እያሴሩ ነዉ አለ‼️

የትግራይ ሐይል አዛዦች በዶክተር ደብረፅዮን የሚመራው የህወሓት ክንፍ በትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ያለው ሃምሳ ሲደመር አንድ ድርሻ እንዲረከብ እንደሚሹ አስታወቁ። ከዚህ በተጨማሪ በትግራይ ያሉ ታጣቂዎች በትግራይ ሰላም እና ፀጥታ ሴክሬታሪያት ስር እንዲሆኑ፥ ከዚህ ውጪ በሆነ ላይ ግን እርምጃ ይወሰዳል ብለዋል። በሌላ በኩል ፓርቲውን ለማፍረስ እና አመራሩን ለመበተን እያሴሩ ነው በማለት ህወሓት የኢትዮጵያ መንግስትን እና የምርጫ ቦርድን ወንጅሏል። በዶክተር ደብረፅዮን የሚመራዉ የህወሓት ክንፍ ቁጥጥር ኮምሽን ትላንት ባወጣው መግለጫ በአስቸኳይ የህወሓት ሕጋዊነት ሰውነት ሊመለስ ይገባል ብሏል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በአሜሪካ ሎስ አንጀለስ አቅራቢያ አዲስ ሰደድ እሳት ተቀሰቀሰ‼️

በአሜሪካ ካፎርኒያ ግዛት በምትገኘው ሎስ አንጀለስ ከተማ ሰሜናዊ ክፍል ትናንት አዲስ የሰደድ እሳት መቀስቀሱ ተነግሯል።

በሰዓታት ውስጥ ከ3 ሺህ 800 ሄክታር በላይ መሬት የሸፈነው ይህ ሰደድ እሳት ነዋሪዎችን ከመኖሪያ ስፍራቸው እያፈናቀለ መሆምኑ ተገልጿል።

ይህንንም ተከትሎም 31 ሺህ ነዋሪዎች መኖሪያ ቤታቸውን ለቀው እንዲወጡ ትዕዛዝ የተላለፈ ሲሆን ለ23 ሺህ ሰዎች ደግሞ በተጠንቀቅ ላይ እንዲሆኑ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል።

ደረቅ አየርና አደገኛ ንፋስ ለሰደድ እሳቱን መዛመት ምክንያት መሆኑ የተገለጸ ሲሆን ወደ ሌላ አካባቢ እንዳይስፋፋም ተሰግቷል።

በፍጥነት እየተስፋፋ ያለውን ሰደድ እሳት ለማስቆምም በርካታ የእሳት አደጋ መከላከያ አውሮፕላኖች እንዲሁም በሺዎች የሚቆጠሩn የእሳት አደጋ ሰራተኞች ጥረት እያደረጉ መሆኑም ተገልጿል።

በሎስ አንጀለስ ከተማ እና አካባቢው ከ16 ቀናት በፊት ከተቀሰቀሰው እሳት ውስጥ ከባድ የተባሉት የኢቶንና ፓላሲደስ እሳቶች አሁንም እየነደዱ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1

20 last posts shown.