ስብዕናችን #Humanity


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Psychology


🔆እየጠየቁ መኖር መልስን፣
መልስን ፈልጎ ማግኘት ዕውቀትን፣
እውቀት ነፃነትን፣ ነፃነት ሙሉ ስብዕናን፣
ሙሉ ስብዕና ሠላምና እርካታን፣
እርካታ ደግሞ ደስተኛ ሆኖ መኖርን ያስገኛል፡፡
አብረን እንደግ !!
@EthioHumanity @Ethiohumanity
✍የተሰማቹን አጋሩን! ቤቱ ሁሌም ክፍት ነው፣ሃሳባቹን ፃፍፍ አርጉልን @EthioHumanitybot

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Psychology
Statistics
Posts filter


📍ቡዳን እንዴት ማወቅ እንችላለን?

✍አሌክስ አብርሃም

♦️ሰሞኑን ስለቡዳ አብዝታችሁ ስታወሩ ነበር። ሁላችሁም ቡዳ ስለሚባል የሆነ ቦታ የሆነ ሰው ውስጥ ተደብቆ ሰወችን ስለሚበላ መንፈስ ነው "አለ የለም" ስትባባሉ የነበረው። መኖር አለ። እኔ የምላችሁ ግን... እናንተ ራሳችሁ ውስጥ የቡዳ መንፈስ እንደሌለ በምን እርግጠኛ ሆናችሁ? ለምን ምርመራውን ከራሳችሁ አትጀምሩም? ለማንኛውም የቡዳ መንፈስ እንዳለባችሁና እንደሌለባችሁ ለማወቅ የሚረዱ 5 ነጥቦችን ልንገራችሁ፤ ከዛ ((ቡዳ ፖዘቲቭ)) ወይም ((ቡዳ ኔጌቲቭ)) መሆናችሁን ራሳችሁ ወስኑ።

1ኛ:- ከምትወዱት ሰው ይልቅ የምትጠሉት ሰው ቁጥር ከበለጠ፣ ጥላቻችሁ በግል የማታውቁትን ሰው ከሆነ፣ ምንም ተበድላችሁ ሳይሆን ያ የጠላችሁት ሰው ቆንጆ፣ ሐብታም ወይም ታዋቂ፣ ወይም የተሳካለት ስለሆነ ብቻ ፀጉር የሚያስነጫችሁ ከሆነ ቡዳ ፖዘቲቭ ናችሁ።

2ኛ:- ሁልጊዜ ሰወችን የምትፈልጉት ለችግራችሁ ብቻ ከሆነና እናንተን ሲፈልጓችሁ የምትሸሹ፣ ችግር ውስጥ ሲገቡ እንደአቅማችሁ የማትረዷቸው ከሆነ ቡዳ ከነልጁ ውስጣችሁ ፈርሿል።

3ኛ:- የሶሻል ሚዲያ አጠቃቀማችሁን ፈትሹ፤ በተደጋጋሚ የምትገኙት ምናይነት ወሬ ላይ ነው? ተጋደሉ፣ ተፋቱ፣ ሚስቱ ከዳችው ባሏ ካዳት፣ ተጣሉ፣ ተለያዮ ተሰዳደቡ ዝምታቸውን ሰበሩ ወዘተ ላይ ከሆነ ቡዳ ውስጣችሁ ተቀምጦ አይናችሁን እንደመስኮት እየተጠቀመ ነው።

4ኛ:- ሀሜተኛ፣ አሽሙረኞች፣ የሰወችን ስም በሐሰት የምታጠፉ፣ አቃጣሪወች፣ ተንኮለኛና አድመኞች፣ ቀናተኞች፣ ትዕቢተኞች፣ ሰውን በመዝለፍ ለማሸማቀቅ የምትሞክሩ (((ፌክ አካውንት ያላችሁ))) የሰው ላይክ የምትቆጥሩ ከሆናችሁ፣ ሌሎች ሲደነቁ "እኔምኮ..." ብላችሁ የድሮ ዝናችሁን በሰው ክፍለጊዜ የምትዘንቁ ከሆ...ነ ቡዳ ጢባጢቤ እየተጫወተባችሁ፤ እንደፈረስም እየጋለባችሁ ነው።

5ኛ:- አካውንታችሁን ሎክ አድርጋችሁ ሌሎችን የምታዮ 😀 ይሄ ቀለል ያለው ነው ፤ አንዳንዴም ኮንፊደንስ ማጣት፣ ወይም ፀጉር ቤት እስከምትሄዱ ኤክሳችሁ ተጎሳቁላችሁ እንዳያያችሁ ከመፈለግ ሊሆን ይችላል። የሆነ ሁኖ የራሳችሁን ቆልፋችሁ ሌሎች መቆለፋቸው ካበሳጫችሁ ግን... 😀😀

💎መፍትሄ፦ ጨክናችሁ ከጥላቻ ውጡ። የሌሎች ውድቀት አያጓጓችሁ። ፍቅር ቡዳን አይነጋጃውን ነው የሚያጠፋው።

ውብ ዛሬ❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot




💡ቀስ እያለ ነጋ!

🔷አንዳንድ ቀን በጣም ከባድ ነው ሁሉም ነገር ይሰለቻል ከአልጋ ላይ ራሱ መነሳት ያስጠላል በጣም ደክሞኛል ስትል እንኳን  ምን ለማለት ፈልገህ እንደሆነ ማንም አይረዳህም

በቃ............... ሁሉም ነገር ጭልምልም ይልብሀል ምን መስራት እንዳለብህ  የት መሄድ እንዳለብህ ራሱ ግራ ይገባሀል  ያስደስትህ የነበረዉ ሁሉ ያስጠላሀል በቃ መሀል ላይ ራስህን ታጣዋለህ፣ ሕይወት እንደ ደራሽ ማዕበል ይሆንብሃል፡፡ በሰላም ይሄዱ የነበሩ ነገሮች ልክ የተመካከሩ ይመስል በአንድ ላይ ይናጋሉ፡፡ የሁኔታዎች አልሳካ ማለት፣ ድንገተኛ ወጪዎች፣ የጉዳዮች መጥመም፣ የሰዎች ክህደት፣ስጋትን የሚፈጥሩ ሁኔታዎች መከሰት፣ ልክ እንደ ማዕበል በአንድ ላይ ይመጣሉ፡፡

💎ህይወት ሁሌ ሙሉ አይደለችም ፣ ማጣት ማግኘት  መደሰት ማዘን መጫወት መከፋት ማዉራት ዝም ማለት መሳቅ ማልቀስ ብዙ ብዙ  ነገር ይገጥመናል ሰው ይፈተንበት ዘንድ የተሰጠው ፈተና ሺ ነው፡፡ እስትንፋሱ እስካለች ድረስ ፈተናው አያልቅም፡፡ ተረጋጋሁ ሲል የሚረበሽ፤አረፍኩ ሲል እንከን የማያጣው ጥቂት አይደለም፡፡

📍ጥያቄው ግን እኛ ሰዎች በጎ በጎዉን ትተን መጥፎው ላይ ብቻ ለምን እንከርማለን ነው??

አንድ እውነታ የሚመሰረተው እውነታ ካልሆነው ነገር ጋር ተነፃፅሮ ነው። ካልሆነ ግን እውነት ሚባል ስያሜም አይኖረውም።  ጥሩ መጥፎ ከሌለ ሊኖር አይችልም። ጥንካሬ ድክመት ካሌለ ሊታወቅ አይችልም።ስለዚህም መከራን አትጥላው። የመከራ ዘር በውስጡ የማንነት እድገትን ይዟልና። ያሰብከው እና ያገኘህው ነገር ሊለያይ ይችላል። ነገር ግን የቱም ሁኔታ ትምህርትን ይዞ ይመጣል፣ የምንኖረው በአንፃራዊ አለም ውስጥ ነውና።

💡ለማንም ሰው ህይወት ስህተት ወይም ትክክል መሆኑን የሚያውቀው ሲፈተን ነው። ጫጩት ለማግኘት የእንቁላሉ ቅርፊት ማስወገድ ሽፋኑን መግለጥ ያስፈልጋል፣ ወርቅ የሚወጣው ከጭቃ ውስጥ ነው።  ዝናብ ሊዘንብ ሲል ነጎድጓድና የመብረቅ ብልጭታ ቀድመው መታየት ይጀምራሉ። ሌቱ ሊነጋጋ ሲል በጣም ይጨልማል። ከከባድ ምጥ በኋላ ልጅ ይወለዳል። ይህ የተለመደ የሕይወት አካል የሆነ ክስተት በእኛም ላይ ሲደርስ መረጋጋት ወሳኝ ነው፡፡

እናም ወዳጄ

🔑ህይወት ሁሌም ለማንም የትም ሙሉ አይደለችም፡፡ ቀን አለና ቀና በል፣ አስብ ባሰብከው ሀሳብ ተፅናና በተፅናናህበትም ቃል ሌሎችን አፅናና!! በሕይወት ሩጫዎችህ መሀል ያለውን ውስብስብ የሕይወት ገፅ ጠንቅቀው የሚያውቁት ጥቂቶች ናቸው። ስለሆነም ባልተረዱህ ብዙ ሰዎች እየተናደድክ ሳይሆን በተገነዘቡህ ጥቂት ሰዎች እየተደሰትክ ኑር። አልሞላ ያለው ነገር ሁሉ ፈጣሪ በራሱ ግዜ አስተካክሎ ጨምሮ ያመጣዋል ።

ዛሬን ባለህ ነገር አመስግነህ ደስ ብሎህ ኑር። ባለህ የማትረካ ከሆንክ ሩጫህ ሁሌ ሌላ ነገር ፍለጋ ብቻ የሆናል፡፡ የሌለህን ነገር ብቻ ካሰብክ በማማረርህ ውስጥ ያለህንም ታጣዋለህ፡፡ ያለህን ነገር ካሰብክ ግን በምስጋናህ ውስጥ የሌለህንም ታገኘዋለህ፡፡

               ውብ አሁን❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot





💫እንኳን ለ 1446ኛው የዒድ አል ፈጥር በአል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን!
                
♦️በመላው አለም የምትኖሩ የእስልምና እምነት ተከታይ ሙስሊም ወገኖቻችን እንኳን ለ1446ኛው የዒድ  በአል በሰላም አደረሳችሁ፣አደረሰን።

✨ የዒድ በአል የእዝነት ÷ የመተሳሰብ ÷ አብሮ የመብላትና የመፈቃቀር በአል በመሆኑ በየ አካባቢያችን በችግር ላይ የሚገኙ ወገኖቻችንን እያሰብን እንዋል።

          ዒድ ሙባረክ !!!❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity


🛑ሠላም ከውስጣችን የሚመነጭ፣ ከቅን አስተሳሰባችን ተምጦ የሚወለድ፣ ከደግ ልቦናችን የሚፈለቀቅ ውስጣዊ ሐብት ነው፡፡ ሠዎች ሠላምን ፍለጋ የማያደርጉት ነገር የለም፡፡ አንዳንዶች ‹‹ሠላምን ማግኘት የምንችለው በጦርነት ነው›› በሚል ፈሊጥ ጠብመንጃ ያነሳሉ፡፡ ጥቂቶች ‹‹ካልደፈረሠ አይጠራም›› በሚል ሃሳብ አደፍርሠው ማጥራትን ይሻሉ፡፡ ነገር ግን ልፋታቸው ከንቱ ሲሆን እናያለን፡፡ በአሸናፊነትና ድል በመንሳት የሚገኝ ሠላም ዕረፍት የሚሠጠው ለጊዜው እንጂ ቋሚ ሠላም አያስገኝም፡፡ ተሸናፊዎቹ ጊዜ ጠብቀውና ዕድል ሲቀናቸው ሠላሙን ሊያደፈርሱት ይችላሉና፡፡

🔷ሠዎች ሠላምን መፈለግ ያለባቸው መጀመሪያ ከራሳቸው ነው፡፡ ጥቂቶች ሠላማዊ ሕሊናን መፍጠር አቅቷቸው ሠላምን ፍለጋ ሲዋትቱ እናያለን፡፡ ለራሳቸው እንኳን ቅድሚያ ሠላም አልሠጡትም፡፡ አዕምሯቸውን በሠላማዊ ሃሳብ አልሞሉትም፡፡ ልቦናቸውን ለሠላም አላስገዙትም፡፡ ስሜታቸውን በሠላማዊ አመለካከት አልገሩትም፡፡ ጥቂቶች እንደውም የሌሎችን ሠላም በመንሳትና ሠላማቸውን በማደፍረስ ሠላም የሚያገኙ ይመስላቸዋል፡፡

♦️ሠላም ከራስ፣ ከቤተሠብ፣ ከመንደር፣ ብሎም ሐገር ጋር ሊደርስ የሚችል እንጂ ከውጪ በጉልበት ወይም በገንዘብ ገዝተን የምናመጣው አይደለም፡፡ ሠላምን መፍጠር የሚችለው ራሱ ሠው ነውና፡፡ በግለሠብ ያለው ሠላም ተሰብስቦ የቤተሠብ፣ የመንደር ብሎም የሐገር ሠላም ይሆናል፡፡

አልበርት አንስታይን ስለሠላም ሲናገር እንዲህ ይላል፡-

‹‹ሠላምን በሃይል ማስጠበቅ አይቻልም፡፡ ሠላም ዕውን ሊሆን የሚችለው በጋራ መግባባት ብቻ ነው፡፡›› ይለናል፡፡

📍እውነት ነው! ሠላምን ማስፈን የሚቻለው በመግባባት፣ ሃሳብን በሃሳብ በማዋሃድ፣ የጋራን ጥቅም በእኩልነት በማስጠበቅ፣ ‹‹እኔ ብቻ ይድላኝ›› የሚሉትን ስግብግብ አስተሳሰብ ወደጎን በማለትና በማስወገድ ጭምር ነው፡፡ መግባባት ሲባል ሠጥቶ መቀበል፤ ተቀብሎ መስጠት ያለበት መርህ ነው፡፡ ለሌላው ሠላም ሳንፈጥር ለራሳችን ሠላም ማግኘት አንችልም!

💎ወዳጆች የሐገርም ሠላም ዕውን የሚሆነው እያንዳንዳችን በምናዋጣት የሠላም አስተሳሰብና ድርጊት ነው፡፡ ሠላማዊ ሠው ሌሎችን ያከብራል፣ ሠላማዊ ሠው የሌሎችን መብትና ነፃነት ያስጠብቃል፣ ሠላማዊ ሠው እሱ የሚያስፈልገው ሁሉ ሌሎችም እንደሚያስፈልጋቸው ቀድሞ ስለሚያውቅ ጥቅማቸውንና ሕይወታቸውን አይቀማም፡፡ ግና ግን ሠላምን በፖለቲካ አሻጥር፣ ጠልፎ በመጣል ሴራ እውን ማድረግ ፈፅሞ አይቻልም፡፡ ሌሎችን በመጣል የሚገኝ ሠላም እውነተኛ ሠላም አይባልም፡፡

ለዚህም እኮ ነው ዳላይ ላማ፡-

‹‹እያንዳንዱ ግለሠብ ሠላሙን በመፈለግ ሂደት ውስጥ የዓለም ሠላምን ይወስናል!›› የሚለን፡፡

ሠላም ምንጩ ግለሠብ ነው፤ መድረሻው ሐገር ነው፤ ወሠኑ ደግሞ ዓለም ነው፡፡ ሠላምን በመፈክር፣ በዘፈን፣ በግጥም፣ በቀረርቶ፣ ወዘተ ነገሮች ማስፈን አንችልም፡፡

💡እነዚህ ያለን ወይም የነበረን ሠላም ለማጎልበት ይጠቅሙ ይሆናል እንጂ የሠላም ምንጭ መሆን ግን አይችሉም፡፡ የሠላም ምንጩ ግለሠብ ነው፡፡ ያ ግለሠብ ደግሞ ለሠላም ካለው አመለካከት ጋር በተያያዘ የራሱንም ሆነ የአካባቢውን፣ አልፎ ተርፎም የሐገሩን ሠላም ይወስናል፡፡ በአንድ ሠላም በሌለው ግለሠብ ምክንያት ቤተሠብ፣ አካባቢ፣ ሐገር እንዴት እንደሚሸበር በዓለማችን እያየን ነው፡፡

🔑የሠላም መነሻው ግለሠብ ነውና እያንዳንዱ ሠው ሠላሙን ይፍጠር፣ ሠላሙን ያስጠብቅ፣ የሌሎችንም ሠላም ያረጋግጥ፡፡ በተለይ መጪው ትውልድ ሠላማዊ እንዲሆን ለልጆቻችን ሠላምን በተግባር እየከወንን ሠላምን እናስተምራቸው፤ እርስ በርስ በሠላም በመግባባትና በመተራረቅ የሠላም አብነት ሆነን እናሳያቸው፡፡

ሠላም ለዓለማችን! ሠላም ለሃገራችን!ዘመኑ ሠላማችንን የምናረጋግጥበት ይሁን።

            ውብ ጊዜ❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


💡አንድ ወጣት ሰው ስለአርምሞ ሊቀስም ከZen መምህር ዘንድ መጥቶ ቢጠይቅ "ታግሰህ መጠብቅ ይቻልሃል ወይ?" አሉት ።

ወጣቱ "ምን ያህል ጊዜ?" መልሶ ጠየቀ።

መምህሩ "አንተን ለማባረር ይሄ መልስህ ብቻ በቂ ነበር። 'ምን ያህል ጊዜ' ብሎ መጠየቅ ማለት ለመጠበቅ ዝግጁ አይደለህም ማለት ነው። ከቻልክ 'ምን ያህል ጊዜ' ብለህ ሳትጠይቅ ዝም ብለህ ከጠብቅክ መጠበቅን ትችላለህ" አሉት።

📍ወጣቱ ነገሩ ገባውና እጅ ነስቶ ከመምህሩ ዘንድ ከረመ። ያለምንም ቀለም ዓመቱ ነጎደ። ሁለተኛው ተከተለ። ሶስተኛውም ተደገመ። 'አሁንስ በዛ! ምንም አልተጀመረም ፤ አንድ ክፍል እንኳን። ሰው ምን ያህል ጊዜ ነው መጠበቅ ያለበት?' ድጋሚ ጥያቄዎች ከአዕምሮው ቦታ ይዘው 'እስከ መቼ?' ብሎ ከመምህሩ ዘንድ አቅንቶ "ሶስት ዓመት ጠበኩኝኮ" ሲል ጠየቃቸው።

💡መምህሩ "እየቆጠርክ ነበር? በቀላሉ ይሄ የሚያሳየው እንዴት መጠበቅ እንዳለብህ አለማወቅህን ነው። መቁጠር? ከኔ ጋር ቀናትን መቁጠር? ላንተ ቀናቶች ዘላለም ሆነው ይሆናል፤ ለኔ ደግሞ ዘላለም ቀናት ሊመስሉ ይችላሉ። አንተ ከንቱ መጠበቅ አለብህ። መጠበቅ ማለት ምን እንደሆነ መማር ይኖርብሃል። ብቻ ተዘጋጅ ከነገ ጀምሮ ትምህርቱን እንጀምራለን" አሉት።

📍ትምህርቱ እንግዳ ነገር ነበር። ወጣቱ ወለል እያጸዳ እያለ መምህሩ ከጀርባው መጥቶ በያዘው ነገር ኋላውን ነረተው። ወጣቱ በርግጎ "ከሶስት ዓመት መጠበቅ በኋላ ይሄ ነው የአርምሞ መግቢያ?" አለው። መምህሩ "በሚገባ። አሁን ንቁ ሁን። በየትኛው ጊዜ፣ በየትኛው ወቅት ስለምጠልዝህ ንቁ ሁን። የራስህ ጠባቂ ሁን" አሉት።

ምቱ እና ንረታው ለወራት ቀጠለ። ምክንያቱም ሽማግሌው ቢያረጅም ኮቴ ቢስ ነበር፤ ድንገት ብቅ ይሉና ወጣቱን ያቀምሱታል። ይሄም በዝቶ ስለተደጋገመ የገላው ሕመም ምሽት ላይ ይጠዘጥዘው ነበር።

📍ሆኖም ቀስ በቀስ የወጣቱ ደመ-ነፍስ ነቃ። ከኋላም ቢሆን መምህሩ ሊመቱት ተቃርበው እያሉ ያመልጥ ጀመር። በሥራ ቢጠመድ እንኳ ቆሌው ይነግረዋል። የሕመሙ ሥቃይ የንቃት ግዴታ ጥሎበት ነበር።

💎ሕመም ለእድገት ግድ ነው። ሥቃይ ለማደግ ፍፁም አስፈላጊ ነው። ካልተሰቃየህ በስተቀር ንቃትህ ሊደምቅ አይችልም። ሥቃይ ልቦናን ያስገዛል፤ ፍቃደ-ስቃይም እልፍ አስተውሎትን ያሸምታል። [ Pain is a must for growth, suffering is absolutely necessary for growth. Unless you suffer you cannot be aware. Suffering brings awareness, and voluntary suffering brings tremendous awareness.]።

🔆ወጣቱ ማምለጥ ይችል ነበር፤ ማንም አላገደውም። ግን ሥቃዩን ፈቀደ። መምህሩን አስቀደመ። ምርጫው ሆነ። ለምን እንደሆነ አሁን ይገለጥለት ጀመር ለወጣቱ። "ይሄ የመምህሩ አስተምህሮ ነው። እንደዚህ ነው አርምሞን የሚያስተምረው" ከልቦናው ጣፈው። አብዝቶ አመሰገነ።

መምህሩ ከጀርባው እያደቡ መጥተው ሳይነርቱት በፊት ወጣቱ ተስፈንጥሮ ገሸሽ ቢል ዱላው ከመሬት ሲወድቅ በጣም ተደሰቱ። በወጣቱ ልቦና አዲስ አስተውሎት ፈነጠቀ፤ እናም መምህሩ ባረኩለት።

💡ዳሩ ግን ከዛን ዕለት ወዲህ ነገሮች ከበዱ። መምህሩ በውድቅት ጨለማ ወጣቱ ሲያሸልብ ይቆጉት ጀመር። 'አሁን ልኩን አለፈ። በጨለማ! ለዛውም በየትኛውም ሰዓት!' እንደውነቱ መምህሩ ስለጃጁ እምብዛም ማንቀላፋት አይችሉም። በየትኛው ጊዜ የነቃ ሲመስላቸው ሄደው ወጣቱን ይነርቱታል። 'ይሄ ቅጥ-አንባሩ የጠፋ ጅልነት ነው። ራሴን ቀን መከላከል አያዳግተኝም፤ መሮጥ፣ ማምለጥ፣ ዞር ማለት እችላለሁ። ግን ሳንቀላፋ ምን ማድረግ ይቻለኝ ይሆን?' አላለም፤ አልጠየቀም አሁን። ዝም ብሎ ተረዳ። 'ሒደቱ ላይገባኝ ይችላል ቢሆንም እነዛ የቀን ዱላዎች ብዙ ትሩፋት ስለነበራቸው ነው ይሄን ልውጠት (transformation) በኔ ላይ ያመጡት። ካለምንም ጥያቄ ይሄንንም እቀበለዋለሁ' አለ።

መምህሩም "ይሄ ጥሩ ምልክት ነው። ለመጀመሪያ ጊዜ እምነት ጥለህ ጥያቄ አላነሳህም። ሁለት ወይም ሶስት ወራት ሲደበደብ ገላው በየቀኑ ቁስል ቢሰማውም አንድ ዕለት ሆነለት፤ በፅልመት ራሱን መከላከል ቻለ። መምህሩም እክፍሉ ሲዘልቁ "ተረጋጉ…ነቅቻለሁ" አላቸው። እንደዚሁ ደጋግሞም ተከሰተ።

🔷 ወጣቱን መነረት የሚቻል አልሆነም። መምህሩ እክፍሉ እንደጠለቁ፣ ፈጽሞ የማይተኛ ይመስል አይኖቹ ፈጠዋል። ግን እንደዛ አልነበረም፤ ወጣቱ ሲያሸልብ በጣም ችኩል ነበር። ሆኖም እውስጥ እንደቀንዲል የበራች ትንሽ የበረዶ ግግር ጫፍ የመሰለች አለላ ንቃት ለቅኝት (watching)፣ ለጥበቃ (waiting) ከሽልብታ ዓለም አምልጣ ወጥታ ስለነበረ ነው ቀድማ ምታባንነው።

📍መምህሩ ተደሰቱ። በበነጋው ማለዳ መምህሩ ከአንድ ዛፍ ስር አርፈው ጥንታዊ መጻሕፍ ያነባሉ። ወጣቱ ያትክልት ሥፍራውን እያጸዳ 'ይሄ ሽማግሌ ለዓመት ያህል ጠዋት፣ ማታ ሲነርተኝ ነበር። እሱን አንዴ ብቻ ብደልቀው እንዴት ይሆናል? ባየው ደስ ይለኛል እንዴት እንደሚሆን?' የሚል ሐሳብ ብልጭ አለበት።

መምህሩም በዛው ቅፅበት መጻሕፉን ከደኑና "አንተ ቂል! ይሄ ከንቱ ሐሳብ ይቅርብህ፤ እኔ ለራሴ አቅመ ደካማ ነኝ" ብለው ለወጣቱ መለሱለት ....

       ❤️ውብ አሁን ለሁላችን😊

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot




✏️እርሳስነት

🔴እርሳስነት ለኑረት ስምረት የተመቸ ተምሳሌት ይመስላል፣ ለመስተጋብር ውበት የተስማማ ምልክት፣ ለመማር የተዘጋጀ ሰው በዙሪያው እልፍ መምህራን አሉለት።

“When the student is ready the master will appear” እንዲሉ…

🟡ተወዳጁ ደራሲ ፓውሎ ኩዌልሆ “Like the Flowing River” በተሰኘው መጽሐፉ ላይ የልጅ ልጃቸውን ታሪክ በሚጽፉ አያት አማካይነት ስለ እርሳስ ልዩ መገለጫዎች ይነግረናል፣ አንድ ሕፃን ሴት አያቱ የሚጽፉት ታሪክ የእርሱ ስለመሆኑ እንዲነግሩት ሲጠይቅ ከሚጽፉት ታሪክ በላይ በሚጽፉበት እርሳስ የተመሰጡት አያት “አዎን ልጄ ታሪኩ ስላንተ ነው… ግና ከምጽፈው ታሪክ ይልቅ የምጽፍበት እርሳስ የተለዩ ነገሮች አሉትና ስታድግ እንደዚህ እርሳስ እንደምትሆን ምኞቴ ነው” ይሉታል።

በአያቱ ንግግር የተገረመው ሕፃን እርሳሱን ትኩር ብሎ ይመለከትና ከሌሎች እርሳሶች የተለየ ነገር እንዳላየበት ለአያቱ መልሶ ይነግራቸዋል።

“አዎን ልክ ነህ” አሉት አያት፣ “የምታይበት መንገድ የምታየውን ነገር ዋጋ ይወስነዋል፣ በደንብ ተመልከት፣ እርሳስ ያሉትን ልዩ ጠባያት መገንዘብ የቻለ ሰው ከፍጥረተ-ዓለሙ ጋር ስሙር እንዲሆን የሚረዱትን አምስት ጥበባት ይማራል…” ሲሉ መለሱለት።

🔴እኒህን አምስት የኑረት መላዎች ከሌሎች አሰላሳዮች ጥልቅ ምልከታ ጋር ማዛነቅ ሻትኩ፣ ልክ እንደዚህ…

1️⃣‘First quality: you are capable of great things, but you must never forget that there is a hand guiding your steps. We call that hand God, and He always guides us according to His will.’

🔷“ታላላቅ ተግባራት የመፈጸም ሰዋዊ አቅም ቢኖርህም በመንገድህ ሁሉ የሚመራህ እጅ እንዳለ ግን መዘንጋት የለብህም፣ እርሱም መለኮት ነው። ሁልጊዜም እንደፈቃዱ ይመራሃል”

♦️ዓለም በስልጣኔ ብትረቅ፣ በቁስ ዕድገት ብታሸበርቅ፣ የሰው ልጅ ትንግርት በሚያስብሉ ተግባራት ቢራቀቅ ያለ መለኮታዊ ድጋፍ የትም ሊደርስ አይችልም። እያንዳንዲቷ እርምጃው መለኮታዊ እገዛ ያሻታል፣ ከራስ አቅም ጣሪያ በላይ ገደብ አልባ ጣሪያ መኖሩን አለመርሳት ደግ ነገር ነው። እብሪትና ማንአለብኝነት ከሚያመጡት አዙሪት ለመውጣትም ሆነ ከኑረት እልፍ ጉድጓድ ለመሻገር ሁነኛው መድኅን መለኮት ነው።

“I’ve forgotten all my learning’s but from knowing you I’ve become a scholar. I’ve lost all my strength, but from your power I am able.” ~ Rumi

2️⃣“በየቆምታዬ ታዛ መቅረጫ ተጠቅሜ እቀርጸዋለሁ፣ ይህ ተግባሬ እርሳሱ በመጠኑ እንዲጨቆን ቢያደርግም ስለቱ ለስራ ምቹ ያደርገዋል። አንተም ብትሆን በኑረት ውስጥ የተሻልክ ትሆን ዘንድ ጥቂት እንግልቶችን እና ጫናዎችን ማለፍ ይኖርብሃል”

🔶ብዙውን ጊዜ የገባንበትን ፈተና ጥልቀት እንጂ ከፈተናው በመውጣት ሂደት የሰነቅነውን ጥበብ አናስተውልም… በዚህም ምክንያት በርካታ የኑረት ክህሎቶች በማስተዋል እጦት ይቀጭጫሉ፣  የብዙ ስኬቶቻችን አሃዱ ግና የሕመማችን ማግስት ነው።

“The wound is the place where the Light enters you.” ― Rumi

3️⃣“እርሳስ ምንጊዜም ቢሆን የሰራነውን ስህተት በላጲስ አጥፍተን የማረም ዕድል ይሰጠናል ፣ ስህተትን ለማስተካከል መድፈር መጥፎ ነገር አይደለም። ይልቁን በቀናው መንገድ ጉዞአችንን እንድንቀጥል የሚረዳን አቅም እንጂ”

🔷በፊቶቻችን የተንኮታኮቱ ጅምሮች፣ የጨነገፉ ሕልሞች፣ ያልተሳኩ ሙከራዎች በርካታ ናቸው። የጅምር እንከን ለዳግም ጅማሬ እንቅፋት ሆኖባቸው ከመንገድ የቀሩ ጓደኝነቶች፣ ትዳሮችና መሰባሰቦች እልፍ ናቸው። ጥፋትን በይቅርታ ማንፃት የተሳናቸው ግትርነቶች፣ ትዕቢትን በአትሕቶ ርዕስ ማጠብ ያቃታቸው አምባገነንነቶች፣ ጭካኔን በአጥፍቻለሁ ዝቅታ ማረቅ የማይሹ ድርቅናዎች የየዕለት ገጠመኞቻችን ናቸው። ይህ ሁሉ ታዲያ መሳሳትን ለመቀበል ድፍረት ከማጣት የሚመጣ እንከን ነው። አልያም ‘ካፈርኩ አይመልሰኝ’ ከሚል አኞነት…

“A man should never be ashamed to own that he has been in the wrong, which is but saying in other words that he is wiser today than he was yesterday.” ― Alexander Pope

“O, happy the soul that saw its own faults.” ~ Rumi

4️⃣ “የእርሳስ ወሳኙ ክፍል ከውጭ የሚታየው እንጨት አይደለም፣ ከውስጥ ያለው መፃፊያ እንጂ፣ ስለሆነም ትኩረት ማድረግ ያለብህ በውስጣዊው ሁነትህ ላይ ነው”

♦️ወጭቱን በአፍአ ጽድት አድርገው የሚይዙ ውስጣቸው ግን በኖራ እንደተለሰነ መቃብር የሚገለሙ በርካታ የአዘቦት ተመሳስሎዎችን እናውቃለን፣ አለማወቁን በቃል ብልጠት የሚሸሽግ ከንቱ… ባዶነቱን በከፈን ድምቀት የሚከልል ሰነፍ ፣  መልከ-ጥፉ ልቡን በስም የሚደግፍ ነውረኛ፣ የነፍሱን እርቃን በመንፈሳዊነት ካባ የሚከፍን አስመሳይ… ቁጥሩ ብዙ ነው።

Beauty is not who you are on the outside, it is the wisdom and time you gave away to save another struggling soul like you.” ― Shannon L. Alder

5️⃣ “እርሳስ ሁልጊዜም አሻራውን ትቶ ያልፋል። አንተም ብትሆን በኑረት የምትሰራው ማንኛውም ነገር ምልክቱን እንደሚተው ልብ ልትል ይገባል። ስለዚህም ድርጊትህን ሁሉ በአስተውሎት ከውን። ለደቀመዛሙርቱ የሚሰጠውን የሚያውቅ መምህር ከራሱ የሚሻሉትን ያፈራል። ፍርሃቱን ከራስ አኑሮ ድፍረቱን የሚጋራ ሰው ለሌሎች ተስፋ ያተርፋል፣ ለዛሬው የሚጠነቀቅ ነገውን አሁን ይሰራል። በብርሃን ላይ የተመሰጠ የጽልመት አምካኝ መላ ያፈልቃል።

ምንህን እየሰጠህ ነው?… “What kind of footsteps will you leave for those who follow you?” ― Kathy Bee …

🔑ፍቅርን ነው ጥላቻ፣ ሰላምን ነው ጸብን፣ አንድነትን ነው መለያየትን፣ ስታልፍ የምናስብህ ለሰላማችን በጣልከው መሰረት ነው ወይስ ለግጭታችን በሰራኸው ሴራ? ለአብሮነታችን በገነባኸው ታዛ ነው ወይስ ለመቋሰላችን ባኖርከው ሰይፍ?

ለሚያነቡህ ምን እየፃፍክ ነው? ለሚሰሙህ ምን እየተናገርክ ነው? ወላጅ ላሉህ ምን ትተሃል? ከቶ አሻራህ ምን ይመስላል? ቅርስህሳ ምን ሸክፏል? ከኑረትህ ምን ተርፎናል?

በአያቱ ተግባር የሚያፍር ዘመነኛ – በተራው ልጁ እንዳያፍርበት ያለው ብቸኛ አማራጭ ልቡናውን ከቂም አንጽቶ የእርሱን ውብ ነገ ዛሬ ላይ መስራት ነው። ይህ ግን ከኢጎ የመላቀቅን ድፍረት ይሻል!!

“Take nothing but memories, leave nothing but footprints!” ― Chief Seattle

                          ✏️በደምስ ሰይፉ

     እርሳስነት – ምርጥ ብልሃት
               ውብ አሁን❤️

💎ሃሳብ ፣ ንባብ፣ ኑረት፣ ሕይወት፣ፍቅር እና ምናብ! ድልድይ👇
@BridgeThoughts
@BridgeThoughts

@EthioHumanitybot


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
✨የትላንት ታሪኮቻችን የሚያስተምሩን ዛሬም ላይ ታሪክ መስራት እንደሚቻል ነው።

ታሪክን መዘከር እና ለትውልድ ማውረስ እንደተጠበቀ ሆኖ ከትናንት ታሪካችን ጽናትን፣ አብሮነትን እና አገራዊ አንድነትን በመላበስ ዛሬ ላይ የትላንቱን ምኒሊክን መሆን፣ በድህነት ላይ መዝመት፣ ኋላቀርነትን መታገል፣ ለመርህ ተገዥ ሆኖ መተባበር የአሁን አድዋ ድል ነው።

✨ታሪክ በራሱ ነፃ አያወጣም። ታሪክን ተመርኩዞ ጭቆናን አሸንፎ፣ ነፃነትን መቀናጀት ግን ይቻላል። አድዋ ! በጥቁር ህዝቦች ታሪክ ትልቁ የድል ማማ! ነውና። በአድዋ ጦርነት ከ100 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን የውስጥ ልዩነቶቻቸውን እና ችግሮቻቸውን ወደ ጎን አድርገው ከ1000 በላይ ኪሎሜትር በእግራቸው በአንድነት ተጉዘው አገራቸውን ከጠላት ወራሪ በመከላከል ታሪካዊ ድል አስመዝግበዋል።

💎ክብር ሃገርን በደም መስዋዕትነት ላቆዩልን ጀግኖች አባቶቻችን።

🌟ይህ ትውልድ የአባቶቹን ጀግንነት ለመድገም የውጭ ወራሪን መጠበቅ የለበትም! እርስ በርስ መፋጀታችንን በማኅበራዊ ሰላም አክመን ÷ኃላቀርነትን በእውቀት ከትበን ÷ ዘመናችንን በይቅር ባይነት በአንድነት በመተሳሰብ አቃንተን፣ የእኛን አደዋን ለመስራት መንቃት አለብን፡፡አንዱ ካንዱ ልብለጥ ማለቱን ይተው፣አንዱ አንዱን ልግፈፍ ማለቱን ይርሳው፣ ያኔ የእኛን አደዋን እንሰራለን ፤ የእኛን አደዋን እናሸንፋለን፡፡

ሁለንተናዊ ኑሮአችን ያስጎመጀ እንዲሆን በማኅበራዊ ፣ በፓለቲካ ፣ በባህል በኢኮኖሚ የእኛን አደዋ ማበጀት አለብን፡፡ ሁላችንም የድል ታሪክን የመድገም ሀላፊነት አለብን።

በድጋሚ እንኳን ለ፻፳፱ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል አደረሰን!❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity


📍እንኳን ለ129ኛው ለታሪካዊ ከኢትዮጵያ አልፎ ለአፍሪካ ነፃነት በር ለሆነው የጥቁር ህዝቦች ኩራት የአድዋ ድል በአል በሰላም አደረሰን።

@EthioHumanity
@EthioHumanity


♦️እብድ ማለት ከተለመደው ውጪ የሚያስብ እና የሚራመድ  ሳይሆን ከተለመደው ጋር ተጣብቆ እውነተኛ ማንነቱን ክዶ ከተወለደ በኋላ የሰማውን የመጨረሻ እውነት አድርጎ በተወለደበት አካባቢ ታጥሮ ብሄሩን ማንነቱ አድርጎ ሀገሩን ብቻ ሰውነቱ አድርጎ አምኖ የሚኖር ማለት ነው።

☯አንተ ሀገር ብቻ አደለህም አንተ አለም ነህ፣ አንተ ዘር ብቻ አደለህም አንተ የፈጣሪ አምሳል ነህ፣ በፈጠረህ አምላክ ውስጥ ስትሆን የፈጠራቸውን ፍጥረቶች ሁሉ በእኩሌታ ማየት እና ማክበር ትጀምራለህ የሰውነት መለኪያው ይህ ነውና። በዚህ አለም የተፈጠርከው እንደ ካርቦን የተፃፈብህን ለማስተላለፍ ወይንም በጉልቻ መሀል እንደ ተለኮሰ እሳት የተጣደብህን ሁሉ ለማብሰል አይደለም። ከቦክሱ ወጥተህ ለማሰብ  እና አለምን ለማየት ሞክር በስሜት ድልቅታ ጋልበህ እንዳትባክን... አንተ ለሰውነት እንጂ ለማሽንነት አልተጠራህም።

♦️በሀይማኖት አጥር ታጥረህ ሌላውን አትንከስ በዘር ድንቁርና ሰክረህ ሌላውን አታራክስ በግለሰብ ጥፋት እልፎችን አትክሰስ፣ ይልቅ ወደ ልብህ ፍሰስ ተገኝ ወደ ፈጠረህ ንፁህ መቅደስ ወደ ሰራህ ፅኑ መንፈስ ክነፍ፣ በጥላቻ አትቁም ከወንዙ ጋር ፍሰስ ወደ አለም ፍለስ አቋርጥ ገስግስ መሬቴ አፈሬ አትበል አትከለል አለም'ም የአንተ ናት አንተም የአለም ነህ።

💡በሰሀራ በረሀ የሚኖሩ አልኬሚስቶች - ፔራሚዶቹን ከመጎብኘትህ በፊት ፔራሚዶቹን በልብህ ፈልገህ ልታገኛቸው ይገባል አለዛ በፔራሚዶቹ ስፍራም ብትሄድ ፔራሚዶቹን አታገኛቸውም!!'' ይላሉ!  እውነትም በውጪ ያጣችሁት ሁሉ በውስጥ ያልፈለጋችሁት ጉዳይ ነው። አፅናፈ አለም እንዲህ ካሉት ጋር ነው ምትሰራው!

📍አሁን አሁን ሰዎች ከውስጣቸው አለም እየወጡ ከውጪ በሚመጣ የሰዎች አስተያየት ልክ ራሳቸውን ይመለከታሉ... ትክክለኛ የህይወት መስታዎታቹህ ነፍሳቹ ነች እናንተ ግን ከነፍሳቹ ቤት ወታቹህ አለምን ለማትረፍ ትጋጋጣላቹ. የመሰላቸውን በሚናገሩ ሰዎች እይታ የህይወት መልካችሁን ትቀርፃላቹህ።
ቡድሀም ይላል መጥፎ አጋጣሚ ከምዕራብም ሆነ ከምስራቅ አይመጣም። ከውስጥህ ነው የሚፈልቀው።

💎የሰው መልክ ተፈጥሮ ናት የምትነፍሰው እስትንፋስ ከልብህ ድልቅታ ጋር ልትጣመር ይገባል ስትኖር ከልብህ ኑር ፣ አታስመስል!! አለም በህብረት ቢደንስብህ እንኳን፣ አንተ ከነፍስህ በሚወጣው ሙዚቃ ብቻ ተወዛወዝ፣ እብድ ይበሉህ ይህ ማእረግህ ይሁን!

💡ጥላ አልባ ሁን በፍቅር ብርሀን ከነፍስህ ጋር አብራ፣ ጭንብልህን ቅደድ የፈጣሪም ብርሀን ከወስጥህ እንዲፈስ ፍቀድ የተሰመረን አድማቂ ለመሆን አልመጣህም፣ አንተ ካርቦን አይደለህም አንተ ከነበሩትም አሁን ካሉትም ወደፊትም ከሚፈጠሩትም የሰው ፍጥረቶች ሁሉ የተለየህ ነህ። ውስጥህን በታትነህ ከሌሎች ጋር አንድ ለመምሰል አትውተርተር።

✍ Dîž Âb

            ውብ አሁን❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot




✨አሃ - /Aha Moment/

“What I always want is to have several little ‘aha’ moments where your brain is very happy.” – Scott Kim

ከመቶ ዓመት በፊት በአንዱ ዕለት ነው፣ ሰውየው የሚያማምሩ አበቦች ባሉበት የቤቱ የአትክልት ስፍራ ላይ ተቀምጦ የዕለቱን ጋዜጦች ያገላብጣል። ድንገት… ‘በሞት የተለዩ ሰዎች’ በሚለው አምድ ላይ የአንድን ሰው ዜና እረፍት አየና ክው ብሎ ደነገጠ፣ ጽሑፉን ሲያነብ ጋዜጣው እንደ መርዶ ነጋሪ ሹክክ ብሎ ቤቱ የተገኘ ጥላቢስ እንጂ ተራ ወረቀት አልመስልህ አለው፣ ክውታና ድንዛዜ፣ ደርሶ ጭውውውውው አለበት።

ብንን ብሎ ጋዜጣውን በድጋሚ ተመለከተው፣ አልተሳሳተም፣ በትክክል የሚያነበው የራሱን ዜና እረፍት ነው፣ Dynamite king dies ይላል። ‘የድማሚቱ ንጉስ አረፈ…’ ያ.. ተራራውን ገምሶ.. ቋጥኙን ፈልፍሎ.. አለታቱን ነድሎ መንገድ የሚተልመውን ድማሚት የፈጠረው ሰው አረፈ እያለ ነው… ሰውየው ራሱን ጠየቀ… ‘ይህን ዜና የማነበው በእውኔ ነው በሕልሜ?’ መልስ የለም።

💡ዜናው በዚህ ቢያበቃ ጥሩ አይደል… ስለ ‘ሟቹ’ ሌላም ነገር ይላል፣ And he was the merchant of death…(የሞት ነጋዴ እንደማለት ነው) ሳይሞት ሞተሃል ከመባሉ በላይ እንደ ሙት የሚታሰብበት መንገድ ሰውየውን የበለጠ አስደነገጠው፣ ተንቀጠቀጠ… ሰበበ ሞት ተደርጎ ነዋ የተገለጸው… የጅምላ ፍጅት ምክንያት ተደርጎ ነው የተሳለው… ‘እውነት ሞቼ ቢሆን ሰዎች የሚያስታውሱኝ እንደዚህ እያሉ ነው?’ ሲል ጠየቀ፣ ‘በፍጹም!!! ይህ ቅጽል መፋቅ አለበት!!’

🧨 ይህ ሰው አልፍሬድ ኖቤል ነው። ኖቤል ድማሚትን ‘በመፍጠሩ’ ይታወቃል፣ ግኝቱ ለመንገድ ስራ ያለው አስተዋጽዎ ጎልቶ የሚነገርለት ቢሆንም ኖቤልን ‘ነፍሰ ገዳይ’ ከሚል ስም አላስጣለውም… የፈረንሳይ ጋዜጦች “Le marchand de la mort est mort” (“The merchant of death is dead.”) ብለው ሲዘግቡ ዜናውን በዚያው ወቅት ፈረንሳይ ውስጥ ከሞተው የአልፍሬድ ኖቤል ወንድም ሉድቪግ ጋር አምታተውት ኖሯል፣ ሆኖም አጋጣሚው ኖቤልን ከጥልቅ እንቅልፉ የሚያነቃው ነበር… እናም ይህን ስም ለውጦ ማለፍ እንዳለበት የወሰነው እዚያው ነበር።

💎በፈጠራው ምክንያት ያገኘውን ሳንቲም ሰብስቦ ለበጎ ተግባር እንዲውል ሰጠ፣ በደህናው ዘመን ስለ ድንቅ ጥበቡ የተበረከተች ሳንቲም በችግሩ ጊዜ ስለ ስሙ መታደስ ወጣች፣ ያቺ ሳንቲም በዝታና በርክታ በዓለም ዙሪያ በሳይንስ፣ በስነጽሑፍ፣ በሰላም፣ በአካባቢ ጥበቃ፣ በፊዚክስና በሌሎችም በርካታ ዘርፎች ከፍ ያለ አስተዋጽዎ ለሚያደርጉ ግለሰቦች ሽልማት ሆና የምትቀርብ ሆነች።

ዛሬ ዛሬ የ Nobel Prize Winner መሆን የልዕልና መግለጫ ሆኗል፣ በዙርያችን ‘እከሌ የኖቤል ተሸላሚ ነው’ የሚለው ስያሜ ትልቅ ማዕረግ ሆኗል፣ ብዙ የምናደንቃቸው የዓለማችን ሰዎች የሽልማቱ አሸናፊ ሆነዋል፣ ጠቅላይ ሚኒስትራችንን ጨምሮ ፣ አዎን… አሁን ኖቤልን ከሞት ጋር አያይዞ ስሙን የሚያነሳ፣ ከውድመት ጋር አቆራኝቶ ስራውን የሚያወሳ አንድ ስንኳ የለም።

ከ’ሞት’ በኋላ በበጎ መታወስ የሚል ቅዥት ሰከንዶችን ተጋርቶኝ አያውቅም፣ ግና ሰው በኑረት ብቻ ሳይሆን በእልፈቱም ለሌሎች መኖር ከቻለ ድንቅነቱ ይገባኛል፣ ያም ሆኖ የበለጠ የሚመስጠው የተረኩ ክፍል ‘በሌሎች ዘንድ የጠለሸን ስም’ ለማደስ የመቁረጡ ጉዳይ ነው።

🔷አስባችሁታል፣ መንግስት ‘ለካ ሕዝብ የሚረዳኝ እንዲህ ነው?’ ብሎ ስሙን ለማደስ ሲተጋ… ፣ ባል በጸጸት ውስጥ ሆኖ ‘ለካ በሚስቴ ዓይን የምመስለው ይህን ነው?’ ብሎ እንከኑን ሲነቅስ… አባት ‘ለካስ ለልጆቼ ጥሩ ወላጅ አልነበርኩም’ ብሎ መንገዱን ለመቀየር ሲወስን… ተቋማት ‘በደንበኞቻችን ዘንድ ያለን ገጽታ ጥሩ አይደለም ለካ’ ብለው ለምርትም ሆነ አገልግሎት መሻሻል ሲሰሩ… ትራፊኮች በአሽከርካሪ ዓይን፣ አሽከርካሪዎች በተሳፋሪ ዓይን…፣ አለቆች በሰራተኛ፣ መምህራን በተማሪ፣ ፍቅረኞች በተፈቃሪያቸው፣ ብቻ ሁሉም በየአንፃራቸው ቦታ ራሳቸውን አስቀምጠው ‘አሃ…’ ቢሉ

🔑አንዳንዴ በሌሎች መስታወት ውስጥ ካላየነው በቀር የማይገለጥ ቁሸት አያጣንም፣ በወዳጅ ምክር ውስጥ ካልሆነ የማይቀና ጉብጠትም እንዲሁ ፣ ‘ለሌሎች’ ሲባል ሁሉ ይፍረስ አይባልም መቼም… ሁሉን ማስደሰት አለመቻል ብቻ ሳይሆን ‘የራስ ጣዕም’ ማጣትም ልክ አይሆንምና

ግን አለ አይደል… ‘በልክ ነኝ’ ካብ ውስጥ ያደፈጠች ክፋት፣ በማናለብኝ ጎሬ ውስጥ የተሸጎጠች ትዕቢት፣ የሌላውን ምቾት የምትነሳ ክርፋት… ምናል.. ‘አሃ…’ እያልን ብናስወግዳት።

ውብ አሁን❤️

✍ ደምስ ሰይፉ

💯 በዚህ ውብ ድልድይ እንሻገር ፣ ሁላችንም ቻናሉን በአብሮነት እንቀላቀል 💯
👇
@BridgeThoughts
@BridgeThoughts

@EthioHumanitybot


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


📍ስለ ህይወት

💡አንድ አባባል አለ በጣም የምወደው ''ቁም ነገሩ ምን ያህል እድሜ ኖረሀል ሳይሆን ምን አይነት ህይወት አሳልፈሀል'' ብዙዎቻችን ካለፍንባቸውን ህይወቶች የምንማረው እሩጫችንን ከጨረስን በኋላ በእርጅና ትናንትን ስንመለከት ነው።  በወጣትነታችን ያለፍንባቸውን የህይወት ዱካዎች አስተውለን ማጥናት ምንችል ቢሆን ግን ነጋችንን ብሩህ የማድረግ ትልቅ እድል ይኖረናል።

"የኋላው ከሌለ የለም የፊቱ" እንዲል ያገሬ ሰው... የዛሬው ህይወታችን ያለፍንባቸው የህይወት ውጣ ውረዶቻችን ቅጂዎች ናቸው ። እናም ስለ ህይወት የገባኝን ከትናንቶቼ የተማርኳቸውን እንደ አባት ልንገራቹህ.

💡በዚህ አለም ላይ ቋሚ ነገር የለም።
ዛሬ የወደዱህ ነገ ይጠሉሀል ዛሬ ያከብሩህ ነገ ይንቁሀል ዛሬ እንደ አስፈላጊ የተመለከቱህ ነገ አንተን ረስተው ሌላ ህይወትን ሲጀምሩ ታያለህ አየህ ሁሌም ቢሆን ለሰዎች አብዝተህ መጨነቅ የለብህም! ከሰዎች አብዝተህ መጠበቅ የለብህም! በዚህ አለም ቋሚ ነገር የለምና ያለህባትን ህይወት እና ግዜ ብቻ በተገቢው ማጣጣም እወቅበት!

📍ሰዎች ደስታ እና ሀዘንህን የሚፅፉልህ የህይወትህ ደራሲ እንዲሆኑ አትፍቀድላቸው! እነግርሀለው አሁንም ያለኸው አንተ እና አንተ ብቻ ናቹህ ስትሞትም የሚወዱህ ቀብረውህ ህይወትን ይቀጥላሉ... ሁሉም የመጣው ለህይወት እንጂ ለአንተ እንዳልሆነ ተረዳ!
ስለዚህም ለራስህ ክብርን ግዜን ፍቅርን መስጠት እወቅበት ከህይወት ጋር ተዛመድ!

አንድ እውነትን ተረዳ ማንም ሚወድህም ሆነ ሚንቅህ አንተ ላይ ካየው ነገር ተነስቶ ብቻ ነው ሰዎችን አብዝተህ ከማመንህ በላይ ራስህን እመን! ራስህ ላይ ስራ! ሌላው ከሰዎች የሚሰጡህን መልካም ነገሮችን ውደድላቸው አክብርላቸው ነገር ግን ይሄ የመጣው ለራስህ ካለህ ጥልቅ ክብር እንደሆነ ማስተዋል መቻል አለበህ!

♦️ስለዚህም የምትወዳቸውን ሰዎች እንዳታጣ የምትደውን ማንነትህን አትጣለው! ሌሎች ሰዎች ደግሞ ለአንተ ያሰቡ በመምሰል እነሱ በሚፈልጉት ልክ እንድትራመድ መንገድ ሊያመቻቹልህ ይችላሉ ይህ ማለት በሌላ ቋንቋ
(የግል ባርያዬ ላደርግህ እያሰብኩ ነው) እንደማለት ነው ። አንተም ስለምትወዳቸው ውለታም ስለዋሉልህ እነሱን ካለማጣት እና ለማስደሰት የራስህን ማንነት ትተዋለህ ሰዎችም ዙሪያህን እንደተቆጣጠሩ ሲሰማቸው ጥለውህ ይሄዳሉ ! አየህ በማንነትህ አትደራደር ማንም እንዲ ሁን ሊልህ ቢሞክር ከመስመሩ እንዳታሳልፈው! ሰዎች የአንተን ነገር ማክበር ሚጀምሩት ለራስህ ካለህ ፅኑ እምነት ተነስተው ነው።

💎ይቺን እወቅልኝ ማንም በዚህ አለም ያለምክኒያት አብሮህ ሊሆን አይችልም ''ማንም" ካላመንክ ይወዱኛል ብለህ ያሰብካቸውን ሰዎች ''ለምን ከኔ ጋር ሆንክ/ሽ?" በላቸው የሀገር ምክኒያቶችን ሲደረድሩልህ ትሰማለህ 

💡ያለ አንዳች ምክኒያት አንተን የሚወድህ ፈጣሪህ ብቻ ነው። ሰዎች ሁኔታዊ እንደሆኑ እወቅ የቱንም ያህል ቢወዱህ እነሱ ሊያዩህ ከሚፈልጉበት ቦታ ወርደህ ካዩህ ይለዩሀል በቃ ይሄ የሰዎች ተፈጥሮ ነው። ከነፍስህ ጋር መፋቀርን ልመድ ሰዎች ሳይኖሩ ሙሉ መሆንን ልመድ ሁሉም ትቶህ ሄዶ መፈንደቅን ልመድ በህይወት ጭለማህ ውስጥ ብቻህን መሳቅን ልመድ! ለህይወት ቁስሎችህ ሁነኛ ዶ/ር መሆንን ልመድ!

📍ራስህን በወደድክ ቁጥር ህይወት አንተን በጥልቅ መንፈስ ማፍቀር ትጀምራለች... ሰዎችም የህይወት አንዷ አካል ስለሆኑ ወደ በአንተው መሳብ ይጀምራሉ። በሰዎች አትደገፍ !  በራስህ መቆም እስኪሳንህ ድረስ ለሰዎች ራስህን አሳልፈህ አትስጥ ሰዎችን ውደድ ግን በሰዎች አትደገፍ ዘወር ቢሉ መቆም እንደምትችል አሳያቸው!

💡ስትወድቅ አይቶ ሚያነሳህ ፈጣሪ እንጂ ሰዎች አይደሉም። ሰዎች ሁሌም የተሻለን ነገር በተፈጥሮዋቸው ይፈልጋሉ ስለዚህ አንተ ከነሱ ግዜ ጥሎህ አንሰህ ከተገኘህ ጥለውህ ይሄዳሉ እንዳትረሳ! በመጨረሻም አምላክህን ህይወትህን እና ራስህን አጥብቀህ አፍቅር ! ህይወት ያን ያህል ቀላል ትሆናለች ጀግናው!

✍Dîž Âb

ውብ አሁን❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot




📍ፍቅርን ለመስበክ እንደ ጦርነት መሳሪያ መደርደር ወታደር ማሰለፍ ፤ ግዳይ መጣል አያስፈልገንም ። ቅን እና በፍቅር የተሞላች ልብ ብቻ በቂ ነው ። ከጦርነት በኋላ የምናተርፈው ነገር የፈራረሰ ከተማና ማንነት ነው ። ጀግና ነኝ ብሎ ከሚፎክረው ገዳይ ልብ ውስጥ ጥልቅ ፍርሃት ፣ ጥላቻ ፣ ጥርጣሬና ትምክህት ነው የምታገኙት ።

ጦርነት እምቅ ሀብትን አውዳሚ
እምቅ እውቀትን በታኝ፣እምቅ ሀይል ያለው ትውልድን አጥፊ ስለሆነ አስተዋይ ነኝ የሚል ሰው ሊጫወተው የማይገባ ድራማ ነው።

ምላስ የጦርነቶች ሁሉ እናት ነው፡፡ ምላስ አዳኝ ነው፤ ምላስ ገዳይ ነው፡፡ ለአንዱ ንፁህ የሆነው ለሌላው መርዝ ነው፤ አንዱን የፈወሰው ሌላውን ይገድለዋል፡፡በአለም ላይ የተደረጉ ጦርነቶች በሙሉ በስተመጨረሻ ሁሉም ሰው በሰላም ለመፍታት ቢሞክር ይህ ሁሉ ባልሆነ ነበር የሚሉ አንድምታ ይፈጥራሉ።እኔ ነኝ ልክ ፣ እኔ ነኝ አሸናፊ በማለት የሚነሳ ትውልድ በእልህ የታነቀ ፣ቂምን ያረገዘ ሰለሆነ የሚመጣውን የሀገር ውድመት አያስተውልም።

የህይወት ለውጦችን ከመቃወም ይልቅ ራስን አስተጋብሮ መራመድ ጥበብ ነው ። ሕይወት ካንተ ውጪ ሳትሆን ከእናንተ ጋር ናት፡፡

📍እናም ወዳጄ

ራስህን ስጋት አታድርግ፡፡ መልካም ሰው ማንንም አያማርርም ። ያለፍቅር ሕይወት ዋጋ የለውም ፡፡ ፍቅር የሕይወት ውሃ ነው ፣ ፍቅርን የሚያቅ ሰው የነፍስ መብራት ነው። ሁሉም ነገር እና ሁሉም ሰው ከማይታዩ ብዙ ህብረቶች ጋር የተሳሰረ ነው። 

የሰዎችን ልብ አትስበር ፡፡ከአንተ ይልቅ ደካማ እንደሆኑ አርገህ ቁልቁል አትመልከት፡፡በአንደኛው የዓለም ክፍል ውስጥ ያለ ሀዘን መላውን ዓለም ሊያሰቃይ ይችላል ፣በዛው ልክ ደግሞ  የአንድ ሰው ደስታ እና ፈገግታ መላውን ዓለም ፈገግ ሊያደርገው ይችላል።

💡አብዛኛዎቹ ግጭቶች እና ውጥረቶች በቋንቋ ምክንያት የሚከሰቱ ናቸው። በፍቅር የሚለመልም እንጂ የሚወድም ግለሰብም ማህበረሰብም ሆነ ሀገር አላየንም ።በፍቅር የተሞላች ልብ ውስጥ ጥንካሬ ፣ቅንነትና ለሁሉ አሳቢነት በአንድንት ጎጆ ሰርተው በፍቅር ሲኖሩ ታያላችሁ ።

ሰው ከፍቅር ውጭ ሊኖር እንዴት ይቻለዋል ! ስለ ፍቅር ስበክ ፣ ስለ ፍቅር  ኑር !

            ውብ አሁን❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot

20 last posts shown.