Video is unavailable for watching
Show in Telegram
✨የትላንት ታሪኮቻችን የሚያስተምሩን ዛሬም ላይ ታሪክ መስራት እንደሚቻል ነው።
ታሪክን መዘከር እና ለትውልድ ማውረስ እንደተጠበቀ ሆኖ ከትናንት ታሪካችን ጽናትን፣ አብሮነትን እና አገራዊ አንድነትን በመላበስ ዛሬ ላይ የትላንቱን ምኒሊክን መሆን፣ በድህነት ላይ መዝመት፣ ኋላቀርነትን መታገል፣ ለመርህ ተገዥ ሆኖ መተባበር የአሁን አድዋ ድል ነው።
✨ታሪክ በራሱ ነፃ አያወጣም። ታሪክን ተመርኩዞ ጭቆናን አሸንፎ፣ ነፃነትን መቀናጀት ግን ይቻላል። አድዋ ! በጥቁር ህዝቦች ታሪክ ትልቁ የድል ማማ! ነውና። በአድዋ ጦርነት ከ100 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን የውስጥ ልዩነቶቻቸውን እና ችግሮቻቸውን ወደ ጎን አድርገው ከ1000 በላይ ኪሎሜትር በእግራቸው በአንድነት ተጉዘው አገራቸውን ከጠላት ወራሪ በመከላከል ታሪካዊ ድል አስመዝግበዋል።
💎ክብር ሃገርን በደም መስዋዕትነት ላቆዩልን ጀግኖች አባቶቻችን።
🌟ይህ ትውልድ የአባቶቹን ጀግንነት ለመድገም የውጭ ወራሪን መጠበቅ የለበትም! እርስ በርስ መፋጀታችንን በማኅበራዊ ሰላም አክመን ÷ኃላቀርነትን በእውቀት ከትበን ÷ ዘመናችንን በይቅር ባይነት በአንድነት በመተሳሰብ አቃንተን፣ የእኛን አደዋን ለመስራት መንቃት አለብን፡፡አንዱ ካንዱ ልብለጥ ማለቱን ይተው፣አንዱ አንዱን ልግፈፍ ማለቱን ይርሳው፣ ያኔ የእኛን አደዋን እንሰራለን ፤ የእኛን አደዋን እናሸንፋለን፡፡
ሁለንተናዊ ኑሮአችን ያስጎመጀ እንዲሆን በማኅበራዊ ፣ በፓለቲካ ፣ በባህል በኢኮኖሚ የእኛን አደዋ ማበጀት አለብን፡፡ ሁላችንም የድል ታሪክን የመድገም ሀላፊነት አለብን።
በድጋሚ እንኳን ለ፻፳፱ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል አደረሰን!❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
ታሪክን መዘከር እና ለትውልድ ማውረስ እንደተጠበቀ ሆኖ ከትናንት ታሪካችን ጽናትን፣ አብሮነትን እና አገራዊ አንድነትን በመላበስ ዛሬ ላይ የትላንቱን ምኒሊክን መሆን፣ በድህነት ላይ መዝመት፣ ኋላቀርነትን መታገል፣ ለመርህ ተገዥ ሆኖ መተባበር የአሁን አድዋ ድል ነው።
✨ታሪክ በራሱ ነፃ አያወጣም። ታሪክን ተመርኩዞ ጭቆናን አሸንፎ፣ ነፃነትን መቀናጀት ግን ይቻላል። አድዋ ! በጥቁር ህዝቦች ታሪክ ትልቁ የድል ማማ! ነውና። በአድዋ ጦርነት ከ100 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን የውስጥ ልዩነቶቻቸውን እና ችግሮቻቸውን ወደ ጎን አድርገው ከ1000 በላይ ኪሎሜትር በእግራቸው በአንድነት ተጉዘው አገራቸውን ከጠላት ወራሪ በመከላከል ታሪካዊ ድል አስመዝግበዋል።
💎ክብር ሃገርን በደም መስዋዕትነት ላቆዩልን ጀግኖች አባቶቻችን።
🌟ይህ ትውልድ የአባቶቹን ጀግንነት ለመድገም የውጭ ወራሪን መጠበቅ የለበትም! እርስ በርስ መፋጀታችንን በማኅበራዊ ሰላም አክመን ÷ኃላቀርነትን በእውቀት ከትበን ÷ ዘመናችንን በይቅር ባይነት በአንድነት በመተሳሰብ አቃንተን፣ የእኛን አደዋን ለመስራት መንቃት አለብን፡፡አንዱ ካንዱ ልብለጥ ማለቱን ይተው፣አንዱ አንዱን ልግፈፍ ማለቱን ይርሳው፣ ያኔ የእኛን አደዋን እንሰራለን ፤ የእኛን አደዋን እናሸንፋለን፡፡
ሁለንተናዊ ኑሮአችን ያስጎመጀ እንዲሆን በማኅበራዊ ፣ በፓለቲካ ፣ በባህል በኢኮኖሚ የእኛን አደዋ ማበጀት አለብን፡፡ ሁላችንም የድል ታሪክን የመድገም ሀላፊነት አለብን።
በድጋሚ እንኳን ለ፻፳፱ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል አደረሰን!❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity