Ethiopian News Hub 🇪🇹


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


እንኳን ወደ ቴሌግራም ቻናላችን በደህና መጡ
👉በአለም ላይ ያሉ አዳዲስ ክስተቶችን
👉ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛው መድረሻ! ልምድ ባካበቱ ጋዜጠኞች
👉አዳዲስ ዜናዎችን
👉ጥልቅ ትንታኔዎችን እና አስተያየቶችን ለእርስዎ ለማቅረብ ያለመታከት ይሰራል። በኛ ቻናል ምንም አያመልጥዎትም - ከፖለቲካ እስከ ንግድ ፣ ከመዝናኛ እስከ ሳይንስ ያለውን ሁሉ አንሸፍናለን


Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


#Tigray

“ በጀት ተፈቅዷል። ትክክለኛ ቁጥሩን በሚመለከት ግን ገና እንነጋገራለን ” - አቶ ጌታቸው ረዳ

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የፌደራል መንግስት፤ ለትግራይ ክልል የበጀት ድጎማ ለመልቀቅ መስማማቱ ገለፁ።

አቶ ጌታቸው ፤ የፌደራል መንግስት ለትግራይ ክልል በጀት ለማስተላለፍ ከስምምነት ላይ መድረሱን የገለፁት ለ “ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ” ድረገፅ በሰጡት ቃል ነው።

ምንም እንኳን በጀት ለማስተላለፍ ስምምነት ላይ ቢደረስም የሚለቀቀውን የገንዘብ መጠን በተመለከተ ግን ገና ውይይት እንደሚካሄድ አቶ ጌታቸው ገልጸዋል።

አቶ ጌታቸው ረዳ ምን አሉ ?

“ በጀት ተፈቅዷል። [ትክክለኛ] ቁጥሩን በሚመለከት ግን ገና እንነጋገራለን ”

NB. ከተሾሙ በነገው ዕለት አንድ ሳምንት የሚሞላቸው አቶ ጌታቸው ረዳ 11 የጊዜያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ አባላትን ይዘው ከፌደራል መንግስት ጋር ለመነጋገር በአዲስ አበባ ከተማ ይገኛሉ።

የትግራይ ክልል የበጀት ድጎማ መቼ እና ለምን ነበር የተቋረጠው ?

የፌዴሬሽን ምክር ቤት በመስከረም 2013 ባስተላለፈው ውሳኔ ነው የትግራይ ክልል የበጀት ድጎማ የተቋረጠው።

የበጀት ድጋፍ እንዲቋረጥ የተደረገው፤ ክልሉ ከፌደራል መንግስት እውቅና ውጭ “ኢ-ህገ መንግስታዊ ምርጫ አካሄዷል” በሚል ነው።

Credit - www.ethiopiainsider.com


ኡጋንዳዊያን ሀብት ንብረታቸውን እየሸጡ ወደ ኢትዮጵያ እየተሰደዱ መሆኑ ተሰምቷል። ኡጋንዳዊያኑ የአለም ፍፃሜ በመድረሱ ወደ ኢትዮጵያ እየገባን ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ የአለም ፍፃሜ ፈጥኖ አይደርስም ማለታቸው Africa News ከ KAMPALA, Uganda ዘግቧል:: https://www.aa.com.tr/en/africa/hundreds-of-ugandan-sect-members-flee-to-ethiopia-fearing-doomsday/2837933#


exit exam.zip
12.9Mb
⨳blueprint for national exit examination to be held in 2015 E.c


ለዘንድሮ ተመራቂ ተማሪዎች ለእያንዳንዱ ዲፓርትመንት ለመውጫ ፈተና የተዘጋጀ(blue print)

ማሳሰቢያ፡-ከላይ ባለው ፋይል ያልተለቀቀ የትምህርት ክፍል ካለ ከዲፓርትመንት ሀላፊያችሁ ጋር በመነጋገር ሙሉ መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ።


ተመራቂ ተማሪዎች ራሳችሁን ለመውጫ ፈተና ከወዲሁ እንድታዘጋጁ  እናሳስባለን‼️


በህንድ ሚስቱ ከሌላ ወንድ ጋር የሄደችበት ባል በበቀል ያፈቀረችውን ሰው ሚስት አገባ

⚡️በህንድ ቢሃር ግዛት ኔራጅ እና ሩቢ ዴቪ የተባሉ ጥንዶች እ.ኤ.አ በ2009 ጋብቻቸውን ፈፅመው አራት ልጆችን ወልደው ለመሳም በቅተዋል። በጊዜ ሂደት ግን የኔራጅ ሚስቱ ሙከሽ ከሚባል ሌላ ወንድ ጋር ግንኙነት ትጀምራለች። ይህንን ግንኙነት ለመቁረጥ የከበዳት ሩቢ ባሏን ትታ ከሙከሽ ጋር ለመኖር ትወስናለች።

⚡️ኔራጅ ሽማግሌዎችን ልኮ ባለቤቱን እና ሙከሽ ቢያስመክርም ፍቃደኛ ሊሆኑ አልቻሉም።ኔራጅ ለፖሊስ ክስ ቢመሰርትም ወዳና ፈቅዳ ወደ ሙከሽ ቤት መግባቷን ትናገርና ክሱ ውድቅ ይሆናል።

⚡️ኔራጅ ጥላው የሄደችው ሚስቱ ያገባት ግለሰብ ባለትዳርና የሁለት ልጆች አባት መሆኑን እንደ ጥረ አጋጣሚ ይወስደዋል።ሚስቱ ወደ ቤት የመመለስ ፍላጎት እንደሌላት ካየ በኋላ የሙኬሽን ሚስት እንድታገባው ይጠይቃታል። እሷም በጥያቄው ተደስታ ጥንዶቹ ባለፈው ወር ጋብቻቸውን ፈፅመዋል።አስገራሚው የፍቅር ታሪክ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በካጋሪያ አውራጃ ውስጥ የከተማው መነጋገሪያ ሆኖ ቆይቷል። ሁሉም ልጆች ወደ እናቶቻች በሚል ስምምነት ፈፅመዋል።


ታዋቂው ቲክቶከር በሪያሊቲ ሾው ሊመጣ ነው

⚡️ሴኔጋል ተወልዶ በጣሊያን ያደገው ታዋቂው ቲክቶከር ካቢ ላሜ በጣሊያን የሪያሪቲ ሾው ቴሌቪዥን ላይ የሚቀርበውን የጣሊያኑን ጎት ታለንት በዳኝነት ለመምራት መቀላቀሉን የአፍሪካን ላይፍስ መረጃ ያሳያል፡፡

⚡️ላሜ በአሁኑ ጊዜ በአለማችን ካሉ ተፅዕኖ ፈጣሪ ቲክቶከሮች በዋናነት የሚጠቀስ ሲሆን የተለያዩ ውስብስብ ዘልማዳዊ ድርጊቶችን እና አፈ-ታሪኮችን እንዴት ቀለል ባለ መንገድ ሊቀርቡ እንደሚገባ የሚያሳዩ አጫጭር ቪዲዮዎችን በማቅረብ ይታወቃል። 

⚡️ላሜ በ2020 የፋብሪካ ስራውን ካጣ በኋላ ወደ ቲክቶኩ ዓለም በመግባት በአጭር ጊዜ ውስጥ ከ150 ሚሊዮን በላይ ተከታዮችን ማፍራት የቻለ እና ዓመታዊ ገቢው 13 ሚሊዮን ዶላር የደረሰ ቲክቶከር ነው።


" ለእኛም የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት ይድረሱልን " - የዳዋ ዞን አስተዳደር

በሶማሌ ክልል ዳዋ ዞን አስተዳደር ባጋጠመ ድርቅ በርካታ እንስሳት የሞቱ ሲሆን  የሰዎች ሕይወትም አደጋ ላይ መውደቁ ተገልጿል።

የዞኑ አስተዳደር ያለው ሁኔታ ከአቅም በላይ መሆኑን አስታውቋል።

ከኦሮሚያ የቦረና ዞን ጋር የሚዋሰነው ዞኑ፣ በድርቅ የተነሳ ከሚሞቱ እንስሳት አልፎ ሰዎች #ለሆስፒታል እየተዳረጉ መሆኑን ገልጿል፡፡

የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ መሐመድ ሀቢቻ ለሪፖርተር የሰጡት ቃል ፦

" የድርቁ ጉዳት ከዞኑ አቅም በላይ ነው።

ዞናችን ከቦረና ጋር በሁለት ወረዳዎች በኩል ይዋሰናል፡፡ ወደ 700 ሺሕ የሚጠጋ አርብቶ አደር ነዋሪ ያለው ሲሆን፣ ለ3 ተከታታይ ዓመታት የደረሰው ድርቅ ከብቱን በሙሉ ጨርሶበታል።

በክልሉ አደጋ ሥጋት ቢሮና በተለያዩ የዕርዳታ ድርጅቶች ርብርብ ዘንድሮ ለድርቁ ተጎጂዎች ዕርዳታ እየቀረበ ነው ይሁን እንጂ ዕርዳታው በቂ አይደለም። ችግሩም ከአቅም በላይ ነው።

በኦሮሚያ ክልል ለሚገኘው ለአጎራባቻችን ቦረና ዞን በአገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ እንዳለው ሁሉ፣ ለእኛም የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት ይድረሱልን። "

ዳዋ ዞን በሥሩ ሞያሌ፣ ሙባረክ፣ ካደዱማና ሁደት የተባሉ አራት ወረዳዎች ያሉት ሲሆን ለሦስት ተከታታይ ዓመታት ዝናብ ባለማግኘቱ ትልቁ የዳዋ ወንዝ ጭምር ደርቋል።

ድርቅ የሚቋቋሙ ግመሎችን ጨምሮ ከብቶችና ፍየሎች በከፍተኛ ቁጥር ማለቃቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።


የቴክኒክና ሙያ ተቋማት መግቢያ ነጥብ ይፋ ሆነ!

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በአዲሱ የትምህርትና ሥልጠና ፖሊሲ እና በ2015 የሥልጠና ዘመን የቴክኒክና ሙያ ተቋማት መግቢያ ነጥብ ላይ መግለጫ ሰጥቷል፡፡

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል እንዳስታወቁት፤ሚኒስቴሩ የሥራ ገበያውን እና የኢንዱስትሪውን ፍላጎት መሰረት በማድረግ የ2015 የሥልጠና ዘመን የቴክኒክና ሙያ ተቋማት መቀበያ መቁረጫ ነጥብን እንዳዘጋጀም ነው የጠቆሙት፡፡

በዚህም መሰረት ከቴክኒክና ሙያ ውጪ ባሉ ማዕከላት የሚስተናገዱትን ሳይጨምር በሥልጠና ዘመኑ 608,666 የሚሆኑ ሰልጣኞች ወደ ቴክኒክና ሙያ ይገባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ሚኒስትሯ ጨምረው ገልፀዋል፡፡

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ በበኩላቸው፤ በዚህ አመት የተዘጋጀው መቁረጨ ነጥብ በ2013/2014 የሥልጠና ዘመን በተለየየ ምክንያት ወደ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስርዓት ያልገቡ ተማሪዎች ግን የሚስተናገዱት በ 2014 ዓ.ም በነበረው የመቁረጫ ነጥብ መሰረት ይሆናል፡፡

የ2015 ወደ ቴክኒክና ሙያ ተቋማት መግቢያ ነጥብ ከላይ ባለው ሰንጠረዥ ላይ ተያይዟል።


ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ መቀሌ ገቡ !!

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በብፁዕ አቡነ ዮሐንስ የሽኝት ሥነ ሥርዓት ላይ ለመገኘት ወደ መቐለ አቀኑ።

ቅዱስነታቸው ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትንና ሊቃውንትን አስከትለው በብፁዕ አቡነ ዮሐንስ ሽኝት ሥነ ሥርዓት ላይ ለመገኘት ወደ መቐለ ሲጓዙ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የኒውዮርክ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በቦሌ አለም አቀፍ ኤርፖርት ተገኝተው ከቅዱስነታቸው ቡራኬ ተቀብለዋል ።

ምንጭ: ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት

#ዳጉ_ጆርናል


ቴዲ አፍሮ 1 ሚሊዮን ብር በቦረና ችግር ላይ ለሚገኙ ዜጎች አደረገ !!

#ዓድዋ_127_ለቦረና

⚡️የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን ቴዲ አፍሮ የዘንድሮን የዓድዋ ድል በዓል መታሰቢያ ምክንያት በማድረግ በድርቅ ሳቢያ አስቸኳይ እርዳታ ለሚፈልገው የቦረና ሕዝባችን የ1ሚልየን ብር ድጋፍ አድርጓል።

Via :- ያሬድ ሹመቴ


በአዲስ አበባ በአንድ ግቢው ውስጥ ጨቅላ ህጻን በመጸዳጃ ቤት ውስጥ ተጥሎ ህይወቱ አልፎ ተገኘ

👉ከ15 ቀናት በፊት በዚሁ ግቢ ውስጥ መንታ ህጻናት ህይወታቸዉ አልፎ ተገኝቷል


ትላንት የካቲት 19 ከምሽት 5:43 ሰዓት ላይ በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ልዩ ቦታዉ አባጃሌ በተባለዉ አካባቢ ጨቅላ ህጻን በመጸዳጃ ቤት ተጥሎ ህይወት አልፎ መገኘቱን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል ።

የህጻኑን አስከሬን የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ከመጸዳጃ ቤት ዉስጥ አዉጥተዉ ለፖሊስ ማስረከባቸውን የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለብሰራት ሬድዮ ተናግረዋል።

ህጻኑ በተጠለበት በዚሁ ግቢ ዉስጥ ከ15 ቀናት በፊት ሁለት መንታ ህጻናት ህይወታቸዉ አልፎ በመገኘቱ የህጻናቱን ወላጅ እናት በቁጥጥር ስር አዉሎ ፓሊስ እያጣራ ባለበት ሁኔታ ይህ ክስተት ማጋጠሙንም አቶ ንጋቱ ጨምረው ነግረውናል።

ትላንት ምሽት በመጸዳጃ ቤት ተጥሎ የተገኘዉን ጨቅላ ህጻን የማን እንደሆነ ጉዳይም ፖሊስ እያጣራ ይገኛል።


ከሁለት ዓመት በፊት በአዲስ አበባ ላይ “ዕልቂትና ውድመት” ሊያስከትል ይችላል የተባለ የኬሚካል ክምችት መኖሩን መንግስት ራሱ አስታውቆ ነበር። ይህ አደገኛ የኬሚካል ክምችት አሁንም መፍትሄ አላገኘም። ዋዜማ ለምን ችግሩን ማስወገድ አልተቻለም? ስትል ጠይቃለች። አንብቡት

ዋዜማ – በግልና መንግስት ተቋማት ወደ አገር ውስጥ ገብተው የመጠቀሚ ጊዜ ያለፈባቸውን ኬሚካሎችን ለማስወገድ ከሁለት አመት በፊት ተይዞ የነበረው አቅድ የዓለም ባንክና ሌሎች የእርዳታ ድርጅቶች ሊሰጡ ቃል የገቡትን ገንዘብ ባለመልቀቃቸው ኬሚከሎቹ አሁንም አደጋ እንደደቀኑ መሆናቸውን የመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጄንሲ አስታወቀ፡፡
የኬሚካል ክምችቱ የተፈጠረው ከውጪ ሀገር ለተለያዩ አገልግሎቶች ተገዝተው በወቅቱ ጥቅም ላይ ባለመዋላቸው የመጠቀሚያ ጊዜያቸው በማለፉ ነው።
የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሃጂ ኢብሳ ለዋዜማ እንደገለጹት የተከማቹ ኬሚካሎቹን ለማስወገድ በ 2013 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ አማካኝነት ጥናት ተደርጎ ለማስወገድ እቅድ ተይዞ የነበረ ቢሆንም ገንዘቡን ማግኘት ባለመቻሉ ከእቅዱ ተግባራዊ መሆን አልቻለም።

‹‹ኬሚካሉን ለማስወገድ በጀት ይፈለጋል፤ ይህን በጀት ገንዘብ ሚንስቴር እፈልጋለሁ አለ፤ ነገር ግን ገንዘቡ አልተገኘም ጉዳዩም ባለበት ቆሟል›› ብለዋል ዳይሬክተሩ፡፡

ኬሚካሉን ለማስወገድ በጀት ከመንግስት መመደብ የማይቻል በመሆኑና ይህን ገንዝብ ማግኘት የሚቻለው ከአለም ባንክ እና ሌሎች የእርዳታ ድርጅቶች ቢሆንም፤ እነዚህ ተቋማት ባለፉት ሁለት አመታት ከኢትዮጵያ ጋር የነበራቸው ግንኙነት ጥሩ ባለመሆኑ ገንዘቡ ተገኝቶ ኬሚካሉ ሊወገድ አልቻለም ብለዋል፡፡

አቶ ሃጂ እንደተናገሩት በአዲስ አበባና ከአዲስ አበባ ውጭ በክምችት ላይ ያለው ኬሚካል ለማስወገድ የሚረዳውን ገንዘብ ለማግኘት በገንዘብ ሚንስቴር የኢኮኖሚክ ትብብር ሚንስቴር ዴእታ ወ/ሮ ሰመሪታ ሰዋሰው ለሚመሩት ዘርፍ መመራቱን ተናግረዋል፡፡
ዋዜማ ስለጉዳዩ ማብራሪያ የጠየቃቸው ወ/ሮ ሰመሪታ ጉዳዩን እናጣራለን የሚል መልስ በመስጠት ስልካቸውን ዘግተዋል፡፡

የመጠቀሚያ ጊዜያቸው ያለፈባቸውና ከፈነዱ በሰዎችና ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያስከትሉ ይችላሉ የተባሉት የግብርናና የኢንዱስትሪ ኬሚካሎች ሲሆኑ ዲዲቲ፣ ኦርጋኖ ፎስፌትና ኦርጋኖ ክሎሪን እና ሌሎችም ይገኙበታል፡፡

የክምችቱ መጠን ምን ያህል እንደሆነ የጠየቅናቸው ባለሙያዎች አብዛኛው ክምችት አዲስ አበባ መሆኑንና ቀላል የማይባል ክምችት በክልል ከተሞች መኖሩን ነግረውናል። የክምችቱን መጠን በአሀዝ መግለፅ ግን አደጋውን የበለጠ አስፈሪ ከማድረግ በዘለለ ሌላ አደጋ ይጋብዛል በሚል ከማብራራት ተቆጥበዋል።

አቶ ሃጂ ከሁለት አመት በፊት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በአዲስ አበባና ከአዲስ አበባ ውጭ ተከማችተው የሚገኙት ኬሚካሎች በቶሎ ካልተወገዱ አደጋቸው የከፋ ሊሆን እንደሚቸል ተናግረው ነበር፡፡

በነሃሴ 2012 ዓ.ም በመካከከለኛው ምስራቅ ውስጥ በምትገኘው ሊባኖስ – ቤይሩት ባጋጠመ የ2,700 ቶን አሞኒየም ናይትሬት የተሰኘ ከባድ የኬሚካል ክምችት ፍንዳታ ከሁለት መቶ በላይ ሰዎች ህይወታቸውን ማለፉን፣ ከ4 ሺህ በላይ ሰዎች ደግሞ የተለያየ መጠን ያለው ጉዳት እንደደረሰባቸውና ከአስራ አምስት ቢሊዮን ዶላር በላይ የኢኮኖሚ ውድመት ማጋጠሙ ይታወሳል፡፡

በኢትዮጵያ ጊዜያቸው ያለፈባቸው ተከማችተው የሚገኙ ዲዲቲ፣ ኦርጋኖ ፎስፌትና ኦርጋኖ ክሎሪን ኬሚካሎችን ለማስወገድ ከ4.5 ሚሊዮን ዶላር በላይ እንደሚያስፈልግ፣ የአካባቢ ደንና አየር ንብረት ለውጥ ኮሚሽን መረጃ ያሳያል፡፡

[ዋዜማ]


ማንችስተር ዩናይትድ ሻምፒዮን ሆኗል🏆

⚡️በዌምብሌይ ስታዲየም በተደረገው የእንግሊዝ ካራባኦ ካፕ ፍፃሜ ጨዋታ ማንችስተር ዩናይትድ ኒውካስል ዩናይትድን 2ለ0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ሻምፒዮን መሆኑን አረጋግጧል።


#MoE

የRemedial ፕሮግራም ምደባ ይፋ ሆኗል።

በ2014 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች የተቋም ምደባችሁን ከአሁን ሰዓት ጀምሮ ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ማየት የምትችሉ መሆኑንና በተመደባችሁበት የትምህርት ተቋሞች በሚያስተላልፉት ጥሪ መሰረት የ Remedial ፕሮግራሙን እንድትከታተሉ ብሏል ትምህርት ሚኒስቴር።


የተመደባችሁበትን ተቋም ለማየት የቀረቡ አማራጮች

Website:

https://placement.ethernet.edu.et
SMS: 9444


ከህዝብ ዕይታ ርቆ የነበረው የባልደራስ ፓርቲ ፕሬዝዳንት አቶ እስክንድር ነጋ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉ ተነገረ!!

ለወራት ከህዝብ ዕይታ ርቆ የነበረው እና ድምፁ ጠፍቶ የሰነበተው እስክንድር ነጋ ቡሬ ላይ ተገኝቶ ወደ ባህር ዳር የተወሰደ ሲሆን በአጠቃላይ ጉዳዮች ለማጣራት በማረፊያ ቤት እንደሚገኝ የወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
#ዳጉ_ጆርናል


የእነ አባ ሳዊሮስ እግድ ተነሳ።

የካቲት 3 ቀን 2015 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን ጉዳይ ሚከታተለው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሁለተኛ መሠረታዊ መብቶች እና ነጻነቶች ምድብ ችሎት በሕገ ወጥ መንገድ በተፈጸመው ሹመት ላይ የተሳተፉት ግለሰቦች ላይ እግድ ማስተላለፉ ይታወሳል።

በቅርቡ የተፈጸመውን ዕርቅ ተከትሎ ፦

- የአባ ሳዊሮስ፣
- የአባ ኤዎስጣቴዎስ
- የአባ ዜና ማርቆስ #ዕግድ_መነሳቱን የቤተክርስቲያና መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

ቀሪዎቹ 26 ግለሰቦች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅጽር ግቢ ውስጥ እንዳይገቡ የተጣለው ዕግድ እንዲቀጥል ፍርድ ቤቱ መወሰኑ ተገልጿል።

#ተሚማ


በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሩሲያን ለማዉገዝ በተደረገ ስብሰባ ኢትዮጲያን ጨምሮ 15 የአፍሪካ ሀገራት ድምፀ ተአቅቦ አደረጉ

በትላንትናዉ እለት በኒውዮርክ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ከአንድ አመት ገደማ በፊት ሩሲያ በዩክሬን ላይ የፈፀመችውን ወረራ የሚያወግዝ ውሳኔን 15 የአፍሪካ ሀገራት ድምፁን ተአቅቦ ሲያደርጉ 28 ሀገራት ደግፈዋል።የውሳኔ ሃሳቡ ወታደሮቹ ከዩክሬን እንዲወጡ እና ጦርነቱ እንዲቆም የሚጠይቅ ነዉ፡፡

መለኪያው በህጋዊ መንገድ አስገዳጅ ሳይሆን ፖለቲካዊ ክብደትን ይይዛል።ዉሳኔዉ በህጋዊ መንገድ አስገዳጅ ሳይሆን ፖለቲካዊ ክብደት ያለዉ ነዉ፡፡በዉሳኔ ላይ በተሰጠዉ ድምጽ 141 የዓለም ሀገራት ሩሲን ሲያወግዙ፣ በ32 ድምፀ ተአቅቦ እና በሰባት ድምጽ ተቃውሞ ቀርቧል።ድምጸ ተአቅቦ ካደረጉ ሀገራት መካከል ግማሽ ያህሉ ከአፍሪካ ናቸዉ፡፡

ደቡብ አፍሪካ፣ ኢትዮጵያ፣ አልጄሪያ፣ አንጎላ፣ ብሩንዲ፣ ናሚቢያ፣ መካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ኮንጎ ብራዛቪል፣ ጋቦን፣ ጊኒ፣ ሞዛምቢክ፣ ሱዳን፣ ቶጎ፣ ኡጋንዳ እና ዚምባብዌ ድምጽ ተአቅቦ ያደረጉ ሀገራት ናቸዉ፡፡ኤርትራ እና ማሊ ዉሳኔዉን የተቃወሙ ብቸኛ የአፍሪካ ሀገራት ናቸው።ሴኔጋል፣ቡርኪናፋሶ፣ካሜሩን፣ኢኳቶሪያል ጊኒ፣ኤስዋቲኒ እና ጊኒ ቢሳው በምርጫው አልተሳተፉም።

ናይጄሪያ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ግብፅ፣ ጋና እና ኬንያ ሩሲያን ከሚያወግዘዉ ድምጸ ዉሳኔዉን ከደገፉት የአፍሪካ ሀገራት መካከል ይገኙበታል።የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ የውሳኔ ሃሳቡን በደስታ መቀበላቸዉን በማንሳት ይህም የአለም አቀፍ ድጋፍ ትልቅ ምልክት ነው ብለዋል።

Via:- ዳጉ ጆርናል


ባለቤቱን ከስምንት ጊዜ በላይ በስለት በመውጋት ለመግደል የሞከረው ባል በ10 አመት ፅኑ እስራት ተቀጣ

በምስራቅ ጎጃም ዞን በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ቀበሌ 09 ልዩ ቦታው ዲማ ኮሌጅ አካባቢ በተከራዩት ቤት ውስጥ ባለቤቱን ከስምንት ጊዜ በላይ በስለት በመውጋት የግድያ ሙከራ የፈጸመዉ ባል በ10 አመት ፅኑ እስራት መቀጣቱ ተነግሯል ።

ተከሳሽ መምህር ጤናው ዘሪሁን ከባለቤቱ ከወ/ሮ ማመኔ አለም ጋር በመኖሪያ ቤታቸው ነሐሴ 16 ቀን 2011 ዓ.ም ከምሽቱ 2፡00 ሰዓት ከቅናት በመነጨ ስሜት አለመግባባት እንደተፈጠረ ተገልጿል ። የተፈጠረውን አለመግባባት መነሻ በማድረግ የባለቤቱን የሰውነት ክፍለ ከስምንት ጊዜ በላይ በስለት በመውጋት ለመግደል እንደሞከረ የተገለፀ ሲሆን ህብረተሰቡ ለፖሊስ በሠጠው ጥቆማ መሠረት በቁጥጥር ስር እንደዋለ የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ፓሊስ መመሪያ ኮሚኒኬሽን እና ሚዲያ ዋና ክፍል ምክትል ኮማንደር ዩሃንስ በየነ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል ።

ፓሊስ አስፈላጊውን ምርመራ በማድረግ የክስ መዝገብ ለዞን አቃቢ ህግ በመላክ ክስ የተመሰረተ ሲሆን ተከሳሽ ለምስራቅ ጐጃም ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአዕምሮ መታወክ ያለበት መሆኑን በማስረዳቱ ፍርድ ቤቱ በህክምና እንዲረጋገጥ ትዛዝ ሰጥቶ እንደነበር ተገልጿል ። ነገር ግን ፍርድ ቤቱ በህክምና እንዲረጋገጥ ትዕዛዝ በሰጠው መሰረት በተደጋጋሚ በአማኑኤል አዕምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ተመርምሮ የአዕምሮ ጤና መታወክ ችግር እንደሌለበት መረጋገጡ ተገልጿል ።

በዚህ መሰረት የምስራቅ ጐጃም ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት የካቲት 13 ቀን 2015 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ጤናው ዘሪሁን ወንጀሉን ስለመፈፀሙ በሠው እና በህክምና ማስረጃ በመረጋገጡ በ10 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ የወሰነበት መሆኑን ጨምረው ምክትል ኮማንደር ዩሃንስ ገልፀዋል ።


የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ-አቢጃን-ኒው ዮርክ የቀጥታ በረራ ከግንቦት 21 ቀን 2015 ጀምሮ በድጋሚ እንደሚጀምር አስታወቀ።

⚡️በረራው ከፈርንጆቹ ሰኔ 2019 ጀምሮ የነበረ ቢሆንም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት በመጋቢት 2020 መቋረጡን አመልክቷል።

⚡️ወደ ኒው ዮርክ የሚደረገው የቀጥታ በረራ በድጋሚ በፈረንጆቹ ጥቅምት 2020 በቶጎ ሎሜ በኩል ተጀምሮ እንደነበር ገልጿል።

⚡️በዚህም ግንቦት 21 ቀን 2015 ዓ.ም በሚጀመረው የአዲስ አበባ- አቢጃን-ኒው ዮርክ የቀጥታ በረራ በሳምንት ለአራት ቀናት እንደሚደረግ አየር መንገዱ አስታውቋል።


የናይጄሪያ እግር ኳስ ክለብ መሪ ሜዳ ውስጥ ውሃ ሽንት ሲሸኑ በመገኘታቸው ተቀጡ

የናይጄሪያ እግር ኳስ ባለስልጣናት በኢባዳ የሚገኘውን የአንደኛ ዲቪዚዮን ክለብ ወደ 1,000 ዶላር የገንዘብ ቅጣት በክለቡ አንድ ባለስልጣን ላይ የጣለ ሲሆን በመጫወቻ ሜዳ ላይ ውሃ ሽንህ ሲሸኑ መታየታቸውን ተከትሎ ነው።

ድርጊቱ የተፈፀመው እሁድ እለት ባለሜዳው ሹቲንግ ስታርስ በሜዳቸው ከአክዋ ዩናይትድ ጋር ጨዋታ ከመጀመሩ በፊት የተነሳ ፎቶ መሆኑ ተመላክቷል። ድርጊቱን ፈፅመዋል የተባሉት አውዋል መሀመድ ከናይጄሪያ ፕሮፌሽናል እግር ኳስ ሊግ (NPFL) ጋር በተገናኘ ከማንኛውም እንቅስቃሴ ለአንድ አመት ታግደዋል። የናይጄሪያን ፕሮፌሽናል እግር ኳስ ሊግ የሚያስተዳድረው አካል ጊዚያዊ አስተዳደር ኮሚቴ ለሹቲንግ ስታርስ በጻፈው ደብዳቤ ጨዋታውን ያዋረደ “አጸያፊ ተግባር” ሲል ገልጿል።

"የባለስልጣኖቻችሁን ስነምግባር መቆጣጠር እንደተሳናችሁ ማሳያው አውዋል መሀመድ በጨዋታ ሜዳ ላይ ውሃ ሽንታቸውን በተመልካች ህዝብ ፊት እንዲህ ማድረጋቸው ነው" ሲል መግለጫው አክሏል።


በመቀሌ የሚገኘው የሞሃ ለስላሳ መጠጥ ፋብሪካ ዳግም ስራ መጀመሩን አስታወቀ

በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ የሚገኘው የሞሃ ለስላሳ መጠጥ ፋብሪካ ምርት ካቋረጠ ከሁለት አመታት በኋላ ዳግም ስራ መጀመሩን አስታዉቋል።

የለስላሳ መጠጥ ፋብሪካዉ ፤ ከተፈረመዉና ተግባራዊ መደረግ ከተጀመረዉ የሰላም ስምምነት በኋላ በተያዘዉ ሳምንት ዳግም ስራ መጀመሩን የሞሃ ለስላሳ መጠጥ ፋብሪካ የማርኬቲንግ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ብዙነህ ፎሌ በተለይ ለብስራት ራዲዮ ተናግረዋል።

እንደ አቶ ብዙነህ ገለፃ ፤ በቅርንጫፉ ከዚህ ቀደም የነበሩ ሁሉም ሰራተኞች ወደስራቸዉ ተመልሰዋል። በዚህም ከ 4 መቶ በላይ የሆኑ ሰራተኞች ካሳለፍነዉ ሰኞ እለት ጀምሮ ዳግም በስራ ገበታቸዉ ላይ ለመሆን በቅተዋል ብለዋል።

ተቋሙ ስራ ባቋረጠባቸዉ አመታት ያጋጠመዉን ኪሳራ በሚመለከት ጥናት የሚካሄድና ወደፊት የሚገለጽ መሆኑን አቶ ብዙነህ አክለዋል። የተጀመረዉም የሰላም ሂደት ላለፉት ሁለት አመታት ከስራ እና ከደሞዝ ዉጪ የነበሩ ሰዎችን ዳግም ወደቀደመ ህይወታቸው የሚመልሳቸዉ መሆኑን የማርኬቲንግ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

በትግራይ ክልል ከሰላም ስምምነቱ ተግባራዊነት በኋላ መነቃቃቶች እየታዩ መሆኑን ብስራት ራዲዮ ከዚህ ቀደም መዘገቡ ይታወሳል።

20 last posts shown.