ኢትዮ ዜና ስፖርት🔴


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Sport


ከእሁድ እስከ እሁድ ፈጣን የመረጃ ምንጭ!
➮የሃገር ቤት ትኩስ ትኩስ መረጃዎች
➮የአፍሪካ መረጃዎችን በሙሉ
➮የአውሮፓ ታላላቅ ሊጎች ሙሉ መረጃ
➮ቁጥራዊ መረጃዎች እና ዳሰሳዎች
➮ጨዋታዎችን በቀጥታ ከየስታዲየሙ
Contact us @EEMET3
@Ethiosportnews_bot
@ethiosportnews_diskbot

ኢትዮ ዜና ስፖርት 2016 ዓ/ም

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Sport
Statistics
Posts filter


የጨዋታ አሰላለፎች !

5:00 ባየር ሌቨርኩሰን ከ ባየር ሙኒክ ( agg 0-3 )

5:00 ኢንተር ሚላን ከ ፊኖርድ ( agg 2-0 )

5:00 ሊቨርፑል ከ ፒኤስጂ ( agg 1-0 )


" ከሳምንቱ የተሻለ እናደርጋለን " አርኔ ስሎት

የሊቨርፑሉ ዋና አሰልጣኝ አርኔ ስሎት በዛሬው ጨዋታ ቡድናቸው የተሻለ እንደሚንቀሳቀስ በሰጡት አስተያየት ገልጸዋል።

" ሰዎች በመጀመሪያው ዙር መጥፎ ጨዋታ እንዳደረግን ያስባሉ እኔ ግን አልስማማም ፒኤስጂ ጥሩ ስለተጫወተ ነው " ሲሉ አርኔ ስሎት ተናግረዋል።

አክለውም " ነገርግን ባለፈው ሳምንት ካሳየነው እንቅስቃሴ የተሻለ ነገር ማድረግ እንደምንችል እናውቃለን “ ብለዋል።

" ሊቨርፑልን ማሰልጠን የፈለኩት ክለቡ ባለው ታሪክ ፤ ተጨዋቾቹ ባላቸው ጥራት እና እናንተ ሊቨርፑል ለሁሉም ነገር እንዲፎካከር ስለምትጠብቁ ነው " አርኔ ስሎት

ኔዘርላንዳዊው የፊት መስመር ተጨዋች ኮዲ ጋክፖ ለጨዋታው ዝግጁ መሆኑን አሰልጣኝ አርኔ ስሎት አያይዘውም አረጋግጠዋል።


የዛሬ ተጠባቂ ጨዋታዎች !

9:00 ኢትዮጵያ መድን ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

12:00 ወላይታ ድቻ ከ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ

2:45 ባርሴሎና ከ ቤኔፊካ ( agg 1-0 )

5:00 ባየር ሌቨርኩሰን ከ ባየር ሙኒክ ( agg 0-3 )

5:00 ኢንተር ሚላን ከ ፊኖርድ ( agg 2-0 )

5:00 ሊቨርፑል ከ ፒኤስጂ ( agg 1-0 )


ሊቨርፑል ሻምፒዮንነቱን መቼ ሊያረጋግጥ ይችላል ?

አርሰናል ከማንችስተር ዩናይትድ ባደረገው የሊግ መርሐግብር ነጥብ መጣሉን ተከትሎ ሊቨርፑል የሊጉ አሸናፊነት እድሉ ሰፍቷል።

ሊቨርፑል በቀጣይ አምስት ጨዋታዎችን ማሸነፍ እና አንድ ጨዋታ አቻ መውጣት የሊግ ሻምፒዮንነቱን ያረጋግጥለታል።

ሊቨርፑል ቀጣይ ሁሉንም ጨዋታዎች የሚያሸንፍ ከሆነ ከቼልሲ የሚያደርገው ጨዋታ አሸናፊነቱን የሚያረጋግጥበት ወሳኝ ጨዋታ ይሆናል።

ሊቨርፑል ከቼልሲ በተጫወተ በሳምንቱ አንፊልድ ስታዲየም ላይ ከአርሰናል ጋር የሚጫወቱ ይሆናል።


ዩናይትድ ከአርሰናል አቻ ተለያዩ !

በፕርሚየር ሊግ የሳምንቱ ተጠባቂ መርሐ ግብር ማንችስተር ዩናይትድ ከአርሰናል ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 1ለ1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።

የማንችስተር ዩናይትድን የመሪነት ግብ ብሩኖ ፈርናንዴዝ በቅጣት ምት ሲያስቆጥር ዴክላን ራይስ አርሰናልን አቻ አድርጓል።

የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?

2️⃣ አርሰናል :- 55 ነጥብ
1️⃣4️⃣ ማንችስተር ዩናይትድ :- 34 ነጥብ

ቀጣይ መርሐግብር ?

እሁድ - አርሰናል ከ ቼልሲ

እሁድ - ሌስተር ሲቲ ከ ማንችስተር ዩናይትድ


ሊቨርፑል መሪነቱን አጠናክሯል !

የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል ከሳውዝሀምፕተን ጋር ያደረገውን የሊግ መርሐ ግብር 3ለ1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።

የሊቨርፑልን የማሸነፊያ ግቦች መሐመድ ሳላህ 2x እና ዳርዊን ኑኔዝ ሲያስቆጥሩ ለሳውዝሀምፕተን ስሞልቦን ከመረብ አሳርፏል።

ግብፃዊው ተጨዋች መሐመድ ሳላህ በውድድር ዘመኑ ሀያ ሰባተኛ የሊግ ግቡን አስቆጥሯል።

መሐመድ ሳላህ በ 2️⃣4️⃣3️⃣ ግቦች በታሪክ የሊቨርፑል ሶስተኛው ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ በመሆን አዲስ ታሪክ ፅፏል።

መሐመድ ሳላህ በሊቨርፑል ታሪክ በአንድ የውድድር አመት አርባ አራት የግብ ተሳትፎ ያደረገ የመጀመሪያው ተጨዋች ሆኗል።

በሌሎች ጨዋታዎች

- ብራይተን ፉልሀምን 2ለ1 ሲያሸንፍ
- ክሪስታል ፓላስ ኢፕስዊች ታውንን 1ለ0 ማሸነፍ ችለዋል።

የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?

1️⃣ ሊቨርፑል :- 70 ነጥብ
2️⃣0️⃣ ሳውዝሀምፕተን :- 9 ነጥብ

ቀጣይ መርሐ ግብር ?

ረቡዕ - ሊቨርፑል ከ ኤቨርተን

ቅዳሜ - ሳውዛምፕተን ከ ዎልቭስ


ማንችስተር ሲቲ ሽንፈት አስተናግዷል !

በእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ መርሐ ግብር ማንችስተር ሲቲ ከኖቲንግሃም ፎረስት ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 1ለ0 በሆነ ውጤት ተሸንፈዋል።

የኖቲንግሀም ፎረስትን የማሸነፊያ ግብ ሁድሰን ኦዶይ ከመረብ ማሳረፍ ችሏል።

ማንችስተር ሲቲ በውድድር ዘመኑ ዘጠነኛ ሽንፈታቸውን አስተናግደዋል።

የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?

3️⃣ ኖቲንግሀም ፎረስት :- 51 ነጥብ
4️⃣ ማንችስተር ሲቲ :- 47 ነጥብ

ቀጣይ መርሐግብር ?

ቅዳሜ - ማንችስተር ሲቲ ከ ብራይተን

ቅዳሜ - ኢፕስዊች ታውን ከ ኖቲንግሀም ፎረስት


የጨዋታ አሰላለፍ !

12:00 ሊቨርፑል ከ ሳውዝሀምፕተን


የዛሬ ተጠባቂ ጨዋታዎች !

9:30 ኖቲንግሀም ፎረስት ከ ማንችስተር ሲቲ

11:30 ባየር ሙኒክ ከ ቦህም

12:00 ብራይተን ከ ፉልሀም

12:00 ሊቨርፑል ከ ሳውዝሀምፕተን

1:00 ሬንስ ከ ፒኤስጂ

2:00 ሊቼ ከ ኤሲ ሚላን

4:45 ኢንተር ሚላን ከ ሞንዛ

5:00 ባርሴሎና ከ ኦሳሱና


" ዩናይትድ የአርቴታን ያህል ጊዜ አይሰጠኝም " አሞሪም

የቀያይ ሴጣኖቹ ዋና አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም ማንችስተር ዩናይትድ ክለቡን እንዲያሻሽሉ አርሰናል ለሚኬል አርቴታ የሰጠውን ጊዜ ያህል እንደማይሰጣቸው ገልጸዋል።

“ ሁለቱ ክለቦች የተለያዩ ናቸው “ ያሉት ሩበን አሞሪም ስራቸው አርቴታ በአርሰናል ገጥሞት ከነበረው ፈተና ጋር ተመሳሳይ እንደሆነ ሲጠየቁ " እንደዛ አይሰማኝም " ብለዋል።

ነገርግን አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ፈተናውን ያለፉበት መንገድ እንደ ትልቅ ማነሳሻ ተደርጎ የሚታይ ነው ሲሉ ሩበን አሞሪም ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል።

አርሰናል የተለየ ክለብ እንደሆነ ይሰማኛል ሲሉ የገለፁት አሰልጣኙ “ ነገርግን ማንችስተር ዩናይትድ አርቴታ የተሰጠውን ያህል ጊዜ አይሰጠኝም “ ሲሉ ተናግረዋል።


እረፍት

ሪያል ሶሴዳድ 0-0 ማንችስተር ዩናይትድ

ኮቤንሀቨን 0-0 ቼልሲ

አልክማር 1-0 ቶተንሀም

⚽ ቤርግቫል ( በራስ ላይ )

ፌነርባቼ 1-2 ሬንጀርስ

⚽ ኤን ነስሪ                ⚽ ዴሴርስ
                                    ⚽ ሴርኒ


የጨዋታ አሰላለፍ !

2:45 ሪያል ሶሴዳድ ከ ማንችስተር ዩናይትድ

2:45 ኮቤንሀቨን ከ ቼልሲ

2:45 አልክማር ከ ቶተንሀም


“ ዛሬ ዩናይትድ ይሸነፋል የሚል ኳስ አያውቅም “

የሪያል ሶሴዳዱ ዋና አሰልጣኝ ኢማኖል አልጓሲል በዛሬው ጨዋታ የአሸናፊነት ግምቱን ለቡድናቸው የሚሰጡ ሰዎች " ኳስ የማያውቁ ናቸው " ሲሉ ገልጸዋቸዋል።

ማንችስተር ዩናይትድ በሊጉ ጥሩ ውጤት እያገኙ ባይሆንም “ ምርጥ አሰልጣኝ ያለው ምርጥ ቡድን ነው “ ሲሉ አሰልጣኙ ተናግረዋል።

አክለውም “ የአሸናፊነት ግምቱን ለሪያል ሶሴዳድ የሚሰጡ ሰዎች ምንም የእግርኳስ እውቀት የሌላቸው እና ተጋጣሚያችንን የማያውቁ ናቸው " ብለዋል።

" ለእኔ ማንችስተር ዩናይትድ የዩሮፓ ሊግ ዋንጫን የማሸነፍ ግምት የምሰጠው ክለብ ነው " ኢማኖል አልጓሲል

https://t.me/Ethioallball


“ ምንም ቢፈጠር አጨዋወቴን አልቀይርም “ ሩበን አሞሪም

የማንችስተር ዩናይትዱ ዋና አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም ከዛሬው የሪያል ሶሴዳድ ጨዋታ በፊት ከጋዜጠኞች ጋር ቆይታ አድርገው ነበር።

ቡድናቸው በውጤት ማጣት ውስጥ የሚገኘው ሩበን አሞሪም “ ምንም ቢፈጠር  አጨዋወቴን አልቀይርም “ ሲሉ አቋማቸውን አሳውቀዋል።

" አጨዋወታችን ችግር የለበትም “ የሚሉት አሰልጣኙ “ ሌሎች በርካታ ችግሮች አሉብን እነሱን ለመፍታት ጥረት እያደረግን ነው “ ሲሉ ገልጸዋል።

አክለውም በአጨዋወት ዘይቤያቸው የወደፊት ስኬታማነት “ አልጠራጠርም “ ሲሉ ይህንን ምንም ቢፈጠር በፍጹም ስለመቀየር አላስብም ብለዋል።


ሊቨርፑል እነማንን ካለመሸነፍ ጉዞ ገታ ?

የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል በዘንድሮው የውድድር ዘመን ባለመሸነፍ ግስጋሴ ላይ የነበሩ ክለቦችን ያለመሸነፍ ጉዞ መግታት ችሏል።

ሊቨርፑል እነማንን ከግስጋሴያቸው ገታ ?

- ፒኤስጂን ከ 2️⃣2️⃣ ጨዋታዎች ያለመሸነፍ ጉዞ በኋላ

- ሊልን ከ 2️⃣1️⃣ ጨዋታዎች ያለመሸነፍ ጉዞ በኋላ

- ባየር ሌቨርኩሰንን ከ 1️⃣1️⃣ ጨዋታዎች ያለመሸነፍ ጉዞ በኋላ

- በርንማውዝን ከ 1️⃣1️⃣ ጨዋታዎች ያለመሸነፍ ጉዞ በኋላ

በሌላ በኩል የአሰልጣኝ አርኔ ስሎቱ ቡድን ሊቨርፑል በዚህ የውድድር ዘመን :-

- የስፔን እና ሻምፒየንስ ሊግ ሻምፒዮኑን ሪያል ማድሪድ አሸነፈ

- የፈረንሳይ ሻምፒዮኑን ፒኤስጂ አሸነፈ

- የጀርመን ሻምፒዮኑን ክለብ ባየር ሌቨርኩሰን አሸናፊ

- የእንግሊዝ ሻምፒዮኑን ማንችስተር ሲቲ አሸነፈ

⏩ በሁሉም ጨዋታዎች የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል ምንም ግብ ሳይቆጠርበት መውጣት ችሏል።


" የምንግዜም ምርጡ አቋሜ ነው " አሊሰን

ሊቨርፑል ፒኤስጂን በረታበት ጨዋታ ኮከብ ሆኖ ያመሸው አሊሰን ቤከር ያሳየውን እንቅስቃሴ " የምንግዜም ምርጡ " ሲል ሰይሞታል።

" በእግርኳስ ህይወቴ ካሳየሁት ጥሩ እንቅስቃሴ ሁሉ ምርጡ ይሄ ነው “ ሲል አሊሰን ቤከር ከጨዋታው በኋላ ተናግሯል።

በጨዋታው ብራዚላዊው ግብ ጠባቂ አሊሰን ቤከር የጨዋታው ኮከብ ተጨዋች በመባል መመረጥ ችሏል።

አሊሰን ቤከር በጨዋታው ምን አሳካ ?

- ዘጠኝ ኢላማቸውን የጠበቁ ሙከራዎች አዳነ።

- ከፍፁም ቅጣት ምት ክልል አራት የግብ ሙከራዎችን አዳነ።

- የሊቨርፑልን የማሸነፊያ ግብ ኤሊዮት ሲያስቆጠር ለግቡ መቆጠር ወሳኝ ሚና ነበረው።


" ውጤቱ የሚገባን አይደለም “ አርኔ ስሎት

የሊቨርፑሉ ዋና አሰልጣኝ አርኔ ስሎት በአሊሰን ቤከር የብቃት ደረጃ መገረማቸውን ከጨዋታው በኋላ ተናግረዋል።

አርኔ ስሎት ሲናገሩም " በዚህ ደረጃ ካለ ግብ ጠባቂ ጋር መስራቴን አላውቅም አሊሰን ቤከር የአለም ምርጡ ነው “ ሲሉ ተደምጠዋል።

ስለ ምሽቱ ድል ያነሱት አሰልጣኝ አርኔ ስሎት “ ውጤቱ ማግኘት ከሚገባን በላይ ነው “ ሲሉ ገልፀውታል።

አክለውም “ ዛሬ ምሽት አቻ ብንወጣ እንኳን እድለኞች ነበርን ፒኤስጂ ትልቅ ብልጫ ወስዶብናል “ ብለዋል።


“ እግርኳስ ፍትሀዊ አይደለችም “ ሉዊስ ኤንሪኬ

የፒኤስጂው ዋና አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ በምሽቱ የሊቨርፑል ጨዋታ ማሸነፍ ይገባቸው እንደነበር ገልጸዋል።

“ ማሸነፍ ይገባን ነበር “ ያሉት ሉዊስ ኤንሪኬ ከሻምፒየንስ ሊጉ ምርጥ ጨዋታዎች አንዱን አድርገናል ድሉ የእኛ መሆን ነበረበት “ ብለዋል።

በጨዋታው የሊቨርፑል ምርጥ ተጨዋች አሊሰን ነበር ሲሉ ያስታወሱት ሉዊስ ኤንሪኬ “ እግርኳስ ፍትሀዊ አይደለችም “ ሲሉ ተደምጠዋል።

" ሊቨርፑልን አንፊልድ ላይ ለመግጠም ዝግጁ ነን ምንም የምናጣው ነገር የለም ለጨዋታው ያለንን ሁሉ እንሰጣለን።“ ሉዊስ ኤንሪኬ



19 last posts shown.