ኢትዮ ዜና ስፖርት🔴


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Sport


ከእሁድ እስከ እሁድ ፈጣን የመረጃ ምንጭ!
➮የሃገር ቤት ትኩስ ትኩስ መረጃዎች
➮የአፍሪካ መረጃዎችን በሙሉ
➮የአውሮፓ ታላላቅ ሊጎች ሙሉ መረጃ
➮ቁጥራዊ መረጃዎች እና ዳሰሳዎች
➮ጨዋታዎችን በቀጥታ ከየስታዲየሙ
Contact us @EEMET3
@Ethiosportnews_bot
@ethiosportnews_diskbot

ኢትዮ ዜና ስፖርት 2016 ዓ/ም

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Sport
Statistics
Posts filter


UEFA በቻምፒየንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ላይ ተጨማሪ ሰአትን ለመሰረዝ እያሰበ ነው - ጋርዲያን ስፖርት

በዚህ ሁኔታ ቡድኖቹ ወዲያውኑ ፍፁም ቅጣት ምት ይመታሉ.


የዋህ አይደለሁም አስቸጋሪ ሁኔታ ላይ ነን “ አሞሪም

የማንችስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም ቡድኑን ከመረከቤ በፊት ስለሚመጣው ጫና አውቅ ነበር በማለት ተናግረዋል።

“ እኔ የዋህ ሰው አይደለሁም “ የሚሉት አሞሪም “ ብዙ ጊዜ ተናግሬያለሁ እግርኳስ በውጤት ላይ የተመሰረተ ስፖርት ነው  “ ሲሉ “ አስቸጋሪ ሁኔታ ላይ ነን “ ብለዋል።

አሰልጣኙ አክለውም “ የሚገጥመን አስቸጋሪ ሁኔታ እስከ ውድድር ዘመኑ መጨረሻ ይቀጥላል “ በማለት ተናግረዋል።

“ ጫናው የሚጠበቅ እና አስደሳች ነው ፤ ቡድኑን ለመረከብ ስስማማ ይህ እንደሚገጥመኝ አውቅ ነበር።“ ሩበን አሞሪም

ስለ ራሽፎርድ የተጠየቁት አሰልጣኙ “ እሱ አሁን የአስቶን ቪላ ተጨዋች ነው ይህንን ጥያቄ እነሱን መጠየቅ ትችላላችሁ " ሲሉ ለጋዜጠኞች መልሰዋል።


https://t.me/Ethioallball


ማርሴሎ በይፋ ጫማውን ሰቀለ !

ብራዚላዊው የቀድሞ የሪያል ማድሪድ ታሪካዊ የመስመር ተጨዋች ማርሴሎ ራሱን ከፕሮፌሽናል እግርኳስ ማግለሉን አስታውቋል።

ማርሴሎ በ 36ዓመቱ ጫማውን መስቀሉን በማህበራዊ ትስስር ገፁ ይፋ አድርጓል።

ማርሴሎ በእግርኳስ ህይወቱ 7️⃣2️⃣1️⃣ ጨዋታዎች ሲያደርግ 5️⃣8️⃣ ጎሎችን አስቆጥሮ 1️⃣1️⃣7️⃣ አመቻችቶ አቀብሏል።

ማርሴሎ በእግርኳስ ህይወቱ ለክለቡ እና ሀገሩ አጠቃላይ 3️⃣1️⃣ ዋንጫዎችን በማሸነፍ ደመቅ ታሪክ መፃፍ ችሏል።


https://t.me/Ethioallball


ማርቲኔዝ የ " ACL " ጉዳት አጋጠመው !

የማንችስተር ዩናይትድ የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ሊሳንድሮ ማርቲኔዝ በክሪስታል ፓላስ ጨዋታ ጉዳት አጋጥሞት ተቀይሮ መውጣቱ ይታወቃል።

ሊሳንድሮ ማርቲኔዝ ያጋጠመው ጉዳት ተጨዋቾችን ለረጅም ጊዜ ከሜዳ የሚያርቀው የ “ ACL “ ጉዳት መሆኑን ክለቡ ባወጣው ይፋዊ መግለጫ አረጋግጧል።

ይህንንም ተከትሎ አርጀንቲናዊው ተከላካይ ሊሳንድሮ ማርቲኔዝ በጉዳት ምክንያት ለረጅም ጊዜ ከሜዳ እንደሚርቅ ተገልጿል።


https://t.me/Ethioallball


ሉክ ሾው በጉዳት ምክንያት በአጠቃላይ 330 የክለቦች እና የሃገር ጨዋታዎችን አምልጦታል።

ይህ ቁጥር በጣም መጥፎ ሰአት ላይ ነው ሉክ ሻው ቢያንስ የእግር ኳስ የውድድር ዘመን ግማሹ 😔


የሜሲ እና ሮናልዶ ልጆች በርካታ ግብ አግብተዋል !

የክርስቲያኖ ሮናልዶ እና ሊዮኔል ሜሲ ልጆች ክርስቲያኖ ጁኒየር እና ቲያጎ ሜሲ በአንድ ጨዋታ በርካታ ግቦችን ማስቆጠር ችለዋል።

ለአል ነስር ከ 15ዓመት በታች ቡድን የሚጫወተው ክርስቲያኖ ጁኒየር ቡድኑ ትላንት አል ኢትሀድን 10ለ9 ሲያሸንፍ 1️⃣0️⃣ ጎሎችን በማስቆጠር አዲስ ታሪክ ፅፏል።

ክርስቲያኖ ጁኒየር ከቀናት በፊት አል ነስር አል ሂላልን 7ለ0 በሆነ ውጤት ሲያሸንፍ ሁሉንም 7️⃣ የማሸነፊያ ግቦችን ማስቆጠር ችሎ ነበር።

ለኢንተር ሚያሚ ከ 13ዓመት በታች ቡድን የሚጫወተው የሊዮኔል ሜሲ ልጅ የሆነው ቲያጎ ሜሲ በበኩሉ ትላንት ሌሊት በአንድ ጨዋታ 1️⃣1️⃣ ጎሎችን ማስቆጠር ችሏል።

የኢንተር ሚያሚ ከ13ዓመት በታች ቡድን ትላንት ሌሊት ከአታላንታ አቻው ጋር ያደረገውን ጨዋታ 12ለ0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።

ቲያጎ ሜሲ ባለፉት አምስት ጨዋታዎች 2️⃣4️⃣ ጎሎችን ሲያስቆጥር ክርስቲያኖ ጁኒየር ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች 1️⃣7️⃣ ጎሎችን አግብቷል።

https://t.me/Ethioallball


“ ዱባይ ስንሄድ እንነቃቃለን “ - ሚኬል አርቴታ

⏩ “ አስቸጋሪ ውድድር ነው “

የመድፈኞቹ ዋና አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ቡድናቸው ዛሬ ምሽት በመጀመሪያ ደቂቃዎች ያገኛቸውን እድሎች ባለመጠቀሙ ለሽንፈት መዳረጉን ገልጸዋል።

“ በመጀመሪያው ያገኘናቸውን እድሎች መጠቀም ነበረብን ነገርግን ያንን አላደረግንም “ ያሉት አርቴታ በዚህ ምክንያት ጨዋታው ወደሌላ አቅጣጫ ተቀይሯል ብለዋል።

“ ቀጥሎ በረጅም ኳስ የመጀመሪያ ግብ ሲቆጠርብን በስነልቦና ወርደን ነበር ፤ ውጤቱን መቀየር እንደምንችል አስበን ነበር አልሆነም “ ሲሉ አርቴታ አስረድተዋል።

የካራባኦ ካፕን “ በጣም አስቸጋሪ ውድድር “ ሲሉ የገለፁት አርቴታ ለንደን ከተመዘገበው ውጤት በኋላ የሚጠብቀን ሥራ ከባድ እንደሆነ እናውቅ ነበር ብለዋል።

“ አሁን ይህንን ረስተን ወደፊት መመልከት አለብን ዱባይ ስንሄድ እንነቃቃለን በድጋሜ ሀይላችንን እንመልሳለን “ አርቴታ

አርሰናል በቀጣይ ቀናት ወደ ዱባይ በማምራት ልምምዱን በዱባይ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።

https://t.me/Ethioallball


“ መጨረሻው እየቀረበ ነው “ ሮናልዶ

ፖርቹጋላዊው የአምስት ጊዜ ባሎን ዶር አሸናፊ ተጨዋች ክርስቲያኖ ሮናልዶ የእግርኳስ ህይወቱ መጨረሻ እየቀረበ መሆኑን አውቃለሁ በማለት ተናግሯል።

በእግርኳስ ደማቅ ታሪክ ከፃፉ ተጨዋቾች መካከል አንዱ የሆነው ፖርቹጋላዊ ኮከብ ክርስቲያኖ ሮናልዶ በዛሬው ዕለት 40ኛ ዓመት የልደት ክብረ በዓሉን አክብሯል።

ሮናልዶ በሰጠው አስተያየትም “ መጨረሻው እየቀረበ መሆኑን አውቃለሁ በህይወቴ ከእግርኳስ ውጪ አዲስ ምዕራፍ ይሆናል “ ሲል ተናግሯል።

ይሁን እንጂ በዚህ ጊዜ ጫማዬን እሰቅላለሁ የሚል ቀነገደብ ማስቀመጥ እንደማይፈልግ ሮናልዶ አያይዞ ገልጿል።

ሮናልዶ አክሎም “ ወደ ስፖርቲንግ ሊስበን እመለሳለሁ የሚል ሀሳብ የለኝም “ ሲል በቀጣይ በአል ነስር ጫማውን ለመስቀል ስለማሰቡ ፍንጭ ሰጥቷል።

የሳውዲ አረቢያው ክለብ አል ነስር ከዛሬ ልምምዳቸው በፊት የክርስቲያኖ ሮናልዶን ልደት አክብረዋል።

https://t.me/Ethioallball


የናፖሊ ዳይሬክተር ማና፡ "ጋርናቾን ለማንችስተር ዩናይትድ አጥብቀን ጥያቄ አቅርበን ነበር።እኛም እንፈልጋለን።" "ከአሌሃንድሮ ጋር በግል ውል መስማማት አልቻልንም፣ በጥር ወር ለመልቀቅ አላስፈላጊ ደሞዝ ጠየቀ እና ተጫዋቾቻችንን ማክበር አለብን።


ጇ ኔቬዝ የተለየ አርማ አጥልቆ ይጫወታል !

የፈረንሳይ ሊግ በቀጣይ በሚደረጉ መርሐግብሮች ላይ በውድድሩ ብዙ ኳስ አመቻችቶ በማቀበል እየመራ ለሚገኘው ተጨዋች አርማ ማዘጋጀቱን አስታውቋል።

በሊጉ በቀጣይ ብዙ ኳስ አመቻችቶ በማቀበል እየመራ የሚገኘው ተጨዋች በክንዱ ላይ “ Top Passeur “ አርማ አጥልቆ እንደሚጫወት ተገልጿል።

የመጀመሪያውን አርማ የፒኤስጂው የመሐል ሜዳ ተጨዋች ጇ ኔቬዝ አጥልቆ በመጫወት የሚጀምር ይሆናል።

ፖርቹጋላዊው የመሐል ሜዳ ተጨዋች ጇ ኔቬዝ በሊጉ ሰባት ለግብ የሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ ማቀበል ችሏል።

የፈረንሳይ ሊግ ከዚህ በፊት በተመሳሳይ የሊጉ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ተጨዋች አርማ አዘጋጅተው እንደነበረ ይታወሳል።


https://t.me/Ethioallball


አርቴታ ከክለቡ ባለቤቶች ጋር ውጥረት ውስጥ ገቡ !

የአርሰናሉ ዋና አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ በዝውውር ጉዳዮች ከክለቡ ባለቤቶች ጋር አለመግባባት ውስጥ መግባታቸው ተገልጿል።

አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ አርሰናል በጥር የዝውውር መስኮት የፊት መስመር አጥቂ አለማስፈረሙን ተከትሎ በክለቡ ባለቤቶች መበሳጨታቸው ተነግሯል።

መድፈኞቹ ጋብሬል ጄሱስ እና ቡካዩ ሳካን በጉዳት ሲያጡ አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ አጥቂ እንደሚገዛላቸው ቃል ተገብቶላቸዋል እንደነበረ ተገልጿል።

ሚኬል አርቴታ ለኦሊ ዋትኪንስ 60 ሚልዮን ፓውንድ ወጪ እንዲሆን ቢጠይቁም የክለቡ ሀላፊዎች ከ 40 ሚልዮን ፓውንድ በላይ ማውጣት አለመፈለጋቸው ተዘግቧል።

አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ በክለቡ ውስጥ ባሉ አንዳንድ ሀላፊዎች የመታለል ስሜት እንደተሰማቸው ተነግሯል።

ስፔናዊው አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ትላንት ስለ ጉዳዩ ለጋዜጠኞች ሲናገሩ “ ተጨዋች ባለመፈረሙ በጣም ተበሳጭተናል " ብለው ነበር።


https://t.me/Ethioallball


አርኖልድ ከቶተንሀም ጨዋታ ውጪ ነው !

ከቀናት በፊት ጉዳት ያጋጠመው የሊቨርፑሉ የመስመር ተጨዋች አሌክሳንደር አርኖልድ በድኑ ነገ ከቶተንሀም ጋር ከሚያደርገው ጨዋታ ውጪ መሆኑ ተገልጿል።

አሌክሳንደር አርኖልድ በጭኑ ላይ ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት “ የነገው ጨዋታ ያመልጠዋል “ ሲሉ አሰልጣኝ አርኔ ስሎት ተናግረዋል።

ተጨዋቹ ሊቨርፑል እሁድ ከ ፕሌይ ማውዝ ጋር በሚያደርገው የኤፌ ካፕ መርሐግብር ወደ ሜዳ ሊመለስ እንደሚችል አሰልጣኝ አርኔ ስሎት ጠቁመዋል።

ሊቨርፑል ነገ ምሽት 5:00 ከቶተንሀም ጋር የካራባኦ ካፕ ግማሽ ፍፃሜ ጨዋታውን የሚያደርግ ይሆናል።


https://t.me/Ethioallball


ሲቲ ለዝውውር ከፍተኛ ወጪ አድርገዋል !

ማንችስተር ሲቲ በጥር የተጨዋቾች የዝውውር መስኮት ለዝውውር ከፍተኛ ወጪ ያደረገ ቀዳሚ ክለብ መሆናቸው ተገልጿል።

ማንችስተር ሲቲዎች በዝውውር መስኮቱ 216 ሚልዮን ዩሮ ለተጨዋቾች ዝውውር ማውጣታቸው ተነግሯል።

የፔፕ ጋርዲዮላው ቡድን ማንችስተር ሲቲ ለዝውውር ያወጣው ቀሪ 1️⃣9️⃣ የሊጉ ክለቦች በድምሩ ካወጡት 213 ሚልዮን ዩሮ የበለጠ ሆኗል።

ከማንችስተር ሲቲ በመቀጠል የፈረንሳዩ ክለብ ሬንስ በርካታ ገንዘብ ወጪ ያደረገው ክለብ በመሆን ተቀምጧል።

በጥር ብዙ ገንዘብ ለዝውውር ያወጡ የአውሮፓ ክለቦች እነማን ናቸው ?

- ማንችስተር ሲቲ :- 218 ሚልዮን ዩሮ

- ሬንስ :- 74.6 ሚልዮን ዩሮ

- ፒኤስጂ :- 70 ሚልዮን ዩሮ

- ሌፕዚግ :- 55.5 ሚልዮን ዩሮ

- ዎልቭስ :- 50 ሚልዮን ዩሮ

- ኮሞ :- 49.2 ሚልዮን ዩሮ

- ብራይተን :- 48.75 ሚልዮን ዩሮ

- ኤሲ ሚላን :- 45.5 ሚልዮን ዩሮ


https://t.me/Ethioallball


ተጨዋች ባለማስፈረማችን ተበሳጭተናል “ አርቴታ

የመድፈኞቹ ዋና አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ቡድናቸው በዝውውር መስኮቱ ተሳትፎ ባለማድረጉ መበሳጨታቸውን ገልጸዋል።

ተጨዋች የማስፈረም ግልጽ ሀሳብ ነበረን ያሉት አርቴታ “ ነገርግን ማሳካት አልቻልንም በዚህም ተበሳጭተናል “ ሲሉ ቡድኑ መጠናከር ይገባው ነበር ብለዋል።

አርሰናል መጠናከር የሚገባው በተወሰነ መልኩ እንደነበር ያነሱት አሰልጣኙ ባሉት ተጨዋቾች ለመጠቀም እንደሚያስቡ አስረድተዋል።

አርሰናል በቀጣይ በአጥቂነት ማንን ይጠቀማል ?

የፊት መስመር አጥቂ ክፍተት ያለበት አርሰናል በዝውውር መስኮቱ አጥቂ ያስፈርማል ተብሎ ቢጠበቅም ሳይስፈርም ቀርቷል።

በጉዳዩ ላይ ቃላቸውን የሰጡት ሚኬል አርቴታ “ የፊት መስመሩ በቀጣይ ተቀያያሪ ይሆናል “ ሲሉ ተናግረዋል።

ሚኬል አርቴታ አክለውም “ ራሂም ስተርሊንግ ፣ ንዋኔሪ እና ጋብሬል ማርቲኒሊ በአጥቂ ቦታ መጫወት ይችላሉ “ ብለዋል።


https://t.me/Ethioallball


ሳንቶስ ከፍተኛ ለውጥ አሳይቷል !

የቀድሞ ተጫዋቹን ከረጅም አመት በኋላ ወደ ስብስቡ የቀላቀለው የብራዚሉ ክለብ ሳንቶስ በክለቡ መሰረታዊ ለውጦችን መመልከት ጀምሯል።

ክለቡ ኔይማርን ማስፈረሙን ይፋ ባደረገ ቀናት ውስጥ 20,000 አባላትን መመዝገቡ ተገልጿል።

ከኔይማር መመለስ በፊት 49,000 ገደማ የነበሩት የሳንቶስ አባላት አሁን ላይ ከ 70,000 መሻገራቸው ተነግሯል።

በተጨማሪም ክለቡ የኔማርን ወደ ክለቡ መመለስ ተከትሎ ከ 500,000 በላይ የኢንስታግራም ማህበራዊ ገፅ ተከታዮች ማፍራታቸው ተነግሯል።

ሳንቶስ በነገው ዕለት ከቦቶፋጎ ጋር የሚያደርጉ ሲሆን የስታዲየም መግቢያ ትኬቶች ተሸጠው መጠናቀቃቸው ተገልጿል።

ኔይማር በዛሬው ዕለት በክለቡ ዝርዝር ውስጥ መመዝገቡን ተከትሎ ነገ 33ዓመቱን በሚያከብርበት ዕለት ለሳንቶስ የመጀመሪያ ጨዋታውን እንደሚያደርግ ይጠበቃል።


አርኖልድ ለምን ያህል ጊዜ ከሜዳ ይርቃል ?

ከቀናት በፊት ጉዳት ያጋጠመው የሊቨርፑሉ የመስመር ተጨዋች አሌክሳንደር አርኖልድ ለረጅም ጊዜ ከሜዳ #እንደማይርቅ ተገልጿል።

አሌክሳንደር አርኖልድ ሊቨርፑል ከቀናት በፊት በርንማውዝን ባሸነፈበት ጨዋታ ጉዳት አጋጥሞት ተቀይሮ መውጣቱ አይዘነጋም።

ተጨዋቹ በጭኑ ላይ የጉዳት ስሜት ሲሰማው በፍጥነት ተቀይሮ መውጣቱ ከባድ ጉዳት እንዳያጋጥመው እንዳደረገ ተነግሯል።

ይህንንም ተከትሎ አሌክሳንደር አርኖልድ ከተወሰኑ ቀናት በኋላ ወደ ሜዳ ይመለሳል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተገልጿል።

https://t.me/Ethioallball






የተጠናቀቁ የዝውውር መረጃዎች !

ክለቦች ቡድናቸውን እንዲያጠናክሩ እድል የሚሰጠው የጥር የተጨዋቾች የዝውውር መስኮት ትላንት ሌሊት በይፋ ተጠናቋል።

በዝውውር መስኮቱ መጨረሻ ሰዓት እነማን ተጨዋች አስፈረሙ ?

⏩ ማንችስተር ሲቲ ስፔናዊውን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ኒኮ ጎንዛላዝ ከፖርቶ ማስፈረማቸውን በይፋ አስታውቀዋል።

- ማንችስተር ሲቲዎች ተጫዋቹን 60 ሚልዮን ዩሮ በማውጣት በአራት አመት ኮንትራት ማስፈረማቸው ይፋ ሆኗል።

⏩ ቶተንሀም የባየር ሙኒኩን የፊት መስመር ተጨዋች ማትያስ ቴል በውሰት ውል ማስፈረማቸውን ይፋ አድርገዋል።

- ቶተንሀም ተጫዋቹን በ 60 ሚልዮን ዩሮ የዝውውር ሒሳብ በቋሚነት ማስፈረም የሚችሉበት አንቀጽ በውሉ ተካቷል።

⏩ የማንችስተር ዩናይትዱ የመስመር ተጨዋች ታይለር ማላሽያ በውሰት ውል ወደ ፒኤስቪ አምርቷል።

⏩ ኤቨርተን የብራዚሉ ክለብ ፍላሚንጎን ተጨዋች ቻርሊ አልካራዝ በውሰት ውል ማስፈረማቸውን በይፋ አስታውቀዋል።

⏩ እንግሊዛዊው ተጨዋዌ ቤን ቺል ዌል ቼልሲን በመልቀቅ ክሪስታል ፓላስን በውሰት ውል ተቀላቅሏል።

⏩ ፉልሀም ብራዚላዊውን ተጨዋች ዊሊያን እስከ ውድድር ዘመኑ መጨረሻ በነፃ ዝውውር በድጋሜ ማስፈረማቸው ተገልጿል።

⏩ ፖርቹጋላዊው ተጨዋች ጇ ፊሊክስ በውሰት ውል የጣልያኑን ክለብ ኤሲ ሚላን ተቀላቅሏል።


#DeadlineDay

⏩ ቶተንሀም የባየር ሙኒኩን የፊት መስመር ተጨዋች ማትያስ ቴል በውሰት ውል ለማስፈረም ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል።

- የ 19ዓመቱ የፊት መስመር ተጨዋች ማትያስ ቴል የህክምና ምርመራውን ለማድረግ ወደ ለንደን በማምራት ላይ መሆኑ ተገልጿል።

⏩ ዌስትሀም ዩናይትድ ጄምስ ዋርድ ፕራውስን በውሰት ካመራበት ኖቲንግሀም ፎረስት በመጥራት ወደ ቡድኑ መመለሳቸው ተገልጿል።

⏩ ኤሲ ሚላን ሜክሲኳዊውን የፊት መስመር አጥቂ ሳንቲያጎ ሂምኔዝ ከፊኖርድ ማስፈረማቸውን በይፋ አስታውቀዋል።

- ተጨዋቹ በኤሲ ሚላን ቤት እስከ 2029 የሚያቆየውን የአራት አመት ኮንትራት መፈረሙ ይፋ ሆኗል።


https://t.me/Ethioallball

20 last posts shown.