4-3-3 World News


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


ይህ የእርሶ፣ የአንተ፣ የአንቺ፣ የእናንተ፣ የኛ የሁላችንም ድምጽ ነው! ለሃሳብ አስተያየት ለመስጠት @atsbaha12 ይጠቀሙ

Related channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


ለኮሪደር ልማት አገልግሎት ላይ የዋሉ መብራቶችን የሰረቀው ተከሳሽ በ5 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ

ወንጀሉ የተፈጸመው የካቲት 18 ቀን 2017 ዓ/ም ከሌሊቱ 8:00 ሠዓት በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 8 ልዩ ቦታው አዋሬ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው።

ተከሳሽ ሄኖክ መኮንን በኮሪደር ልማት ላይ የተገጠሙ መብራቶችን ቆርጦና ነቅሎ በመውሰድ ሊያመልጥ ሲል በወቅቱ ስራ ላይ በነበሩ የፖሊስ አባላት እጅ ከፍንጅ በቁጥጥር ስር መዋሉን የምርመራ መዝገቡ ያስረዳል።

ተከሳሽ ላይም ተገቢው የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች በማደራጀት ምርመራ ተጣርቶበት በአቃቤ ህግ ክስ ተመስርቶበታል፤

የተከሳሽን መዝገብ የተከታተለው በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት የካ ምድብ 1ኛ ወንጀል ችሎት የካቲት 26 ቀን 2017 ዓ/ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ሄኖክ መኮንን ጥፋተኛ መሆኑን በማስረጃ በማረጋገጥ ተከሳሽን ያርማል ሌሎች ወንጀል ፈፃሚዎችን ያስተምራል በማለት በ5 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አስተላልፎበታል። (ዳጉ_ጆርናል)

@Ethionews433 @Ethionews433


ወደ አገልግሎቱ ተመልሷል


X(Twitter) በመላው አለም አገልግሎቱ በአሁኑ ሰዓት ተቋርጧል

@Ethionews433 @Ethionews433


ፈረንሳይ ሁለት ቁልፍ መገልገያዎችን በማስረከብ ከሴኔጋል ወታደራዊ ኃይሏን ማስዉጣት ጀመረች

ፈረንሳይ ከሴኔጋል ወታደራዊ ኃይሏን አርብ ዕለት ማስለቀቅ የጀመረች ሲሆን ሁለቱን ቁልፍ መገልገያዎችን ለምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር በማስረከብ በቀጣናዊ ስትራቴጂዋ ላይ ሰፊ ለውጥ አድርጋለች። በሴኔጋል የሚገኘው የፈረንሳይ ኤምባሲ በሰጠው መግለጫ አርብ ማርች 7 ቀን 2025 የፈረንሣይ ወገን በማርቻል እና ሴንት-ኤክሱፔሪ ወረዳ ውስጥ ያሉትን መገልገያዎች እና መኖሪያ ቤቶች ለሴኔጋል ወገን አስረክቧል ብሏል።

"በሀን ፓርክ አቅራቢያ የሚገኙት እነዚህ ወረዳዎች ከ2024 ክረምት ጀምሮ ወደ ሴኔጋል ለመመለስ ዝግጁ ነበሩ።" ይህ እርምጃ ላይ የተደረሰው የሴኔጋል ፕሬዝዳንት ባሲሩ ዲዮማዬ ፋዬ የውጭ ኃይሎችን ከአገሪቱ ለማስወጣት ያደረጉትን ግፊት ተከትሎ በምዕራብ አፍሪካ ፈረንሳይ መገኘቱን የሚቃወሙ ሰፊ ዘመቻ መከፈተን ያሳያል። የፈረንሳይ በአካባቢው ያለው ተጽእኖ ቀስ በቀስ እየቀነሰ መጥቷል።

በአካባቢው ሀገራት እየጨመረ በመጣው ተቃውሞ የተነሳ ፈረንሳይ ጦሯን ከቡርኪናፋሶ፣ ኒጀር እና ቻድን ለቀው መውጣታቸው ይታወሳል። የፈረንሳይን መውጣት ተከትሎ ባለፈው ወር የጋራ ኮሚሽን የተቋቋመ ሲሆን የፈረንሳይ ጦር በቅርቡ በዳካር የሚገኙ 162 የሴኔጋል ሰራተኞችን አሰናብቷል። የፈረንሳይ ኤምባሲ ግን በሴኔጋል ምን ያህል ወታደሮቹ እንደቀሩ አልገለጸም።

ፈረንሳይ የአፍሪካ ወታደራዊ አሻራዋን በከፍተኛ ደረጃ ለመቀነስ ማቀዷን ያስታወቀች ሲሆን፥ ጅቡቲ በአህጉሪቱ ብቸኛ የፈረንሳይ ቋሚ መቀመጫ ትሆናለች ተብሎ ይጠበቃል። ፓሪስ እንደገለጸችው የመከላከያ ስልጠና ወይም ወታደራዊ ድጋፍን ከዚህ በኃላ በሀገራት ጥያቄ መሰረት ብቻ ለማድረግ ውሳኔ አሳልፋለች።

በስምኦን ደረጄ

@Ethionews433 @Ethionews433


"እኔ ስታርሊንክን ባጠፋው የዩክሬይን የጦር ግንባር ይፈርሳል" ሲል ኤሎን መስክ ተናገረ፡፡

አሜሪካዊው ቢሊየነር አሎን መስክ ዛሬ ባሰፈረው መልእክት የሳተላይት ኢንተርኔት አገልግሎት መስጫ የሆነውን ስታር ሊንክ ለዩክሬይን ጦርነት ወሳኝ መሆኑን አስታውቋል፡፡

የዩክሬይን ማናቸውም ወታደራዊ ግንኙነቶች የሚከናወኑት በእሱ ባለቤትነት በሚተዳደረው በዚሁ ስታር ሊንክ አማካኝነት እንደሆነም ገልጿል፡፡ መስክ በኤክስ ገፁ ላይ ‹‹እኔ ፑቲንን ከዩክሬይን ጋር በሚደረገው ጦርነት ፈትኜዋለሁ፡፡ እናም የእኔ ስታር ሊንክ ሲስተም ለዩክሬይን የጀርባ አጥንት ነው›› ካለ በኋላ ስታር ሊንኩን ቢያጠፋው የዩክሬይን የጦር ግንባር ሙሉ በሙሉ እንደሚፈራርስ አስረድቷል፡፡

ለአመታት በተደረገው በዚህ ጦርነት ዩክሬን ላታሸንፍ ነገር ይህንን በማድረጉና ሰዎች በመሞታቸው እንደሚፀፅተውም አስረድቷል፡፡ ጨምሮም ‹‹አሁን ሁሉም የሚመለከተው ሁሉ ይህ ሰው እየበላ ያለው ጦርነት እንዲቆም ማድረግ አለበት፡፡ አሁን ሰላም ያስፈልጋል›› ብሏል፡፡

ኤሎን መስክ ይህንን መልእክት ያሰፈው የዩክሬይኑን ፕሬዝደንት ዘለንስኪን ከሩሲያ ጋር የማያልቅ ጦርነት ማድረግ እንደሚፈልጉ ገልፆ ‹‹ጨካኝ›› ካላቸው ከቀናት በኋላ ነው፡፡ ሩሲያና ዩክሬይን ጦርነቱን ከጀመሩ ሶስት አመታት የሞላቸው ሲሆን በሁለቱም በኩል ከፍተኛ ሰብአዊ ጉዳት መድረሱ የሚታወቅ ነው፡፡

@Ethionews433 @Ethionews433


በማይናማር በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 32 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ
።።።።።።።።።።።።።።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መንግሥት በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ ትኩረት ሰጥቶ በመንቀሳቀስ በማይናማር በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 32 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ማድረጉን አስታውቋል።

ሕንድ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በኩል በማይናማር በእገታ ሥር ቆይተው ወደ ታይላንድ ከተሻገሩ 133 ኢትዮጵያ መካከል 32ቱ ዛሬ ወደ ሀገራቸው መግባታቸው የዘገበው ኢቢሲ ነው።

@Ethionews433 @Ethionews433


የኢራቅ ማስጠንቀቂያ

፡።።፡፡።።፡።።፡።።፡።።።።።።።።

ኢራቅ የሶሪያ ግጭት የመላ ቀጠናውን ሰላም ሊያናጋው ይችላል በሚል አሳሰበች፡፡

ባግዳድ የደማስቆ ፖለቲካ መታወክ መካከለኛው ምስራቅን አደጋ ውስጥ ያስገባዋል ያለች ሲሆን በተለይም ለአላዋይቶች አስቸጋሪ ሁኔታ ይፈጠራል የሚል መግለጫ ሰታለች፡፡

የበሽር አል- አሳድ ደጋፊዎች ከጊዚያዊ መንግስቱ ወታደሮች ጋር የገቡበት ውጥረት ሶሪያን የርስበርስ ጦርነት ውስጥ ዳግም እንዳይከታት ስጋት ደቅኗል፡፡

በህዝብ ቁጥር የሚያንሱት አላዋይት ማህበረሰብ የሶሪያን ፖለቲካ ከአምስት አስርት ዓመታት በላይ ተቆጣጥረው አገሪቱን የአምባገነን አገዛዝ ምድር አርገዋታል በሚል ይወቀሳሉ፡፡

በዕርግጥ "የአሳድ መንግስት እንጂ እኛ ፖለቲካዊ ተጠቃሚዎች ሆነን አናውቅም" የሚል መከራከሪያንም ያቀርባሉ አልዋይቶች።

የኢራቅ መንግስት በሶሪያ ምድር እየሆነ ያለውን ሁሉ በቅርበት እየተከታተለው መሆኑንም ያሳወቀ ሲሆን ግጭቱ የደማስቆን ቀውስ ከድጡ ወደ ማጡ ያደርገዋል ብሏል፡፡

ምንም እንንኳን የባግዳድ መንግስት የውስጥ ፖለቲካውን ማረቅ ባይችልም በሶሪያ ፖለቲካ ውስጥ ጣልቃ የመግባት አዝማሚያ እንዳለው ተጠቁሟል።

መካከለኛው ምስራቅ ወደ ባሰ ምስቅልቅል ከመግባቱ በፊት ቀድሞ ውጥረቱን ማብረድ ያሻል የሚል ማሳሰቢያ ከተለያዩ ወገኖች እየተሰጠ ይገኛል፡፡

ልዩነቶች በድርድር እንዲቋጩም ጥሪ ቀርቧል፡፡

የባግዳድ ጦር በኢራቅ እና ሶሪያ ድንበር የወታደሮቹን ቁጥር ከፍ አደጓል፡፡

በሶሪያ ዳግም ቀውስ መፈጠሩ እንደ ኢራን እና የሊባኖሱ ሔዝቦላህ ዓይነቶቹ ሀይሎች አቅማቸውን አጠናክረው በድጋሚ ደማስቆ ሊገቡ ይችላሉ የሚል ፖለቲካዊ ትንታኔም እየተሰጠ ነው፡፡

አልጀዚራ እና ዘ ኒው አረብ እንዳስነበቡት፡፡

@Ethionews433 @Ethionews433


የሩሲያ ጦር ግስጋሴ በታሪካዊቷ ኮንስታንቲኖፕል

፡፡።።።፡፡።።።፡፡።።።።።፡፡።።።፡፡።።።

የሩሲያ ጦር የዩክሬኗን ኮንስታንቲኖፕል መንደር መቆጣጠሩን አሳወቀ፡፡

የዩክሬን ጦር ከኮንስታንቲኖፕል ተጠራርጎ መውጣቱን ይፋ ያደረገችው ሞስኮ ወታደሮቼ ወደፊት እየገሰገሱ ነው ብላለች፡፡

በዶንባስ (ሉሃንስክ እና ዶኔትስክ) ግዛት የምትገኘው ኮንስታንቲኖፕል በባይዛንታይን አገዛዝ ወቅት የነበረን ስያሜ ከታሪክ እና ከእምነት ጋር በማስተሳሰር ዛሬም መጠሪያዋ አድርጋ ትጠቀማለች፡፡

"የቱርኳ ኮንስታንቲኖፕል በ1922 ዓ.ም ወደ አሁኗ ኢስታንቡል ስያሜዋ መቀየሩ ይታወሳል"።

ለዚህም ነው የሩሲያ ጦር አሁን ላይ የዩክሬኗን ኮንስታንቲኖፕል መቆጣጠሩን ከታሪክ አንጻርም ትልቅ ድል አድርጎ የሚቆጥረው፡፡

ሞስኮ ወታደሮቿ በአካባቢው ላይ የሩሲያን ባንዲራ ሲሰቅሉ የሚያሳይ ምስል በቴሌ ግራም ማህበራዊ ትስስር ገጽ ላይ አጋርታለች።

እንደ አር ቲ ዘገባ በዚህ ግንባር በውጊያ ላይ የነበሩ ከ50 በላይ ወታደሮቿን ዩክሬን አታለች፡፡

አሜሪካ ለዩክሬን የምታደርገውን ወታደራዊ ድጋፍ እና የሳተላይት አሊያም የመረጃ ልውውጥ ማቆሟ ሩሲያ አጋጣሚውን እየተጠቀመችበት እንደሆነ ያሳያል ተብሏል።

ላለፉት 24 ሰዓታት 1,300 የጦር ዓባላቷን ዩክሬን ከማጣቷም ባሻገር አሜሪካ ሰራሽ ሂማርስ የሮኬት ማስወንጨፊያ ስርዓትን ጨምሮ በርካታ ቁልፍ የጦር መሳሪያዎች ወድመዋል ብሏል የሩሲያ ጦር፡፡

ዩክሬን ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት በጉዳዩ ላይ ያለችው ነገር የለም ሲል የዘገበው አር ቲ ነው፡፡

@Ethionews433 @Ethionews433


የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሰራተኞች 30,000,000 ሚሊዮን ብር ለመቆዶኒያ ድጋፍ አደረጉ

@Ethionews433 @Ethionews433


"ክብሬ ተነክቶ አልደራደርም" ኢራን
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የኢራኑ ሁለንተናዊ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሚኒ "ምዕራባውያን የኑክሌር ድርድርን ለተጽዕኖ ፈጣሪነታቸው ማረጋገጫ እየተጠቀሙበት ነው" ሲሉ ወቀሱ፡፡

አያቶላህ ይህን ሀሳብ የስጡት ዶናልድ ትራምፕ የኑክሌር ድርድርን በተመለከተ ስምምነት ላይ ካልተደረሰ ሀይል ልንጠቀም እንችላለን ማለታቸውን ተከትሎ ነው፡፡

ሪፐብሊካኑ ዶናልድ ትራምፕ ዋሽንግተን ሀይል ልትጠቀም እንደምትችል ፍንጭ መስጠታቸው ኻሚኒን አባሳጭቷቸዋል፡፡

አንዳንድ ጫና መፍጠር የሚፈልጉ መንግስታት ድርድሩ ላይ ትኩረት ያደርጋሉ ነገር ግን ዓላማቸው መፍትሄ ማምጣት አይደለም ብለዋል፡፡

"እነዚህ መሪዎች ዓላማቸው የሚፈልጉትን ሁሉ በአንድ አገር ላይ መጫን እና የተጽዕኖ ፈጣሪነታቸውን አድማስ ማስፋት ነው" የሚል አቋማቸውን አንጸባርቀዋል መሪው፡፡

አያቶላህ በኤክስ ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት"ሶስት የአርውሮፓ አገራት ኢራን የ2015ቱን የኑክሌር ስምምነትን አላከበረችም" የሚል መግለጫ ማውጣታቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡

" እናንተስ ግዴታችሁን ተወታችኋል ወይ ተብለውም መጠየቅ አለባቸው" በሚልም ሀሳባቸውን በጥያቄ መልክ አጠናክረዋል፡፡

ዶናልድ ትራምፕ በቀደመው የስልጣን ዘመናቸው የ2015ቱን የኑክሌር ስምምነት 2018 ላይ ጥለው መውጣታቸው አይዘነጋም፡፡

ሪፐብሊካኑ የኑክሌር ስምምነቱን (JCPOA) ሲያቋርጡ በኢራን ላይ ዳግም ማዕቀብ ጥለውም ነበር፡፡

ስምምነቱን አምስቱ ቋሚ የጸጥታው ምክር ቤት ዓባላት እና ጀርመን(ፒ5+1) በኦባማ የፕሬዚዳንትነት ዘመን መፈረማቸው ይታወሳል፡፡

በአሁኑ ሰዓት የኑክሌር ድርድሮች ቢቀጥሉም በዋሽንግተን እና በቴህራን መካከል ባለው ፖለቲካዊ አለመግባባት ሳቢያ ነገሮች መልካቸውን እየለወጡ ይገኛል፡፡

ለዚህም ነው ኢራን ክብሬን እና ብሄራዊ ጥቅሜን የጠበቀ ውይይት እስካልተደረገ የኑክሌር ድርድር ብሎ ነገር የለም በሚል እየሞገተች የሚገኘው፡፡

ቴህራንን ያላማከለ የትኛውም ድርድር ረብ የለሽ ነው ብለዋል አያቶላህ አሊ ኻሚኒ

ዘገባው የአልጀዚራ እና የአር ቲ ነው፡፡

በ-ቢኒያም ካሴ

@Ethionews433 @Ethionews433


የመከላከያ አቅሞችን የምናጎለብተው “ለመዋጋት አይደለም” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ

ኢትዮጵያ የመከላከያ አቅሟን የምታገጎለብተው “ትናንሽ አቅም ይዘው ለሚሳሳቱ ኃይሎች ብዙ ጊዜ እንዲያስቡ ለማስቻል” እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ “እነዚህን አቅሞች የምናጎለብተው ለመዋጋት አይደለም። ውጊያን ለማስቀረት ነው” ብለዋል።

አብይ ይህን ያሉት “ስካይ ዊን ኤሮኖቲክስ ኢንዱስትሪ” የተባለ የሰው አልባ አውሮፕላኖች (ድሮኖች) ማምረቻ ትላንት ቅዳሜ የካቲት 29፤ 2017 በመረቁበት ወቅት በሰጡት ገለጻ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለወታደራዊ አገልግሎት የሚውሉ ምርቶችን በሚያመርቱ ፋብሪካዎች ተገኝተው ማብራሪያ ሲሰጡ፤ የትላንቱ በአንድ ሳምንት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜያቸው ነው።

ባለፈው ረቡዕ በኦሮሚያ ክልል አምቦ ከተማ አቅራቢያ የሚገኘውን የሆሚቾ ጥይት ፋብሪካ የጎበኙት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ፤ ኢትዮጵያ ከወታደራዊ ግብዓት አንጻር የነበረባትን “ውስንነት ከሞላ ጎደል ፈትታለች” ብለው ነበር። የጠቅላይ ሚኒስትሩ የፋብሪካ ጉብኝትም ሆነ ያቀረቡት ገለጻ፤ ኢትዮጵያ “ከኤርትራ ጋር ወደ ሌላ ዙር ጦርነት ለመግባት በዝግጅት ላይ ለመሆኗ ማሳያ” አድርገው የቆጠሩ ወገኖች አሉ።

ይህን አመለካከት የተረዱ የሚመስሉት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ በትላንቱ ገለጻቸው፤ “እነዚህን አቅሞች የምናጎለብተው ለመዋጋት አይደለም። ውጊያን ለማስቀረት ነው። ትናንሽ አቅም ይዘው ለሚሳሳቱ ኃይሎች፤ ብዙ ጊዜ [ሰጥተው] እንዲያስቡ ለማስቻል ነው። ውጊያን ለማስቀረት (deter) ለማድረግ ከፍተኛ አቅም ስላለው ነው” ሲሉ ተደምጠዋል።

Via ኢትዮጵያ ኢንሳይደር

@Ethionews433 @Ethionews433


በሶሪያ በተቀሰቀሰው ግጭት ከ 1000 በላይ ሰዎች መሞታቸው ተገለፀ ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በአዲሱ የሶሪያ የጸጥታ ሃይሎች እና በቀድሞው የበሽር አልአሳድ መንግስት ታማኝ ተዋጊዎች መካከል በተቀሰቀሰው ግጭት እና የበቀል ግድያ በሁለት ቀናት ውስጥ ከ1,000 በላይ ሰዎች መሞታቸው ተገልጿል ።

መቀመጫውን በብሪታኒያ ያደረገው የሶሪያ የሰብአዊ መብት ታዛቢ ቡድን እንዳስታወቀው ከማቾቹ መካከል 745 የሚሆኑት ንፁሀን ዜጎች ሲሆኑ ፣125 የሶሪያ የጸጥታ ሃይሎች እና 148 የአሳድ ታማኝ ተዋጊዎች ተገድለዋል ሲል አስታውቋል።

ይህ የበርካታ ሰዎችን ህይወት የቀጠፈው ግጭት በታህሳስ ወር የሶሪያ መንግስት ሀይሎች የአሳድ አማፂያን ካስወገዱ ወዲህ አስከፊው ግጭት መሆኑን የሰብአዊ መብት ታዛቢ ቡድኑ ገልጿል ።

ባሳለፍነው ሀሙስ የበሽር አል አሳድ ታማኝ ሃይሎች፣ በሀገሪቱ የባህር ጠረፍ አካባቢ ላታኪያ በተባለችው ከተማ የመንግስት ጸጥታ ሀይሎች ለደህንነት ስራ እየተንቀሳቀሱ ባሉበት ድንገት በከፈቱት ጥቃት ግጭቱ መቀስቀሱ ይታወሳል።

ዘገባው የዘጋርዲያን ነው

በ-ሰላማዊት ወልደገሪማ

@Ethionews433 @Ethionews433


የኢትዮ ኤርትራን ሰሞንኛ ውጥረት❗️

ክሊንግዲል የተባለ የኔዘርላንድ የምርምር ተቋም የኢትዮ ኤርትራን ሰሞንኛ ውጥረት አስመልክቶ ማስጠንቀቂያ አውጥቷል፡፡

ተቋሙ ሁለቱ አገራት ወደ ግጭት እንዳይገቡ የአውሮፓ እና አፍሪካ ህብረትን ጨምሮ ኃያላን አገራት ዲፕሎማሲያዊ ጫና እንዲያደርጉ ጠይቋል፡፡

ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ወደ ግጭት ከገቡ ከባድ ቀውስ ሊፈጠር ይችላል በማለት ተናግሯል፡፡ ተቋሙ የአውሮፓ እና አፍሪካ ህብረት ሁለቱን አገራት ችግራቸውን በሰላም እንዲፈቱ የዲፕሎማሲ ስራ እንዲሰሩም ጥሪ አቅርቧል፡፡ ሁለቱም አገራት ተቃዋሚዎችን ከመርዳት ይታቀቡ ያለም ሲሆን፤ በድንበር እና በባህር በሩ ጉዳይ ንግግር እንዲጀምሩ ጠይቋል፡፡

በየካቲት አጋማሽ በኤርትራ ወታደራዊ ግዳጅ መታወጁን ያስታወሰው ተቋሙ፤ ይህም በአገራቱ መሀል ግጭት ሊቀሰቀስ ይችላል የሚለውን መላምት የሚያጠናክር ነው ብሎታል፡፡፡ ግጭቱ ከተቀሰቀሰ በቀውስ ውስጥ ለሚታመሰው የአፍሪካ ቀንድ ቀጠና ተጨማሪ ራስ ምታት ነው ያለ ሲሆን፤ ከቀጠናው አልፎ ለአውሮፓም መዘዝ ይዞ መምጣቱ አይቀርም ብሏል፡፡

ኤርትራ የአብይ ዐሕመድን የባህር በር ፍላጎት እንደ ስጋት ተመልክታዋለች የሚለው የተቋሙ የማስጠንቀቂያ ሪፖርት፤ ከግብጽ ጋር የምታደርገው ግንኙነትም የዚህ ስጋት ውጤት እንደሆነ አንስቷል፡፡

@Ethionews433 @Ethionews433


የደቡብ ኮሪያ  ፕሬዝዳንት ዩን ከእስር ተለቀቁ 

የደቡብ ኮሪያ ፍርድቤት በክስ ላይ የነበሩት ፕሬዝዳንት ዩን ሱክ ዮል የእስር ማዘዣ እንዲሰረዝ መወሰኑን ተከትሎ አቃቢ ህግ በውሳኔው ላይ ይግባኝ ላለመጠየቅ በመወሰኑ ዛሬ በሴኡል ከሚገኘው እስርቤት ተለቀዋል፡፡

ዮን በእ.አ.አ ታህሳስ 3 ቀን ባሳለፉትና ለአጭር ጊዜ በቆየው የማርሻል ህግ ምክንያት ከስራቸው እንደታገዱ የሚቆዩ ሲሆን በአመፅ የቀረበባቸው ክስም እንዳለ ይቆያል ተብሏል፡፡

የወንጀል ጉዳዩ በስልጣን ላይ በሚኖራቸው ቆይታ ዙርያ ክሚታየው የፍርድ ሂደት የተለየ ሲሆን በህገ-መንግሥታዊው ፍርድ ቤት ወደ ሥራ ይመለሱ ወይም ከሥልጣናቸው ይነሱ በሚለው ጉዳይ ላይ በሚቀጥሉት ቀናት ውሳኔ ይሰጣል ተብሎም ይጠበቃል።


@Ethionews433 @Ethionews433


የረመዳን ጾም ረጅም ሰአት የሚጾምባቸው የአለም ሀገራት

በተለያዩ አካባቢዎች ባለው የሰዓት አቆጣጠር ልዩነት ምክንያት እስከ 16 ሰዓታት የሚጾሙ አማኞች ቁጥር በርካታ ነው።

በጾሙ ወቅት ጸሀይ ወደ ማደሪያዋ እስክትገባ ድረስ አማኞች ከምግብ፣ መጠጥ እና ሌሎችም ስጋዊ ፍላጎቶች ተቆጥበው ይውላሉ።(አል አይን)

@Ethionews433 @Ethionews433


ወጣቱ ኢትዮጵያዊ ዲፕሎማት - ቸርነት ሀሪፎ

ወጣቱ ኢትዮጵያዊ ዲፕሎማት ቸርነት ሀሪፎ በተባበሩት መንግሥታት የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት (ኢጋድ) ቋሚ ተወካይ ሆኖ ተሹሟል፡፡

በ20ዎቹ መጀመሪያ ዓመታት ዕድሜው በዲፕሎማትነት የተሾመው ቸርነት ሀሪፎ፤ የሹመት ደብዳቤውን ለመንግሥታቱ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ አቅርቧል።

ዲፕሎማቱ ፤ በዓለም አቀፍ መድረክ ምሥራቅ አፍሪካን ለመወከል በመብቃቴ ኩራት ይሰማኛል ሲል በማኅበራዊ ትሥሥር ገጹ የተሰማውን ደስታ አጋርቷል፡፡

የ23 ዓመቱ ቸርነት ሀሪፎ ሹመቱን ተከትሎ ከተለያዩ አካላት ከፍተኛ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል።

የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁም (ዶ/ር)፥ ለቀጣናው ትብብር ያለህ ተነሳሽነት ሁላችንንም የሚያነሳሳ ነው በማለት ለወጣቱ ዲፕሎማት ስኬታማ የሥራ ጊዜን ተመኝተውለታል።

በኃይለማርያም ተገኝ

@Ethionews433 @Ethionews433


በትግራይ ክልል የአምስት ሰዎች ህይወት የቀጠፈ ጥቃት ደረሰ

በትግራይ ክልል ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች በሰላማውያን ሰዎች ላይ ጥቃት አድርሰዋል ሲል የትግራይ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት አስታውቀል።

ዳጉ ጆርናል በተመለከተውና ፅህፈት ቤቱ ከደቂቃዎች በፊት ያጋራውን መረጃ መሰረት ትላንት የካቲት 28 ቀን 2017 ዓ/ም በራያ አላማጣ ወረዳ ጥሙጋ ላይ ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቂዎች በተፈፀመ ጥቃት የአምስት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ ሁለት ሰዎች በከባድ መቁሰላቸው ገልፆል።

ጥቃቱ ምሽት 4:00 ገደማ መፈፁሙን የገለፀው ፅህፈት ቤቱ የጥቃቱ ሰለባዎች ደግሞ በቤተክርስትያን ውስጥ የፀሎት ስነስርዓት ሲፈፅሙ የነበሩ ስቪሎች ናቸው ብሏል።

የትግራይ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ጥቃቱን ጭካኔ የተሞላበት ጭፍጨፋ ሲል የገለፀው ሲሆን የክልሉ መንግስት ከሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት ጋር በመሆን የድርጊቱ ፈፃሚዎች በቁጥጥር ስር ለማዋል ክትትል እያደረገ መሆኑን አክሏል።

በሚሊዮን ሙሴ

@Ethionews433 @Ethionews433


#የሚዘጉ መንገዶች ስለማሳወቅ

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ከቢሊግርሃም ኢቫንጀሊስቲክ አሶሴሽን ጋር በመተባበር የካቲት 29 እና 30 ቀን 2017 ዓ/ም በመስቀል አደባባይ የሚያደረገው የስብከተ ወንጌል አገልግሎት መርሀ ግብር ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።

በዚህም መሠረት በሁለቱም ቀናት ከቀኑ 5:00 ሠዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስኪጠናቀቅ ድረስ፦

. ከኦሎምፒያ ወደ መስቀል አደባባይ (ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ)

. ከጥላሁን አደባባይ ወደ ሳንጆሴፍ መብራት (ጥላሁን አደባባይ ላይ)

. ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ (ለገሃር መብራት)

. ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድየም (ቴሌ ማቋረጫ ላይ)

. ከሀራምቤ መብራት ወደ መስቀል አደባባይ (ሀራምቤ መብራት ላይ )

. ከብሔራዊ ቤተ መንግሥት ወደ መስቀል አደባባይ (ብሔራዊ ቤተመንግሥት ላይ)

. ከቅዱስ ዑራኤል አደባባይ ወደ መስቀል (ባምቢስ መቅረዝ ሆስፒታል መታጠፊያ) ላይ የሚዘጋ ሲሆን አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳስቧል።

@Ethionews433 @Ethionews433


የቴሌ ኔይቶርክ መቆራረጥ ...

በቀይ ባህር ውስጥ በሚያልፍ ከፍተኛ ባንድዊድዝ ተሸካሚ ዓለም አቀፍ ባህር ጠለቅ የኢንተርኔት መገናኛ መስመር ላይ ባጋጠመ መቋረጥ ምክንያት....

የኢንተርኔት አገልግሎት በሌሎች አማራጭ መስመሮች ብቻ እየሰራ በመሆኑ ሰሞኑን የኢንተርኔት አገልግሎት ፍጥነት መቀነስ እና መቆራረጥ እያጋጠመ ይገኛል ሲል የኢትዮ ቴሌኮም አስታውቋል።

ቴሌ እንዳሳወቀው ከሆነ አገልግሎቱን በፍጥነት ለማስቀጠል ከአገልግሎት አቅራቢዎቹ ጋር ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ መሆናቸውን የገለፁ ሲሆን

ደንበኞች በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እየጠየቅን፤ ለአገልግሎት መስተጓጎሉ ይቅርታ እንጠይቃለን ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላለፈዋል።

@Ethionews433 @Ethionews433


በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳድር የትምህርት ቢሮ ሀላፊ ፤ ፋና እና የኢትዮጵያ ፕረስ ድርጅት የሰሩት ዘገባዎች የተሳሳቱ ናቸዉ አሉ

በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳድር የትምህርት ቢሮ ሀላፊ የሆኑት ዶ/ር ኪሮስ ግዑሽ ፋና እና የኢትዮጵያ ፕረስ ድርጅት የሰሩት ዘገባዎች የተሳሳቱ ናቸዉ አሉ።

መንግስታዊ የሆኑት የሚዲያ ተቋማቱ በትግራይ አዲሱን የትምህርት ስርዓት ለመተግበር የሚያግዙ መጽሃፍት ህትመት ዝግጅት ተጠናቋል ብለዉ ነበር።

የትምህርት ቢሮዉ ሃላፊ ግን በፌስቡክ ገጻቸዉ ላይ በበጀት እጥረት ምክንያት የመጽሐፍቱ ህትመት ዝግጅት አልተጀመረም ማለታቸዉን ዳጉ ጆርናል ተመልክቷል።

ሃላፊዉ እንደዚህ አይነት የተዛባ መረጃ ከበጎ አድራጎት ድርጅቶች ገንዘብ ለማሰባሰብ የምናደርገውን ጥረት ያደናቅፋል ያሉም መሆኑን ዳጉ ጆርናል የታዘበ ሲሆን በሚዲያ ተቋማቱ የተሰሩ ዘገባዎች እንዲታረሙም ጠይቀዋል።

በበረከት ሞገስ

@Ethionews433 @Ethionews433

20 last posts shown.