Ethiopian Digital Library


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Education


በዚህ ቻናል ስለ
👉ትምህርት፣
👉ሥራ እና
👉ማህበራዊ ጉዳይ
መረጃ ያገኛሉ!
Contact: @ethiodlbot

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Education
Statistics
Posts filter


በሜታ ወልቂጤ በአንዲት ታዳጊ ህጻን ላይ የተፈጸመው አሰቃቂ ግድያ

በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ሜታ ወልቂጤ ወረዳ አንዲት ህጻን ከቤት ተወስዳ ከተደፈረች በኋላ ተገድላ መገኘቷ ቁጣ ቀስቅሷል። “በኛ የደረሰ በማንም አይድረስ” የሚሉት የተጎጂ ቤተሰብ በታዳጊ ልጃቸው ላይ ለደረሰው ቀሰቃቂ ወንጀል ፍትህ እንሻለለን ብለዋል።

ሲምቦ ብርሃኑ ትባላለች፡፡ የስምንት ዓመት ታዳጊ ህጻን ናት፡፡ የአንደኛ ክፍል ተማሪ፡፡ በዚሁ ባሳለፍነው ሳምንት ባለፈ ረቡዕ ጥር 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ከትምህርት ቤት ተመልሳ ምሳ እንደበላች ከመኖሪያ ቤቷ የደረሰችበት ሳይታወቅ ቀርቷል ፡፡ በዕለቱ ፍለጋ የወጣው ቤተሰብ ታዳጊዋን ከነሙሉ ጤንነትና በህይወት ለማግኘት ግን አልታደሉም፡፡

ሮጣ ያልጠገበች ታዳጊዋ ለአዕምሮም በሚከብድ ሁኔታ ከተደፈረች በኋላ “እንዳትናገር በሚል” ከመኖሪያ ቤታቸው ጀርባ በቅርብ ርቀት ላይ ህይወቷ አልፎ መገኘቱን አንድ የቤተሰቧ አባል ለዶቼ ቬለ ተናግረዋል። ታዳጊዋ ከተገደለች በኋላ ተሰቅላ መገኘቷን የገለጹት የቤተሰብ አባሉ “ጫማዋን ያወለቁባትና የሰቀሏት ቦታ አንድ አይደለም የ50 ሜትር ገደማ ርቀት አለው” ብለዋል።

በወረዳው የኤላ ከተማ በታዳጊዋ ላይ የተፈጸመው ጥቃት አባት የመንግስት ሰራተኛ መሆናቸው እና በስራ ቦታ መሆናቸው እንዲሁም እናት የ2 ወር እመጫት በመሆናቸው አጋጣሚውን በመጠቀም እንደነበር የቤተሰቡ አባል ተናግረዋል።

የተጎጂ ቤተሰብ አባል የሆኑት አስተያየት ሰጪ ቀጥለው፤ “የታዳጊዋ ቤተሰብ ቤት በፊት ለፊት በኩል ሆቴል በመሆኑ የሚገባውና የሚወታው ብዙ ነው፡፡ በጓሮ በኩል ፑል መጫወቻም አለ፡፡

ደፋሪዎችም በዚያው በጀርባ በር እንደወሰዷት ነው የቤተሰብ ስጋት” ያሉን አስተያየት ሰጪው፤ 2009 ዓ.ም. የተወለደችው ታዳጊዋ ሲምቦ ገና በ8 ዓመቷ ለዚህ ለአሰቃቂው ድርጊት ሰለባ መሆኗን በቁጪት ተናግረዋል፡፡

“ባለሙያዎች በሰውነቷ ላይ የታየውን ፈሳሽ በመውሰድ ምርመራ እያደረጉ ነው” ያሉን የቤተሰብ አባል እስካሁን በቁጥጥር ስር የዋለ ተጠርጣሪ አለመኖሩንም ገልጸዋል፡፡ ባለፈው ረቡዕ ከሰዓት በኋላ 9 ሰዓት ተኩል የተገኘው የታዳጊዋ አስክሬን በትናንትናው እለት ስርዓተ ቀብሩ መፈጸሙን የአዲስ አበባው ወኪላችን ስዩም ጌቱ ዘግቧል።

ዶቼ ቬለ በታዳጊዋ ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ድርጊት እና ቀጣይ እርምጃዎች ለመጠየቅ ለወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብርሃኑ አጀማ በእጅ ስልካቸው ላይ ቢደወልም ስልካቸው ስለማይነሳ አስተያየታቸውን በዚህ ዘገባ ማካተት አልተቻለም፡፡
ምስል ፤ ከቤተሰብ አባል የተገኘ
#DW #ዶቼ_ቬለ

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


GlobeDock Academy is honored to be recognized at the Great Rift Valley Innovation Summit! 🎉 Now, we need your support to win the People’s Choice Award! 🏆

📚 Support GlobeDock at the GRV Summit and help us continue transforming education in Ethiopia.

🗳 Cast your VOTE NOW! 👇
🔗 https://vote.grvsummit.com/dashboard










Mekdela Amba University Vacancy

Experience: 0 year

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


የቻይና ሲሆን ደህንነት ምናምን ይላሉ...አይ አለም

ጣሊያን ከሰሞኑ መነጋገሪያ የነበረውን የAi app Deepseek ን ከደህንነት ስጋት ጋር በተገናኘ ምክንያት አግዳለች::

ያም ሆነ ይህ ቻይና አሜሪካን መገዳደር ጀምራለች::

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


🔴 በ2017 ዓ.ም ለአቅም ማሻሻያ ትምህርት (Remedial Program) ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች ምዝገባ የካቲት 6 እና 7/2017 ዓ.ም እንደሚከናወን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል። https://tinyurl.com/dbu-rcp-2017 ሊንክ ላይ በመግባትና የአድሚሽን ቁጥራችሁን በማስገባት የተመደባችሁበትን ግቢ ማወቅ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል።

🔴 በ2017 ዓ.ም ለአቅም ማሻሻያ ትምህርት (Remedial Program) ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች ምዝገባ ጥር 28 እና 29/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
የምዝገባ ቦታ
✔️የስማችሁ የመጀመሪያ ፊደል ከA-H የሆነ የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በቡሬ ካምፓስ
✔️የስማችሁ የመጀመሪያ ፊደል ከA-E የሆነ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በቡሬ ካምፓስ
✔️ሌሎቻችሁ የማኅበራዊ እና የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በዋናው ካምፓስ

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


አዲሱ የትራንፕ አስተዳደር የግብረሰዶማዊያን ምልክት በየትኛውም የአሜሪካ ግዛት እንዳይያዝ ከልክለዋል። ሰውየው ከመጽሃፍ ቅዱስ ውጪ አሻፈረኝ ብለዋል። በተጨማሪም ይህንን መመሪያ የጣሱ የመንግስት ሰራተኞች ከስራ መባረርን ጨምሮ የዲሲፕሊን እርምጃ ሊወስዱ እንደሚችሉ ትእዛዝ ሰጥተዋል::

The new Trump administration has banned the display of gay symbols in any US state. He refused to do so outside of the Bible.
He also ordered that government employees who violate this directive could face disciplinary action, including dismissal. Trump admin tells U.S. embassies they can't fly pride flag on flagpoles

www.nbcnews.com

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library




የመውጫ ምዘና ላልወሰዱ መምህራን ማስረጃ እንዳይሰጥ - ትምህርት ሚኒስቴር

ሚኒስቴሩ ለዩኒቨርሲቲዎች እና ለክልል ትምህርት ቢሮዎች በጻፈው ደብዳቤ፥ የመውጫ ምዘና ላልወሰዱ መምህራን ማስረጃ እንዳይሰጥ አሳስቧል፡፡በሚኒስቴሩ የመምህራን ትምህርት አመራሮች ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) ከሳምንት በፊት የተጻፈው ደብዳቤ፥ " በክረምት መርሐግብር ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ ለመሸጋገር የትምህርት ማሻሻያ ስልጠና የሚከታተሉ መምህራን፣ ስልጠና ሳያጠናቅቁ መረጃ እየተሰጠ እንደሆነ ደርሼበታለሁ " ብሏል፡፡

በክረምት መርሐግብር ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ደረጃ ለማሻሻል ስልጠና እየወሰዱ ያሉ መምህራን፣ የማስተማር ሙያ (PGDT) መውሰድና የመውጫ ምዘና ማጠናቀቅ እንዳለባቸው በመስከረም 2017 ዓ.ም የትምህርት ሚኒስቴር ማሳወቁን በደብዳቤው ገልጿል፡፡ ይሁን እንጂ አንዳንድ ክልሎች ከዚህ በተለየ የማስተማር ሙያ ስልጠናም ሆነ የመውጫ ምዘና ላልወሰዱ መምህራን፣ የደረጃ ዕድገት እየሰጡ መሆኑናቸውን መረዳቱን አሳውቋል፡፡

ማንኛውም ሠልጣኝ የትምህርት ማስረጃ ማግኘት የሚችለው የትምህርት ምዘና ወስዶ ማለፍ ሲችል መሆኑ እየታወቀ፣ የዲግሪ ትምህርታቸውን እንደጨረሱ በማድረግ የትምህርት ደረጃ ማሻሻያና የደረጃ ዕድገት የሚሰጡ አንዳንድ ተቋማት መኖራቸውን ሪፖርተር ያነጋገራቸው መሪ ሥራ አስፈጻሚው ተናግረዋል፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር ወጪያቸውን በመሸፈን የሚያስተምረው የበቁ መምህራንን ለማፍራት ነው ያሉት ኃላፊው፤ ማንኛውም ተቋም የመውጫ ምዘና ወስደው ላላለፉ ዕጩ መምህራን ምንም ዓይነት ማስረጃ እንዳይሰጥ በደብዳቤ ማሳወቁን አስረድተዋል፡፡ #ሪፖርተር

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ከመጭው አመት ጀምሮ የዩንቨርስቲ ምርጫ ውስጥ ሊገባ ነው

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ከ2018 ዓ.ም ጀምሮ የተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ምርጫ ውስጥ እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስቴር ተናግሯል።

ዩኒቨርሲቲው እያከናወናቸው ላሉ ሥራዎች በጥናት ላይ የተመሰረተ ድጋፍ እንደሚያደርግ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ገልጿል። ከቀጣይ ዓመት ጀምሮም የተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ምርጫ ውስጥ የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲም እንደ አንድ አማራጭ እንደሚካተት ተጠቁሟል።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


የአጠቃላይ ትምህርት ፀደቀ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 17ኛ መደበኛ ስብሰባው ከፍተኛ የትምህርት አቀባበል ያላቸው ተማሪዎች የሚገኙበትን የትምህርት ክፍል ሳያጠናቅቁ ወደ ቀጣዩ ክፍል መሸጋገር የሚያስችል የአጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ አዋጅን አፅድቋል። የአዋጁ መፅደቅ ብቁ የትምህርት ባለሙያ፣ አመራርና አደረጃጀት ለመፍጠር የሚያስችል ነው ተብሏል።

የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) ለምክርቤት ባቀረቡት ሪፖርት እንደገለፁት፣ የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍን መሠረት አድርገው ከተቀረጹ መርሐግብሮችና ዕቅዶች አንጻር ትምህርትን ለመምራት የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ ባለመኖሩ ዘርፉን በሚፈለገው ደረጃ አላደገም።

ይህንን መሰረታዊ ችግር ለመፍታት አዲስ አዋጅ ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል ብለዋል። አዋጁ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና በዘርፉ እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ የሚደረገውን ሪፎርም ያግዛል። በአዋጁ ከፍተኛ የትምህርት አቀባበል ያላቸው ተማሪዎች የሚገኙበትን የትምህርት ክፍል ሳያጠናቅቁ ወደ ቀጣይ ክፍል መሸጋገር እንዲችሉ ተደርጎ መዘጋጀቱንም ተናግረዋል።

አዋጁ ብቁ የትምህርት ባለሙያ፣ አመራርና አደረጃጀት ለመፍጠር ይረዳል ያሉት ሰብሳቢው፣ በመላው ሀገሪቱ ሁሉም የአጠቃላይ ትምህርት ተቋማት የሚከናወነው የመማር ማስተማር ሂደት የሀገሪቱን እሴት ጠብቆ እንዲካሄድ ግልጽ አቅጣጫ የሚሰጥ ስለመሆኑ አስረድተዋል።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


መምህራንና ተማሪዎች ዕገታ

በጎጃም አካባቢዎች በመምህራንና ተማሪዎች ዕገታ ምክንያት ዘንድሮ ማስተማር ጀምረው ያቆሙ ትምህርት ቤቶች መኖራቸውንና በርካታ ተማሪዎች በወላጆች ላይ በሚደርስባቸው ማስፈራሪያ ሳቢያ ትምህርት እያቋረጡ መኾኑን ዋዜማ ተረድታለች።

በርካታ የገጠር ትምህርት ቤቶች መምህራን፣ ርዕሳነ መምህራንና የትምህርት ተቆጣጣሪዎች በየጊዜው በፋኖ ታጣቂዎች እንደሚታገቱ ዋዜማ ተገንዝባለች።

ባንዳንድ አካባቢዎች ዕገታውን በመፍራት ወደ ትምህርት ቤት የማይገቡ መምህራን ደሞ፣ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እንደሚታሠሩ ምንጮች ገልጸዋል።

በክልሉ የዚህ ዓመት የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ እስከ የካቲት 30 ድረስ መራዘሙን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ትናንት አስታውቋል። #Wazema

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


🛑 በዚህ ዘመን ተፈላጊ የሆነውን የቪድዮ ኤዲቲንግ  ሙያ  በስልካችሁ ብቻ መማር ትፍልጋላችሁ ?

📌 ማንኛውም ጀማሪ የሆነ ሰው ሊማርበት የሚችል እና ወደ መካከለኛ ቪድዮ ኤዲተርነት ከፍ የሚልበት በዝርዝር ያስረዳውበት ሙሉ የ 2 ሰዓት ኮርስ ነው።

📌 አሁን ላይ በቪድዮ ኤዲተርነት Upwork ላይ ከ    International Client  ጋር እየሰራሁ እገኛለሁ!

📌እናንተም አሁኑኑ ይህንን ሙያ ለመማር እና በዶላር ተከፋይ ለመሆን ከፈለጋችሁ ይህ ቪድዮ ለእናንተ ነው።

ቪድዮውን በዝርዝር ለማየት
👇 👇👇
https://youtu.be/a5ST4u9b-Dc


መቄዶንያ በመላው ኢትዮጵያ 44 ቅርንጫፎች ያሉት ከወደቁበት የተነሡ ሰዎች ወደ አእምሮአቸው ሲመለሱ ወደ ሥራ የሚገቡበት ብዙ ሥልጠና ያለው በሆስፒታል ደረጃም ብዙ ቁጥር የሚያስተናግድ ሥፍራ ነው::

በመሥራት ላይ ያሉትና የፊታችን የካቲት 1 2017 ዓ.ም. በሰይፉ ኢቢኤስ ዩቲዩብ ቻናል በሚደረግ የገቢ ማሰባሰቢያ ይጠናቀቃል::

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
የእኛ ሀገር ትምህርት...

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library




በሸገር ራዲዮ 102.1 ላይ የሰማሁት አንድ ታሪክ ደስ ስላለኝ ላካፍላችሁ

ገርጂ አካባቢ የሚኖሩ አባትና ልጅ የወደቀ ገንዘብ ያገኛሉ(911 ዶላር እና 11 ብር)።ከገንዘቡ ጋር የፓስፖርት ኮፒም አብሮ ነበር።ለሰውየው ለመመለስ አስበው በፓስፖርቱ ላይ በተጠቀሰው ስም ያፈላልጉት ገቡ።አጡት። ከፎቶው እንደተረዱት ባለገንዘቡ 'ፈረንጅ ' ነው።

ሁለት አመት ሙሉ ነጭ ሲያዩ እያስቆሙ ስሙን እየጠየቁ ከፎቶው እያመሳከሩ አፈላለጉት። የሰፈር ሰው ሁሉ 'ስለምን ትሞኛላችሁ?! ገንዘቡን ተጠቀሙበት!' አላቸው።የሰው ሃቅ አንነካም አሉ።እንደውም በመሃል ልጅየው ታሞ ሆስፒታል ገባ።ኦፕራሲዮን ይደረግ ተባለ። ገንዘብ ከየት ይምጣ?!
'አባዬ በዛ በፈረንጁ ገንዘብ ልታከም?' አላቸው።

አባት 'አላህ በሰው ሃቅ እንድታተከም አይፈቅድም!ፈቃዱ ከሆነ በጥበቡ ያድንሃል! ' አሉት።ያ ችግርም ታለፈ ።
ከሰሞኑ ገንዘቡን የጣለውን ሰው አገኙት። ህንዳዊ ነው።ያችኑ 911 ዶላርና አብራ የነበረችውን 11 ብር ሰጡት።
ምን ሊል እንደሚችል ገምቱ።

ጋዜጠኛው ሰዎቹንም እሱንም አፈላልጎ ኢንተርቪው አደረጋቸው።
ጠዋት ወደ ስራ እየሄድኩ ህንዳዊው ለኢትዮጵያውያን ያለውን አድናቆት ሲገልጽ እየሰማሁት ልቤ ሲሞቅ ይሰማኝ ነበር!!
አንዳንዴ እንደዚህ አይነት ታሪኮችን ስሰማ ያ የድሮው የኢትዮጵያዊ ጨዋነት እንዳልጠፋ አስብና ደስ ይለኛል።

ከዘገባው የገረመኝ 'ታሪኩን የሰሙ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ለአባትና ለልጅ ገንዘብ አሰባስበው 200 ዶላር ላኩላቸው! ' የሚለው ነው።ሰዎቹ በዚህ ደስ ቢላቸውም እኔ ግን ብዙም ደስ አላለኝም። ማድነቅም በትላልቅ ሚዲያዎች ላይ ማቅረብም ያለብን የእነኚህን አይነቶቹን ሰዎች ነበርኮ!
ብዙ ሰዎች የወደቀ ገንዘብ አግኝተው መልሰዋል። የነኚህ ግን ይለያል።ሁለት አመት ሙሉ ያውም ድህነትና ችግር እየፈተነህ?!ሃቁን ለባለሃቁ መመለስ!!
አቅራቢው ጋዜጠኛ ወንድሙ ሃይሉ ነው።

Andualem Buketo

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

20 last posts shown.