ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Religion


🥰 እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሄርን ያመስግነው።
መዝ. ፻፶ ፡ ፮
❝በጎንም ለማድረግ ብትቀኑ የሚያስጨንቃችሁ ማነው?
1.ጴጥ 3፡13

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Religion
Statistics
Posts filter


ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ:
የአእላፍት ዝማሬ ይቀላቀሉ 👇 👇 👇

https://t.me/yeaelafat_zemare/40


ሠላሜ ነህ ፀትታዮ
ወደቤ ነህ ማረፊያዬ
ሁን ከኔ ጋራ አሁን ከጎኔ
ፍቅር እኮ መድህኔ

https://t.me/Ethiopian_Ortodoks




ምርኩዜ🥺
ክፍል ፩
የሰው ልጅ እንደዚህ ሲንገዳገድ አይቼ አላውቅም አንድ ጊዜ ወደግራ ደግሞ ወደቀኝ ብቻ ምን አለፋችሁ ካሁን ካሁን ወደቀ እያለ ሰው ይመለከታል በሁለት ሊትር ሃይላንድ የተሞላ ድራፍት በቀኝ እጁ ይዟል በግራ እጁ ደግሞ ሲጋራውን ጨብጧል በብብቱ መሃል ደግሞ ጫቱን ይዞ እየተወላገደ ይራመዳል ያገኘውን ሰው ሁሉ እግዚአብሔርን አትከተሉት እንደኔ ያሰቃያችኋል እያለ ይመክራል መንገደኛው ሁሉ ወይ ጊዜ ሰው እንዴት በጠራራ ፀሃይ ይሰክራል እያለ ይመፃደቅበታል ድሮ የሚያውቁት ደግሞ አይ እንደዛ እንዳልተከበርክ በሀይላንድ ፀበሉን በፌስታል እምነቱን በክብሪት ጧፉን እንዳለኮስክ እንዲህ ተበላሽተህ ቀረህ እያሉ ከንፈራቸውን መምጠጥ ከጀመሩለት ሰነባብተዋል የሰፈሩ ህፃናት እንኳን ሳይቀሩ ባዶ እጁን ሲያዩት እንደ አበደ ሰው ነው የሚቆጥሩት ደግነቱ እሱ ባዶውን አይሄድም እንጂ ሁልጊዜ አቋራጭ መንገድ እያለ ወደ ቤቱ የሚገባው ዙሪያ ጥምጥም ሄዶ ነው እንድ ቀን አንድ ሰው ለምን በሚካኤል በኩል አድርገህ በአቋራጭ አትሄድም ሲለው እኔ ሚካኤል በተጠራበት በኩል ማለፍ ስለማልፈልግ ነው እንጂ ዙሪያ ጥምጥም መንገድ ፈልጌ አይደለም ግን እስከለተ ሞቴ በሚካኤል በር አላልፍም አለው ከዚያ ወዲህ ማንም ሰው ጠይቆት አያውቅም ለሰፈሩ አዲስ የሆኑ መጤ ሰዎች አይ ይሄ ሰው በቃ ሁልጊዜ መጠጣት መስከር ነው አይደል የሚያውቀው ሰውስ ቆይ ለምንድን ነው ብር የሚሰጠው አንዳንድ ሰዎች የጠቀሙት እየመሰላቸው በነፍሱ ይጫወቱበታል ወይ ዘመን እያሉ ይማረራሉ ሁልጊዜ ስለሱ መጥፎ ሲወራ የሚያቀጠቅጣቸው አንድ አባት እኔ ምላችሁ ልጆቼ ዛሬ ቅዱስን ያየው ሰው አለ እንዴ አለ አንዷ ቀልጠፍ ብላ ውይ ጋሼ ደግሞ አሁን ቅዱስ እዚህ ይኖራል ብለው ነው ያው እዛው መጠጥ ቤት እየተጋተ ይሆናል እንጂ…

ይቀጥላል
✍ ብርሃኑ ባውቄ

2.2k 0 30 15 96

ክርስቶስን ያከበሩ፤ መንገዱን የተከተሉ ብዙ ሴቶች አሉ፤ እውነትን የመሰከሩ፤ ስለ ቃሉ የኖሩ ብዙ ሴቶች አሉ፤ መስዋዕትነትን የከፈሉ በሰማዕትነት ያለፉ ብዙ ሴቶች አሉ፤ ታላላቅ የምድር ነገስታትን፤ ታላላቅ ነቢያትን የወለዱ ብዙ ሴቶች አሉ፤ ከነዚህ ሁሉ ግን አንቺ ትበልጫለሽ። [አቡነ ሺኖዳ ]

ቅድስት ሆይ ለምኝልን🤲🌷

2.6k 0 9 13 159

Forward from: የአእላፍት ዝማሬ | Melody Of Myriads
አንተ ሰይፍና ጦር ጭሬም ይዘህ ትመጣብኛለህ እኔ ግን ዛሬ በተገዳደርኸው አምላክ ስም በሰራዊት ጌታ በእግዚአብሔር ስም እመጣብሃለሁ።
1ኛ ሳሙ 17፡45

ዐድዋ - ቅዱስ ጊዮርጊስ ገበዘ ኢትዮጵያ




የካቲት 23 ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ያረገወ ተዐምር ይኽ ነው፡፡

በዚያን ወራት የኢትዮጵያ ንጉሥ ነገሥት ዳግማዊ ዓፄ ምኒሊክም ሀገሬ
ኢትዮጵያን እወዳለሁ የሚል ኢትዮጵያዊ ኹሉ ፈጥኖ ይነሣ፡፡የጦር መሣሪያውን
ተሸክሞ ይከተለኝ ዘንድ በሰመ ማርያም አደራ እላላለሁ ሲል ዐዋጅ አሰነገረ፡፡
ዳግመኛም በፈረሶቻቸው መጣብር ላይ በጦራቸው አንደበት ላይ በጋሻቸው
እምብርት ላይ የመስቀል ምልክት እንዲያደርጉ ጭፍሮቹን አዘዛቸው፡፡ መስቀል
ጠላትን ድር አድራጊ እንደኾነ አስቀድሞ ያውቅ ነበር፡፡

ወደ አንዷ የትግራይ አውራጃም ምድረ ዐደዋ ደረሰ
፡፡ የዚኽ ሣህለ ማርያም ዳግማዊ ምኒልክ ሚስት እቴጌ ጣይቱ(ወለተ ሚካኤል)በንጉሡ ትእዛዝ ታቦተ ጊዮርጊስ አስይዞ ከሊቀ ጳጳሳት አባ ማቴዎስና ከቀሳውስቱና መነኮሳቱ ከንጉሡ ሣህለ ማርያም ዳግማዊ ምኒልክም ጋር ወደ ጦርነቱ ተጓዘች፡፡ በዚህም ጊዜ ኹላቸው ካህናት የእመቤታችንን ሥዕል ይዘው ወደ ንጉሡ ምኒልኮ መጥተው ከሊቀ ጳጳሱ አቡነ ማቴዎስ ጋር ተቀላቀሉ፡፡ ሌሊቱን ሙሉ ጸሎት ምሕላ ሲያደርሱ አደሩ፡፡
ቅዳሜ ለእሁድ አጥቢያ ይኸውም ወርኃ የካቲት ኻያ ኹለትቀን ነው፡፡ ንጉሡ ሣህለ ማርያም ዓፄ ምኒልክም የጦር ልብሱን ለብሶ ከሠራዊቱ ጋር ጦር ግንባር ገባ፡፡ ከዚያም ከሮማውያን የጠላት ጦር ጋር ተገናኝቶ ከሌሊቱ 11ሰዓት ጦርነቱ
ተጀመረ፡፡ እቴጌ ጣይቱ ሌሊት በታቦተ ቅዱስ ጊዮርጊስና በእመቤታችን ቅዶስት ድንግል ማርያም ሥዕል ፊት በጸሎትና በስግደት እያደረች ሲነጋ ወደ ጦርነቱ ቦታ በመሔድ እጅግ በሚያስደንቅ የአነጋገሯ ኃይል ቃል በጦርነቱ መኻል እየተገኘች ለንጉሡ ወታደሮች የሞራልና የብርታት ድጋፍ ትሰጣቸው ነበር፡፡
በዚያም ጊዜ ንጉሡ ሣህለ ማርያም ዓፄ ምኒልክ በጦርነቱ መኻል ሳለ ሊቀ
ጳጳሳቱ አባ ማቴዎስና ኹላቸው ካህናትም ታቦተ ጊዮርጊስንና ሥዕለ ማርያምን ይዘው ከንጉሡ በስተኃላ ቆመው ጸሎተ ምሕላ ያደርሱ ነበር፡፡

ንግሥቲቱ እቴጌ ጣይቱም በጸሎት ጊዜ በመዓልትም በሌሊትም ከእነርሱ
አትለይም ነበር፡፡ ኹላቸው ካህናትም በአምላካቸው እግዚአብሐር የሕግ ታቦት
ፊት መለከት ይነፋ ነበር፡፡
በዚህም ዕለት ይኸውም በወርኃ የካቲት 23 ቀን በሮማውያንና
በኢትዮጵያውያን መካከል ከፈተኛ ጦርነት ኾነ፡፡ በሰማይም ታላቅ ተዐምር
ተደረገ፡፡ የቀስተ ደመና ምልክት ታየ፡፡ ከቀስተ ደመና ውስጥ መልኩ አረንጓዴ
የሚመስል ጢስ ይወጣ ነበር እንደ ክረምት ነጎድጎድ ያለ ድምፅም ተሰማ፡፡
ከዚኽ የነጎድጎድ ድምፅ የተነሣ በሮማውያን ወታደሮች ዘንድ ከፍተኛ ድንጋጤና
ሽብር ሆነ ለመዋጋትም አልቻሉም፡፡

ይልቁንም ኃያሉ ገባሬ ተዐምር ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ በአምባ ፈረሱ ላይ ተቀምጦ ከነፋስ ይልቆ እየሀፋጠነ በዓየር ላይ በተገለጸ ጊዜ ሮማውያን በግንባራቸው ፍግም እያሉ ወደቁ፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ አምላካቸው ሊረዳቸው መጣ፡፡ እንግዲህ ማን ያድነናል አሉ፡፡ ምድር ጠበበቻቸው፡፡ በዚህም ጊዜ የኢትዮጵያ ሠራዊት የሮምን ጦር ሠራዊት ፈጇቸው፡፡
የተረፋትንም ማረኳቸው ፈጽመው እስኪያጠፏቸውም በሮማውያን ላይ
የእግዚአብሔር ሥልጣን የኢትዮጵያን እጅ እየበረታች ሔደች፡፡
የኢትያጵያው ንጉሠ ነገሥት ሣህለ ማርያም ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ
በእግዚአብሔር ኃይል በገባሬ ተዐምራት ቅዱስ ጊዮርጊስ ተራዳኢነት
የሮማውያንን የጦር ሠራዊት በጦርነት ድል አድርጎ የድል አክሊል ተቀዳጀ፡፡

በነቢዩ ዳዊት የምስጋና ቃል የድል ዘውድ ያቀዳጀኝን እግዚአብሔር ባለ ዘመኔ ኹሉ አመሰግነዋለሁ ለፈጣሪዬ እዘምራለሁ አለ፡፡
ሕዝቡም ኹሉ በክብር ከፍ ያለ እግዚአብሔርን በፍጹም ምስጋና
እናመሰግነዋለን የሮማዉያንን ኃይል ቀጥቅጦ አጥፍቷልና ሠረገሎቻቸውንም
ሰባብሯልና ሠራዊቱንም ኹሉ በምድር ላይ በትኗልና እያሉ አመሰገኑ፡፡
በፈጣሪው ኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል በጦርነቱ መኻል የረዳቸው ቅዱስ
ጊዮርጊስንም በፍጹም አደነቁ፡፡ የሮማ የጦር ሠራዊትም በኢትዮጵያውያን ፊተቀ ተዋረዱ ዳግኛም በኢትያጵያ ላይ ራሳቸውን ከፍ ከፍ አላደረጉም፡፡

ይኽ የኢትዮጵያ ንጉሥ ነገሥት ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክም ከዐድዋ ጦርነት
ከተመለሰ በኃላ የኹላቸው ኢትዮጵያውያን ከተማቸው በኾነች ዋና ከተማ አዲስ
አበባ መኻል በሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ስም ሕንፃ ክርስቲያን ተከለ፡፡
ስሟንም ገነተ ጽጌ ብሎ ሰየማት፡፡
ንጉሡ ሚኒሊክን ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ በጦርነት ቦታና ሀገሩ
ችግር በገጠማት ጊዜ ኹሉ ይረዳው ነበር፡፡

የኃያሉ ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ጸሎቱና በረከቱ ከኹላችን
ኢትያጵያውን ጋር ይኹን፡፡

ቅድስት ሀገራችን ኢትዮጵያንም በነፃነት ይጠብቅልን ለዘለዓለሙ አሜን፡፡

(ገድለ ቅዱስ ጊዮርጊስ)

https://t.me/Ethiopian_Ortodoks


በንጽሕና ለመኖር እየታገለ የሚወድቅን እግዚአብሔር አያዝንበትም። ድካሙን እና ያልተቋረጠ ጥረቱን አይቶ ድል የሚነሣበትን መንፈሳዊ ጸጋ ይሰጠዋል እንጂ። እንድትኖር በታዘዝከው ልክ ለመኖር ሞክረህ ስላልሆነልህ በራስህ ተስፋ አትቁረጥ። መሆንህን ብቻ ሳይሆን ፈልገህ መሞከርህን እግዚአብሔር ይቆጥርልሃል። ሰይጣን አቁስሎህ ስለሻረው ጠባሳህ አትቆጭ። ብዙ ጠባሳ እኮ  ለሚዋደቅ ጀግና ወታደር የክብር ምልክቱ ነው። አፈ ወርቅ ዮሐንስ እንደሚለው የማይቆስለው የማይዋጋ ብቻ ነው።

ዲያቆን አቤል ካሳሁን

3.3k 0 26 4 107

ውድ የኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ  ቤተሰቦች

ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ30ሺ በላይ ቤተሰብ በላይ አፍርቷል ፤ ይህ የሆነው በእኛ ጥረት ብቻ ሳይሆን በእናንተም ጭምር ነው ።

መርጣችሁ ስለምትከተሉን ከልብ እናመሰግናለንእዚህ ለመደረስ ያገዛቹን በሙሉ ከልብ እናመሰግናለን !  

በዚህ መንፈሳዊ ቻናል ላይ ያላችሁን አስተያየት። በኮመንት ላይ ያስቀምጡልን ።💬

በቀጣይ 40...K




አቤቱ ተወዳጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ፦
የምንኮራበት ክብራችን የምንደምቅበት አክሊላችን አንተ ነህ፤ ቀና ያልንብህ ትምክህታችን ያረፍንብህ ክንዳችን አንተ ነህ፤ እግራችን እንዳይሰናከል የምትጠብቀን እንዳንባዝን የምታረጋጋን አንተ ነህ፤
ጌታችን ሆይ፦ ፍቅርህን የሚመስለው የለም፡፡

እንዳንወድቅ የምትጠብቀን ብንወድቅ የምታነሳን አንተ ነህ፤ እንዳንደክም የምትራራልን ብንደክም የምታበረታን አንተ ነህ፤ እንዳንታመም ባንተ እንታመናለን ብንታመምም ስላንተ ተስፋ አለን፤
ጌታችን ክርስቶስ ሆይ፦ እንዳንተ ያለ ለእኛ ማን አለን? እንዳንሰናከል መላእክቱን ስለእኛ አዘጋጀልህን ጠላቶች እንደበዙብን አይተህ ወዳጆችን አበዛኅልን፤ ፈተናወቻችንን አይተህ መውጫውን ደግሞ አመላከትከን የቀደመውን ፍቅራችንን ብንቀንስ ያንተን ፍቅር አበዛህልን፤

ጌታችን ክርስቶስ ሆይ፦ እንዳንተ ያለ ለእኛ ማን አለን? ራቅንህ አንተ ወደኛ ቀረብክ፤ በግብራችን ናቅንህ አንተ ግን እኛን አከበርክ፤ ያለአንተ መኖር እንደማንችል ታውቃለህና ክፋታችንን ሳታይ ራራህልን ስንፍናችንን ሳታይ ቀረብከን ፤
ጌታችን ክርስቶስ ሆይ፦ እንዳንተ ያለ ለእኛ ማን አለን? ተወዳጅ ሆይ፦ እንዳንተ ያለ ለእኛ ማን አለን? ማንም የለንምና ክብራችንን አውቀን እንኖር ዘንድ አንተን ሳናስብ የምንውልበት ጊዜ አይኑረን፡፡

🌷ክብርና ምስጋና ላንተ ይሁን
🙏

4.4k 0 41 4 106

ጥፋት እኮ

ሰም ቢፈልግ ኮርቶ በኔ በተጠራ
ነውር እኮ ቤት ቢኖረው ሰውነቴ የሱ ሥፍራ

ኃጢያት እኮ

አባት ቢሻ ደም አምጬ በወለድኩት
ክፋት እኮ መልክ ቢሆን ቁርጥ እሱን በመሰልኩት 

በደል እኮ

ትግል ቢሻ እኔ እኮ ነኝ ጦር ጉልበቱ
ዝሙት እኮ ውበት ቢሆን መልኬ ነበር ምልክቱ

መራቆቴ

ምህረት አቅፎት በቸር ክንድህ ባመለጠ
እንኳን ልትፈርድ በሸሸከው በመረሳት ዋጋ ቀለህ

ደግ እኮ ነህ

ሁሉን ሸፋኝ ምን በገጼ ተገለጠ
እንደገና ለመከዳት ዛሬም በሬን ታንኳኳለህ
🙏

@Ethiopian_Ortodoks


#ጸልየህ_ልታደርገው_ትችላለህ?

ማልዶ ቤተ ክርስቲያን ተሳልሞ ወደ ሥራ የሚሄድ አንድ መንፈሳዊ ሰው በጉዞው ከሌላ መንገደኛ ሰው ጋር ይገናኛል። ጥቂት እንደ ተጨዋወቱ ይህ በመንገድ ያገኘው ሰው ከደረት ኪሱ የሲጋራ ፓኮ በማውጣት አንዱን መዝዞ እንዲወስድ ይጋብዘዋል። ያም መንፈሳዊ ሰው "አይ  ይቅርብኝ" ሲል እምቢታውን ገለጸ። ባለ ሲጋራውም "ኃጢአት ነው ብለህ ስላሰብህ ነው እምቢ ያልከኝ? ማጨስ እኮ ከአስጨናቂዋ ሕይወት ፋታ ለመውሰድና ራስን ዘና ለማድረግ ይረዳል። ግድ የለህም አንዱን ሞክር" እያለ ሊያግባባው ጣረ።  በመጨረሻም መንፈሳዊው ሰው "ግድ የለም ለእኔ ይቅርብኝ። ባይሆን አንተ ይጠቅመኛል ካልህ በቃ ሲጋራውን ከመለኮስህ በፊት አንድ "አባታችን ሆይ" ጸልይና ጀምር" አለው። በዚህ ጊዜ ያ መንገደኛ ደንግጦ እንዲህ ሲል መለሰ "ጸሎት ጸልዬማ እንዴት እንዲህ አደርጋለሁ?!"

በጸሎት ልትጀምር የማትችላቸው ማናቸውም ነገሮች ለአንተ መልካም አይደሉም። በልብህ ኃጢአት እንድታደርግ የሚገፉፉህ ክፉ ሐሳብ ሲመጣ "ይህን ጸልዬ ማድረግ እችላለሁ?" ብለህ ራስህን ጠይቅ። ከጸሎት ጋር የማይጣጣም ከመሰለህ እርሱ ኃጢአት ነውና ተወው። ጸልዮ የሚዘሙት፣ ጸልዮ የሚሰርቅ፣ ጸልዮ ባልንጀራውን የሚሳደብ፣ ጸልዮ በወንድሙ ላይ ክፉ የሚያደርግ ማን ነው?

4.3k 0 46 3 113

በዚህ አለም እንግዳ መሆንህንና ወደ ሰማያዊው እንደምትመለስ ዘወትር አስታውስ። ያን ግዜ ለዚህ አለምና በደስታው ተስፋ ማድረግን ትተዋለህ

ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሽኖዳ

5.4k 0 30 4 154

ጾም የሥጋ ረሀብ አይደለም፤ የነፍስ ምግብ እንጂ። አንዳንድ ሰዎች እንደሚያስቡት ጾም የሥጋ ሥቃይ ሰማዕትነት ወይም መስቀል አይደለም፤ ሥጋ ከነፍስ ጋር የሚተባበርበት ደረጃ ላይ ለመድረስ ከፍ ከፍ የሚልበት እንጂ። ስንጾም የመጾማችን ዕቅድ ሥጋችንን ለማንገላታት አይደለም፤ ጠባዩን ለመግራት እንጂ። ይህ በመሆኑም  አንድ የሚጾም ሰው መንፈሳዊ እንጂ ሥጋዊ ሰው አይሆንም ማለት ነው።

ጾም መናኝ ነፍስ ስለሆነ በምናኔ ውስጥ ያለ ባልንጀራ ሥጋውን ይዞ ይጓዛል እንጂ፤ ብቻውን አይጓዝም። ጾም ማለት የተራበ ሥጋ ማለት አይደለም የመነነ ሥጋ እንጂ። ጾም የሥጋ ረሀብ አይደለም የሥጋ ልዕልና እና ንጽህና እንጂ ለመብላት የሚናፍቅ የሚራብ ሰውነት ያለበት ሁኔታ ማለትም አይደለም፤ መብላት ዋጋውን የሚያጣበትና ሰውነት ለመብላት ካለው ፍላጎት ራሱን የሚያላቅቅበት ሁኔታ እንጂ።

አቡነ ሺኖዳ

6k 0 61 2 94

🙏🙏🙏ይቅርታ🙏🙏🙏

እኔ አብይ ጾም ከመድረሱ በፊት ይቅርታ ለመጠየቅ 1ኛ መሆን እፈልጋለሁ
ይቅርታ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ያስቀየምኳችሁ
ይቅርታ በኔ ምክንያት ትንሽም ብትሆን ያናደድኳቹህ

የምታቁኝም የማታቁኝም ሁላችሁንም ይሄን ፅሁፋ ያነበባችሁ በሙሉ ከዚ በፊት ያረኩትን ደግሜ ላላደርገዉ ከልቤ ይቅር እንድትሉኝ እጠይቃችኋለሁ ሁላችሁም በልባቹ ይቅር ሳትሉ እንዳታልፉ

🙏 የዓብይን ጾም ሁላችንም በይቅርታ እንጀምር 🙏

7.3k 0 229 5 173

➝የት እሄዳለሁ
➝አልልም ሲከፋኝ
➝ኪዳነ ምህረት አንች እያለሽልኝ
➝ኪዳነ ምህረት የረዳችዉ አሜን ይበል❤🙏

➝⓰እናቴ ሚስጥርኛዬ♥️

5.1k 0 11 37 182

ሰሚነሽ ኪዳነምህረት ❤

5.9k 0 2 10 203

#የዘመመ_ዘመን

ኪስህ ገንዘብ ሲኖር ስትበትን ስትመዘው
ከጎንህ ሰው አለ እንደልጅ ´ምታዘው
ብዙ አፋሽ አጎንባሽ በዙሪያህ ታያለህ
ገና ሳታስነጥስ ይማርህ ባይ አለህ
እንቅፋት ሳይመታህ እኔን ´ሚል ለይምሰል
አይጠፋም ብዙ ሰው ሳታስል የሚያስል
አጣሁ ያልክ እለት ግን ኪስህ ሲሆን ባዶ
አንተ በዚህ ስትሄድ እነሱ በማዶ
አይደለም እንቅፋት ስትውል ብታስነጥስ
ለሞት ብታጣጥር ሰው የለም የሚደርስ
ነገ ለሚነጋ ዛሬ ቀን ቢጨልም
እንኳን ያበላኸው…..
እንኳን ያጠጣኸው….
የራስህ ጥላ እንኳን ካንተ ጋር አይደለም
ብዙም አትገረም…
በዘመመ ዘመን እንደዚህ ናት አለም!

ነገር ግን ወዳጄ አንድ ነገር እመን የፈጠረህ ወደዚህ ምድር ያመጣህ ዛሬን ያዋለህ አምላክህ ፈጣሪህ መቼም እንደማይተውህ አስታውስ
ምክንያቱም እሱ ቸር ሩኅሩህ የሁሉ አባት ነውና በሱ ተመካ🥰✝

20 last posts shown.