Posts filter


የዓለም ምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ ለሰብአዊ እርዳታ ከፍተኛ የገንዘብ እጥረት ማጋጠሙን አስታወቀ

የተባበሩት መንግስታት የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) በኢትዮጵያ ለሚያደርገው የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት በአስቸኳይ 228 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የገንዘብ እጥረት እንዳጋጠመዉ ይፋ አደረገ።

ይህ የገንዘብ እጥረት ከመጋቢት እስከ ነሐሴ 2017 ዓ.ም. ያለውን ጊዜ የሚሸፍን ሲሆን ቀድሞውንም የምግብ ርዳታ እየተቀነሰ ባለበት ወቅት ላይ የከፋ ችግር ሊያስከትል እንደሚችል አስጠንቅቋል።

ድርጅቱ ባወጣው ሪፖርት እንዳመለከተው በከፍተኛ የገንዘብ እጥረት ምክንያት የእርዳታ ምግቡን ወደ 65 በመቶ ዝቅ ለማድረግ ተገዷል።


ኢትዮ ኤይድ በሚል ለተቸገሩ ጎረቤት ሀገራት እርዳታ
የሚቀርብበት አዲስ አዋጅ ለፓርላማ ቀረበ

ኢትዮጵያ ለሚያጋጥሙ አደጋዎች ሁሉ በራስ አቅም ምላሽ ለመስጠት በየዓመቱ ከበጀቷ 3 በመቶ ያህል ገንዘብ ለመሰብሰብ እያንዳንዱ ነዋሪ የማዋጣት ግዴታ አለባት ተብሏል።

በዚህም ኢትዮ ኤይድ በሚል ከራሷ አልፋ ለተቸገሩ ጎረቤቶች እርዳታ ታቀርባለች ተብሏል፡፡ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ረቂቅ አዋጅ ላይ በፓርላማው ውይይት ሲደረግ ነው ይህ የተባለው፡፡


አዲሱ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የቃልኪዳን ሰነድ ፈረሙ

አዲሱ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ "ከሕገ መንግሥቱን" እና "ከሀገር ሉዐላዊነት"፤ "ያፈነገጡ ግንኙነቶች እና እንቅስቃሴዎች እንዲቆሙ የማድረግ" ኃላፊነትን የሚጥልባቸው የቃል ኪዳን ሰነድ ላይ መፈረማቸው ተገልጿል።

የቃል ኪዳን ሰነዱ፤ የቀድሞ ታጣቂዎች ትጥቅ መፍታት እና መልሶ መቋቋም ተግባር በአፋጣኝ እንዲጠናቀቅ የማድረግ ኃላፊነትንም ለጊዜያዊ አስተዳደሩ ይሰጣል ተብሏል።




ትራምፕ ተጨማሪ ታሪፍ እንደሚጥሉ አስጠነቀቁ

ዶናልድ ትራምፕ ተጨማሪ 50% ታሪፍ ቻይና ላይ ለመጣል ዝተዋል። ቻይና ወደ አሜሪካ የምትልካቸው ሸቀጦች ላይ ቻይና የጣለችው 34% ታሪፍ የማይነሳ ከሆነ ተጨማሪ 50% ታሪፍ ቻይና ላይ እንደሚጥሉ አስታውቀዋል።

ባለፈው ሳምንት ቻይና ላይ ለጣሉት ታሪፍ በምላሹ ቻይና 34% ታሪፍ እንደምትጥል አስታውቃለች። ትራምፕም ቻይና የጣለችውን የአጸፋ ታሪፍ እስከ ማክሰኞ ድረስ ካላነሳች 50% ተጨማሪ ታሪፍ እንደሚጥሉ አስጠንቅቀዋል።


በትግራይ ክልል ከአንድ ሚሊየን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸው ተሰማ

በትግራይ 1.2 ሚልዮን ሕጻናት እና አዳጊዎች ወደ ትምህርት ገበታ አለመመለሳቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። በትግራይ ከጦርነቱ በኋላ ጭምር የቀጠሉት ሰብአዊ፣ ማሕበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች እንዲሁም መፍትሔ ያላገኘው የተፈናቃዮች ጉዳይ አሁንም በትግራይ ሚልዮኖች ከትምህርት እንዲርቁ ማድረጉ ተገልጿል።


በቀነኒ አዱኛ ሞት ዙሪያ ፖሊስ የምርመራ ውጤቶች አሁንም አልደረሱኝም አለ

በፍቅር አጋሩ ቀነኒ አዱኛ ግድያ ተጠርጥሮ በእስር ላይ የሚገኘው ድምጻዊ አንዱአለም ጎሳ በዛሬው ዕለት በአራዳ ምድብ ችሎት ለሦስተኛ ጊዜ የቀረበ ሲሆን፤ ፖሊስ በችሎቱ "የፌደራል ፖሊስ ፎረንሲክ የምርመራ ውጤቶቹ አሁንም አልደረሱኝም" በማለት 14 ቀን ተጨማሪ ቀናት ጠይቋል።

በዛሬው ዕለት በችሎቱ የፖሊስ የምርመራ ውጤት ይጠበቅ የነበረ ቢሆንም ፖሊስ የ15 ሰዎች መረጃ ማሰባሰቡን በመግለጽ፤ ነገር ግን ፎረንሲክ የምርመራ ውጤቶቹ ስላልደረሱት ተጨማሪ ቀናትን ጠይቋል።

የአንዱዓለም ጠበቃ በበኩሉ የቀነኒ ዲያሪ እሱ ጋር እንዳለ ጠቅሶ፤ ቀነኒ ሯሷን ለማጥፋት በተደጋጋሚ መድኃኒት ወስዳ እንደነበር ተፅፎ ማግኘቱን አስታውቋል።


በኢትዮጵያ የተከሰከሰው ቦይንግ የፍርድ ሂደት ሊጀመር ነው

ቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን መጋቢት 1፣ 2011 ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ ሲበር ቢሾፍቱ አካባቢ መከስከሱ ይታወቃል። ቦይንግ ከስድስት ዓመት በፊት በኢትዮጵያ ከደረሰው የአውሮፕላን መከስከስ አደጋ ጋር በተያያዘ ዛሬ በፍትሐብሔር ፍርድ ቤት ፊት ይቆማል።


ከአደጋው ጋር በተገናኛ ለመጀመሪያ ግዜ ለፍትሐብሔር ፍርድ ቤት የሚቀርብ ጉዳይ ይሆናል ነው የተባለው።




ሁለት የሕዝብ እንደራሴዎች ወደ እስራኤል እንዳይገቡ ታገዱ

እስራኤል ሁለት የብሪታንያ የሕዝብ እንደራሴዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ወደ ሀገሯ እንዳይገቡ መከልከሏ ተሰምቷል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤቱ አባላት ወደ እስራኤል ያቀኑት ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ነበር ተብሏል።

እስራኤል ባለሥልጣናት ሁለት የሌበር ፓርቲ የፓርላማ አባላት ወደ ሀገሯ እንዳይገቡ መከልከሏን እና ማሠሯን የዩናይትድ ኪንግደም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴቪድ ላሚ ተችተዋል።


አሜሪካ ለደቡብ ሱዳን የሰጠችውን ቪዛ እንዲሻር መወሰኗ ተሰማ

የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት ኃላፊ ማርክ ሩቢዮ የደቡብ ሱዳን ፓስፖርት ባለቤት ለሆኑ ሰዎች የተሰጠው ሁሉም አይነት ቪዛ እንዲሻር መደረጉን አስታውቀዋል።

ኃላፊው ቅዳሜ ምሽት ባስታወቁት መሰረት የደቡብ ሱዳንን ፓስፖርት ይዘው የአሜሪካ ቪዛ የተሰጣቸው ቪዛቸው እንደተሻረ ያሳወቁ ሲሆን የደቡብ ሱዳንን መንግስትም አሜሪካ ላይ ጥቅሙን ለማስጠበቅ የሚጥር ብለው ገልፀውታል።


የደቡብ ኮሪያ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ዩን ሱክ ዬውል ቢሮዋቸውን እንዲለቁ ማድረጉ ተገለጸ

የደቡብ ኮሪያ ህገመንግስታዊ ፍርድ ቤት በሃገሪቱ ላይ የወታደራዊ አስተዳደር ህግ በማውጣት ክስ የቀረበባቸውን ፕሬዝዳንት ዩን ሱክ ዬውል ቢሮዋቸውን እንዲለቁ ውሳኔ መስጠቱ ተገልጻል፡፡

ይሄም የፍርድቤቱ ውሳኔ በዋና ከተማዋ ሴኡል በሰውዬው ደጋፊዎችና ተቃዋሚዎች ላይ ሁለት አይነት ስሜት ፈጥሩዋል ተብሏል፡፡


በሩስያ ጥቃት በርካታ ሰዎች መገደላቸው ተሰማ

ሩስያ በማዕከላዊ የዩክሬይን ግዛት በምትገኝ የፕረዚደንት ቮሎዶሚር ዘለንስኪ የትውልድ ከተማ ላይ በፈጸመችው የሚሳይል ጥቃት የሞቱ ሰዎች ቁጥር 18 መድረሱን የአካባቢው አስተዳዳሪዎች ዛሬ ገለጹ። ትላን በክሪቪሪክ ከተማ በተፈጸመው ጥቃት 61 ሰዎች ቆስለዋል ነው የተባለው።

የግዛቲቱ ገዥ ሰርሒ ሊሳክ ለአሶሽየትድ ፕረስ እንዳሉት ከሞቱት 18ቱ መካከል አንድ የ9 ዓመት ሕጻን ይገኝበታል። ከቆሰሉት 61 ሰዎች መካከልም የ3 ወር ሕጻንና ሽማግሌዎች ይገኙበታል ሲሉ የስራ ሓላፊው ተናግረዋል።




የማያንማር ሚስ ቱሪዝም የቁንጅና ውድድር አሸናፊ በሰሞኑ መሬት መንቀጥቀጥ ህይወቷ እንዳለፈ ተነገረ

ሚስ ቱሪዝም ማያንማር ተብላ ከሰባት አመት በቁንጅና ውድድር አሸናፊ የነበረችው ሲሊሚ ሰሞኑ በማዕከላዊ ምያንማር በደረሰው አውዳሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ህይወቷ እንዳለፈ የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

ሚስ ቱሪዝም ምያንማር ድርጅት በፌስቡክ ባወጣው መግለጫ ሲሊሚ 7.7 በሬክተር ስኬል በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ ወቅት በማንዳሌይ በሚገኘው የስካይ ቪላ ህንፃ ፍርስራሽ ውስጥ ሲሊሚ ተቀብራ አስከሬኗ በነፍስ አድን ቡድኖች መገኘቱን ገልጿል።

ሲሊሚ እ.ኤ.አ. በ2018 በተካሄደው ሚስ ቱሪዝም ወርልድ ውድድር ምያንማርን ወክላለች።

ኤኤፍፒ ሐሙስ እንደዘገበው በአደጋው የሟቾች ቁጥር ወደ 3,000 ከፍ ብሏል።


''ፑቲን የተኩስ አቁም ላይ ያላቸው አቋም በሳምንታት ውስጥ ያሳውቁ'' አሜሪካ

ፕሬዚዳንት ፑቲን ስለ ሰላም እንዲሁም የተኩስ አቁም ላይ ያላቸው አቋም "በሳምንታት ውስጥ" እንደሚታወቅ የአሜሪካ ከፍተኛ ዲፕሎማት ተናግረዋል።

ፑቲን ለዩክሬን ጦርነት ሰላማዊ እልባት ለመስጠት "በወራት ውስጥ ሳይሆን በሳምንታት" ውሳኔ ላይ ሊደርሱ እንደሚገባ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ተናግረዋል።

ማርኮ ሩቢዮ "ጦርነቱን ለማስቆም የሩሲያው ፕሬዚዳንት ውሳኔ ላይ መድረስ አለባቸው" ሲሉ በብራስልስ ከነበረው የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል-ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ በኋላ ነው የተናገሩት።


የሁቲ አማጽያን የቀይ ባህር እንቅስቃሴ የኢትዮጵያ የአበባና ፍራፍሬ ምርት ላይ ተጽእኖ ማሳደሩ ተገለጸ

በቀይ ባህር ላይ የሚንቀሳቀሱት የሁቲ አማጺያን በመርከቦች ዝውውር ላይ የፈጠሩት ተጽእኖ የአበባ እንዲሁም የአትክልትና ፍራፍሬ አምራች እና ላኪዎች ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ማሳደሩን የግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡


አማጽያኑ ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ ብቻ በየመን እና እና በአፍሪካ መካከል በሚገኘው የባብ ኤል መንደብ የባህር ሰርጥ በሚጓዙ ከ100 በላይ የንግድ መርከቦች ላይ በሚሳኤል እና በድሮን ጥቃቶች የፈጸሙ ሲሆን፤ በዚህም ምክንያት በርካታ የመርከብ ድርጅቶች ጥቃቱን በመፍራት በመስመሩ የሚያደርጓቸውን ጉዞዎች ለመቀየር እየተገደዱ ይገኛል።


ጅቡቲ ላይ ለሶስት ቀናት ሥራ ባለመኖሩ ምክንያት በኢትዮጵያ የነዳጅ እጥረት መፍጠሩን የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን አስታወቀ


በአዲስ አበባ የነዳጅ ማደያዎች ከሰሞኑን እጅግ ረጃጅም የናፍጣ ሰልፍ መታየቱ ተመልክቷል። በርካቶችም ናፍጣ ለመቅዳት ረጅም ሰዓታት እየተሰለፉ የስራ ሰዓታቸው እየባከነ ይገኛል።

የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ፤ " ባለፉት ቀናት በአንዳንድ አካባቢዎች የነዳጅ እጥረት በተወሰነ መልኩ ተከስቷል " ሲል ለኤፍ ኤም ሲ ተናግሯል።

የነዳጅ እጥረቱ በጅቡቲ የኢድ አልፈጥር በዓልን ተከትሎ ለሶስት ቀናት ሥራ ባለመኖሩ ነዳጅ ወደ ኢትዮጵያ ካለመግባቱ ጋር ተያይዞ የተፈጠረ ነው ሲል አሳውቋል።

የተከሰተውን የናፍጥ እጥረት ለመፍታት ከመጠባበቂያ ዴፖ ለማደያዎች የማከፋፈል ሥራ ተሰርቷል ብሏል።

የነዳጅ ሰልፉ ከዋጋ ጭማሪ ጋር የተያያዘ እንዳልሆነም መ/ቤቱ በሰጠው ቃል ጠቁሟል።




በእስራኤል ጥቃት ከሃያ በላይ ሰዎች መገደላቸው ተሰማ

እስራኤል ከሰሜን ጋዛ ለተፈናቀሉ ቤተሰቦች መጠለያ ሆኖ በማገልገል በሚገኝ ትምህርት ቤት ላይ በፈጸመችው የአየር ጥቃት ቢያንስ 27 ፍልስጤማውያን መገደላቸውን የጋዛ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

ዳር አል አርቃም በተሰኘው ትምህርት ቤት በተፈጸመው ጥቃት ከተገደሉት በተጨማሪ በርካቶች መቁሰላቸውን በሐማስ የሚተዳደረው የጤና ሚኒስቴር የአካባቢውን ሆስፒታል ዋቢ አድርጎ ጠቅሷል።

የእስራኤል መከላከያ በበኩሉ ትምህርት ቤቱን ሳይጠቅስ የሐማስ የትዕዛዝ እና የቁጥጥር ማዕከልን መምታቱን ገልጿል።

የጋዛ የጤና ሚኒስቴር ቀደም ብሎ እስራኤል በ24 ሰዓታት ውስጥ ባደረሰችው ጥቃት 97 ፍልስጤማውያን መገደላቸውን አስታውቆ ነበር።

20 last posts shown.