ገድለ ቅዱሳን Gedle Kidusan Acts of Saints


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Religion


ይህ ገጽ ስለ ቅዱሳን ክብር ተዓምር ገድል ይናገራል::

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Religion
Statistics
Posts filter


"ቅዱስ ጊዮርጊስ ሆይ! በአፌ ብቻ ሣይሆን ከልቤ እወድሃለሁና ሰላም እልሃለሁ።
ስለዚህ አባት ሆይ! ምስጋናዬን አታቃልብኝ ተቀብለህ ዋጋዬን አሰጠኝ እንጅ። ለእኔ የድሃው ንጹሕ ወርቄ አንተ ጊዮርጊስ ነህና።"
(መልክአ ጊዮርጊስ)


"አስተጋይድ ፈረሰከ ወአብድር እምዐውሎ ቅዱስ ጊዮርጊስ
ለከ ይብለከ ልሣነ ምኒልክ ንጉሠ ነገሥት"
(ቅዱስ ጊዮርጊስ ከዓውሎ ነፋስ ይልቅ ፈረስህን አቀዳድም ይልሃል የንጉሠ ነገሥት ምኒልክ አንደበት።)

እንኳን ለቅዱስ ጊዮርጊስ ኃያል ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!


እንኳን አደረሳችሁ!

‹‹ኦ ፍጡነ ረድኤት እምሩጸተ ነፋስ
ወዐውሎ ለዘይጼውዓከ በተወክሎ
ጊዮርጊስ ቅረብ ለምሕረት ወለተሣህሎ፡፡
ተወከፍ ወትረ ጸሎትየ ወቃለ ጽራኅየ ኵሎ፡፡ እስመ ልበ አምላክ ርኅሩኅ በኀቤከ ሀሎ፡፡››

"ቅዱስ ጊዮርጊስ ሆይ! አንተን በመታመን ለጠራህ ሁሉ ፈጥነህ ስትደርስለት ከዓውሎ ነፋስ ይልቅ በተፋጠነ ሩጫ ነው እኮን፡፡
ጊዮርጊስ ሆይ! የዘወትር ጸሎቴንና የቃሌንም የልመና ጩኸት ትቀበል ዘንድ ለይቅርታና ለምሕረት ፈጥነህ ወደ እኔ ቅረብ።"
(መልክአ ጊዮርጊስ)


"አንቲ ውእቱ ተስፋሁ ለአዳም አመ ይሰደድ እምገነት።"
(አባ ሕርያቆስ)
እንኳን ለቅድስት ኪዳነ ምሕረት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!


"አባቴ ጊዮርጊስ ሆይ! የልቤን ኀዘን ስነግርህ ፈጥነህ ጸሎቴን ስማኝ፤ ነገሬንም አድምጠኝ።
ያዘኑትን የምታረጋጋ ሆይ ወደ እኔ ቅረብ፤ በአጠገቤም ተገኝተህ አለሁልህ በለኝ።"
(መልክአ ጊዮርጊስ)


‹‹ኦ ፍጡነ ረድኤት እምሩጸተ ነፋስ
ወዐውሎ ለዘይጼውዓከ በተወክሎ
ጊዮርጊስ ቅረብ ለምሕረት ወለተሣህሎ፡፡
ተወከፍ ወትረ ጸሎትየ ወቃለ ጽራኅየ ኵሎ፡፡
እስመ ልበ አምላክ ርኅሩኅ በኀቤከ ሀሎ፡፡››

"ቅዱስ ጊዮርጊስ ሆይ! አንተን በመታመን ለጠራህ ሁሉ ፈጥነህ ስትደርስለት ከዓውሎ ነፋስ ይልቅ በተፋጠነ ሩጫ ነው እኮን፡፡
ጊዮርጊስ ሆይ! የዘወትር ጸሎቴንና የቃሌንም የልመና ጩኸት ትቀበል ዘንድ ለይቅርታና ለምሕረት ፈጥነህ ወደ እኔ ቅረብ።"
(መልክአ ጊዮርጊስ)


"ወነአምን በአሐቲ ጥምቀት ለሥርየተ ኃጢአት።"
(ሠለስቱ ምእት)
እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ!


"ክቡሩ አባት ሆይ! ሥጋዊና መንፈሳዊ ጥበብን ግለጽልኝ። ይልቁንም የጸሎትህ ኃይለ ቃል ረዳቴ በመሆን ዓሥራት በኩራት አድርጎ ይጠብቀኝ።"
(መልክአ ገብረ መንፈስ ቅዱስ)


"ዘወትር በማይጠልቅ በብሩህ ፀሐይ ፊት በምድር ዳርቻዎች ሁሉ የስምህ ባለሟልነት የደረሰ የአእላፍ ሰማዕታት አለቃቸው ሰላምታ ለአንተ ይገባል።
ክንፈ ፈጣን ከራድዮን ዖፍ የተባልህ ጊዮርጊስ ሆይ የአፍ እስትንፋስን ተቀብለህና ተሸክመህ ሕማሜን በትን።"
(ሊቁ አርከ ሥሉስ)

በቤተ ክርስቲያን ትውፊት ዛሬ (ጥር ፪ ቀን) የታላቁ ቅዱስና ሊቀ ሰማዕታት ማር ጊዮርጊስ የልደት በዓሉ ነው፡፡
የማር ጊዮርጊስ በረከቱ ይደርብን፡፡


"ቤዛ ኩሉ ዓለም ዮም ተወልደ"
(ቅዱስ ያሬድ)
እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ!






እንኳን ለቅዱስ አምላካችን አማኑኤል፣ ዕለተ ማርያም እና ዕለተ ጌና ስቡሕ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።
†††በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ወንድሞቻችሁ እና እህቶቻችሁ እንዲያነቡት ተጋሩት(share it)
በዲያቆን ዮርዳኖስ አበበ




ታኅሣሥ ፳፯ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
፩.ቅዱስ አብሳዲ ሰማዕት
፪.አባ አላኒቆስ ሰማዕት
፫.አባ በግዑ ጻድቅ
፬.አባ ፊልጶስ

ወርኀዊ በዓላት
፩.ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
፪.አቡነ መብዓ ጽዮን ጻድቅ
፫.ቅዱስ መቃርስ (የመነኮሳት ሁሉ አለቃ)
፬.ቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድ
፭.ቅዱስ ገላውዴዎስ ሰማዕት (ንጉሠ ኢትዮጵያ)
፮.ቅዱስ ቢፋሞን ጻድቅና ሰማዕት
፯.ማር ቅዱስ ፊቅጦር ሰማዕት

"መቶ በግ ያለው ከእነርሱም አንዱ ቢጠፋ ዘጠና ዘጠኙን በበርሃ ትቶ የጠፋውን እስኪያገኘው ድረስ ሊፈልገው የማይሔድ ከእናንተ ማን ነው? ባገኘውም ጊዜ ደስ ብሎት በጫንቃው ይሸከመዋል። ወደ ቤትም በመጣ ጊዜ ወዳጆቹንና ጐረቤቶቹን በአንድነት ጠርቶ 'የጠፋውን በጌን አግኝቼዋለሁና ከእኔ ጋር ደስ ይበላችሁ።' ይላቸዋል። እላችኋለሁ እንዲሁ ንስሐ ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በሰማይ ደስታ ይሆናል።"
(ሉቃ ፲፭፥፫-፯)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር


እንኳን ለሰማዕቱ አባ አብሳዲ እና ለጻድቁ አባ በግዑ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።
†††በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ወንድሞቻችሁ እና እህቶቻችሁ እንዲያነቡት ተጋሩት(share it)
በዲያቆን ዮርዳኖስ አበበ






እንኳን ለቅድስት አንስጣስያ ሰማዕት እና ቅዱስ አቦሊ ጻድቅ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።
†††በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ወንድሞቻችሁ እና እህቶቻችሁ እንዲያነቡት ተጋሩት(share it)
በዲያቆን ዮርዳኖስ አበበ

እስኪ ዛሬ በጥቂቱ የተባረኩ (ቡሩካት) እናቶቻችን እንዘክር። "ቅድስት" የሚለው ቃል ለሁሉም ቅዱሳት እናቶች ቢሰጥም ቅሉ ለድንግል ማርያም ሲሰጥ ግን ትርጉሙ ይለያል። እርሷ "ቅድስተ ቅዱሳን፣ ንጽሕተ ንጹሐን፣ ቡርክት እምቡሩካን፣ ኅሪት እምኅሩያን" ናትና።

ከሰው ልጆችም ሁሉ ትበልጣለች። ይቅርና የሰው ልጅን ንጹሐን መላእክትንም በንጽሕናና በቅድስና ትበልጣቸዋለች። እርሷ እመ ብርሃን፣ የአምላክ እናቱ፣ የሰውነታችን መመኪያ ናትና።

እመቤታችንን "ቅድስት" ስንል "ጽንዕት፣ ንጽሕት፣ ክብርት፣ ልዩ" ማለታችን ነው።
፩."ንጽሕት" ትባላለች። ሌሎች ሰዎች (ቅዱሳን) ቢነጹ ከገቢር፣ ከነቢብ ኃጢአት ነው እንጂ ከኃልዮ ኃጢአት አይደለም። እርሷ ግን ከነቢብ፣ ከገቢር፣ ከኃልዮ ንጽሕት ናት።
"ለመኑ ተውኅቦ ተደንግሎ ኅሊና ለመላእክትሂ ኢተክህሎሙ።
(ኃጢአትን ከማሰብ መጠበቅ ከሰው ልጆች ለማን ተሰጠው፤ ይህስ ለመላእክትም አልተቻላቸውም።)" እንዲል።
(ተአምረ ማርያም)
፪."ጽንዕት" እንላታለን። ሴቶች ቢጸኑ ለጊዜው ነው እንጂ በኋላ በጊዜው ተፈትሆ አለባቸው። እመቤታችን ግን ቅድመ ጸኒስ፣ ጊዜ ጸኒስ፣ ድኅረ ጸኒስ፣ ቅድመ ወሊድ፣ ጊዜ ወሊድ፣ ድኅረ ወሊድ ድንግል ናትና።
"ጽንዕት በድንግልና አልባቲ ሙስና" እንዳላት።
(ቅዱስ ያሬድ)
ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስም "ወትረ ድንግል ማርያም - ማርያም ዘላለማዊት ድንግል ናት።" እንዳለ።
(መጽሐፈ ቅዳሴ)
፫.ድንግልን "ክብርት" እንላታለን። ሌሎች ሴቶች ቢከብሩ ጻድቃን ሰማዕታትን፣ ነቢያት ሐዋርያትን ወልደው ነው። እመቤታችንን ግን የምናከብራት "ወላዲተ አምላክ - የአምላክ እናቱ" ብለን ነውና።
፬.እመቤታችንን "ልዩ" እንላታለን። ከእርሷ በቀር እናት ሁና ድንግል፣ እመቤት ሁና አገልጋይ የሆነች በድንግልና ወልዳ ወተትን (ሐሊበ ድንግልናዌን) ያስገኘች ሌላ ሴት የለችምና።

የእመ ብርሃን ይቆየንና ደግሞ ሌሎች ቅዱሳት እናቶቻችንን እንመልከት። እናቶቻችን ስናከብር የምንጀምረው በቅድስት ሔዋን ነው። ብዙ ጊዜ የእናታችን ሔዋን ጥፋቷ እንጂ በጐ ነገሯ፣ ደግነቷ፣ ንስሐዋ አይነገርላትም። ሆኖም እናታችን ቅድስት ሔዋን ክብር የሚገባት ሴት ናት።
ክርስቶስ ሰው የሆነ እርሷንና ልጆቿን ለመቀደስ ነውና። "ከመ ይስዓር መርገማ ለሔዋን ዲበ ዕፅ ተሰቅለ" እንዲል።
(ድጓ)

ቀጥሎ በብሉይ ኪዳን እነ ሐይከል፣ እድና፣ ሣራ፣ ርብቃ፣ አስኔት፣ ሲፓራ፣ ሐና፣ ቤርሳቤህን የመሰሉ እናቶቻችን በበጐው መንገድ ፈጣሪን ደስ አሰኝተዋል። በዘመነ ሥጋዌም ቅዱሳቱ ሐና፣ ኤልሳቤጥ፣ ማርያም፣ ሶፍያ፣ ሰሎሜ፣ ዮሐና እና ሠላሳ ስድስቱ ቅዱሳት አንስት በጐነታቸው ያበራል።

ከዚያ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ለሁለት ሺህ ዓመታት የተነሱ አእላፍ ቅዱሳት እናቶቻችንን ግን ዘርዝረን አንዘልቃቸውም። በቅድስናቸው አራዊትን ያሰገዱ፣ ነገሥታትን ያንቀጠቀጡ፣ አጋንንትን የረገጡ፣ በዘንዶ ላይ የተጫሙ ብዙ እናቶችን ቤተ ክርስቲያን አፍርታለች።

ዛሬም ቢሆን በበርሃና በከተማ በጐውን ጐዳና የተከተሉ ብዙ እናቶች እንዳሉን እናውቃለን። አንድም እናምናለን። ግን በከተሞች የምንመለከተው ሥርዓቱን የለቀቀው የበርካታ እኅቶቻችን አካሔድ ለሃገርም ለቤተ ክርስቲያንም ትልቅ ስጋት ነው። ክብርና ነውር የማይለይበት ዘመን ይመስላል።

ይህንን እያነበባችሁ ያላችሁ እኅቶቼ! አንድ ነገር ልንገራችሁ። በመልካቸው ብዙዎችን ያጋጩ፣ አጊጠው በመታየታቸው ብዙዎችን ያሰናከሉ፣ ለብዙ ምዕመናንም የጥፋት ምክንያት የሆኑ ብዙ ሴቶች በታሪክ ነበሩ።

የሚያሳዝነው ግን ዛሬ ያሉት ከመሬት በታች ነው። አፈር በልቷቸዋል። ስም አጠራራቸውም ጠፍቷል። በጣም የሚያሳዝነው ደግሞ ዛሬ በዘላለማዊው እሳት እየተቃጠሉ በሲኦል በጥልቁ ውስጥ አሉ።

እናም ወገኖቼ! ይህን አውቀን እንንቃ። ይህ ዓለም ጠፊም አጥፊም ነውና። እድሜአችን ቢረዝምና ከዚህ በኋላ ለመቶ ዓመታት ብንኖርም እርሱም ማለቁ አይቀርምና። ምርጫችን ዘላለማዊው ሕይወት ይሁን ትላለች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን።



20 last posts shown.