Getachew shiferaw


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Other


Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Other
Statistics
Posts filter




"የአማራ ሕዝብ ወሰንና ማንነት ጉዳይ በሕልውና ትግሉ ሂደት ቀይ መስመር ነው!"

ፋኖ




የሰላም ስምምነት የተፈራረመውም፣ ሰላም አስፍነናል ብሎ ድግስ የከረመውም "የፌደራል" ብልፅግና ነው። ጦርነት ሲከፈት መጀመሪያ መግለጫ መስጠት ያለበት እሱ ነው። ለድግሱ ከፊት ከርሞ፣ ለጓዳ ስምምነት ሲባል ናዝሬት ጠርቶ አስተናግዶ አሁን አማራ ክልል የጎን መግለጫ አሰጥቶ ዝም ሊል አይችልም።

የአማራን ግዛቶች አሳልፎ ለመስጠት "የኢትዮጵያ መሬቶች ናቸው። ፌደራል ያስተዳድራቸዋል" ይላል። ወረራ ሲፈፀም "ራሳችሁ መግለጫ አውጡ" ብሎ ይሸሻል። እውነታው አላማቸው አማራው ማስወጋት ስለሆነ ነው! ስምምነቱ ሲጣስ መግለጫ መስጠት ያለበት የፌደራሉ አገዛዝ ነው! ስትጨባበጥ ከርመህ፣ ትጥቅ እንዳይፈታ አድርገህ አሁን አማራን ሲወጋ ክልሉ መግለጫ ያውጣ ልትል አትችልም።

ሰላም እየፈጠርን ነው ብለህ ለዓለም እንዳወራኸው ሁሉ፣ ሲጣስም ለዓለም መንገር ያለብህ ራስህ ነህ። የሰላም ጊዜ ከፊት፣ ሲጣስ በጎን መግለጫ አይሆንም።


አላማጣ አዳሩን ንፁሃንን ሲገድል፣ በርካቶችን ሲያፈናቅል ያደረው ኃይል የደቡብ አፍሪካው ስምምነት በተፈረመ በወር ውስጥ ትጥቅ መፍታት የነበረበት ነው። አብይ አህመድ ትጥቅ እንዳይፈታ አደረገው!

ተፈናቃይ ስለመመለስ ኮሚቴ አዋቅሮ ያለ ፀጥታ ኃይል፣ ያለ ትህነግ መዋቅር ይመለሳል ብሎ መግለጫ በሰጠ በሳምንቱ የትህነግን ታጣቂ ንፁሃንን እየገደለ እንዲገባ ማገዝ ብቻ ሳይሆን መከላከያ የትህነግ ወረራ የተከላከሉትን አማራዎች ገደለ።

የትህነግ ሰዎች በይፋ በአብይ አህመድ ድጋፍ ነው የገባነው ብለዋል። የትህነግ ታጣቂ ባለፉት ቀናት ጦርነት ከፍቶ ንፁሃንን ሲገድል ነው የሰነበተው። በአጭሩ አብይ አህመድና ብርሃኑ ጁላ በአማራ ላይ ይህ ወረራ እንዲካሄድ ትዕዛዝ የሰጡ ናቸው።

ንፁሃን የተገደሉት፣ የተፈናቀሉት፣ የተዘረፉት በአብይ አህመድና ብርሃኑ ጁላ ትዕዛዝ፣ በብልፅግና እና ትህነግ/ህወሓት የጓዳ ውል ነው።

በተረፈ ትህነግ ወዳጅ ይሆናል ብላችሁ የምታስቡ ካላችሁ እርማችሁን አውጡ። ትህነግ ከብልፅግና ጋር ነው የሚሰራው። በጋራ ነው የወረሩን። አማራን ለመውረር ሲመክሩ ከርመው ንፁሃንን እያፈናቀሉ፣ እየገደሉ ነው። ነገ በጋራ ፋኖ ላይም ቢሆን መዝመታቸው የማይቀር ነው!




አማራዎች የትህነግ/ህወሓትን ወረራ ተከላከላችሁ ተብለው በብልፅግና ትዕዛዝ ተገድለዋል!



የትህነግን ወረራ ለመቀልበስ እየተዋጉ የዋሉ አማራዎችን መከላከያ ገድሏቸዋል። ትህነግን ከእነ ከባድ መሳሪያው ያስገባው መከላከያ የትህነግን ወረራ ሲመክት የዋለውን የአላማጣ ወረዳ አስተዳደር ሞላ ደርበው ገድሏል። ሌሎችም የትህነግ/ህወሓትን ወረራ እንዳይከላከሉ መከላከያ መሳሪያ "አውርዱ" ብሎ ተኩሶባቸዋል።

በትህነግ ወረራ ምክንያት በርካቶች የተፈናቀሉና የተጎዱ ሲሆን ለዚህ ተጠያቂው ብልፅግና ነው! አማራ ከደመኛ ጠላቱ የዘር ፍጅትን እንዳይከላከል በብልፅግና ትዕዛዝ እየተጠቃ ነው!


ራያ በአብይ አህመድና ብርሃኑ ጁላ ቀጥታ ትዕዛዝ ተወርሯል!

ትህነግ/ህወሓት በአብይ አህመድና ብርሃኑ ጁላ ቀጥታ እገዛ ራያን ወርሯል። በጓዳ ስምምነት መሰረት ንፁሃን ላይ ከባደ መሳሪያ ጭምር እየተኮሱ ነው!

1) ወረራ ፈፃሚው በሰላም ስምምነቱ ትጥቅ ይፍታ የተባለ አሁን ብልፅግና በጀት የሚከፍለው የጌታቸው ረዳ ጊዜያዊ አስተዳደር የሚያዘው ኃይል ነው።

2) ሰሞኑን ያለ ታጣቂ ተፈናቃይ ይመጣል፣ የፌደራል መንግስቱ ይቆጣጠረዋል ተብሎ መግለጫ ተሰጥቶ ትህነግ በወረራ እንዲይዘው ተደርጓል

3) የጋራ ኮሚቴ ተብሎ የተቋቋመው በቀደም ተገናኝቷል። በጓዳ ስምምነቱ መሰረት ወርራችሁ ያዙ ተብለዋል።

4) የሰላም ስምምነቱ የአማራ ግዛቶች በአማራ ክልል ስር እንዲቆዩ በግልፅ ደንግጓል።

5) አብይ የባህርዳር ሎሌዎቹ አልነበርንም እንዲሉ ወደ አሜሪካ እንዲሄዱ አድርጎ ነው ያስወረረው።




ብልፅግና በይፋ ከኢራን ጎን ተሰልፌያለሁ እያለ ነው!

ይህ ዘገባ ሆን ተብሎ የተሰራ ነው። ከቱርክ ቀጥሎ ከኢራን ድሮን የሚያገኘው ብልፅግና ውለታውን በፕሮፖጋንዳ እየተወጣ ነው። በዚህ ፍጥነት ከኢራን ጋር መቆሙን የገለፀበት ገራሚ የፕሮፖጋንዳ ዘገባ ነው!

1) እስካሁን በርካታ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ከሚገልፁት ውጭ በቁጥር ሁሉ አስቀሞጦ፣ የእስራኤል ስትራቴጅክ ቦታዎች ተጠቁ ብሎ በግልፅ በርዕስ ያስቀምጣል።

2) ይህን የፕሮፖጋንዳ ዘገባውን ታማኒ ለማስመሰል ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች እንደዘገቡት አድርጎ ያቀርባል። ዝርዝር ላይ ግን በማስረጃነት የሚያቀርበው የኢራንን የፕሮፖጋንዳ ቻናል ነው።

3) ጦርነቱ የሁለቱ አገራት ሆኖ ርዕስ ያደረገው የኢራን ቻናል ላይ የወሰደውን ሆኖ በውስጥ ዘገባው የእስራኤልን ባለስልጣን ቃል በትንሹ አካትቷል። የዘገባው አንጓ ግን ኢራን ስኬታማ ጥቃት እንዳደረገች ማሳየት ነው። ብዙ ጊዜ መሰል ዜናዎች ሲሰሩ የሁለቱም በርዕስነት የሚካተቱበት መንገድ ይገለፃል።

4) ኢቲቪ በትዕዛዝ የዘገበው ባይሆን በዚህ ደረጃ ፕሮፖጋንዳ አይሆንም ነበር። አሊያም ዜናውን ኢራን ይህን ያህል ኢላማ መታሁ አለች ብሎ በዘገብ ይችል ነበር። ይህም ፕሮፖጋንዳን ማስተጋባት ቢሆንም አሁን ከሰራው ይሻለው ነበር።

5) ኢቲቪ በዚህ መንገድ እየዘገበ ያለው የእስራኤል መንግስት በይፋዊ መግለጫ ጥቃቱን መቀልበሱን በገለፀበት፣ የአንድ የኢራን ጣቢያን እንደ ገለልተኛ ዓለም አቀፍ ጣቢያዎች አድርጎ በርዕስ አጉልቶ፣ ቀባብቶ ነው።

ይህ ዓለምን ያሰጋ ጦርነት ነው። ለብልፅግና ደግሞ ትርፍ አለው። ድሮን ያገኝበታል። ለዛም ነው በዚህ ደረጃ የዓለም አቀፍ ጦርነት ላይ ወገንተኝነትን የሚያሳየው።

ኢቲቪ የሚሰራው በብልፅግና ቀጥተኛ ትዕዛዝ ነው። አሁን ባለው የኢትዮጵያ ሁኔታ ደግሞ እያንዳንዱ ዘገባ የፖለቲካ ቃና ተሰጥቶት፣ ከብልፅግና ኃይል ተዋቅሮ እያረመ የሚወጣ ነው። የአገር ውስጡ አልበቃ ሲል ከአለም ጦርነትም አተርፋለሁ ብሎ የሚሰራው ፕሮፖጋንዳ ነው።




ማጭበርበሪያ!

ደብረፅዮን የሚመራው ትህነግ/ህወሓት የወልቃይት፣ ራያ፣ ጠለምትና አበርገሌ ወረዳና ቀበሌ አስተዳደሮችን መልምሎ ትግራይ ውስጥ ፅ/ቤት ከፍቶላቸዋል። ከስር እንደሚታየው በአማራ ግዛቶች ስም የፌስቡክ ገፅ ከፍተው የሚያስተዳድራቸው ትህነግ/ህወሓት እንደሆነ አድርገው፣ ሽሬና መቀሌ የወረዳና የቀበሌ እንዲሁም ከተማ አደረጃጀቶች እንደሆኑ አድርጎ ባነር አሳትሞ እየሰበሰበ፣ በአካባቢዎቹ ስም ህገወጥ ማህተም ቀርፆ ደብዳቤ እየፃፈ ወደ አዲስ አበባ መጥቶ ደግሞ "ተፈናቃዮች ይመለሱ" ይላል።

ሰሞኑን በነበረው ስብሰባ ሞንጆሪኖና የትህነግ ጀኔራሎች ትህነግ/ህወሓት ያለምንም ልዩነት የተስማማበትን እስከነ መዋቅሩ መመለስ አቋም እንዲያራምዱ ተደርጎ፣ እነ ደብረፅዮን ከዚህ ሀሳብ የሚለዩ መስለው ቀርበዋል። ጌታቸው ረዳም ሆነ ደብረፅዮን በዚህ ጉዳይ ከጀኔራሎቹ ጋር ልዩነት የላቸውም። የቤት ስራ ነው የተከፋፈሉት። በውይይት የተወሰኑት እንዲሳተፉ ቀሪው የተለየ አቋም የያዘ መስሎ በተግባር እንዲሰራ ነው። በዚህ ማጭበርበሪያ መሰረት ከብልፅግና ጋር እየተሰበሰቡ ነው። ብልፅግና የአማራን ርስቶች በዚህ ሂደት አሳልፎ ለመስጠት እየሰራ ነው።


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


"ፎርማት" ተደርጎ ተከራዬ!

እኔ አይደለሁም ያልኩት። አለቃው ነው። እንደ አመታዊ የፋይናንስ ሪፖርት ቁጠሩት። ኤርሚያስ ለገሰ መከራየቱን አለቃው ቴድሮስ ፀጋዬ በቀጥታ ስርጭት ተናግሯል። እነ ቴድሮስም ከሌላ ቀምተው ነበር የተከራዩት። አሁን ባለጊዜ ጨምሮ ወሰደው።

ትህነግ ኤርሚያስን በቴድሮስ በኩል ነበር የሚያዘው። አሁን አለቃው በብስጭት "ፎርማት ተደርጎ ተከራይቷል" ብሏል። ያው እነ ቴድሮስ (አንዱ የትህነግ ክንፍ) ኪራዩን መክፈል ስላልቻሉ ሌላ ተከራየው። የፖለቲካ ገበያው ሲሞቅ ዋጋ አስወደደ።

በእርግጥ ቴድሮስ ይህን ያለው በድሮው ዕዝ ስለማይሰራለት እንጅ ኤርሚያስ በሌሎች ቡድኖች በኩል ለትህነግ እየሰራ ነው። ደሞዝ ጨምሩኝ ብሎ ካልሆነ ከዛ ሰፈር ያለው የረዥም ጊዜ ውል ነው። ግን ፖለቲካው ተለዋዋጭ ስለሆኑ ሁለት ቦታ ተቀጥሯል። ፖለቲካው ሲገለባበጥም ቋሚ ገቢ ይኖረዋል። እየተገለባበጠ መስራት ነው።

ከወራት በፊት እንደፃፍኩት ኤርሚያስ ሬድዮ ነው። ባትሪ ያለው እስከመጨረሻው ከፍቶ ያስጮኸዋል። እስካሁን ይህን ራዲዮ ከፋች የነበረው ቴድሮስ አሁን በሌላ ሰው እጅ ነው ብሏል። የማስታወቂያ ከሰጡት በመሃል በመሃል ይዘፍንላቸዋል። የተሻለ የሚከፍለው ከሆነ ልዩ ዞንም፣ ልዩ ወረዳም የፈለገ ይከራየዋል። የሀሰተኛ ፖስተሮችም ቢሆን ካገኙት ማሪያምን እየሰደበ ፕሮግራም ከመስራት ወደኋላ አይልም።

ኤርሚያስ በቀጥታ ስርጭት ተሸጠ ተለወጠ ሲባል ደፍሮ የድሮ አለቃውን አይናገርም። ምክንያቱም በርካታ መረጃ ተይዞበታል።




የተፈለገው ይሄ ነው!

ትህነግ ወደራያና ወልቃይት ተፈናቃይን አልመልስም ብሏል። ከእነ ሙሉ መዋቅሬ ነው የምመለሰው ብሎ እየሰራ ነው። ብልፅግና ሰሞኑን ያለ በጀት ከህዝብ ገንዘብ ሰብስበው ልማት የሚሰሩትን አስተዳደሮች አፈርሳለሁ ያለ ሲሆን ትህነግ እስከ ቀበሌ ድረስ አመራር፣ የፓርቲ መዋቅር፣ ፀጥታ አደራጅቶ እየጠበቀ ነው። ትግራይ ውስጥ ቁጭ ብለው የራያና ወልቃይት እስከ ቀበሌ ድረስ መዋቅር ተብለው ተዘጋጅተው መግለጫ እየሰጡ፣ መታወቂያ እያደሉ፣ በማህተም ደብዳቤ እየፃፉ ይገኛሉ። ብልፅግና ይህን ያውቃል።

የተፈለገው የህዝብ አስተዳደርን አፍርሶ ለትህነግ ማስረከብ ነው። የመጀመሪያው ትህነግ የሁመራ ፅ/ቤት ብሎ ያደራጀው መዋቅር የሚጠቀምበት ገፅ ማስረጃ ሲሆን ሁለተኛው የአላማጣ ከንቲባ ብሎ ማህተም አስቀርፆ ደብዳቤ የሚፅፍበት ነው። ሁሉም ወረዳዎች፣ ቀበሌዎች፣ ከተሞች መሰል መዋቅር አዘጋጅቶ ህጋዊ አስመስሎ እየሰራው ነው።

"ተፈናቃይ ይመለስ" ማለቱን ተከትሎ ደግሞ "ኬር ኢትዮጵያ" በሚባል ድርጅት ድጋፍ በርካታ መታወቂያ ተዘጋጅቷል። ራያና ወልቃይትን የማያውቀውን ጨምሮ በርካታ ህዝብ መታወቂያ ተሰጥቶት እናሰፍራለን እያሉ ነው።

አንድም የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ግዴታውን ሳይወጣ፣ በስምምነቱ መሰረት በአማራ ክልል እንዲቆዩ የተደነገገላቸውን አካባቢዎች አሳልፎ ለመስጠት በተሰራው ደባ የልብ ልብ የተሰማው ትህነግ ለአካባቢዎቹ በህገወጥ ማህተምና ደረሰኝ የሚጠቀም ሙሉ መዋቅር አዘጋጅቷል። ብልፅግና ይህን ያውቃል። ወንጀል ግን አይመስለውም። የህዝብ አስተዳደር የሚያፈርሱት ግን ለዚህ ህገወጥ ቡድን አሳልፎ ለመስጠት ነው!


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


ከአንተ ኢሳያስ አፈወርቂን ይቅር ቢሉት ይቀላቸዋል!

ኤርሚያስ ለገሰ ትህነግ "ይቅር" ይለኛል ብሎ የትህነግ የወልቃይትና ራያ አስመላሽ ኮሚቴ ሆኖ ከርሟል። ሰሞኑን በይፋ አብይን ደግፎ ተናግሮ ተናደውበታል። በሙዚቃ አቀናብረው ያስቀመጡትን እያወጡለት ነው። ለጊዜው በከፈሉህ ትሰራለህ እንጅ መቸም አይለቁህም። አንተን ከሚምሩህ ኢሳያስን በቀላሉ ይቅር ይሉታል።


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


ይለይላችኋ! ምን አገባን!

የፖለቲካው አሰላለፍ ሲለይለት ግልጥ እያለ ይመጣል! ቴድሮስ ፀጋዬ ኤርሚያስ ከኦሮሞ ብልፅግና ጋር ሲገናኝ ደርሶበት ካባረረው ቆይቷል። ለኤርሚያስ ቴድሮስ ነበር ከህወሓት ጋር መገናኛ ገመዱ፣ አሁን አማራጭ ፍለጋ የትግራይ አክቲቪስት በየቀኑ ያቀርባል። ያም ሆኖ ኤርሚያስ አልተረፈም። ፖለቲካው ከረር ሲል የኦሮሞ ብልፅግና አጀንዳውን ሲያመጣ ፀቡ ግልፅ እየወጣ ነው።

በነገራችን ላይ ኤርሚያስ "አንተምኮ ወገን አለህ" ተብሎ የኦሮሞ ብልፅግናን በይፋ ከወገነ ቆይቷል። ትህነግን ደግሞ ለጥቅም። ዞሮ ዞሮ ይለይላችሁ! የሚያገባን ነገር የለም!

20 last posts shown.