Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


كناشة ابن منور

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


በረመዳን ወር ቀን ላይ ከወር አበባ የጠራች ሴት ቀሪውን የቀኑን ክፍል ከሚያስፈጥር ነገር የመቆጠብ ግዴታ አለባትን?
~
አንዲት ሴት የወር አበባ ላይ በመሆኗ ሳትፆም ቀርታ ቀን ላይ ከደሙ ብትጠራ ከምግብና ከመጠጥ የመቆጠብ ግዴታ እንዳለባት የሚያስቡ ብዙ ናቸው፡፡ በርግጥም ይህን አቋም የመረጡ ዐሊሞች አሉ፡፡ ነገር ግን ይሄ አቋም “ለቀኑ ክብር” በሚል ወይም ጤነኛ ያልሆነን ቂያስ በመጠቀምና መሰል ምክንያት ላይ በመንተራስ እንጂ ቀጥተኛ ማስረጃ የሚደግፈው አይደለም፡፡ ፆመኛ ያልሆነን ሰው “ባንተ ላይ መመገብና መጠጣት ሐራም ነው፤ ያለበለዚያ ወንጀለኛ ነህ” ማለት ግልፅ ማስረጃ ይፈልጋል፡፡

ለምሳሌ አንዲት ሴት የወር አበባ ካየች በሷ ላይ ፆም መፆም ሐራም ነው፡፡ መፆም በሷ ላይ ሐራም የሆነባትን ሴት “መመገብም ባንቺ ላይ ሐራም ነው” ማለት ትክክል አይደለም፡፡ “መብላት የለባትም” ከተባለ ግን እራት ከበላችበት ሰዓት ጀምሮ ወይም ልክ እንደ ፆመኛ ሌሊት ተነስታ ሱሑር ከበላችበት ሰዓት ጀምሮ ፀሐይ እስክትጠልቅ ድረስ ያለ ምግብና ያለ ውሃ መቆየት አለባት ማለት ነው፡፡ ይህ እንግዲህ ኋላ ቀዷ ማውጣቷ የማይቀር ከመሆኑ ጋር ነው፡፡ ይሄ እይታ ትክክል እንዳልሆነ በርካታ ዑለማኦች ገልፀዋል፡፡

ኢብኑ መስዑድ ረዲየላሁ ዐንሁ እንዲህ ይላሉ፡- “በቀኑ መጀመሪያ ላይ የበላ ሰው በመጨረሻውም ይብላ፡፡”
ይህ ምን ማለት ነው? በሆነ ምክንያት ፆመኛ ባለመሆኑ ሳቢያ በቀኑ የመጀመሪያ ክፍል ላይ መመገብ የተፈቀደለት ሰው በየትኛውም የቀኑ ክፍል መመገብ እንደሚችል የሚጠቁም ነው፡፡ ይህ አቋም የታቢዒዮቹ ጃቢር ብኑ ዘይድ እና አጧዕ ብን አቢ ረባሕ፣ እንዲሁም የኢማሙ ማሊክ፣ የሻፍዒይ፣ የአሕመድ በአንድ ዘገባ፣ የኢብኑ ሐዝም፣ የኢብኑ ዑሠይሚን እና የሌሎችም የብዙሃን ዑለማእ እይታ ነው፡፡
ይህ እንግዲህ በረመዳን ወር በቀኑ ክፍለ ጊዜ ከወሊድ ደም የጠራችን፣ ከህመሙ ያገገመን፣ ከመንገድ የተመለሰን ሰው እና መሰል ሸሪዐዊ ዑዝር ያላቸውን ሁሉ የሚመለከት ነው፡፡

ማሳሰቢያ፡-
-
የሚያፈጥርበት ምክንያት ለሰዎች የሚሰወር የሆነ ሰው ሲመገብም ሆነ ሲጠጣ በተቻለ ከሰዎች እይታ ገለል ቢል በዲኑ በክፉ ከመጥጠርጠር ይጠብቀዋል፡፡ ዑዝሩ ወይም ሰበቡ በውል የሚታወቅ ከሆነ ግን በግልፅ ቢመገብና ቢጠጣም ችግር የለውም፡፡ ወልላሁ አዕለም።
=
(ኢብኑ ሙነወር፣ ሚያዚያ 13/2010)
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


ቁርኣንን ያለ ውዱእ መንካት ይቻላልን?
~
ቁርኣንን ያለ ውዱእ መንካት አይቻልም የሚለው የአራቱም የፊቅህ መዝሀቦች አቋም ነው። አልፎም ባጠቃላይ የብዙሃን ዑለማእ አቋም ነው። መረጃ የሚደግፈውም ይህንኑ ነው። ሁለት መረጃዎችን እጠቅሳለሁ:-

♻️ [መረጃ አንድ]:- ሐዲሣዊ ማስረጃ ♻️

ነብያችን ﷺ ወደ የመን በላኩት ደብዳቤ ላይ
أَنْ لَا يَمَسَّ الْقُرْآنَ إِلَّا طَاهِرٌ
"ቁርኣንን ጦሀራ የሆነ እንጂ እንዳይነካው" ሲሉ አሳስበዋል። [ሙወጦእ: 468]
ሐዲሡን ሸይኹል አልባኒይ ረሒመሁላህ "ሶሒሕ" ብለውታል። [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 7780]

👉🏾 ብዥታ!
~
ቁርኣንን ያለ ውዱእ መንካት ይቻላል የሚሉ ዓሊሞች ግን "የሐዲሡ መልእክት ሌላ ነው። 'ጦሀራ የሆነ እንጂ እንዳይነካው' ማለት 'ሙስሊም እንጂ እንዳይነካው' ማለት ነው" ይላሉ። ለዚህም "ሙስሊም አይንነጀስም" የሚለውን ሐዲሥ ያጣቅሳሉ።
ይሄ ግን - ወላሁ አዕለም - ልክ አይደለም። ይልቁንም መልእክቱ በቀጥታ ጦሀራ/ውዱእ የሌለው ሰው እንዳይነካው ማለት ነው። የሐዲሡ ሌሎች ዘገባዎች ይህንን መልእክት ግልፅ ያደርጉልናል። ለምሳሌ:-

✅ 1ኛ፦ የዐብዱረዛቅ ዘገባ ላይ እንዲህ የሚል እናገኛለን፦
لَا يُمَسُّ الْقُرْآنُ إِلَّا على طُهْرٍ
"በጦሀራ ላይ ተሁኖ እንጂ ቁርኣን አይንነካም።" [አልሙሶነፍ: ቁ. 1328]

✅ 2ኛ:- የኢብኑል ሙንዚር ዘገባ ላይ ደግሞ እንዲህ የሚል እናገኛለን፦
لَا تَمَسَّ الْقُرْآنَ إِلَّا على طَهورٍ
"በጦሀራ ላይ ሆነህ እንጂ ቁርኣን እንዳትነካ።" [አልአውሰጥ፡ 2/103]

▶️ ልብ በሉ! ሙስሊሙን ሰው ነው "በጦሀራ ላይ ሆነህ እንጂ ቁርኣንን እንዳትነካ" ያሉት። ይህም ሐዲሡን "ሙስሊም ያልሆነ እንዳይነካው ማለት ነው" በማለት የተረጎሙት ልክ እንዳልሆኑ ያሳያል።

♻️ [መረጃ ሁለት]:- ቁርኣናዊ ማስረጃ ♻️

በቁርኣን ውስጥም እንዲህ የሚል መጥቷል:-
{ لَّا یَمَسُّهُۥۤ إِلَّا ٱلۡمُطَهَّرُونَ }
"የተጥራሩት እንጅ ሌላ አይነካውም።" [አልዋቒዐህ፡ 79]

በርግጥ የዚች አንቀፅ ቀጥተኛ መልእክት ጥብቁን ሰሌዳ (ለውሐል መሕፉዝን) የሚገልፅ እንደሆነ አገባቡ ያሳያል። ይሁን እንጂ መልእክቱ ለቁርኣንም የሚውል እንደሆነ ጥቆማ አለው ይላሉ ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያ ረሒመሁላህ። [ሸርሑል ዑምደህ: 384] ዝርዝሩን ከዚህ በላይ ላለማስረዘም ስል ስለተውኩት በቦታው ተመልከቱት።

ባይሆን ይህንን ሃሳብ የሚደግፍ አንድ የሶሐቢይ ንግግር ልጥቀስ። ሶሐቢዩ ሰልማኑል ፋሪሲይ - ረዲየላሁ ዐንሁ - ናቸው። ዐብዱረሕማን ብኑ የዚድ - ረሒመሁላህ - እንዲህ ይላሉ፦

"ከሰልማን ጋር በሆነ ጉዳይ ላይ ነበርን። እሳቸው ጉዳያቸውን ለመፈፀም (ለመፀዳዳት) ሄደው ተመለሱ። 'ውዱእ አድርግማ የዐብደላህ አባት! ምናልባት ከቁርኣን ስለሆኑ አንቀፆች ልንጠይቅህ እንችላለን' አልናቸው። በዚህን ጊዜ (ሰልማን) እንዲህ አሉ፦
فَاسْأَلُوا، فَإِنِّي لَا أَمَسُّهُ، إِنَّهُ {لَا يَمَسُّهُ إِلَّا الْمُطَهَّرُونَ}
'ጠይቁ! እኔ አልነካውም። ነገሩ {የተጥራሩት እንጅ ሌላ አይነካውም}።'
ከዚያም "ጠየቅናቸው። ውዱእ ሳያደርጉ ቀሩልን" አሉ። [ሙሶነፍ ኢብኒ አቢ ሸይባህ፡ ቁ. 1100]

መግቢያዬ ላይ እንደገለፅኩት ጦሀራ የሌለው ሰው ቁርኣንን ሊነካ አይገባም የሚለው የብዙሃን ዑለማእ አቋም ነው። ኢብኑ ዐብዲል በር እንዲህ ይላሉ፦
أجمع فقهاء الأمصار الذين تدور عليهم الفتوى وعلى أصحابهم بأن المصحف لا يمسه إلا طاهر
"ጦሀራ ላይ የሆነ ካልሆነ በስተቀር ሙስሐፍ እንደማይንነካ ፈትዋ የሚቀርብላቸው የሙስሊም ሃገራት ሊቃውንት እና ባልደረቦቻቸው ወጥ ስምምነት ላይ ደርሰዋል።" [አልኢስቲዝካር፡ 8/10]
ከኢብኑ ሁበይራም በተመሳሳይ ኢጅማዕ እንዳለበት ተጠቅሷል። [አልኢፍሷሕ፡ 1/68]

ይሄ እንግዲህ እነሱ በሚያውቁት መጠን ነው። እንጂ ጥቂቶች ቢሆኑም የተለየ ሃሳብ ያንፀባረቁ ተገኝተዋል።

የሆነ ሆኖ ቁርኣንን ያለ ውዱእ መንካት አይቻልም የሚለው ከሶሐቦች ውስጥ ከ0ሊይ፣ ከሰዕድ ብኑ አቢ ወቃስ፣ ከኢብኑ ዑመር፣ ከሰልማኑል ፋሪሲይ - ረዲየላሁ ዐንሁም - ተገኝቷል። ከሶሐቦች ውስጥ እነዚህን የተቃረነ አይታወቅም ይላሉ ነወዊይ እና ኢብኑ ተይሚያህ። [አልመጅሙዕ፡ 2/80] [መጅሙዑል ፈታዋ፡ 21/266]
ይህንን ሃሳብ አስምሩበት። ከሶሐቦች ውስጥ እነዚህን የተቃረነ አይታወቅም። ስለዚህ ውዝግቡ የመጣው ከሶሓቦች በኋላ ነው ማለት ነው። አዋቂው አላህ ነው።

ማሳሰቢያ፦ ሞባይልና መሰል 'ዲቫይሶች'ን ተጠቅሞ መቅራት እዚህ ውስጥ አይገባም። እንዲሁም ትርጉምና የተፍሲር ኪታቦችም የሙስሐፍ ብይን ስለሌላቸው ያለ ጦሀራ መንካት ይቻላል።
=
(ኢብኑ ሙነወር፣ ረመዷን 21/1444፣ ሚያዚያ 04/2015)
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


በኒያ ጉዳይ መጨናነቅ አያስፈልግም
~
ኢብኑ ተይሚያ ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፦

"ነገ ረመዷን እንደሆነ ያወቀና ሊፆመው የፈለገ ሁሉ ፆሙን ነይቷል።"

[መጅሙዑል ፈታዋ፡ 25/215]
=
የቴሌግራም ቻናል :-
t.me//IbnuMunewor


* "በረመዳን የተፈፀመ (ሱና የሆነ) ኸይር ስራ በሌላ ጊዜ እንደተፈፀመ ግዴታ ዒባዳ ነው።
* በረመዳን የተፈፀመ ግዴታ ዒባዳ በሌላ ጊዜ እንደተፈፀመ ሰባ ግዴታ ዒባዳ ነው።"

ይሄ ሐዲሥ ደካማ ነው። ደካማ እንደሆነ ከገለፁ ዐሊሞች ውስጥ የተወሰኑትን ልጥቀስ፦

1- ኢብኑ ሐጀር:- [አተልኺሱል ሐቢር፡ 3/1121]፣
2- አል0ይኒይ:- [ዑምደቱል ቃሪ : 10/383]፣
3- አልባኒይ:- [ተኽሪጁል ሚሽካት ፡ 1906] [ዶዒፉ ተርጊብ፡ 589]፣
4- ኢብኑ ዑሠይሚን:- [ፈታዋ ኑሪን ዐለ ደርብ: 2/ 568]

ማሳሰቢያ:-
~
ይሄ ማለት ከላይ በተጠቀሰው ደካማ ሐዲሥ ላይ ባለው መልኩ ለመደምደም ሶሒሕ ማስረጃ ያስፈልጋል ለማለት እንጂ በተከበሩ ቦታዎች እና ጊዜዎች ውስጥ የሚፈፀሙ ተግባራት ከሌሎች ተግባራት ልዩነት የላቸውም ለማለት አይደለም። በተከበሩ ቦታዎች እና ጊዜያት ውስጥ የሚፈፀሙ ተግባራት ኸይርም ሆኑ ሸር በሌላ ቦታዎች እና ጊዜዎች ከሚፈፀሙት ተግባራት መጠናቸው ከፍ ይላል። ለምሳሌ ሐረም ውስጥ የሚሰገድ ሶላት ከሌላ ቦታ ሶላት መጠኑ በጣም ይለያል። ወንጀልም ላይ እንዲሁ። በዙልሒጃ የመጀመሪያ አስሩ ቀናት የሚፈፀም ዒባዳ በሌላ ጊዜ ከሚፈፀመው በጣም ይበልጣል። ረመዳንም የተከበረ ወር እንደመሆኑ ከሌሎች ጊዜያት ብልጫ አለው። ይሁን እንጂ ከላይ በሰፈረው ዶዒፍ ሐዲሥ ላይ በተጠቀሰው መልኩ መጠኑን ለይቶ ለመናገር ሶሒሕ ማስረጃ ያስፈልጋል።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


"መጀመሪያው እዝነት፣ ...”
~
ረመዳን ላይ በየመሳጂዱ እንዲህ የሚል ተደጋግሞ የሚነገር ሐዲሥ አለ:-
أولُ رمضانَ رحمةٌ، وأوسطُه مغفرةٌ، وآخرُه عتقٌ من النارِ
“የረመዳን ወር መጀመሪያው እዝነት ነው። መካከሉ ምህረት ነው። መጨረሻው ደግሞ ከእሳት ነፃ መውጫ ነው።”

ሐዲሥ ደካማ (ዶዒፍ) ነው። ለማስረጃነት የሚያበቃ ጥንካሬ የለውም። ሐዲሡ ደካማ እንደሆነ የገለፁ የሐዲሥ ሊቃውንት ዝርዝር፦

1ኛ፦ አልዑቀይሊይ:- [አዱዓፋኡል ከቢር፡ 2/162]
2ኛ፦ ኢብኑ ዐዲይ:- [አልካሚል ፊ ዱዐፋእ፡ 4/325]
3ኛ፦ አልኸጢቡል በግዳዲይ:- [አውሃሙል ጀምዕ ወተፍሪቅ፡ 2/147]
4ኛ፦ አዘሀቢይ:- [ሚዛኑል ኢዕቲዳል : 2/179]
5ኛ፦ ኢብኑ ሐጀር:- [ሊሳኑል ሚዛን፡ 5/59]
6ኛ፦ አልአልባኒይ፦ [አዶዒፋህ፡ ቁ. 1569] [ዶዒ ፉል ጃማዕ፡ 2135]

ማሳሰቢያ፦
~
ከመልእክት አንፃር ከታየ ረመዳን ለተጠቀመበት እና አላህ ላደለው ሰው ሙሉ ወሩ እዝነትም፣ ምህረትም፣ ከእሳት ነፃ መውጫም ነው ይላሉ ዓሊሞች።
=
የቴሌግራም ቻናል :-
t.me/IbnuMunewor


ረመዳን ጋር የሚያያዙ ለማስረጃነት ብቁ ያልሆኑ በነብዩ ﷺ ስም ሊወሩ የማይገባቸው ደካማ (ዶዒፍ) ሐዲሦች”
~
1. “የረመዳን ወር መጀመሪያው እዝነት ነው፡፡ መካከሉ ምህረት ነው፡፡ መጨረሻው ደግሞ ከእሳት ነፃ መውጫ ነው፡፡” ሐዲሡ ደካማ እንደሆነ የገለፁ የሐዲሥ ሊቃውንት[አዶዒፋህ፡ 2/262]
2. “ፁሙ ጤናማ ትሆናላችሁ፡፡” [አድዶዒፋህ፡ 1/420]
3. “ከረመዳን አንድ ቀን ያለ ምክንያት ወይም ያለ ህመም ያፈጠረ አመት ቢፆም እንኳን አይተካውም፡፡” [ዶዒፉ ሱነኑ ቲርሚዚ፡ 1/626]
4. “ጌታዬ ሆይ! ረጀብንና ሸዕባንን ባርክልን፡፡ ረመዳንንም አድርሰን፡፡” [ዶዒፉልጃሚዕ፡ 4395]
5. “ጌታዬ ሆይ ላንተ ፆምኩኝ፡፡ በሪዝቅህም አፈጠርኩኝ፡፡” [ዶዒፉልጃሚዕ፡ 4349]
6. “ለአላህ በእያንዳንዱ ፊጥራ ጊዜ ላይ ከእሳት ነፃ የሚወጡ አሉት፡፡” [አዶዒፋህ፡ 2/262]
ረመዳን በገባ ቁጥር በየመሳጂዱ ስለሚደጋገሙ ምናልባትም ለደረሰው መማሪያ ይሆን ዘንድ ሼር እናድርግ ባረከላሁ ፊኩም፡፡
=
የቴሌግራም ቻናል :-
t.me/IbnuMunewor


ፆም #የማያበላሹ ነገሮች
~
ቀጥሎ የተዘረዘሩት ፆም አያጠፉም / አያስፈቱም።

1- መድሃኒት በመርፌ መወጋት (ለምሳሌ ኢንሱሊን)፣
2- ምግብ መቅመስ (ሆን ተብሎ ከተዋጠ ፆም ያጠፋል)፣
3- የአይን ጠብታ፣ ኩል መክኳል፣ የጆሮ ጠብታ፣
4- አካልን ለማቀዝቀዝ መታጠብ፣
5- የሽቶ ወይም የበኹር ሽታ፣
6- መፋቂያ በማንኛውም ሰዓት መጠቀም፣
7- ዋገምት/ሒጃማ (ሚዛን በሚደፋ አቋም ፆም አያበላሽም)፣
8- ማስታወክ ወይም ማስመለስ (ሚዛን በሚደፋ አቋም ፆም አያበላሽም።)
9- ለምርመራ ደም መስጠት፣ ደም መለገስ፣
10- በፊንጢጣ / በፈጋራ በኩል የሚገባ መድሃኒት፣
11- ዝንብ፣ አቧራ ፣ ... ድንገት መግባት፣
12- ምራቅን መዋጥ፣
13- የአስም ህመምተኞች በአፍንጫ የሚጠቀሙት Sprayer
14- ለምርመራ ወይም ለሌላ በብልት ወይም በፈንጢጣ የሚገቡ ነገሮች፣ ካቲተር፣ ሉፕ፣
15- የማደንዘዣ መድሃኒቶች፣ ኦክስጂን፣
16- በአፍ የሚገቡ እንደ ኢንዶስኮፒ ያሉ መመርመሪያዎች (ፈሳሽ ወይም ሌላ ነገር ይዘው የሚገቡ ካልሆኑ)
17- ጆሮ ማሳጠብ፣ ጥርስ ማስነቀል፣ ጥርስ ማሳጠብ (በፆም ወቅት ባይደረግ የተሻለ ነው)፣
18- ፆም የሚያበላሹ ነገሮችን ተገዶ መፈፀም

እነዚህ ነገሮች በሙሉ ፆም አያበላሹም። ከተለያዩ መረጃዎች የተሰበሰቡ ናቸው።
=
የቴሌግራም ቻናል :-
t.me/IbnuMunewor


የአይን ጠብታ ለፆመኛ
~
ሸይኽ ኢብኑ ዑሠይሚን ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፦
لا بأس على الصائم أن يقطر في عينه وإن وجد طعمه في حلقه فإنه لا يفطر به ، لأنه ليس بأكل ولا شرب، ولا بمعنى الأكل والشرب .
"በፆመኛ ላይ አይኑ ውስጥ ጠብታ ቢያደርግ ችግር የለውም። ጣእሙን ጉሮሮው ላይ ቢያገኘው እንኳ በሱ ፆሙን አይፈታም። (ፆሙ አይጠፋም።) ምክንያቱም ይሄ መመገብም መጠጣትም አይደለምና። እንዲሁም የመመገብና የመጠጣትን ይዘት የሚያዝም አይደለምና።"
[መጅሙዑል ፈታዋ፡ 19/ 205]
=
የቴሌግራም ቻናል:-
https://t.me/IbnuMunewor


እያንቀላፉ ሶላት መስገድ፣ ቁርኣና መቅራት እና ዱዓእ ማድረግ አይገባም።
=
የቴሌግራም ቻናል:-
https://t.me/IbnuMunewor


ሱስ ማቆም ለምትፈልጉ ረመዷን ወርቃማ ጊዜ ነው። የሚፈልገው ቁርጠኝነት ነው። አላህ ያንሳላችሁ።
=
የቴሌግራም ቻናል:-
https://t.me/IbnuMunewor


አክታን መዋጥ
~
1. ከአቅም በላይ ከሆነ
ማስወገድ በማይችለው መልኩ ከጭንቅላቱ ቀጥታ ወደታች የሚወርድ አክታ ከሆነ ሊጠነቀቀው አይችልም፡፡ አላህ ደግሞ ከአቅም በላይ በሆነ ነገር አይዝም፡፡

2. መቆጣጠር ሲቻል ቢዋጥስ?
ሆነ ብሎ አውጥቶ አፉ ጋር ካደረሰው በኋላ መትፋት ሲችል ቢውጠው ፆሙ ይበላሻል ያሉ ዐሊሞች አሉ፡፡ ከፊሎቹ ግን ይህም ቢሆን አይበላሽም ብለዋል፡፡ ለምሳሌ ሸይኽ ኢብኑ ዑሠይሚን ረሒመሁላህ “ፆሙ አይበላሽም” የሚለውን መርጠዋል፡፡ ታዲያ “ፆሙ አያበላሽም” ይበሉ እንጂ ድርጊቱ ፆመኛ ለሆነም ይሁን ላልሆነ ሰው ሐራም እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ ምክንያታቸው ደግሞ አንደኛ አፀያፊ ነው፡፡ ሁለተኛ ምናልባትም በሽታ አምጪ ተህዋሲያንን የተሸከመ ሊሆን ስለሚችል ወደ ሆድ ሲገባ ጉዳት ሊያስከትል ይችላል የሚል ነው፡፡ [ሸርሑል ሙምቲዕ፡ 6/428] ከውዝግብ ለመውጣት ሲባል መራቁ ራሱን የቻለ ዋጋ አለው፡፡ ወልላሁ አዕለም፡፡
=
የቴሌግራም ቻናል:-
https://t.me/IbnuMunewor


ለባለሃብቱ!
~
ለገቢዎች ባለስልጣን መስሪያ ቤት የምትከፍለውን ግብር እያሰብክ ከዘካ እንዳትዘናጋ። ዘካ ለደካሞች የሚሰጥ ሐቅ እንጂ ለሹማምንት የሚሰጥ ግብር ወይም ጉቦ አይደለም። አኺል ከሪም! ገንዘቡን የሰጠህ አላህ ነው። እንጂ ካንተ የበለጠ የሚለፉ ድሃዎች በዙሪያህ አሉኮ። በእውቀቴ አገኘሁት እንዳትል ካንተ የበለጠ የተማሩ ድሃዎች ሞልተዋልኮ። ጥለኸው ለምትሄደው ገንዘብ ብለህ በራስህ ላይ አትሳሳ። እውነተኛው ያንተ ገንዘብ ማለት ለአኺራህ ያሻገርከው ነው። ዐብዱላህ ብኑ ሺኺር - ረዲየሏሁ ዐንሁ - እንዲህ ይላሉ፦
أتَيْتُ النَّبيَّ صلى الله عليه وسلم، وَهُوَ يَقْرَأُ: {أَلْهَاكُمُ التَّكَاثُرُ} قَالَ: ((يَقُولُ ابْنُ آدَمَ: مَالِي، مالي، وَهَلْ لَكَ يَا ابْنَ آدَمَ مِنْ مَالِكَ إلا مَا أكَلْتَ فَأفْنَيْتَ، أَو لَبِسْتَ فَأَبْلَيْتَ، أَوْ تَصَدَّقْتَ فَأَمْضَيْتَ؟)
"ነብያችን ﷺ ዘንድ መጣሁኝ። {በብዛት መፎካከር (ጌታችሁን ከመገዛት) አዘነጋችሁ} የሚለውን እየቀሩ ነው። ቀጥለው እንዲህ አሉ፦
'የአደም ልጅ 'ገንዘቤ ገንዘቤ!' ይላል። የአደም ልጅ ሆይ! በልተህ ከጨረስከው፣ ለብሰህ ካሳለቅከው፣ ሶደቃ ሰጥተህ አጅሩን ካሻገርከው ውጭ ገንዘብ አለህ'ንዴ?' " [ሶሒሕ ሙስሊም፡ 2958]
እወቅ! የምታወጣው ካጠቃላይ ገንዘብህ 2.5 ከመቶ ብቻ ነው። መቶ ብር ያለው ሰው ሁለት ብር ከሃምሳ ሳንቲም ቢያወጣ ብዙ ነው ወይ? ምስሉ ላይ በጣት የተጠቆመችዋን ተመልከት። ካጠቃላይ ሃብትህ ይቺን ታክል ለዘመዶችህ፣ ለጎረቤቶችህ፣ ለምታውቃቸው ምስኪኖች ብታወጣ ብዙ ነውን? በአኺራ እጥፍ ድርብ ምንዳ እንደሚጠብቅህ የቂን የለህም ወይ?
ደግሞም እወቅ! ወላሂ ሶደቃ ሃብትን አይቀንስም። ይልቁንም ይበልጥ በረካ እንዲኖረው ነው የሚያደርግልህ። አላህ ትእዛዙን ለመፈፀም ያግራልህ።
=
ቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor


በፆም ወቅት ጁኑብ መሆን
~
1- መብላት መጠጣት በሚፈቀድበት የሌሊቱ ክፍል ላይ ሐላል ግንኙነት የተፈቀደ መሆኑ ግልፅ ነው። አላህ እንዲህ ይላል:-
{ أُحِلَّ لَكُمۡ لَیۡلَةَ ٱلصِّیَامِ ٱلرَّفَثُ إِلَىٰ نِسَاۤئكُمۡۚ }
"በፆም ሌሊት ወደ ሴቶቻችሁ መድረስ ለናንተ ተፈቀደላችሁ።" [አልበቀረህ: 187]

2- በሌሊቱ ክፍል ጁኑብ ሆኖ ሳለ ሳይታጠብ የፈጅር ወቅት ቢገባ ፆሙ ላይ ችግር የለውም። እናታችን ዓኢሻህ - ረዲየላሁ ዐንሃ - እንዲህ ትላለች፦
كَانَ رسول الله صلى الله عليه وسلم يُدْرِكُهُ الفَجْرُ وَهُوَ جُنُبٌ مِنْ أَهْلِهِ، ثُمَّ يَغْتَسِلُ وَيَصُومُ.
"የአላህ መልእክተኛ ﷺ ከባለቤታቸው ጀናብተኛ ሆነው የፈጅር ወቅት ይደርስባቸው ነበር። ከዚያ ታጥበው ፆማቸውን ይቀጥላሉ።" [አልቡኻሪይ እና ሙስሊም]

3- በቀኑ ክፍለ ጊዜ ተኝቶ ኢሕቲላም በመሆኑ ጀናባ የገጠመው ሰው ፆሙ ላይ ተፅእኖ የለውም። ምክንያቱም እንቅልፍ ላይ ያለ ሰው እስከሚነቃ ድረስ ተጠያቂነት የለበትምና። በኢስላም ማንም ቢሆን ከአቅሙ ውጭ በሆነ በማይችለው ነገር አይጠየቅም። አላህ እንዲህ ይላል፦
{لَا يُكَلِّفُ اللَّهُ نَفْسًا إِلَّا وُسْعَهَا}
"አላህ ነፍስን የችሎታዋን እንጂ አያስገድዳትም።" [አልበቀራህ: 286]
ነብዩም ﷺ መፆም ያሰበ ሆኖ ሳለ ጀናባ ሆኖ እንደሚነጋበት ለነገራቸው ሰው እሳቸውንም እንደሚገጥማቸውና ፆሙ ላይ ችግር እንደሌለበት ነግረውታል። [ሙስሊም ዘግበውታል።]

4- በቀኑ ክፍለ ጊዜ ከቀጥታ ግንኙነት ውጭ ባለ መንገድ ራሱን በማርካት (ኢስቲምናእ በማድረግ) ጁኑብ የሆነ ሰው አብዛኞቹ ዑለማእ ዘንድ ፆሙ ተበላሽቷል። ፆሙ እንደማይበላሽ የገለፁ ቢኖሩም ራስን ከውዝግብ ማራቅ የተወደደ ነው።

5- በቀኑ ክፍለ ጊዜ ቀጥታ ግንኙነት የፈፀመ ሰው ፆሙ ይበላሻል። ከዚያም ባሻገር ለጥፋቱ ጥብቅ ማካካሻ ይጠበቅበታል።

=
ቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor


አደራ! ቁርኣን እንቅራ
~
በርግጠኝነት እዚህ ሶሻል ሚዲያ ላይ ከሚርመሰመሱ ወገኖቻችን ውስጥ ቁርኣን ያልቀሩ ብዙ ወገኖች ይኖራሉ። ወላሂ ሊቆጨን ይገባል። በዚህ አማራጮች በበዙበት ዘመን እንዴት ድንቁርናን አሚን ብለን ተቀብለን በጨለማ ውስጥ እንኖራለን? የትም ብንሆን ካለንበት ቦታ ሆነን መማር እንደሚቻል የሚታወቅ ነው። አላህ ባገራልን መንገድ እንማር። ነብያችን ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም "ከናንተ በላጫችሁ ቁርኣንን የተማረና ያስተማረው ነው" ብለዋል። [ቡኻሪ፡ 5027]
ስለዚህ ያልተማርን ጊዜ ሰጥተን እንማር። የተማርን መልክቱን እንማር፣ ባወቅነው እንስራ። በየቀኑ ከጊዜያችን ውስጥ ለቁርኣን ድርሻ ይኑረን። በምንችላት መጠን ለመሐፈዝ እንሞክር። የእድሜ መግፋት ቁርኣን ከመማር አያግድም። በርካታ ሶሐቦች በጎልማሳነት ዘመናቸው ነው ቁርኣን የቀሩት። ሸይኽ ዐብዱል ሙሕሲን አል0ባድ "አንድ ሰው ከሃምሳ አመቱ በኋላ ቁርኣን ሊሐፍዝ ይችላል ወይ?" ተብለው ተጠይቀው ነበር። ምላሻቸው እንዲህ የሚል ነበር፦
"አዎ! እኔ ራሱ ከሃምሳ በኋላ ቁርኣን ከሐፈዙት ውስጥ ነኝ። ሶሐቦች - ረዲየላሁ ዐንሁ - ትልልቅ ሰዎች ሆነው ነው ኢስላም ያገኛቸው። ከመሆኑም ጋር ቁርኣንን ሐፍዘዋል።"
ስለዚህ በየትኛውም ምክንያት በልጅነቱ ቁርኣን ያልቀራ ሁሉ እራሱን አያዳክም። "በአላህ ፈቃድ እችላለሁ" ብሎ ይነሳ። ኢንሻአላህ ይችላል። አለማወቅን ታቅፈን ፈፅሞ ምቾት ሊሰማን አይገባም። ሰው እንዴት ቁርኣን ሳይቀራ እድሜውን ይፈጃል?!
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን!
~
ከሁለት ቀን በፊት አዲስ አበባ አባ ኮራን ሰፈር በደረሰ የእሳት አደጋ የተነሳ እጅግ በርካታ ሰዎች በቃጠሎው ህይወታቸው አልፏል። አንዳንዶች ሟቾቹ ከሃምሳ በላይ ናቸው እያሉ ነው። ከሟቾቹ ውስጥ በርካቶቹ ወደ ውጭ ሀገር ሊሄዱ ከክፍለ ሀገር የመጡ ሴቶች ናቸው የተባለ ሲሆን ቤተሰቦቻቸው የልጆቻቸውን ሞት እንዳልሰሙና የተፈጠረውንም ነገር እንደማያውቁ እየተነገረ ነው።
የሚያሳዝነው ይሄ ሁሉ ሰው አልቆ ጉዳዩ ለዜና እንኳ አለመብቃቱ ነው። ሚዲያዎቻችን "ኤለን መስክ 14ኛ ልጁን ወለደ" ፣ "ኦዚል ወደ ፖለቲካ ገባ"፣ ... በሚሉ "ይበልጥ አሳሳቢ" በሆኑ ጉዳዮች ስለተጠመዱ ትኩረት አልሰጡትም።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor


ዛሬ እሁድ ረፋድ በሑዘይፋ መስጂድ የደዕዋ ፕሮግራም ይኖራል ኢንሻአላህ።

አድራሻ :- ከየሺ ደበሌ ከፍ ብሎ።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor


በረመዳን ወር ፆም ላይ እያለ ግንኙነት የፈፀመን ሰው የሚመለከቱ ህግጋት
~
1. በረመዳን ወር ፆም ላይ እያለ የግብረ ስጋ ግንኙነት የፈፀመ ሰው በቁርኣን፣ በሱናና በኢጅማዕ ፆሙ ይበላሻል፡፡
2. በተጨማሪ ለፈፀመው ከባድ ጥፋት ማካካሻ (ከ -ፋ -ራ) የመፈፀም ግዴታ አለበት፡፡ [ቡኻሪና ሙስሊም]
3. ሴቷ በጥፋቱ ላይ ተገዳ ከገባች ቀዷም፣ ማካካሻም የለባትም፡፡ [ሸርሑል ሙምቲዕ፡ 6/404] በምርጫዋ ከገባች ማካካሻ ይመለከታታል ወይስ አይመለከታትም የሚለው ብርቱ ውዝግብ ስላለበት አልፌዋለሁ፡፡
4. በእለቱ ፆመኛ ሳይሆን ቀርቶ ግንኙነት ቢፈፅም ማካካሻ አይመለከተውም፡፡
5. አንድ ሰው ረስቶ በመብላቱ ወይም በመጠጣቱ ምክንያት ፆሙ የተበላሸ መሰለውና ከዚያ በኋላ ግንኙነት ቢፈፅም ማካካሻ የለበትም፡፡ ረስቶ መብላትና መጠጣት ፆም እንደማያፈርስ እያወቀ ከዚያ በኋላ ግንኙነት የፈፀመ ሰው ማካካሻ አለበት፡፡
6. በፆም ግንኙነት መፈፀም ሐራም መሆኑን የማያውቅ ሰው ጥፋቱን ቢፈፅም በጥፋቱ ተጠያቂ አይሆንም፡፡ ማካካሻም የለበትም፡፡ “ክልክልነቱን አውቃለሁ፡፡ ቅጣቱን ነው የማላውቀው” ቢል ከተጠያቂነት አይተርፍም፡፡ ማካካሻም ይመለከተዋል፡፡ [አልመጅሙዕ፡ 6/381]
7. ፆመኛ መሆኑን ረስቶት (ምናልባት ካጋጠመ) የፈፀመ ሰው ቀዷም ማካካሻም የለበትም፡፡
8. ፈጅር ገና ያልወጣ መስሎት ግንኙነት የፈፀመና ኋላ ላይ ፈጅር ወጥቶ እንደነበር ያረጋገጠ ሰው ቀዷም ማካካሻም የለበትም፡፡
9. ግንኙነት እየፈፀመ እያለ ፈጅር የወጣበት ሰው ቀጥታ ማቆም አለበት፡፡ ካቆመ ቀዷም ማካካሻም የለበትም፡፡ ከቀጠለ ግን ማካካሻ ይመለከተዋል፡፡
10. አንድ ሰው ግንኙነት በመፈፀሙ ምክንያት ማካካሻ ግዴታ ከሆነበት በኋላ በእለቱ ህመም ወይም መንገድ ቢያጋጥመው ማካካሻው አይቀርለትም፡፡
11. በመብላት ወይም በመጠጣት ፆሙን ካፈረሰ በኋላ ግንኙነት የፈፀመ ሰው አቡ ሐኒፋ፣ ማሊክ፣ አሕመድ፣ ኢብኑ ተይሚያ፣ ኢብኑል ቀይም፣ ኢብኑል ዑሠይሚን፣ ... ማካካሻ እንዳለበት ገልፀዋል፡፡ ምክንያታቸው ደግሞ በዚህ አይነት ሰው ላይ ማካካሻ ግዴታ ባይሆን ግንኙነት ለመፈፀም ያለመ ሁሉ ሆን ብሎ አስቀድሞ ፆሙን በመብላትና በመጠጣት የማፍረስ ብልጠት ሊጠቀም ይችላል የሚል ነው፡፡
12. ግንኙነቱን የፈፀመው ከረመዳን ወር ውጭ ከሆነ ፆሙ ትርፍ ፆምም ይሁን የረመዳን ቀዷም ይሁን ሌላ ግዴታ ፆምም ቢሆን ማካካሻ የለበትም፡፡ ማካካሻ የሚመለከተው ግንኙነቱ በረመዳን ወር ፆም ላይ ሆኖ ከፈፀመ ብቻ ነው፡፡
13. በረመዳንም ሙሳፊር ወይም መንገደኛ ከሆነ ግንኙነት ቢፈፅምም ቀዷ እንጂ ማካካሻ አይመለከተውም፡፡ ምክንያቱም መንገደኛ ፍላጎቱ ከሆነ የማፍጠር ሐቅ አለውና፡፡
14. በአንድ ቀን ደጋግሞ ግንኙነት የፈፀመ ሰው ያለበት ማካካሻ በኢጅማዕ አንድ ብቻ ነው፡፡ ግንኙነቱ በተለያየ ቀን የተፈፀመ ከሆነ በቀኖቹ ብዛት ልክ ማካካሻ አለበት፡፡
15. እስካሁን ያሳለፍነው ቀጥታ ግንኙነት ከተፈፀመ ነው፡፡ እንጂ ግንኙነቱን በሌላ አካሎቿ ለምሳሌ ጭኗ ላይ ቢያደርገው ቀዷእ እንጂ ማካካሻ የለበትም የሚለው አቋም የብዙሃን ዑለማእ ምርጫ ነው፡፡ ግንኙነቱ የተፈፀመው በፊንጢጣ (ዱቡር) ከሆነ ድርጊቱ በራሱ ወንጀል ከመሆኑም ባለፈ ማካካሻ አለበት፡፡
16. ግንኙነቱ በረመዳን ቀን እስከሆነ ድረስ የፈፀመው ከተፈቀደለት ሴት ጋርም ይሁን በሐራምም ይሁን የማካካሻው ብይን እንዳለ ነው፡፡ እያወራን ያለነው ስለ ወንጀሉ እንዳልሆነ ይታወስ፡፡

ማካካሻውን በተመለከተ
-
[ሀ]. በረመዳን ቀን ግንኙነት በመፈፀም ፆሙን ያፈረሰ ሰው ጥፋቱን ለማካካስ የተቀመጡት ነጥቦች ሶስት ናቸው፡፡ እነሱም፦

1- ባሪያ ነፃ መውጣት፣
2- ሁለት ወር በተከታታይ መፆም እና
3- ስልሳ ምስኪኖችን ማብላት፡፡ [ቡኻሪና ሙስሊም]
እነዚህ ትእዛዞች በቅደም ተከተል /በተራ/ እንጂ በምርጫ አይደለም የሚፈፀሙት፡፡ በአሁኑ ጊዜ ባሪያ እንደሌለ ይታወቃል። ስለዚህ 2ኛና 3ኛ ምርጫዎች ይቀራሉ ማለት ነው። 2ኛውን የሚችል ሰው ወደ 3ኛው መዝለል አይችልም፡፡

[ለ]. ስለዚህ የሚችል ከሆነ ሁለት ወር በተከታታይ መፆም አለበት ማለት ነው፡፡ የጨረቃውን ወር አንድ ሲል ተከትሎ ከሆነ የሚፆመው ሁለቱም ወራት 29፣ 29 በድምሩ 58 ቀን ሆነው ቢያልቁም ሁለት ወር ሙሉ እንደፆመ ነው የሚቆጠረው፡፡ የጀመረው ከወሩ መጀመሪያ ካልሆነ ግን ስልሳውን ቀን መድፈን አለበት፡፡ ፆሙን ሆን ብሎ በመሀል ያቋረጠ ሰው እንደገና አንድ ብሎ መጀመር ግዴታው ነው፡፡ በመሀል የተቋረጠው በህመም፣ የወር አበባና መሰል ከአቅም በላይ በሆነ ሰበብ ከሆነ ከቆመበት ይቀጥላል፡፡ መጠንቀቅ የሚችሉት አይነት ምክንያት ከሆነ ግን በዚህ ማቋረጥ አይቻልም፡፡ ያለበለዚያ እንደገና አንድ ማለት ግድ ነው፡፡ ሌላው ቀርቶ በመሀል ላይ ከማካካሻው ውጭ የሆነ ሌላ አይነት ፆም እንኳን ማስገባት አይቻልም፡፡ [አልሙግኒ፡ 7/367]

[ሐ]. ሁለት ወር በተከታታይ መፆም ያልቻለ ሰው የሚኖረው ምርጫ 60 ምስኪኖችን ማብላት ነው፡፡ እዚህ ላይ ማከታተል ግዴታ አይደለም፡፡ ባይሆን አንድን ምስኪን በመደጋገም ሳይሆን የተለያዩ ምስኪኖችን ሊሆን ይገባል የሚያበላው፡፡ የማስረጃው ቀጥተኛ መልእክት ይህን ስለሆነ የሚጠቁመው እራስን ከውዝግብ ማራቁ የተሻለ ነው፡፡ የሚያበላው ቤተሰቡን ከሚመግበው ምግብ መካከለኛ ከሚባለው ያነሰ መሆን የለበትም፡፡

[መ]. ሶስቱንም የማካካሻ አይነቶች መፈፀም ያልቻለ ሰው እስከሚችል ድረስ ይጠብቃል እንጂ ከማካካሻ ነፃ አይሆንም፡፡ [አልኢስቲዝካር፡ 10/105]
ወላሁ አዕለም፡፡
=
(ኢብኑ ሙነወር፣ ሚያዚያ 06/2010)
https://t.me/IbnuMunewor




በረመዷን በብዛት የሚፈፀሙ ስህተቶች
~
① ሶላት ሳይሰግዱ መፆም፣
② ሌሊቱን በጫት ካሳለፉ በኋላ ሰሑርን አስቀድሞ በመመገብ ሱብሕ ሳይሰግዱ መተኛት፣
③ ቀኑን በእንቅልፍ፣ ሌሊቱን በተከታታይ ፊልም (ሙሰልሰላት) ማሳለፍ፣
④ ረመዷንን ጠብቆ መንዙማና ነሺዳ እየለቀቁ ሰዎችን ከቁርኣን ማዘናጋት፣
⑤ ተራዊሕን በንቃት እየሰገዱ ፈጅር ሶላትን በእንቅልፍ ማሳለፍ፣
⑥ ተራዊሕ ላይ በየአራቱ ረከዐ መሐል የቢድዐ እና የሺርክ እንጉርጉሮዎችን ማስገባት፣
⑦ የተራዊሕ ኢማሞች በጣም ረጅም የቁኑት ዱዓእ ማድረግ፣
⑧ መግሪብ ሶላት ሲጠናቀቅ ስርአት በሌለው መልኩ ለፊጥራ መጣደፍ (ሰጋጆችን የሚያቋርጥ፣ የሰው ጫማ የሚያቀያይር፣… አለ)
⑨ ሌሊት ላይ "ተሰሐሩ" እያሉ መዞር፣
(10) የሱሑር ጊዜ ሳያልቅ ለጥንቃቄ በሚል ቀድሞ አዛን ማድረግ፣
(11) ሱሑር ላይ "ነወይቱ ሰውመ ገዲን" እያሉ በቃል መነየት፣
(12) እያንቀላፉ ተራዊሕ መስገድ፣
(13) ልጆች "እንፁም" ሲሉ ማበረታታት ሲገባ መከልከል፣ "ውሃ አያስፈጥርም፣ ተደብቀህ ብላና ትፆማለህ" እያሉ መዋሸትና ውሸት ማለማመድ፣
(14) ሴቶች በተጋነነ የምግብ ዝግጅት ሰፊ ጊዜያቸውን ማቃጠል፣
(15) ሴቶች ሽቶ ተቀብተው ለተራዊሕ መውጣት፣
(16) በተራዊሕ ወቅት የሴቶችና የወንዶች በየ ጎዳናውና በየካፌው አላስፈላጊ መዝረክረክ፣
(17) ሃሜት፣
(18) ፊጥራ ላይ ከመጠን በላይ መመገብ፣
(19) ቀኑን በካርታ፣ በዳማ እና መሰል አጉል ነገሮች ማሳለፍ፣
(20) ሙዚቃ ማዳመጥ፣
(21) የሰው ስራ የሚሰሩ ተቀጣሪዎች ጧት በሰዓት አለመግባት (አማና መጠበቅ፣ ቃልን ማክበር ግድ ይላል። ግዴታ ያልሆኑ ዒባዳዎች ተፅእኖ የሚያሳድሩብን ከሆነ መተው ወይም መቀነስ ነው)፣
(22) በተለይ በስራ ቦታዎች ላይ በመንዙማና በነሺዳ ማሳለፍ (መሆን ያለበት ከተመቼ ቁርኣን መቅራት፣ ካልሆነ ዚክር ማድረግ ወይም ደዕዋ ማዳመጥ፣ ካልሆነ ዝምታ ይሻላል።)
(23) ለይለተል ቀድርን ለማየት ሰማይ ሰማይ እያንጋጠጡ ተሰብስበው እያወሩ መጠበቅ (የሚታይ ነገር የለም)፣
(24) አንዳንድ አካባቢዎች የዒሻእ ሶላትን በጣም በማዘግየት ሰው ጀማዐ ላይ እንዳይካፈል እንቅፋት መሆን፣
(25) አንዳንድ አካባቢዎች መስጂድ ውስጥ ጫት ይዞ ገብቶ መቃም፣
(26) አንዳንድ አካባቢዎች "ተርቲብ" ብለው ንፍሮ፣ ቆሎና መሰል ምግቦችን ወደ መስጂድ እንዲያቀርቡ ሰዎችን ማስገደድ፣ ወዘተ
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor


ሙአዚኖች ሱብሕ ሶላት ላይ አትቸኩሉ። ወቅቱ መግባቱን ሳታረጋግጡ አዛን አታድርጉ። { وَكُلُوا۟ وَٱشۡرَبُوا۟ حَتَّىٰ یَتَبَیَّنَ لَكُمُ ٱلۡخَیۡطُ ٱلۡأَبۡیَضُ مِنَ ٱلۡخَیۡطِ ٱلۡأَسۡوَدِ مِنَ ٱلۡفَجۡرِۖ } ነው የሚለው። ቀደም ብሎ አዛን የሚደረግ ከሆነ ቤታቸው ውስጥ የሚሰግዱ ሰዎች፣ በተለይም ቶሎ ሰግደው መተኛት የሚፈልጉ አካላት ወቅት ሳይገባ ሊሰግዱ ይችላሉና ጥንቃቄ ያስፈልጋል። በተጨማሪም ወቅቱ ካልተጠበቀ ሰዎች ሰሑር በትክክል እንዳይመገቡ እንቅፋት ይሆናል። ሙአዚንነት አማና ነው። አማናችሁን በትክክል ተወጡ።
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor

20 last posts shown.