KOMBOLCHA PREPARATORY SCHOOL


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Education


HIGH SCHOOL (STAY AT HOME)

Related channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Education
Statistics
Posts filter


ለ12ኛ ክፍል ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በሙሉ:-
1ኛ. ከ27-28/11/2015 ዓ.ም ከጠዋት ፈረቃ ት/ቤት በመገኘት ከንብረት ክፍል የተዋሳችሁትን መማሪያ መጽሃፍ እንድትመልሱ እናሳውቃለን።
2ኛ. ዩኒፎርማችሁን ለበጎ አድራጎት ክበብ እንድሁም ስትጠቀሙበት የነበረውን አጋዥ መጽሃፍት ለላይብራሪ ክፍል በመስጠት በጎ ስራ እንድትሰሩ ለማስታወስ እንወዳለን።
ት/ቤቱ


12ኛ ክፍል ተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርስቲ በሰላም ገብተዋል።


የተመደባችሁበትን የመኝታ ክፍል ብሎክ Dormitary placement Natural male and female(2015) የሚለውን ከፍታችሁ እዩ። ሌሎች መረጃዎች ከዚህ በላይ ያለውን ተመልከቱ


ለተፈጥሮ ሳይንስና ተማሪዎች በሙሉ ወደ ዩኒቨርስቲ መግቢያ ሰዓታችን ዕሁድ በ23/11/2015 ከሰከሰዓት 9:00 _10:00 ብቻ ስለሆነ 8:00 ላይ ት/ቤት በመገኘት የያዛችሁትን ዕቃ አሰፈትሻችሁ የከተማ አስተዳደር ባዘጋጀው መኪና በአንድነት እንድትሄዱ እናሳስባለን። ከዩኒቨርስቲው መርሃ ግብር ውጭ በተናጠል መሄድ ክልክል ነው።










Forward from: KOMBOLCHA PREPARATORY SCHOOL
አድሚሽን ካርዳችሁ ያሉት መረጃዎች ጋር በማገናዘብ ተለማመዱ።


አድሚሽን ካርድ ያልወሰዳችሁ የ12ኛ ክፍል ተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ነገ ረቡዕ 19/11/2015 ዓ.ም 10:00 ት/ቤት በመገኘት መውሰድ ትችላላችሁ።


ለ12ኛ ክፍል ተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ማክሰኞ በ18/11/2015 ዓ.ም ከሰዓት 8:30 ኦረንቴሽን ስለሚሰጥ በሰዓቱ እንድትገኙ እናሳስባለን።


Forward from: Wollo university Institute of Technology KIoT
ተፈታኞች ከዛሬ ጀምሮ ይገባሉ።

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ የሆኑ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ከዛሬ ሐምሌ 16 ጀምሮ ወደ ዩኒቨርሲቲያችን ይገባሉ።

ተፈታኝ ተማሪዎች ከሚማሩባቸው ትምህርት ቤቶች ወደ ተመደባችሁበት ዩኒቨርሲቲያችን የምትጓጓዙት በተዘጋጁላችሁ ተሽከርካሪዎች ነው።

ተፈታኞች ዩኒፎርማችሁን መልበስ ፤ ብርድልብስና አንሶላ ይዛችሁ መገኝት ይጠበቅባቸኋል። 

ወደ መፈተኛ ተቋማት ቆሎ፣ ጭኮ፣ በሶ የመሳሰሉ ደረቅ ምግቦችን ይዞ መግባት የሚፈቀድ ሲሆን የቴክኖሎጂ ውጤቶች፣ ሞባይል፣ አይፓድ፣ ላፕቶፕ የመሳሰሉ እንዲሁም ማንኛውም ጌጣጌጥ ይዞ መግባት ፈፅሞ የተከለከለ ነው።

ተማሪዎች ከቤታችሁ ስትወጡ፦
- መታወቂያ ፣
- አድሚሽን ካርድ
- የት/ቤት ዩኒፎርም መያዛቸሁን እንዳትረሱ ፤ ወላጆችም ይህንን እንድታስታውሷቸው ጥሪ እናቀርባለን።


ለማህበራዊ ሳይንስና ተማሪዎች በሙሉ ወደ ዩኒቨርስቲ መግቢያ ሰዓታችን ሰኞ በ17/11/2015 ከጠዋት 3:00 _4:00 ብቻ ስለሆነ 2:00 ላይ ት/ቤት በመገኘት የያዛችሁትን ዕቃ አሰፈትሻችሁ የከተማ አስተዳደር ባዘጋጀው መኪና በአንድነት እንድትሄዱ እናሳስባለን። ከዩኒቨርስቲው መርሃ ግብር ውጭ በተናጠል መሄድ ክልክል ነው።


አድሚሽን ካርዳችሁ ያሉት መረጃዎች ጋር በማገናዘብ ተለማመዱ።


Forward from: Wollo university Institute of Technology KIoT
" ተፈታኞች በአካልም ይሁን በስነልቦና እራሳችሁን ዝግጁ አድርጉ " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና መርሃ ግብርን ይፋ አድርጓል።

በዚህም ፥ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ሐምሌ 16 እና 17/2015 ዓ.ም ወደተመደቡበት ተቋም ይገባሉ።

ሐምሌ 18/2015 ዓ.ም ገልጻ ይሰጣቸዋል።

ከሐምሌ 19 እስከ 21/2015 ዓ.ም ፈተናቸውን ይወስዳሉ። ከሚቀጥለው ቀን ጀምሮ ተማሪዎች ወደመጡበት ይመለሳሉ።

የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች  ደግሞ ሐምሌ 22 እና 23/2015 ዓ.ም ወደተመደቡበት ተቋም ይገባሉ።

ሐምሌ 24/2015 ዓ.ም ገለጻ ይሰጣቸዋል።

ከሐምሌ 25 እስከ 28/2015 ዓ.ም ፈተናቸውን ይወስዳሉ።  ከሚቀጥለው ቀን ጀምሮ ተማሪዎች ወደመጡበት ይመለሳሉ።

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናውን በሚውስዱበት ጊዜ የፈተናውን ህግና ስርዓት እንዲያከብሩ በጥብቅ አሳስቧል።

ተፈታኝ ተማሪዎች ለፈተናው ግልጋሎት ከሚሰጡ የፅህፈት መሳሪያዎች እርሳስ፣ ላጲስ፣ መቅረጫ እና ስክቢቶ ውጭ ወደ ፈተና ክፍል ይዞ መግባት ፈፅሞ የተከለከለ መሆኑን እንዲያውቁት ብሏል።

ተማሪዎቹ ከቤታቸው ሲወጡ፦
- መታወቂያ ፣
- አድሚሽን ካርድ
- የት/ቤት ዩኒፎርም መያዛቸውን እንዳይረሱ ፤ ወላጆችም ይህንን እንዲያስታውሷቸው ጥሪ ቀርቧል።

ወደ መፈተኛ ተቋማት ቆሎ፣ ጭኮ፣ በሶ የመሳሰሉ ደረቅ ምግቦችን ይዞ መግባት የሚፈቀድ ሲሆን የቴክኖሎጂ ውጤቶች፣ አይፓድ፣ ላፕቶፕ የመሳሰሉ እንዲሁም ማንኛውም ጌጣጌጥ ይዞ መግባት ፈፅሞ የተከለከለ ነው።






Forward from: Unknown
12ኛ - Copy - Copy.docx
26.0Kb
summary of female dormitory placement.docx
17.6Kb
summary of female dormitory placement




12ኛ ክፍል ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ነገ ቅዳሜ ጠዋት 2:30 ት/ቤቱ አዳራሽ እንድትገኙ ለማስታወስ እወዳለሁ።

20 last posts shown.

4 993

subscribers
Channel statistics