Christian Tadele Tsegaye


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Religion


This channel serves as a platform to reflect political and socio-economic views of Christian Tadele Tsegaye.

Related channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Religion
Statistics
Posts filter


ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር የነረበን ቆይታ።

«በጀት በሕጋዊ አሰራር ካልተመራ የጭቆና በትር መሆኑ አይቀሬ ነው።»

https://press.et/?p=105678&fbclid=IwAR3a6kC0bIIElbDxXtialZ3POKDHbSgYfQYgc1ijrbbigkdzhglW1VovM9s


Executive_Summary_Ethiopia_Annual_Human_Rights_Situation_Report.pdf
375.1Kb
Emailing Executive Summary - Ethiopia Annual Human Rights Situation Report (June 2022 – June 2023).pdf


English Version of THE ANNUAL HUMAN RIGHTS SITUATION REPORT of the Ethiopian Human Rights Commission (Executive Summary)


[በኢትዮጵያ ያለው] የሕግ የበላይነት እጅግ አሳሳቢ በሆነ ሁኔታ የላላ [ነው]።

~ ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ (ፒኤችዲ)
****
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በያመቱ የሚያወጣውን የተጠቃለለ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት ሐምሌ 05/2015 ዓ/ም ይፋ አድርጓል።

ኮሚሽኑ ሪፖርታቸውን በቀጥታ ለሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት እንዲያቀርቡ በሕግ ከተደነገገላቸው የዴሞክራሲ ተቋማት አንዱ ቢሆንም እሰከከዛሬ ድረስ ዓመታዊ ሪፖርቱን እንዲያቀርብ በምክርቤቱ ሁኔታዎች አልተመቻቹለትም። (ሌሎች በቀጥታ ለሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት ዓመታዊ ሪፖርታቸውን ማቅረብ ያለባቸው አካላት እንባ ጠባቂ፣ ጠቅላይ ፍርድቤት፣ ፀረ ሙስና ኮሚሽንና ዋና ኦዲተር ይገኙበታል። ከዋና ኦዲተር በስተቀር አንዳቸውም ሪፖርታቸውን እያቀርቡ አይደለም። ተደጋጋሚ ጥያቄዎች ብናቀርብም እስካሁን አዎንታዊ ምላሽ አላገኝንም።)

ገዥው ፓርቲ መንግስታዊ ሥልጣኑንና ሕግጋትን ለሥልጣኑ ማደላደያነት በመጠቀም መብት ጠያቂዎችንና ተቺዎችን ከሕግ ውጭ የማሰር፣ የመግደል፣ የመሰወር እና ሌሎችንም ከፍተኛ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን እየፈፀመ ስለመሆኑ በምክርቤት ልዩ ልዩ አብነቶችን በማቅረብና በማስረጃ በማስደገፍ ጭምር ስንሞግት ነበር። በእንደራሴነት የምናቀርባቸውን ኃቀኛ አስተያየቶች በመቀበል አሰራሩን እና አመራሩን ከማስተካከል ይልቅ በሰብአዊነት ላይ የሚፈጽማቸውን ወንጀሎች በሰላማዊ ሰልፍ ለመደበቅ ሲታትር የባጀው ገዥው የብልጽግና ፓርቲ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሚያወጣቸውን ሪፖርቶችም «የጽንፈኞች ክስ ነው በሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በኩል የወጣው» የሚል አቋም ስለመውሰዱ የቀደሙ የውስጥ ለውስጥ ውይይቶች አረጋግጠዋል።

ይሁንና ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ (ፒኤችዲ) ኮሚኑ ባወጣው ዓመታዊ ሪፖርት ላይ ባስተላለፉት ቁልፍ መልእክት ውስጥ፤

1/ በሕግ የተደነገገውን አሠራር በቂ ባልሆነ ምክንያት ወደ ጎን በመተው ከሕግ ውጪ የሚፈጸሙ አሠራሮች፣ ድርጊቶች ወይም ሂደቶች፣

2/ በሕግ የተደነገገውን በማስፈጸም ሂደት ተገቢውን የተሳትፎ፣ የምክክር እና የጥሞና ጊዜ ሳይወስዱ ለማስፈጸም መሞከር፣

3/ ተቋማት በሕግ ከተሰጣቸው ሥልጣን ወሰን ውጪ/በመተላለፍ አልያም ከወሰኑ በታች/ሥልጣን እና ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ባለመወጣት እንዲሁም

4/ የተጠያቂነት አለመኖር (impunity)

የሕግ የበላይነት ላለመኖሩ እርስ በእርሳቸው ተመጋጋቢ የሆኑ ምክንያቶች እና አመላካቾች መሆናቸውን አጽንዖት ሰጥተዋል።

በሰብአዊነት ላይ የሚፈፀም ወንጀል በሰው ልጆች ላይ ሁሉ የሚፈፀም ወንጀል በመሆኑ ሁላችንም ገዥው የብልጽግና ፓርቲ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ባወጣው ዓመታዊ ሪፖርት ላይ ግልጽ ማብራሪያ እንዲሰጥና ተጠያቂነትን እንዲያሰፍን ሁላችንም ልንተጋ ይገባል።


የኢትዮጵያ_ሰብአዊ_መብቶች_ሁኔታ_ዓመታዊ_ሪፖርት_ከሰኔ_ወር_2014_ዓ_ም_እስከ_ሰኔ_ወር_2015_ዓ.pdf
3.8Mb
Emailing የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት (ከሰኔ ወር 2014 ዓ.ም. እስከ ሰኔ ወር 2015 ዓ.ም.).pdf


የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የ2015 ዓ/ም ዓመታዊ ሪፖርት።




9.  በአገራችን የተጀመሩ ልዩ ልዩ ኘሮጀክቶች ፍትኃዊነት፣ እኩል ተጠቃሚነትና ሁሉን-አቀፍ ተደራሽነትን ባረጋገጠ መልኩ በፍጥነት እንዲጠናቀቁ  የሚኒስትሮች ምክር ቤት ተገቢውን ቁጥጥር እንዲያደርግ እና ትኩረት  እንዲሰጥ ቋሚ ኮሚቴው ያሳስባል፡፡ የተከበረው ምክርቤት እና በስሩ ያቋቋማቸው ቋሚ ኮሚቴዎችም ተገቢውን የቁጥጥር ሥራ እንዲሰሩ ቋሚ ኮሚቴው ይጠይቃል፡፡

10.   አንዳንድ ኘሮጀክቶች ያለቅድመ አዋጭነት ጥናት እና የአካባቢ ተጽእኖ ግምገማ ወደ ሥራ በመግባታቸው የኢኮኖሚ አዋጭነት እና  የአፈፃፀም መጓተት ችግሮች እየፈጠሩ ስለመሆናቸው የፌዴራል ዋና ኦዲተር የክዋኔ ኦዲት ሪፖርቶች ያሳያሉ፡፡ ስለሆነም የሚኒስትሮች ምክር ቤት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ የመንግሥት ኘሮጀክቶችን አቅዶ እንዲንቀሳቀስ ቋሚ ኮሚቴያችን ያሳስባል፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም በስሩ ባቋቋማቸው ቋሚ ኮሚቴዎች በኩል ኘሮጀክቶች በስትራቴጂክ እቅድ ተይዘው እና በበቂ ጥናት ተደግፈው ወደ ሥራ መግባታቸውን የማረጋገጥ ኃላፊነቱን እንዲወጣ እንጠይቃለን፡፡

ማጠቃለያ

በ2014 ዓ.ም የተከበረው ምክር ቤት የ2013/14 በጀት ዓመት የኦዲት ሪፖርትን ባዳመጠበት ወቅት ቋሚ ኮሚቴያችን ባቀረበው የማጠቃለያ አስተያየት መሠረት በፌዴራል ዋና ኦዲተር በሚቀርቡ ተከታታይ ሪፖርቶች በአንድ የምርጫ ዘመን ለ3 ጊዜ አስተያየት መስጠት ያልተቻለባቸው መስሪያ ቤቶችን እና የጎላ ችግር ያለባቸው ሆነው በመገኘታቸው ተቀባይነት የሚያሳጣ አስተያየት የተሰጠባቸውን መስሪያ ቤቶች በኃላፊነት የመሩ የሥራ ኃላፊዎች ለመንግሥት የሥራ ኃላፊነት የማያበቃ ገዳቢ ሆኖ እንዲያዝ የሚል ሐሣብ አቅርበን የተከበረው ምክር ቤትም በሙሉ ድምጽ የተቀበለው እና ያፀደቀው በመሆኑ፣ ይህንኑ የምክር ቤቱ ውሣኔ የሕግ መሠረት ለማስያዝ፣ በምክር ቤቱ እና በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት ለሚፀድቁ ሹመቶች የመመዘኛ መስፈርት ደንብ ውስጥ እንዲካተት ቋሚ ኮሚቴያችን እያሳሰበ፣ የመንግሥት እና የሕዝብ ኃብቶችን በማስመለስ አጥፊዎችም በሕግ እንዲጠየቁ ይደረግ ዘንድ በአጽንፆት እንጠይቃለን፡፡


በዓመታዊ የዋና ኦዲተር ሪፖርት ላይ የቀረበ የማጠቃለያ አስተያየት፤
*
አመሰግናለሁ የተከበሩ ምክትል አፈ-ጉባዔ፣

የተከበራችሁ የምክር ቤት አባላት፣

ምክር ቤታችን በ2014 በጀት ዓመት ያፀደቀው በጀት የመንግሥት ፋይናንስ አስተዳደር አዋጅ፣ ደንብና መመሪያ በሚፈቅደው መሠረት በትክክል ሥራ ላይ መዋሉን ለማረጋገጥ የፌዴራል ዋና ኦዲተር ባከናወነው ኦዲት ባቀረበው ሪፖርት በርካታ የሂሣብ አያያዝ ግድፈቶች እና የውስጥ ቁጥጥር ድክመቶች መኖራቸውን እንዲሁም አፈፃፀማቸው ከሕግ እና ከተዘረጋው አሰራር ውጪ መሆናቸውን ያሳያል፡፡ በመሆኑም የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሪፖርቱን በመገምገም በምክር ቤቱ እና በፌዴራል ዋና ኦዲተር ትኩረት ሊያገኙ የሚገቡ አንኳር ምክረ-ሃሣቦችን እና የማጠቃለያ አስተያየቶችን እንደሚከተለው አቀርባለሁ፡፡

የፌዴራል ዋና ኦዲተር የመንግሥት እና የሕዝብ ኃብት ለታለመለት እና ለታቀደለት ተግባር በትክክል ሥራ ላይ እንዲውል ለመቆጣጠር እና ለመከታተል ይረዳው ዘንድ የሰው ኃይል አደረጃጀት፣ የመረጃ አያያዝ፣ ተግባራትን በዕቅድ መፈፀም እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶ መስራት ዋና ዋና ጥንካሬዎቹ መሆናቸውን ቋሚ ኮሚቴው ገምግሟል፡፡

በሌላ በኩል የዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ለክልሎች የሚተላለፈውን የድጎማ በጀት ኦዲት ሪፖርት አስመልከቶ ለምክር ቤቱ ባቀረበው ሪፖርት ላይ የበላይ አመራሩን በቂ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችን እንዲሁም የሕግ እና ፖሊሲ ድጋፍ የሚሹ አሰራሮችን ለይቶ አለማቅረቡን እንዲሁም የ2014 በጀት ዓመት የፌዴራሉ መንግሥት አጠቃላይ ገቢ እና ወጪ ኦዲት ሪፖርት በተመለከተ ባቀረበልን ዓመታዊ የኦዲት ሪፖርት የተብራራ ነገር አለማቅረቡን ቋሚ ኮሚቴው በድክመት አይቶታል፡፡

የፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የኦዲት ግኝትን ለማሻሻል የክትትል ኦዲትን ማሳደግ፣ የአገሪቱን የ1ዐ ዓመት መሪ ዕቅድ ለማስፈፀም እንዲቻል የልማት ኘሮጀክቶችን የዕቅድ ክትትልና የአፈፃፀም ግምገማ በማድረግ ውጤት ማስገኘት፣ የፋይናንስ ሕጋዊነት ኦዲትና የክዋኔ ኦዲት ሥራዎች በዓለምአቀፍ ደረጃ ጥራታቸውን የጠበቁ በማድረግ የሪፖርቱን ተዓማኒነት በማሳደግ ተቀባይነቱን ማረጋገጥ፣ የመስሪያ ቤቱን የውስጥ አሰራር ውጤታማነቱንና ቅልጥፍናን የሚያረጋግጡ ሪፎርሞች ለመተግበር ከኦዲት ኮሚሽን ጋር በቅርበት መስራትን ቁልፍ ተግባሩ አድርጎ ሊወስድ ይገባል፡፡

የተከበረው ምክር ቤትም በስሩ ባደራጃቸው የቋሚ ኮሚቴዎች በኩል ለኦዲት ሪፖርቶች ልዩ ትኩረት በመስጠት የአስፈፃሚ መስሪያ ቤቶችን ዕቅድና የአፈፃፀም ሪፖርት ሊገመግምና ውጤት እንዲመጣ ጥረት ሊያደርግ ይገባዋል፡፡

የ2014 በጀት ዓመት የኦዲት ሪፖርት ግምገማን መነሻ በማድረግ በቋሚ ኮሚቴው በኩል የቀረቡ ምክረ-ሐሣቦች፤

1.  የገንዘብ ማስመለስ ምጣኔ 0.65% ብቻ መሆኑ አስፈፃሚው አካል ለኦዲት ግኝት ትኩረት ያለመስጠቱን እንዲሁም በመቆጣጠር ተጠያቂነትን የማስፈን ኃላፊነት የተጣለበት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በስሩ የተቋቋሙ ቋሚ ኮሚቴዎች የኦዲት ግኝት ሪፖርቶችን የቁጥጥር መሣሪያ አድርገው ከመጠቀም እና በአጠቃላይ አስፈፃሚውን አካል ከመቆጣጠር አኳያ ውሱንነቶች ያሉባቸው መሆኑን አመላካች ነው፡፡ የመቆጣጠር እና ከፊል የመቆጣጠር የሕግ ኃላፊነት ያለባቸው አካላት ማለትም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት፣ ገንዘብ ሚኒስቴርና የፍትሕ ሚኒስቴር በአግባቡ በሕግ የተሰጣቸውን ኃላፊነት መወጣት ካልቻሉ የመንግሥትና የሕዝብ ኃብትና ንብረት ከመንግሥት ሕግ አሰራርና መመሪያ ውጪ ጥቅም ላይ መዋሉ የብሔራዊ ደኀንነት ስጋት ሆኖ መምጣቱ የማይቀር ነው፡፡ ስለሆነም በተለይም የተከበረው ምክር ቤት ተጠያቂነትን ሊያሰፍን ይገባል፡፡

2.  ነቀፌታ የሌለበት አስተያየት የተሰጣቸው ተቋማት ቁጥር ከዓመት ወደ ዓመት እያደገ መምጣቱ በመልካም ጎኑ የሚታይ ሆኖ አስተያየት መስጠት ያልተቻለባቸውና የጎላ ችግር ያለባቸው ሆነው በመገኘታቸው ተቀባይነት የሚያሳጣ አስተያየት የተሰጣቸው ተቋማት 25 የሚደርሱ መሆናቸው በተለይም እነዚህ ተቋማት ከሚያንቀሳቅሱት ፋይናንስ፣ የሰው ኃይል እንዲሁም ለአገር እና ሕዝብ ካሏቸው ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታዎች አንፃር ሲታይ በኦዲት ግኝቱ የተሰጣቸው አስተያየት አሳሳቢ ያደርገዋል፡፡ ስለሆነም የተከበረው ምክር ቤት እና በስሩ ያቋቋማቸው የቋሚ ኮሚቴዎች የጉዳዩን አሳሳቢነት በማጤን ተገቢውን ትኩረት በመስጠት የማስተካከያ እርምጃ ሊወስዱ ይገባል፡፡

3.  እጅግ ከፍተኛ የሆነ ተሰብሳቢ ገንዘብ መኖሩ እና ከዓመት ዓመት የሚስተዋለው የመሰብሰብ ምጣኔም ለዜሮ የቀረበ መሆኑ፣ ዜጎች በተቋማት እና በፋይናንስ ሕጎች፣ መመሪያዎችና አሰራሮች ላይ ያላቸውን አመኔታ ከመሠረቱ ተጠየቅ ውስጥ የሚከት ነው፡፡ ስለሆነም የተከበረው ምክር ቤት ብርቱ አቋም ወስዶ የመንግሥት መስሪያ ቤቶች የፋይናንስ ሕግጋትንና መመሪያዎችን በማክበር የተጣለባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ በአጽንፆት እንዲያሳስብ እንዲሁም የመንግሥትና ሕዝብ ኃብትና ንብረት እንዲመለስ ጥብቅ ቁጥጥር እንዲያደርግ፣ ተጠያቂነትንም እንዲያሰፍን በአንክሮ እንጠይቃለን፡፡

4.  በተለያዩ የመንግሥት ተቋማት ተመን ሳይወጣላቸው ከሕግ ውጪ የሚሰበሰቡ ገንዘቦች መጠን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመምጣቱ፣ ይኸውም ለሙስና እና ብልሹ አሰራር እንዲሁም ለቁጥጥርና ኦዲት ሥራ አመቺ ባለመሆኑ፣ የተከበረው ምክር ቤት አስቸኳይ ማስተካከያ እንዲደረግበት ውሳኔ ሊያሳርፍ ይገባል፡፡ የሚኒስቴሮች ምክር ቤትም ከዚህ አንፃር የሚስተዋሉ ጉድለቶችን በቁልፍ ተግባር ይዞ ማስተካከያ ሊያደርግ ይገባዋል፡፡

5.  የመንግሥት ተቋማት ከሕግና መመሪያ ውጪ ግዥዎችን እየፈፀሙ በመሆኑ፣ ይኸውም ለከፍተኛ የኃብት ብክነትና ብልሹ አሰራር አጋላጭ በመሆኑ፣ የተከበረው ምክር ቤት ተገቢውን ቁጥጥር በማድረግ ተጠያቂነት እንዲሰፍን አቋም ሊወስድ ይገባል፡፡

6.   የመንግሥት መስሪያ ቤቶች በየተቋሞቻቸው ያሉ ንብረቶችን በሕግ እና በአግባቡ ጥቅም ላይ መዋላቸውን የማረጋገጥ ኃላፊነታቸውን በወጉ መወጣት እንዳለባቸው ቋሚ ኮሚቴው ያሳስባል፡፡

7.  የመንግሥት መስሪያ ቤቶች ከዓመት ዓመት ያለው የበጀት አጠቃቀም የኦዲት ሪፖርት እንደሚያሳየው ጥቅም ላይ ያልዋለ በጀት እጅግ ከፍተኛ መሆኑን እንዲሁም ከተደለደለው በጀት በላይ ያለፈቃድ አዛውረው በመጠቀም በኩል ያለው ችግርም ከፍተኛ መሆኑን ያሳያል፡፡ ስለሆነም የተከበረው ምክር ቤት በበጀት ማጽደቅ ወቅት የኦዲት ሪፖርቱን መነሻ ያደረገ የበጀት ግምገማ እንዲያደርግ እና ተገቢውን ማስተካከያ እንዲያደርግ ቋሚ ኮሚቴው ምክረ-ሐሳቡን ያቀርባል፡፡

8.  በበርካታ የመንግሥት ተቋማት እጅግ ከፍተኛ የሆነ የገንዘብ መጠን ወጪ ተደርጎ ደጋፊ ሰነድ ባለመቅረቡ ኦዲት ማድረግ እንዳልተቻለ የዋና ኦዲተር ሪፖርት ያሳያል፡፡ የመንግሥት መስሪያ ቤቶች ለኦዲት ሥራ አስፈላጊ የሆኑ ሰነዶችን ለምርመራ ማቅረብ የሕግ ግዴታ እንዳለባቸው በኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥት እና በፌዴራል ዋና ኦዲተር ማቋቋሚያ አዋጅ ላይ በግልጽ ተደንግጓል፡፡ ከዚህ አንፃር የሚስተዋሉ የሕግ ጥሰቶችን እንዲሁም ለብልሹ አሰራር እና ለምዝበራ አጋላጭ ሁኔታዎችን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት፣ የገንዘብ ሚኒስቴርና የፍትሕ ሚኒስቴር ተገቢውን ትኩረት በመስጠት ተጠያቂነትን ሊያረጋግጡ ይገባል፡፡


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከአሐዱ ቲቪ ጋር የነበረንን ቆይታ ነገ በእለተ ትንሳዔ ከቀኑ 7:00 ጀምሮ እንዲከታተሉ እንጋብዛለን።




የመቃብር ጠባቂዎች ኃይል ትንሳዔውን አላስቀረውም፤
*
በቅድሚያ በአገር ውስጥና በውጭ ለምትገኙ ለመላው ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያዊያት እንኳን ለ2015 ዓ.ም የስቅለትና የትንሳዔ በዓል በሰላም አደረሰን፤ አደረሳችሁ።

በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በታላቅ ድምቀት ከሚከበሩ በዓላት መካከል አንዱ የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለትና የትንሳዔ በዓል ነው፡፡ ትንሳዔ የሚለው ቃል በክርስትና ኃይማኖት አስተምኅሮ መሰረት «መነሳት» ማለት ሲሆን ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፥ አዳም በሳተ ጊዜ፥ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ ብሎ በገባለት ቃል መሰረት በቀራኒዮ ተሰቅሎ በ3ኛው ሌሊት «መግነዝ ፍቱልኝ፥ መቃብር ክፈቱልኝ» ሳይልና የመቃብር ጠባቂዎች ኃይል ሳያግደው ሞትን ድል አድርጎ መነሳቱን የምናበስርበትና የምናስብበት የፍቅር፣ የደስታና የድል በዓል ነው።

የትንሳዔ በዓል ኃቅንና እውነትን ወግነው ለቆሙ ሁሉ ከሞት አጠገብ ሕይወት፤ ከመቃብር አጠገብ ትንሳዔ መኖሩን የምናስብበት፤ ፈጣሪ ለሰው ልጆች ያለውን ጥልቅ ፍቅር በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ሞታችንን በሞቱ ድል አድርጎ የመዳንን ጸጋ ያገኘንበት፤ ስለ ፍቅር የሚከፈለውን መራራ መስዋእትነትን ያየንበት፤ ትኅትናንና ይቅር ባይነትን የምንማርበት ታላቅ በዓል ነው፡፡

ትንሳዔ የተስፋ መሟሸሽንና ሞትን የማሸነፍ በዓል ነው፤ በእለተ አርብ በጦር ጉልበታቸው የሚተማመኑ ሮማውያንና ሁሉን እናውቃለን በሚሉ ፈሪሳውያን የሀሰት ክስና ፍርድ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ መዋሉን ተከትሎ ፀሐይ የጨለመችበት፣ ጨረቃ ደም የለበሰችበት፣ ከዋክብት የረገፉበት እና ሞት የነገሰበት እንዲሁም ብዙዎች ተስፋ የቆረጡበት እለት ነበር፡፡ የጌታ ትንሳዔ በመከራና በጨለማ ውስጥም ሆነው ኃቅንና እውነትን ወግነው ለቆሙትና በጽናት ለጠበቁት ግን ከጨለመችው ፀሐይ ባሻገር አማናዊ ብርሃን፣ ደም ከለበሰችው ጨረቃ ባሻገር በደሙ የሚድኑ የሰው ልጆች መኖራቸውን፣ ከረግፉ ከዋክብት ባሻገር በሞቱ ሞትን ድል የሚነሳ አምላክ መኖሩን ያዩበት የድል እለት ነው፡፡

ዛሬ ላይ የዘመናችን መቃብር ጠባቂዎች የሕዝባችንን ፈተና በማብዛት እጅግ አስከፊ ለሆነ ሰቆቃ ዳርገውት ይገኛሉ። ይኼ ፈተና ትናንትም የነበረ፤ ዛሬም የቀጠለ፤…ነገ ግን በብርቱ የጋራ ትግላችን ወደ የሁሉም፥ በሁሉም የሆነች ፍትኅ የሰፈነባት፣ ነፃነት የለመለመባት፣ እኩልነት የተንሰራፋባትና ዴሞክራሲ የዳበረባት ኢትዮጵያን እውን በማድረግ በድል የምንደምቅበት ይሆናል። ነገ የሌላቸው አካላት ዛሬያችንን ቢያበላሹትም፤ ትናንት የሌላቸው ሰዎች ለትዝታ አልቦነት ደዌያቸው ፈውስ ዛሬያችንን ቢያጠለሹትም፥ ከአምላክ ጋር ወጀቡን በድል ተሻግረን በትንሳዔያችን እንደምቃለን። ይኼ ተጠየቅ የማይቀርብበት እውነታ ነው። በትናንታችን ብቻ ሳይሆን በነጋችንም ብሩኅ ተስፋ የሚቀኑ የጥፋት ማኅበርተኞች ከዚህም በላይ በብርቱ እንደሚፈትኑን ለኃቅ የቀረበ ግምት ነው። ፈተናው በበረታ ቁጥር ትንሳዔያችን እየቀረበ ለመሆኑ ማረጋገጫ ነውና፥ በጽናት እንበርታ።

የመቃብር ጠባቂዎች ኃይልና ብርታት የክርስቶስን ትንሳዔ እንዳላስቀረው ሁሉ፤ የዘመናችን መቃብር ጠባቂዎች የሕዝባችንን የፍትኅ፣ የነፃነት፣ የእኩልነትና የዴሞክራሲ ትንሳዔ የማርዘም ካልሆነ የማስቀረት አቅም ከቶውንም ሊኖራቸው አይችልም። ትንሳዔው እንደማይቀር፤ ያለስቅለትም ትንሳዔ እንደማይኖር እሙን ነው። ከተባበርን፣ ከተናበብን፣ ከተደማመጥንና በጋር ጸንተን ቆመን የሕዝባችንን አቅም በሚገባ መጠቀም ከቻልን፥ በስቅለቱና በመከራው መጨረሻ ሕዝባችን ትንሳዔን ሲጎናፀፍ፥ የሕዝባችን ጠላቶች ደግሞ የኃፍረትን ማቅን ይለብሳሉ።

የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳዔ በዓልን ስናከብር አንድነታችንን በማጠናከር፤ ቤት ንብረት ወድሞባቸው የተፈናቀሉትን፣ ተንከባካቢ የሚሹ አረጋውያንን፣ የጎዳና ተዳዳሪዎችን፣ የኑሮ ሁኔታ ያልተሟላላቸውን እንዲሁም የታመሙና በእስር ላይ የሚገኙ ወገኖቻችንን በመጠየቅ እንዲሆን የአደራ መልእክቴን አስተላልፋለሁ።

መልካም የስቅለትና ትንሳዔ በዓል!


Video is unavailable for watching
Show in Telegram






4) የመከላከያ ሰራዊት አባላት በሕዝባቸውና የቁርጥ ቀን ባለውለታቸው በሆነው ልዩ ኃይል ላይ የሚወስዱትን እርምጃ እንዲያቆሙና ወደ ካምፓቸው እንዲመለሱ፤ በተለይም የአማራ ልዩ ኃይል አባላት የአገር አንድነት የመጨረሻ ምሽግ ከሆነው የመከላከያ ኃይል ጋር ወደ ግጭት የሚያስገቡ ጉዳዮችን በማስወገድ ተረጋግተውና አንድነታቸውን ጠብቀው በካምፓቸው እንዲሰበሰቡ፤ የአማራ ሕዝብ ለልዩ ኃይሉ ተገቢውን ድጋፍ ሁሉ እንዲያደርግ፤ መላው ኢትዮጵያውያንም የብልጽግና ፓርቲ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴን ኢሕገመንግስታዊ አገር አፍራሽ እርምጃ በአንድነት እንድታወግዙ ጥሪያቸንን እናቀርባለን።

5) የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ልኂቃን፣ ሚዲያዎችና የማኅበረሰብ አንቂዎች ግጭት አባባሽ ከሆኑ ጉዳዮች በመታቀብ የገዥውን ፓርቲ ፋሽስታዊ እርምጃዎች በመርሕና ሕግ በመመርኮዝ በጽናት ትታገሉ ዘንድ ከአደራ ጭምር ጥሪያችንን እናቀርባለን።

6) የዓለምአቀፍና የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ የብልጽግና ፓርቲ ከገባበት አገርን የማፍረስ እኩይ ተልእኮው በመታቀብ ሕግ አክብሮ እንዲንቀሳቀስ፤ በየጊዜው ግጭቶችን እየጠመቀ በንፁኃን ላይ የሚያደርሰውን የዘር ፍጅትና ማንነት ተኮር ጅምላ ጭፍጨፋዎች እንዲያቆም፤ የሰብአዊ መብቶችን አክብሮ የመንቀሳቀስ ዓለምአቀፋዊ መርሆ እንዲያከብር አስፈላጊ እርምጃዎችን ሁሉ በመውሰድ ታሪካዊ ኃላፊነታችሁን ትወጡ ዘንድ ጥሪ እናቀርባለን። ይህ የማይሆን ከሆነ ግን ዓለምአቀፍ ማኅበረሰቡ በሩዋንዳ የዘር ፍጅት የፈፀመውን ታሪካዊ ስህተት እንደሚደግም ማስጠንቀቅ እንፈልጋለን።


ሚያዝያ 03፣2015 ዓ/ም
አዲስ አበባ፥ ሸዋ፣ ኢትዮጵያ


የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የክልል ልዩ ኃይሎች እንዲፈርሱ ያሳለፈውን ውሳኔ በፌዴራል መንግስት ስምና በመከላከያ ሰራዊት የኃይል እርምጃ ለማስፈፀም የሚያደርገውን ፋሽስታዊ እርምጃ ሊያቆም ይገባል፤
ኢትዮጵያና ሕዝቦቿ ባለፉት አስርት ዓመታት በተለይም ባለፉት አምስት ዓመታተ እጅግ አስከፊ በሆነ ርሀብና ጠኔ፣ ስደትና መፈናቀል፣ ማንነት ተኮር ጅምላ ግድያዎችና የዘር ፍጅቶች እንዲሁም በማያባሩ ግጭቶችና የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ውስጥ ይገኛሉ። ሕዝባዊ የፍትኅ፣ የእኩልነት፣ የነፃነትና የዴሞክራሲ ጥያቄዎች ሲበረቱበት የኢሕአዴግ አገዛዝ የሄደባቸውን የጥፋትና አገር የማፍረስ እኩይ ስምሪቶች የመንፈስ ግብር ወራሹ የሆነው ገዥው የብልጽግና ፓርቲም ዓይነትና መጠናቸውን አሳድጎ ቀጥሎባቸዋል። ፓርቲውና የፓርቲው አመራሮች በአመራር ስልታቸውና ብቃታቸው ላይ እንደአካልና ግለሰብ የሚቀርቡባቸውን ጥያቄዎችና ትቺቶች የብሔርና ኃይማኖት ቅርጽ በመስጠት ነቀፌታዎቹ የሆነ ብሔርና ኃይማኖት ላይ የቀረቡ በማስመሰል ወደለየለት ሕዝብን በሕዝብ ላይ የሚያነሳሳ የዘር ፍጅት ቅስቀሳ ገብቷል። አገዛዙ ግጭትን እንደኅልውና ማስቀጠያ መሣሪያ እየተጠቀመበት ይገኛል።
ለአብነትም የብልጽግና ፓርቲ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በመጋቢት፣2015 ዓ/ም የክልል ልዩ ኃይል አደረጃጀትን በተመለከተ ያሳለፈውን ውሳኔ ተከትሎ አገራችን ከነበረችበት አንፃራዊ መረጋጋት፣ ሰላምና ተስፋ መፈንጠቅ ወደ ትርምስ፣ ስጋትና የመበተን አደጋ ገብታለች። ይህንንም ተከትሎ ለኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን በጎ እሳቤ ያላቸው ወገኖች ሁሉ ገዥው ፓርቲ የወሰነውን አስተውሎት የጎደለው ውሳኔ እንዲያጤነው ደጋግመው ቢወተውቱም ካፈርሁ አይመልሰኝ በሚመስል ጎረምሳዊ ግብር ውሳኔውን የተቹ ንቁ ዜጎችን የመንግስት የፀጥታ መዋቅሮችን በመጠቀም ወደ ማፈን ተሸጋግሯል፤ የአገር መከላከያ ሰራዊቱንም ከሕግና ሕገመንግስታዊ መርሆዎች ባፈነገጠ መልኩ በፓርቲ ጥርነፋ በማስገባት በሕዝብና የክልል መንግስት መዋቅሮች ላይ በይፋ በማዝመት በንፁኃን ላይ ግድያና አፈናዎችን በመፈፀም ላይ ይገኛል።

በዚህም በ6ኛው ዙር ምርጫ የሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባል ሆነን በእንደራሴነት የተመረጥን እኛ፦
1) የተከበሩ ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ
2) የተከበሩ ክርስቲያን ታደለ
3) የተከበሩ ሙሉቀን አሰፋ
4) የተከበሩ አበባው ደሳለው እና
5) የተከበሩ ዘመነ ኃይሉ

የብልጽግና ፓርቲ፤ በመረጠን ሕዝባችን ላይ እየፈፀመ ያለውን ፋሽዝም በጽኑ እያወገዝን፤የተፈፀሙ ሕገመንግስታዊ ጥሰቶቸንና መደረግ ያለባቸውን ምክረሐሳቦች እንደሚከተለው እናቀርበቀለን።

1) ብልጽግና ፓርቲ እንደሌሎች የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሁሉ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተመዝግቦ የሚንቀሳቀስ ሆኖ ሳለ፤ በሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴው የክልል ልዩ ኃይሎችን በተመለከተ ያስተላለፈው ውሳኔ በየትኛውም የአገሪቱ ሕግ ለፓርቲው በሥልጣንነት ያልተፈቀደ ሆኖ አግኝተነዋል። የብልጽግና ፓርቲ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ውሳኔ ፓርቲው ሕገመንግስታዊ የመንግስትና ሕዝብ ተቋማትን እንደፓርቲው አደረጃጀት የቆጠረ፤ ለብቻው በፓርቲ ደረጃ በሕዝብና መንግስት ተቋማት ላይ አዛዥ ናዛዥ እንደሆነ አድርጎ ያቀረበ በመሆኑ ከሕግ፣ ሞራልና አሰራር አንፃር ተቀባይነት የሌለው ከመሆኑም ባሻገር በሰላማዊና ሕጋዊ መንገድ ተመዝግበው የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የታጠቀ ኃይል ማንቀሳቀስ የማይችሉ መሆናቸውን የሚደነግገውን የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ስነምግባር የተመለከተውን አዋጅ ቁጥር 1162/2011 የተላለፈ ነው። በመሆኑም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይኸንኑ የብልጽግና ፓርቲ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ሕግ የጣሰ ውሳኔ በመርመር በፓርቲው ላይ ተገቢውን የሕግ እርምጃ እንዲወስድ እንጠይቃለን።

2) በኢፌዴሪ ሕገመንግስት የክልሎችን ሥልጣን በሚደነግገው አንቀጽ 52/2/ሰ ሥር «የክልሉን ፖሊስ ኃይል ያደራጃል፤ ይመራል፤ የክልሉን ሰላምና ፀጥታ ያስጠብቃል» በማለት ክልሎች የየራሳቸውን የፖሊስ ኃይል የማደራጀት ሕገመንግስታዊ መብት እንዳላቸውና አደረጃጀቱና አመራሩም በራሳቸው የሚወሰን መሆኑን በማያሻማ መልኩ ያስቀምጣል። የክልል ልዩ ኃይሎች በክልል መንግስታት ምክርቤቶች በኩል በአዋጅ የተቋቋመው የፖሊስ ኃይል አካል ሲሆኑ ተጠሪነታቸውም ለየክልሎቹ ፖሊስ ኮሚሽኖች ነው። ሰይጣን ላመሉ ከመጽሐፍ ያጣቅሳል እንዲሉ የብልጽግና ፓርቲ ክልሎች የመደበኛ ፖሊስ ብቻ ነው የተፈቀደላቸው የሚል የዓይናችሁን ጨፍኑ ላሞኛችሁ ሙግት ቢያቀርብም ቅሉ፤ እንደኃይማኖታዊ ቅዱስ መጽሐፍ በሚያመልከው የኢፌዴሪ ሕገመንግስት ውስጥ አንድም ቦታ መደበኛ ፖሊስ ብቻ ስለመፈቀዱ የሚያትት የሕግ ድንጋጌ የለውም። ይልቁንም በዚሁ ሕገመንግስት አንቀጽ 52/1 ላይ «ለፌዴራል መንግስት በተለይ ወይም ለፌዴራሉ መንግስትና ለክልሎች በጋራ በግልጽ ያልተሰጠ ሥልጣን የክልል ሥልጣን ይሆናል» የሚለው ድንጋጌ «የልዩ ኃይል ፖሊሰ» ማቋቋምን የክልሎች ልዩ መብት አድርጎ የሚያስቀምጥ ነው። የክልሎች የልዩ ኃይል አደረጃጀት ሕገመንግስታዊ አይደለም ቢባል እንኳን በአንድ ፓርቲ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ውሳኔ ሳይሆን ባቋቋሟቸው የክልል መንግስታት በኩል የማቋቋሚያ አዋጆቻቸው ማስተካከያ እንዲደረግበት ተደርጎ የሕግ ክፍተቱ  የሚታረም ሆኖ መሰል መብቶች ለክልሎች የተተው መሆናቸው ተጠየቅ የሚቀርብባቸው አይሆኑም።

3) የፌዴራል መንግስቱና የአገር መከላከያ ሰራዊት የአንድ ፓርቲ የግል ንብረቶች አለመሆናቸው እየታወቀ በተለይም በኢፌዴሪ ሕገመንግስት አንቀጽ 87 ስለመከላከያ መርሆዎች በሚያትተው ንዑስ አንቀጽ 5 «የመከላከያ ሰራዊቱ ተግባሩን ከፖለቲካ ድርጅቶች ወገናዊነት ነፃ በሆነ አኳኋን ያከናውናል» የሚለውን ድንጋጌ በመጣስ እንዲሁም የአገር መከላከያ ሰራዊት በፖሊስ ሰራዊት በተለይም በክልሎች የፖሊስ አደረጃጀት ላይ ውሳኔ ለመስጠትና ማስተካከያ ለማድረግ የሕግ ሥልጣን ሳይኖረው በመረጠን ሕዝብና በራሱ በጀት በሚያስተዳድራቸው ሕዝባዊ ተቋማቱ ላይ የታወጀው ጦርነት የለየለት ፋሽስታዊ ተግባር ሆኖ አግኝተነዋል። ጣልቃገብነቶችም በኢፌዴሪ ሕገመንግስት አንቀጽ 51/14፣ 55/16 እና 62/9 መሰረት የተከናወኑ ባለመሆናቸው ግልጽ ሕገመንግስታዊ ጥሰቶችና አገር አፍራሽ ተልእኮዎች ናቸው።  የፌዴራል መንግስቱ በክልሎች ላይ በተለይም በአማራ ክልል እያደረገ ያለው ጣልቃገብነት የብልጽግና ፓርቲ በመቃብሬ ካልሆነ አልደራደርባቸውም የሚልላቸውን ፌዴራሊዝምና የኢፌዴሪ ሕገመንግስት ጭምር ገደል የከተተ ነው። በተለይም ሰራዊቱ በማናቸውም ጊዜ ለሕገመንግስቱ ተገዥ መሆን እንዳለበት የሚደነግገውን አንቀጽ 87/4 ድንጋጌ የሻረ ነው።

በብልጽግና ፓርቲ የተፈፀሙ መሰል የአገር አፍራሽነት ሕገመንግስታዊ ጥሰቶችን የሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት፣ የፌዴሬሽን ምክርቤትና መላው ኢትዮጵያውያን በጽኑ እንድታወግዙት ጥሪያችንን እናቀርባለን። በተለይ ሕገመንግስታዊ ሥርዓትን የመጠበቅና የማስጠበቅ የሕግ ግዴታ ያለባችሁ ተቋማት አስፈላጊውን እርምጃ ሁሉ በመውሰድ የብልጽግና ፓርቲን አገር የማፍረስ እኩይ ተልእኮ ታስቆሙ ዘንድ በአጽንዖት እናሳስባለን።






ሲሳይ መሸለም ያለበት ሰው ነው!
****
ከሞቀ ቤታቸው በግፈኞች ለተፈናቀሉ እና ሀብት ንብረታቸው ለወደመባቸው ወገኖች የእለት ደራሽ ፍጆታዎችን የሚያደርሰው፤ ቀና ሰዎችን በማስተባበር መጠለያ በማስገንባት እናቶችን፣ ሕፃናትንና አረጋውያንን ከሜዳ ያነሳው ሲሳይ አውግቸው (ረ/ፕሮፌሰር) ሕግን ባልተከተለ መንገድ መታሰሩ ተገቢነት የለውም።

ሲሳይ መሸለም እንጂ መታሰር ያለበት ሰው እንዳልሆነ አሳሪዎቹም ያውቁታል። ሕግ አስፈፃሚው የመብት ጥያቄ የሚያቀርቡ ዜጎችን በኃይል ማፈን እንደፋሽን ተያይዞታል። መሰል የሕግ ስነሥርዓትን ያልተከተሉ የአፈናና የኃይል እመቃ እርምጃዎች ከፍ ሲሉ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች፥ ብሎም የዜጎችን ሕገመንግስታዊ መብቶች ማጣበብ መሆናቸውን ለማስታወስ እንወዳለን።

20 last posts shown.

11 341

subscribers
Channel statistics