Muktarovich Ousmanova


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Politics


Ethiopia forever

Related channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Politics
Statistics
Posts filter


በመላው ሀገሪቱ የሀይል መቋረጥ አጋጥሟል


በኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚሰሩ የጉምሩክ ሰራተኞች እንደአዲስ ሊዋቀሩ ነው ተባለ

በቅርብ ጊዜያት በርካታ ቅሬታዎችን ያስተናገደው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጉምሩክ የስራ ክፍል፤ ሰራተኞች በአዲስ መልክ እንደሚደራጁ የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ።

ከብሔራዊ ቴሌቭዥን ጣቢያ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ በ2016 ስምንት ወራት ውስጥ 49 የጉምሩክ ሰራተኞች እና ከፍተኛ አመራሮች ላይ አስተዳደራዊ እና ሕጋዊ እርምጃ ተወስዷል ብለዋል።

ኮሚሽኑ በሰራተኞቹ ላይ የሚቀርቡትን ቅሬታዎች ለመቅረፍ "ረጅም ጊዜ" የወሰደ ጥናት መካሄዱ ታውቋል።

በጥናቱ መሰረት በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ የሚሰሩ የጉምሩክ ኮሚሽን ሰራተኞን ለመቀየር፣ ለማሸጋሸግ እና በድጋሚ ለማዋቀር ዝግጅት ተደርጓል ተብሏል።

በመጋቢት መጀመሪያ "በተለያዩ አጋጣሚዎች የሚሰነዘሩ አሉባልታዎችና የስም ማጥፋት ዘመቻዎች ከእውነት የራቁ ናቸው" በማለት የብሔራዊ የአየር ትራንስፖርት ፋሲሊቲ ኮሚቴ መግለጫ ቢሰጥም አየር መንገዱ በበኩሉ በቅሬታዎቹ ላይ ምርመራ መጀመሩን እንዳስታወቀ ከዚህ ቀደም የመረጃ ምንጫችን መዘገቡ ይታወሳል ።

ምንጭ፦ አዲስ ማለዳ


የህወሓት ታጣቂዎች በራያ ህዝብ ላይ ከትናንት በስተያ ጠዋት የከፈተው ውጊያ በመከላከያ ሠራዊቱ፣ በአማራ ሚልሻና በራያ ወጣቶች ቅንጅት አፃፋውን አግኝቶ አሁን ተረጋግቷል ብለዋል። ታጣቂዎቹ ሾልከው በገቡባቸው የራያ አከባቢዎች በተለይ ጨማሮ እና ኮስም በሚባሉ አካባቢዎች የህዝብን ንብረት እና የኮስም 1ኛ ትምሀርት ቤትን ዘርፈውና አውድመው ሄዷል ብለዋል። ከዚህ በተጨማሪ አንድ መስጊድ ለማቃጠል ሙከራ አድርገው በመከላከያ ሰራዊት ከሽፏል ብለዋል፣የቁርዓን ትምህርት ቤቶችን ግን አቃጥለዋቸዋል ብለዋል፣ያሳዝናል። በጦርነቱ ያ ሁሉ እልቂት ተፈፅሞ እንደገና ሌላ ፀብ መጫር ለትግራይ ህዝብ ይበጀዋል? ቆም ብሎ ማሰብ ያስፈልጋል።
አዩዘሀበሻ
ፎቶ:-ከቦታው
ጥቆማ❗❗👇
👉ፈጣን እና ያልተሰሙ መረጃዎችን ለማግኘት፣ከስር ባለው ሊንክ የቴሌግራም ቻናሉን join አድርጉ፣ለሌሎች ጋብዙ❗👇👇👇
http://t.me/ayuzehabeshaofficial
http://t.me/ayuzehabeshaofficial


ለቴሌግራም ተጠቃሚዎች የመረጃ አቦሸማኔ ልጠቀማችሁ❗❗
👉መረጃ ለማድረስ ቴሌግራም ተመራጭ እየሆነ ነው❗👇
ከአራቱም ማዕዘን በአቦሸማኔ ፍጥነት ጥርት ያሉ እና የተረጋገጡ መረጃዎችን በየደቂቃው የምታገኙበት ነው። የትም ያልተሰሙ ብዙ መረጃዎችን ስለምታገኙ Join አድርጉና ቤተሰብ ሁኑ።
👉ቻናሉን ብዙ ሰው ስለሚከታተለው ምርትና አገልግሎታችሁንም ብታስተዋውቁ ትጠቀሙበታላችሁ።
👇ከስር ባለዉ ሊንክJoin አድርጉ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s


በአዳባ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ7 ሰዎች ሕይወት አለፈ

በምዕራብ አርሲ ዞን አዳባ ወረዳ ኤጀርሳ ቀበሌ ትናንት ምሽት 2 ሰዓት አካባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሰባት ሰዎች ሕይወት አለፈ።

የምዕራብ አርሲ ዞን ትራፊክ ክፍል ሃላፊ ኮማንደር ከማል አማን እንዳሉት፤ አደጋው የደረሰው ከጉብሳ ወደ አዳባ እህል ጭኖ ሲጓዝ የነበረ ከባድ ተሽከርካሪ ፍሬን በጥሶ በመገልበጡ ነው።

በአደጋው ሹፌሩ፣ ረዳቱን እና ከላይ ተሳፍረው የነበሩ ሰዎችን ጨምሮ የሰባት ሰዎች ሕይወት ማለፉን ተናግረዋል።

በሁለት ሰዎች ላይም ከባድ ጉዳት እንደደረሰ ሃላፊው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል።

በመላኩ ገድፍ


በሞጆ ከተማ በደረሰ የእሳት አደጋ የአባትና የልጅ ህይወት አለፈ

በሞጆ ከተማ አስተዳደር ሉቦ መጋላ በተሰኘዉ አካባቢ በትናንትናው እለት ከቀኑ 6ሰዓት ገደማ በተከሰተ የእሳት አደጋ የአባትና ልጅ ህይወት ማለፉን ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ሰምቷል።
የሞጆ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ኮሚኒኬሽን ክፍል ሃላፊ ዋና ኢንፔክተር ነጋሽ ለገሰ ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት በባጃጅ አሽከርካሪነት ስራ ላይ የተሰማራዉ አባት በቤቱ ዉስጥም ቤንዚን ይሸጥ ነበር ብለዉናል።
ከስራ ገብቶ በእረፍት ላይ የነበረዉ አባት አዲሱ ቢራ የ 37 አመት ጎልማሳ ሲሆን ልጅ አብርሃም አዲሱ የ3 አመት ህጻን ነበር። ለአደጋዉ መንስኤ የሆነዉ ሁለት ጄሪካን ቤንዚን በቤት ዉስጥ እንዳለ እናት ምግብ ለማብሰል ለሞከረችበት ወቅት እሳቱ መነሳቱን ነግረውናል።
አደጋዉ ካጋጠመ በኋላ የሶስት አመት ልጁን ለማዳን ወደ እሳት ዉስጥ ገብቷል የተባለዉ አባት እርሱም ሆነ ልጁ ከፍተኛ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዉ በአዳማ ሃይለማርያም ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው በትናንትናው እለት ህወታቸዉ እንዳለፈ ማለፉን የሞጆ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ኮሚኒኬሽን ክፍል ሃላፊ ዋና ኢንፔክተር ነጋሽ ለገሰ ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።
በአደጋዉ እናት በሰዉነቷ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባታል የተባለ ሲሆን በህክምና ክትትል ላይ ትገኛለች ሲል ብስራት ሬዲዮ ነው የዘገበው።


ሰበር
ድሬደዋ የጎርፍ አደጋ ደርሶ በሰውና በንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል
(ዝርዝሩን ተመልሼ አቀርባለሁ)


📲 ስልክዎትን ለመቀየር ወይም አዲስ ለመግዛት አስበዋል 🤔?

አዳዲስ እንዲሁም በመጠኑ ያገለገሉ ስልኮችን ከተሟላ ዋስትና እና ጥገና ጋር ይዘን ቀርበናል📱ለበለጠ መረጃ ቻናላችንን ይጎበኙ

https://t.me/sellphone2777

📞 0929008292

📩 inbox @bina27

📍አድራሻ- ቦሌ ከሸገር ህንፃ አጠገብ

📨 ክፍለ ሀገር ላላቸሁ ደንበኞችቻችንም በ DHL መላክ ጀምረናል


📌 ላይመለስ ሄዷል | #ነፍስ_ኄር 💔 😢

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና የባህርዳር ከተማ አማካይ ስፍራ ተጫዋች የሆነው አለልኝ አዘነ ድንገተኛ ህልፈተ ህይወት ተሰምቷል ።

ለአርባምንጭ ታዳጊ ቡድን እስከ ዋናው ፤ ለሀዋሳ ከተማና ህይወቱ እስካለፈበት ጊዜ ድረስ ለባህርዳር ከተማ በሊጉ የሚጫወተው አለልኝ አዘነ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንም ጥሪ ተደርጎለት አገልግሎቱን ሰጥቷል ።

በቅርቡ በቅድስት ቤተክርስቲያን ስርአተ-ጋብቻዉን የፈፀመው ተጨዋቹ በጉዳት ምክንያት ከክለቡ ስብስብ ጋር ያልነበረ ሲሆን በትዉልድ ቦታው አርባምንጭ መጋቢት 18/2016 ዓ.ም ንጋት ላይ ህልፈተ ህይወቱ ተሰምቷል ።

የቀብር ስነስርዓቱም በዛሬው ዕለት በአርባ ምንጭ ከተማ እንደሚፈፀም ታዉቋል ። ለቤተሰቦቹ ፣ ለቡድን አጋሮቹ ፣ ለአድናቂዎቹ እንዲሁም ለመላው የስፖርት አፍቃሪ መፅናናቱን ይስጥልን ።

[ አሟሟቱን በተመለከተ የተለያዩ መረጃዎች እየወጡ ሲሆን '' #ራሱን_አጠፋ '' የሚለዉ ከሚወጡት መረጃዎች አንዱ እና ዋነኛው ነው ]


ከሚደርሱኝ ጥቆማዎች በመነሳት ማረጋገጥ የቻልኳቸው የቤት ፈረሳ መረጃዎች

- አያት ዞን አንድ ውስጥ ያሉ በርካታ 'ዘመናዊ' ሊባሉ የሚችሉ መኖርያ ቤቶች ስፍራው ለሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች ግንባታ ስለሚፈለግ ተነሱ እንደተባሉ፣ ባለፈው እሁድ እለት በመንግስት አካላት ስብሰባ ተጠርተው ይህ በይፋ እንደተነገራቸው አረጋግጫለሁ። ይህ በአካባቢው ቤቶችን የማንሳት ጉዳይ ቀጣይ እንደሆነም ታውቋል።

- በቦሌ ክ/ከተማ በተለምዶ ጉርድ ሾላ ንግድ ባንክ አካባቢ አስፓልት ዳር ያሉ የግል ቤቶች ተለክተው አንዳንዱ ቤት እስከ ሳሎኑ፣ አንዳንዱ ደግሞ እስከ መኝታ ቤት ድረስ እንዲፈርስ መደረጉ ታውቋል። እስከ ሳሎን ድረስ ብቻ በልኬት የፈረሰባቸው ቀሪውን መኝታ ቤታቸውንና ኪችናቸውን ዛሬ ለመሸፈን መግቢያና መውጪያ በራቸውን ሲሰሩ በድጋሜ አፍርሰውባቸው እንደገና ፍቃድ አውጡ እንደተባሉ ተረጋግጧል።

#AddisAbaba

Photo: File
ኤሊያስ መሰረት ያጋራው


ንግድ ባንክ የሲስተም ችግር ተጠቅመው ገንዘብ የወሰዱበትን ደንበኞች ስም ዝርዝር ለጥፏል!
ቀጣይ ካልመለሳችሁልኝ ፎቶ እለጥፋለሁ እያለ ነው!
ስማችሁን ቼክ አድርጉ!


ልዩ የቴሌግራም ቻናል ጥቆማ‼️👇
መረጃ ለማድረስ እንዲሁም ለመከታተል ቴሌግራም ተመራጭ እየሆነ ነው❗
ከሁሉም የሀገሪቱ ክፍል ያልተሰሙ እና አዳዲስ መረጃዎችን ለመከታተል ከስር ያለውን ሊንክ ተጭነው join በማድረግ ተከታተሉ።
ብዙ አዳዲስ መረጃዎችን ታገኛላችሁ እንዲሁም በቻናሉ ማስታወቂያ ብታሰሩ እጅግ አዋጪ ነው።
ቻናሉን ለማግኘት ከስር ያለውን ሊንክ ይጫኑ👇👇👇👇👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s


ዶዶላ ❗ አሳዛኝ ዜና‼️
በምዕራብ አርሲ ዶዶላ ከተማ ላይ ትላንት ማታ 3:00 አከባቢ የሸኔ ታጣቂዎች አንድ ካህንን ከእነቤተሰቡ እንዲሁም ካገባ ገና ሶስት ወር እንኳ ያልሞላውን ዲያቆን እና አብራው ስትኖር የነበራቸውን እህቱን በአሰቃቂ ሁኔታ ገድለዋቸው ሄደዋል ተብሏል።
ከሁለቱ ቤተሰቦች አጠቃላይ ሰባት ሰዎችን ገድለዋቸው ሄደዋል ብለዋል። አንድ ህፃን እንደ አጋጣሚ ያለቤተሰብ ቀርታ ተርፋለች ብለዋል። ከዚህ በተጨማሪ ለስራ ከሲዳማ ክልል የመጡ አራት ወጣቶችም ተገድለዋል ብለዋል። አጠቃላይ 11 ሰው ሞቷል ብለዋል።ጥቃቱ የተፈፀመው ከገብረክርስቶስ ቤተክርስቲያን 50ሜርቀት ላይ ነው ብለዋል። ግድያውን የፈፀሙት በቢለዋና በጥይት ነው ሲሉ የአዩዘሀበሻ ምንጮች ተናግረዋል(አዩዘሀበሻ)።
ነፍስ ይማር❗😥
ጥቆማ❗❗👇
👉 ፈጣን እና ያልተሰሙ መረጃዎችን ያግኙ፣ከስር ባለው ሊንክ join አድርጉ❗👇👇👇
http://t.me/ayuzehabeshaofficial
http://t.me/ayuzehabeshaofficial


እምጥ ይግቡ ስምጥ የማይታወቅ ደብዛቸው ለቀናት፣ ለሳምንታት ብሎም ለወራት የሚጠፋ ሰዎችን ዜና መስማት የተለመደ እየመሰለ ነው። ይህ ክስተት ባለፈው ወር ለሥራ ከቤታቸው የወጡ አንድ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ የፌደሬሽን ምክር ቤት አባል ላይ ጭምር መድረሱን ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ ወንድማቸው ነግረውናል።

DW


📲 ስልክዎትን ለመቀየር ወይም አዲስ ለመግዛት አስበዋል 🤔?

  አዳዲስ እንዲሁም በመጠኑ ያገለገሉ ስልኮችን ከተሟላ ዋስትና እና ጥገና ጋር ይዘን ቀርበናል📱ለበለጠ መረጃ ቻናላችንን ይጎበኙ

https://t.me/sellphone2777

📞 0929008292

📩 inbox @bina27

📍አድራሻ- ቦሌ ከሸገር ህንፃ አጠገብ

📨 ክፍለ ሀገር ላላቸሁ ደንበኞችቻችንም በ DHL መላክ ጀምረናል


ለውርስ ብሎ እናቱን የገደለው በቁጥጥር ስር ዋለ

በሐረሪ ክልል በሲጊቻ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ገንደ ሰመተር ተብሎ በሚጠራው መንደር ውስጥ ነዋሪ የሆኑት የገዳይ አጎት ሐሰን አብዱላሂ የተባለው የሟች ልጅን መሀመድ የሱፍን እናትህን ካልገደልካት የድርሻህን መሬት አልሰጥህም በማለቱ ወላጅ እናቱን ወይዘሮ መይረማ ሐሰንን በድንጋይ ሆዷ አካባቢ በመምታት ህይወቷ እንዲያልፍ አድርጓል።

በወቅቱ እናት ከወደቀችበት አንስተዋት ሆስፒታል ሲወስዷት ህይወቷ በማለፉ ገዳይ እዛው ሆስፒታል ጥሏት በመሠወሩ ፖሊስ ባደረገው ክትትል ከምሽቱ 2:00 ሰአት አካባቢ ገዳይና እንዲገድል ትእዛዝ የሰጠውን አጎቱን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እየተጣራባቸው መሆኑን ታውቋል ሲል የሀረሪ ፖሊስ ዘገባ ያሳያል


ደብረማርቆስ ‼️
በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረማርቆስ ከተማ በረቡ ገበያ መውጫ ቦሌ ሰፈር፣15ተኛ ሻለቃ አካባቢ እና ወደ ባህር ዳር መውጫ ጎተራ ሰፈር ዛሬ ከሰዓት ጀምሮ የተኩስ ልውውጥ መስማታቸውን ነዋሪዎቹ ገልፀውልኛል። በዚህ የተነሳ ሱቆችም ተዘጋግተዋል ብለዋል። በተለይ ቦሌ ሰፈር እስከዚህ ሰዓት ድረስ(12:36) ተኩሱ ይሰማል ብለዋል። ስለደረሰው ጉዳት አሁን ማወቅ አልተቻለም(አዩዘሀበሻ)።
ጥቆማ❗❗👇
👉 ፈጣን እና ያልተሰሙ መረጃዎችን ያግኙ፣ከስር ባለው ሊንክ join አድርጉ❗👇??👇👇
http://t.me/ayuzehabeshaofficial
http://t.me/ayuzehabeshaofficial

17 last posts shown.