Posts filter


በተለመዶ የጣራና ግድግዳ እየተባለ የሚጠራው የቤትና ቦታ ግብር ያለቅጣትና ወለድ የሚከፈልበት ጊዜ እየተጠናቀቀ በመሆኑ ግብር ከፋዮች ከወዲሁ እንዲከፍሉ ተጠየቀ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በተለመዶ የጣራና ግድግዳ እየተባለ የሚጠራ የቤትና ቦታ ግብር የሚከፍሉ ግብር ከፋዮች ግብሩ ያለቅጣትና ወለድ የሚከፈልበት ጊዜ እየተጠናቀቀ መሆኑን በመገንዘብ ከወዲሁ ግብራቸውን እንዲከፍሉ ተጠየቀ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የገቢ አወሳሰንና አሰባሰብ ዳይሬክተር አቶ ወንድማገኝ ካሳዬ እንደገለፁት በመዲናዋ 429 ሺህ 829 ግብር ከፋዮች የቤትና ቦታ ግብር ክፍያ እንዲፈፅሙ ይጠበቃል፡፡

ይሁንና እስካሁን ባለው ሂደት 228 ሺህ 222 ግብር ከፋዮች የቤትና ቦታ ግብር መፈፀማቸውን በመግለፅ ይህም የዕቅዱ 51 በመቶ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

አክለውም የቤትና ቦታ ግብራቸውን ከከፈሉ ግብር ከፋዮችም 2 ነጥብ 24 ሚሊዮን ብር መሰብሰቡን ተናግረዋል፡፡

የቤትና ቦታ ግብር በተለምዶ የአፈር፣ የቤትና ጣሪያ በሚሉና መሰል ስያሜዎች እስከ የካቲት 30 ድረስ የሚሰበሰብ የግብር አይነት መሆኑ ተገልጿል።


(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴዎድሮስ አድሀኖም ዛሬ ባደረጉት ንግግር የትራምፕን ውሳኔ ተችተዋል፡፡ ፕሬዘደንት ትራምፕ አሜሪካ ከጤና ድርጅቱ መውጣቷንና የምታደርገውን ድጋፍ ማቆሟን ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡

ዶክተር ቴዎድሮስ በድርጅቱ ስራ አስፈፃሚ ቦርድ ስብሰባ ላይ ባደረጉት ንግግር ‹‹በዚህ ውሳኔ እጅግ አዝነናል፡፡ አሜሪካ ይህንን መለስ ብላ እንደምታጤነው ተስፋ አለኝ›› ብለዋል፡፡ ትራምፕ በውሳኔያቸው ላይ የአለም ጤና ድርጅት ፈጣን የማሻሻያ እርምጃዎችን እንዳልወሰደ የጠቀሱ ቢሆንም ዶክተር ቴዎድሮስ ግን በዛሬ ንግግራቸው ‹‹የአለም ጤና ድርጅት ባለፉት ሰባት አመታት በታሪክ ውስጥ እጅግ ጥልቅና ሰፊ ማሻሻያዎችን አድርጓል›› ብለዋል፡፡

ትራምፕ ይህ ድርጅት ፍትሀዊ ባልሆነ ሁኔታ ከአሜሪካ ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚፈልግ ገልፀው የነበረ ሲሆን ዶክተር ቴዎድሮስ በበኩላቸው በዛሬ ንግግራቸው ሌሎች የገንዘብ ምንጮችንና ለጋሾችን ሲፈልጉ መቆየታቸውን ገልፀዋል፡፡

የኮቪድ ወረርሽኝን በተመለከተም ድርጅቱ አስፈላጊውን እርምጃ መውሰዱን ጠቅሰው በአሰራራቸው ላይ ፈተናዎችና ድክመቶች መኖራቸውን የገለፁት ዶክተር ቴዎድሮስ ድርጅታቸው ለሁሉም አገራት ያለማዳላት እንደሚሰራም መናገራቸውን ኤኤፍፒ ዘግቧል፡፡


Ads❗❗ ላልጀመራችሁ❗❗
የፈረንጆቹ 2025 ምርጡ ፕሮጀክት የተባለው stars❗
ይህ አዲስ ፕሮጀክት በቴሌግራም ባለቤቶች የተመሰረተ ነው። መስራት የምትችሉ እንዲሁም ክርፕቶከረሲን መለማመድ ለምትፈልጉ ጥሩ አጋጣሚ ነው።
መስራት ለምትፈልጉ ከስር በተቀመጠው ሊንክ "Start" በማለት ካሁኑ ስሩ👇👇👇
https://t.me/Stars_MeBot/stars?startapp=473382500


📌ልዩ የበዓል ቅናሽ
⚡️#ቦሌ አዲሱ ስታዲየም ፊት ለፊት

➯ 60% ለከፈለ 40% በነፃ!!!
በካሬ 59,910 ብር

➯ 40% ለከፈሉ --20%ቅናሽ
79,950 ብር በካሬ

❤️3 መኝታ 145 ካሬ = 8,686,950 ብር ብቻ

📍ቦሌ አዲሱ ስታዲየም ፊት ለፊት ላይ እጅግ ዘመናዊ የመኖሪያ አፓርትመንቶችን ይዞላችሁ መቷል

📌የካሬ አማራጭ
👉90 ካሬ ባለ 1 መኝታ (5,391,900 ብር)
👉105 ካሬ ባለ 2 መኝታ (6,290,550 ብር )
👉110 ካሬ ባለ 2 መኝታ (6,590,100 birr)
👉140 ካሬ ባለ 3 መኝታ (8,387,400 ብር )
👉145 ካሬ ባለ 3 መኝታ (8,686,950 ብር )

💥 ለበለጠ መረጃ # 0972707205

Telegram- @Realestateconsult12

Whatsapp- https://wa.me/0946404247?text


ሰበር ዜና

ክቡር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚደንት ሆነው ተመረጡ።

ሦስተኛ ቀኑን የያዘው የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ክቡር ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) በ ከፍተኛ በሆነ ድምጽ መርጧቸዋል። ተመራጩ የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት በጉባኤተኛው ፊት ቃለ መሀላ ፈጽመዋል።

በተያያዘ ዜና ጉባኤው ክቡር አቶ ተመስገን ጥሩነህን እና ክቡር አቶ አደም ፋራህን የፓርቲው ምክትል ፕሬዚደንቶች አድርጎ እጅግ ከፍተኛ በሆነ ድምጽ መርጧል።

ሁለቱ ምክትል ፕሬዚደንቶች በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት በጉባኤተኛው ፊት ቃለ መሀላ ፈጽመዋል።


#ፒያሳ ሱቅ ሽያጭ #ከቴምር ሪልስቴት
👉3.9ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ900,000ብር 4ተኛ እና 5ተኛ
👉4.2ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.2ሚሊዮን 3ተኛ
👉4.8ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.5ሚሊዮን 2ተኛ
👉5.5ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2ሚሊዮን 1ኛ
👉 7ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2.8ሚሊዮን ግራውንድ በውስጥ በኩል
👉10ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 4ሚሊዮን ግራውንድ በውጪ በኩል
+251939770177
+251996856273


የብልጽግና ፓርቲ በሦስተኛ ቀን የጉባዔ ውሎው የፓርቲውን ፕሬዚደንትና ምክትል ፕሬዚዳንቶች ምርጫ በማካሄድ ላይ ይገኛል።


በአሜሪካ ፊላዴልፊያ የአውሮፕላን አደጋ ደረሰ። ታካሚን ይዞ እየሄደ ያለ አውሮፕላን መሀል ከተማ ውስጥ ወደቆ ነው የተከሰከሰው። በሳምንት ውስጥ ሁለተኛው አደጋ ነው። በዋሽንግተን ሄሎኮፍተርና የመንገደኞች አውሮፕላን ተጋጭተው 60 ሰዎች መሞታቸው የሚታወስ ነው። በዚህ አደጋ የሞቱት ብዛት እየተጣራ ነው።


ግጭት እንዳይነሳ የሰጉ የሽረ ከተማ ነዋሪዎች ገንዘባቸው ከባንክ እያወጡ ነው ‼️
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

የህወሓት ወታደራዊ አመራሮቹ ውሳኔ ተከትሎ ደግሞ ግጭት እንዳይነሳ የሰጉ የሽረ ከተማ ነዋሪዎች ገንዘባቸው ከባንክ እያወጡ ይገኛሉ ።


በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሰዎች ለቅሶ እና ገበያ ሲሔዱ ጭምር እየታገቱ እንደሚገኙ ነዋሪዎች ተናገሩ

ከአንድ ሳምንት በፊት ከደብረልባኖስ አከባቢ ወደ ያያ ጉሌሌ ለገቢያ ሲጓዙ የነበሩ አንድ ተሽከርካሪ ሙሉ 50 ሰዎች ግድም የሚሆኑ ነጋዴዎች ሳዲኒ ብዮ በሚባል የያያ ጉሉለ ወረዳ ታፍነው እንደተወሰዱ እስካሁን አለመመለሳቸውን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።

በተለያዩ ጊዜያት አደባባይ ወጥተው ተፋላሚዎች ሰላም እንዲያወርዱ በአከባቢቸው ህዝቡ መማጸኑን የሚስታውሱት ነዋሪ አሁን ላይ ያ ሁሉ ተማጽኖ መና ቀርቶ አስገድዶ ስወራ እና እገታዎች በታጠቁ አካላት ስለሚፈጸሙ የአከባቢው ነዋሪዎች ገቢያ እና ለቅሰው ለመውጣት የሚሰጉበት አስቸጋሪ ያሉት ሁኔታ መፈጠሩን አስረድተዋል፡፡

“ታጣቂዎች በየቦታው ሰው ይወስዳሉ” የሚሉት አስተያየት ሰጪዋ በተለይም ሰው ገቢያም ሆነ ለቅሶ እንኳ ለመሄድ ስጋት እንደሚገባው አስረድተዋል፡፡

አንድ የአከባቢው ነዋሪ በዚህን ወቅት ከከተማ በመራቅ መንቀሳቀሱ ስጋት እንደሚፈጥር አስረድተው ማህበረሰቡ እለት በእለት ስጋት ወሮት እንደሚኖርም መግለጻቸውን የጀርመን ድምጽ አስደምጧል።

“በገጠር እውነት ለመናገር እንጀራ እንኳ መሶቡ ውስጥ የሚያድርለት ሰው ማግኘት ይከብዳል፤ የትኛውም ጉልበተኛ ይገባል በልቶ ይወጣል፤ ጋግሮ ልጆቹን እንዳይመግብ ሌማቱን ገልብጦ ባዶ የሚያስቀረው አካል ስላለ ይህን ሁሉ ስቃይ ህዝቡ የሚናገርበት መድረክም ሆነ ቦታ የለውም” ሲሉ ሌላኛው አስተያየት ሰጪ መናገራቸውንም ዘገባው አካቷል።

በመንግስት የጸጥታ ሃይልም ሆነ በአከባቢው በሚንቀሳቀሱ ታጣቂው ሃይሎች ስልክ ስለሚለቀም ስልክ ይዞ የሚንቀሳቀስ ሰው በገጠር አይገኝም ያሉት አስተያየት ሰጪው መረጃ እንኳ መለዋወጥ አዳጋች ሆኖ ህዝቡ ከዚህ በፊት ሲኖር ከነበረው ሃምሳ ኣመት ወደ ኋላ ተመልሶ እየኖረ ነው ብለዋል፡፡


በአዲስ አበባ ፖሊስ "ለጥያቄ ትፈለጊያለሽ?" በሚል ተወስዳ የታሰረችው ምሥራቅ ተረፈ ላይ ፖሊስ የ7 ቀናት የምርመራ ጊዜ መጠየቁ ተሰማ

ፖሊስ፣ ምሥራቅን አዲስ አበባ፣ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ ችሎት እንዳቀረባት፣ ፍርድ ቤቱም ፖሊስ ያቀረበውን ጥያቄ በመቀበል፣ "ምርመራውን አጠናቆ እንዲያቀርባት" በሚል ለጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም ቀጠሮ መስጠቱን ተከትሎ፣ ምሥራቅ አሁን በአዲስ አበባ ፖሊስ እስር ላይ እንደምትገኝ ወዳጆቿ ገልጸዋል።


ገጣሚ እና የጦቢያ ግጥም በጃዝ ፕሮግራም አዘጋጅ ምስራቅ ተረፈ ለእስር ተዳረገች

(መሠረት ሚድያ)- ገጣሚ እና የጦቢያ ግጥም በጃዝ ፕሮግራም አዘጋጅ ምስራቅ ተረፈ ትናንት ጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም በፖሊስ ለጥያቄ ትፈለጊያለሽ ተብላ ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እንደተወሰደች ታውቋል።

የመሠረት ሚድያ ምንጮች እንደጠቆሙት ምስራቅ ዛሬ ጥር 23 ቀን 2017 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ ፖሊስ ምርመራ ለማጣራት ጊዜ እንዲሰጠው ፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት አቅርቧት ፍርድ ቤቱ ፖሊስ ምርመራውን አጣርቶ እንዲያቀርብ 7 ቀን በመስጠት ለጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም ቀጠሮ ሰቷል፣ ምስራቅ ተረፈ ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ተመልሳለች።

ምስራቅ የኪነጥበብ ምሽቶችን በሀገር ውስጥ እንዲሁም በውጭ ሀገራት በማዘጋጀት እንዲሁም የራሷን ግጥሞች በማቅረብ በብዛት ትታወቃለች።

እንደ ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ እና ገጣሚ ትእግስት ማሞ ያሉ የደመቁባቸውን ዝግጅቶች በማሰናዳት የምትታወቀው ግለሰቧ ግጥም፣ መነባንብ፣ ዲስኩር እንዲሁም ጥበብ እና ጥበብ ነክ ስራዎች ይበልጥ እንዲለመዱ እንደለፋች ብዙዎች ይናገራሉ።

ገጣሚ ምስራቅ አሁን ላይ የታሰረችበት ምክንያት ምን እንደሆነ ግልፅ እንዳልሆነ ታውቋል።

መረጃን ከመሠረት!


ፍትህ ለሲምቦ ብርሃኑ

ሲምቦ ብርሃኑ ትባላለች የ8 አመት ታዳጊ ስትሆን ነዋሪነቷ በምዕራብ ሸዋ ሜታ ወልቂጤ ወረዳ ሲሆን የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ከተፈፀመባት በኋላ ህይወቷ ሲያልፍ አስክሬኗን ሰቅለው ሄዷል። ለታዳጊዋ ሲምቦ ብርሃኑ ፍትህ እየተጠየቀ ይገኛል።
የሚያንገበግብ ወንጀል 😢


ዋሽግተን-ትራምፕ በBRICS አባል ሐገራት ሸቀጦች ላይ 100% የግብር ጭማሪ ለማድረግ ዛቱ

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ የBRICS አባል ሐገራት የአሜሪካዉን ዶላር ትተዉ በሌላ ገንዘብ ለመገበያየት ከወሰኑ ለዩናይትድ ስቴትስ ገበያ በሚያቀርቡት ሸቀጦቻቸዉ ላይ የ100% የቀረጥ ጭማሪ ለማድረግ ዛቱ።ትራምፕ Truth Social በተባለዉ የማሕበራዊ መገናኛ ዘዴያቸዉ ባሠራጩት ማስጠንቀቂያ እንዳሉት የBRICS አባል ሐገራት ከዶላር ለማፈንገጥ ማሰባቸዉ «ማብቃት አለበት።» ትራምፕ የBRICS አባል መንግሥታትን ለዩናይትድ ስቴትስ «የጠላትነት አዝማሚያ» የሚታይባቸዉ በማለት ወርፈዋቸዋልም።እነዚሕ ሐገራት፣ ትራምፕ «ግዙፍ» ያሉትን የአሜሪካን ዶላር ለመተካት አዲስ ገዘብ ካሳተሙ ወይም በሌላ ገንዘብ ለመጠቀም ከወሰኑ ከአሜሪካ ገበያ መሰናበት አለባቸዉ።ትራምፕ እንደሚሉት መስተዳድራቸዉ ወደ አሜሪካ በሚገቡ የየሐገራቱ ሸቀጦች ላይ የ100% የቀረጥ ጭማሪ ያደርጋል።ቡድኑን በመሠረቱት አምስት ሐገራት ስም የመጀመሪያ ፊደላት ተገጣጥሞ BRICS ተብሎ የሚጠራዉ ቡድን ባሁኑ ወቅት 10 አባል መንግስታትን ያስተናብራል። BRICS በኢንዲስትሪ የበለፀጉትን 6 ምዕራባዉያን ሐገራትና ጃፓንን የሚያስተናብረዉ ቡድን 7 የሚያደርሰዉን ተፅዕኖ ለመቋቋም ያለመ ነዉ። ሩሲያና ቻይናን የመሳሰሉ የBRICS ጠንካራ አባላትና መሥራቾች የአሜሪካ ዶላር በዓለም ገበያ ላይ የሚያደርሰዉን ጫና አጥብቀዉ ይተቻሉ።ማሕበራቸዉ አማራጭ መገበያያ እንደሚያስፈልገዉም ያሳስባሉ።የአሜሪካዉ ፕሬዝደንት ግን ዶላርን መተካት «አስደናቂ» ከሚሉት ከአሜሪካ ምጣኔ ሐብት መሰናበት ነዉ።


በአዳዲሶቹ ሳይቶቻችን መሪ 1 ፣ አያት ዞን 3 እና ዞን 8

ከባለ 1-4 መኝታ አፓርትመንት ቤቶችን ከ 2ኛ ፎቅ ጀምሮ በ 8% ቅድመ ክፍያ ብቻ ለሽያጭ አቅርበናል ።
እንዲሁም ግንባታቸው ከ 85% በላይ የደረሱ አፓርትመንት ቤቶችን በአያት ባቡር ጣቢያ ፣በሲኤምሲ ሚካኤል እና

በአያት ዞን 8 የሚገኙ ሳይቶቻችን በ 25% ቅድመ ክፍያ ብቻ
እየሸጥን እንገኛለን።

ለሳይት እና ቢሮ ጉብኝት ይደውሉ
☎️0942585355
"አያት ዞሮ መግቢያዬ"


(ዘ-ሐበሻ ዜና) የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የብሪክስ አባል ሀገራት የአሜሪካ ዶላርን በሌላ የመገበያያ ገንዘብ እንዳይተኩ፣ እንዳይሞክሩትም ዛሬም እንደገና አስጠነቀቁ::

ትራምፕ ዛሬም በማህበራዊ ሚዲያቸው በፃፉት መልዕክት "ሀገራቱ የአሜሪካን ማስጠንቀቂያ ወደ ጎን በመተው በዓለም አቀፍ ገበያ ዶላርን መጠቀም የሚያቆሙ ከሆነ 100% ቀረጥ ይጣልባቸዋል:: ይህን የሚሞክር ማንኛውም ሀገር ካለ 'ሄሎ ታሪፍ' እያለ፣ [የ]አሜሪካን [ገበያ] ይሰናበት" ብለዋል::


📌ልዩ የበዓል ቅናሽ
⚡️#ቦሌ አዲሱ ስታዲየም ፊት ለፊት

➯ 60% ለከፈለ 40% በነፃ!!!
      በካሬ 59,910 ብር

➯ 40% ለከፈሉ --20%ቅናሽ
      79,950 ብር በካሬ

❤️3 መኝታ 145 ካሬ = 8,686,950 ብር ብቻ

📍ቦሌ አዲሱ ስታዲየም ፊት ለፊት ላይ እጅግ ዘመናዊ የመኖሪያ አፓርትመንቶችን ይዞላችሁ መቷል

📌የካሬ አማራጭ
👉90 ካሬ ባለ 1 መኝታ (5,391,900 ብር)
👉105 ካሬ ባለ 2 መኝታ (6,290,550 ብር )
👉110 ካሬ ባለ 2 መኝታ (6,590,100 birr)
👉140 ካሬ ባለ 3 መኝታ (8,387,400 ብር )
👉145 ካሬ ባለ 3 መኝታ (8,686,950 ብር )


💥  ለበለጠ መረጃ   #  0972707205

Telegram- @Realestateconsult12

Whatsapp- https://wa.me/0946404247?text


ቀሲስ በላይ መኮንን በ5 ዓመት ጽኑ እስራትና በ10 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ተቀጡ

የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በእነ ቀሲስ በላይ መኮንን መዝገብ ላይ የቀረቡ የግራ ቀኝ ማስረጃዎችን መርምሮ በዛሬው የችሎት ቀጠሮ በጽኑ እስራትና በገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወሰነ።

የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በተከሳሾች ቀሲስ በላይ መኮንን፣ በግብርና ኢንቨስትመንት ላይ የተሰማራው እያሱ እንዳለ፣ በኮሚሽን ስራ ላይ የተሰማራው በረከት ሙላቱ እና አለምገና ሳሙኤል እንዲሁም የኒሞና ንግድ ስራ ኃላ/የተ/የግል ማህበር ስራ አስኪያጅ አበራ መርጋ በተባሉ ተከሳሾች ላይ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ ቁጥር 32 ንዑስ ቁጥር 1 (ሀ) እና የሙስና ወንጀሎች ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 32 ንዑስ ቁጥር 2 እና ንዑስ ቁጥር 3 ስር የተመለከተውን ድንጋጌ እና በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ ቁጥር 382 ንዑስ ቁጥር 1 ስር የተመለከተውን ድንጋጌ መተላለፋቸውን ጠቅሶ ዝርዝር ክስ አቅርቦባቸው ነበር።

በዚህም ተከሳሾቹ ከአፍሪካ ህብረት ምንም አይነት የክፍያ ትዕዛዝ ባልተሰጠበት ሁኔታ ላይ ተከሳሾች በተለያየ መጠን ክፍያ እንዲፈጸምላቸው የሚል አጠቃላይ የ6 ሚሊየን 50 ሺህ ዶላር ሀሰተኛ የክፍያ ሰነድ በአንደኛ ተከሳሽ አማካኝነት ለባንኩ መቅረቡ ተጠቅሶ በሁሉም ተከሳሾች ላይ ከባድ የማታለል ሙስና ወንጀል ክስ ማቅረቡ ይታወሳል።


🚨 𝐎𝐅𝐅𝐈𝐂𝐈𝐀𝐋: (ዘ-ሐበሻ ዜና) በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ በሚገኘው ፖቶማክ ወንዝ 64 ሰዎችን የጫነ ንብረትነቱ የአሜሪካ አየር መንገድ የሆነ አውሮፕላን እና 3 ወታደሮችን የጫነ የጦር ሂሊኮፕተር መጋጨታቸውን ተከትሎ በተፈጠረው አደጋ ዙሪያ፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ስለአደጋው ሙሉ በሙሉ ገለጻ እንደተደረገላቸው ምሽቱን በሰጡት መግለጫ ገለጹ። "እግዚአብሔር ነፍሳቸውን ይማር" ሲሉ የጀመሩት ትራምፕ "በመጀመሪያ ምላሽ ሰጪዎቻችን እየሰሩት ላለው አስደናቂ ስራ እናመሰግናለን፣ ሁኔታውን እየተከታተልኩ ሲሆን ተጨማሪ ዝርዝር መረጃዎችን እሰጣለሁ" ብለዋል።

ትራምፕ የአደጋው መንስኤ ምን እንደሆነም ጥያቄ አንስተው "ይህ መፈጠር ያልነበረበት መጥፎ ሁኔታ ነው... ጥሩ አይደለም!!!" ብለዋል።
የአደጋው መንስኤ በትክክል ምን እንደሆነ ተጣርቶ በሚመለከታቸው ባለስልጣናት ይነገራል። እስካሁን ነፍስ ለማዳን እየተደረገ ባለው ጥረትም የ18 ሰዎች አስከሬን እንደተገኘ ከዚህ ቀደም ባቀረብነው መረጃ ላይ መግለጻችን ይታወሳል።
#NewsUpdate #americanairlines #Trump #newsusa


በአቶ መለስ ዜናዊ ዘመነ መንግስት የሚኒስትሮች ካቢኔ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ብርሃኑ አዴሎ ገብረማርያም ለኢትዮጵያ ሰብለአዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነርነት ለመሰየም ዛሬ ጥር 22 ቀን 2017 ዓም ቀርበዋል። ሌሎች አራት ተወዳዳሪዎችም መቅረባቸው ታውቋል።

20 last posts shown.