Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Religion


ትክክለኛው ኢስላማዊ አስተምህሮ፦
1) ከቁርኣን፣
2) ከሐዲሥ፣ [በሰለፎች አረዳድ]
3) ከታማኝ ዑለማዎችና
4) ከትክክለኛ ቂያስ ተጠናቅሮ ይቀርብበታል።
√ አዳዲስና ወቅታዊ ኢስላማዊ የሆኑ ጉዳዮችም ይዳሰሳሉ።
√ አላማዬ በዲኔ ላይ ያለውን የመረጃ ክፍተት መሙላት ነው።
ማንኛውም አስተያዬት ሲኖራችሁ @Murad_Tadesse ላይ አስፍሩት።
ስህተትም ባያችሁ ጊዜ አርሙኝ።
ጀዛኩሙል`ሏህ ኸይራ!

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Religion
Statistics
Posts filter


በሌላ ሰው ስም በአዲስ ፈቃድ በአዲስ ስም ትመለሳለች እንዲህ እያለች ትቀጥላለች ..... በእርግጠኝነት ይቺ ሴትዮ በጊዜ በህግ ቁጥጥር ውስጥ ካልዋለች ገና ብዙ ግፍ እናም ማጭበርበሮች እንሰማለን! ብዙ ጊዜ የእሷ ድርጅት መሆኑ የሚረጋገጠው ነገሩ ከተበላሸ በሗላ ነው። ሲበዛ በብዙ ሌብነት የተካነች አደገኛ ሴት ናት። ነገሩን ስላቅ የሚያደርገው ደግሞ ምርጥ ስራ ፈጣሪ ሴት ተብላ መሸለሟ እናም በዚሁ ዘርፍ አገራችንን ወክላ ደቡብ አፍሪካ ድረስ ሂዳ መሳተፏ ነው። ሌላው ደግሞ በጣም ያስገረመኝ እናም ያሳዘነኝ ነገር እኔ በተጭበረበርኩበት ድርጅት ባይሆንም ከታች ከጠቀስኳቸው ድርጅቶች በአንዱ የተጭበረበሩ ተበዳዮች በሜን ስትሪም ሆነ በፖድካስት ሚድያ ቀርበው አቤት ብለው እንኳን ምንም እርምጃ አለመወሰዱ ነው። የብዙ ጊዜ ዛቻዋም "ክስ አያዋጣችሁም ትጎዳላችሁ" ነበር። እየሆነ ያለውም ይሄው የእሷ ቃል ይመስላል። በርግጥ እኔ በግሌ ምንም የቀረኝ ነገር አልነበረም እናም ወደ አዲስ አበባ መምጣትም ሆነ ክስ መመስረት የምችልበት አቅሙ ስለሌለኝ ለጊዜው እየደወልኩ ፣በመልዕክት እናም በቮይስ ከመለመን ውጭ እስካሁን የሞከርኩትም ሆነ ያደረግኩት ነገር የለም። እሱ የሚኖሩ አብዛኞቹ ተበዳዬች ግን በብዙ እየደከሙ እንደሆነ አውቃለሁ እስካሁን መፍትሄ ባያገኙም። ከእነዚህ ድርጅቶች ውስጥም እኔ በግሌ የደረስኩባቸው የድርጅት ስሞች፦
1,ኢትዮ ኤርስ ንግድና ኢንቨስትመንት ሃ/የተ/የግ/ማ
2,ሩቢ ቪዛ ኮንሰልታንሲ ሶሉሽን
3,ኤ አይ ኤም አልትራ ኢዱኬሽን ኮንሰልታንሲ
4,ካባ ሆልዲንግ ካምፓኒ
5,የሎው ካርድ ኮንሰልታንሲ
6,ፔስኮ ፔስት ሶሉሽን
7,ጆፕሊንክ ማንፓወር ሶሉሽን......
ከሌሎች ተበዳዮች ባገኘሁት መረጃ ድርጅቶች ከ12 በላይ እንደሆኑ ነው የሰማሁት(ያረጋገጥኩት ባይሆንም)
እነዚህን ድርጅቶች በሚድያ የሚያስተዋውቁላቸው ደግሞ በህዝብ ዘንድ ተፅዕኖ ፈጣሪ እና ተሰሚነት ያላቸው አርቲስቶች ናቸው። ከእነዚህም ውስጥ
1, አርቲስት? ዳናይት መክብብ
2,አርቲስት ሩታ መንግስተኣብ
3,አርቲስት አምለሰት ሙጬ
4,አርቲስት ሙሉዓለም ታደሰ
5,ቲክታከር ዩቲ ናስ
5,ቲክታከር ፊዮና....
እነዚህን ድርጅቶች የሚዘውሩ ግለሰቦች ደግሞ፦
1,ቤተልሄም ታደሰ ይማም
2,ገሊላ በለጠ ሳህሉ
3,በለጠ ሳህሉ
4,አቤል ተስፋዬ አሻግሬ
5,ሩት መኮንን
6, ዳዊት በለጠ
7,እዮሲያስ ታደሰ ይማም እናም ሌሎች
በአጠቃላይ የቤተሰብ የማፍያ ኢምፓየር ነው እየገነቡ ያሉት።
እናም በሚመለከተው አካል ተጣርቶ ተገቢውን እርምጃ እንዲወሰድ እጠይቃለሁ! ለቀጣይም መሰል ማጭበርበሮች እንዳይፈፀሙ እኛም ተበዳዬች ፍትህ እንድናገኝ ማንኛውም ጋዜጠኛ፣ አክቲቪስት እና ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች እባካችሁን በምትችሉት ሁሉ ይሄን መረጃ ይመለከተዋል ለምትሉት የመንግስት አካልም ሆነ ተቋም አድርሱልን! ይሄ የግለሰብ ችግር አይደለም የብዙ ገንዘባቸውን ፣ተስፋቸውን እናም እድሜያቸውን ሳይቀር መሀል አዲስ አበባ ላይ ህጋዊ ፈቃድ ባላቸው ህገ ወጥ ሰዎች የተጭበረበሩ ወጣቶች ድምፅ ነው!
ፎቶዋን አስተያየት መስጫው ላይ አስቀምጣለሁ የሰው በደል የሚሰማችሁ እናም የምትኖርበትን አካባቢ የምታውቁ በውስጥ መስመር አሳውቁኝ»

ትላለች! (የሴት ፎቶ ስለሆነ ትቼው ነው።)

4.3k 0 14 14 53

ተው! አትመኑ አላልኩም?

እስኪ ይህን ጽሑፍ አንብቡት!

አብዛሃኛው ቲክቶከር፣ አርቲስትና ተከታይ ያለው ገፅ ዳጎስ ያለ የማስታወቂያ ገንዘብ ከተከፈለው መረጃ አያጣራም፤ ዝም ብሎ እውነታውንም ፌኩንም አግበስብሶ ያስተዋውቃል እንጂ «የት አለ ፈቃዳችሁ? የት አለ እውቅናችሁ? እስከየት ድረስ ነው እርግጠኝነቱ?» ብሎ እስከ ጥግ አያጣራም።

እስኪ አንብቡ…

«መሀል አዲስ አበባ ላይ ህጋዊ ፈቃድ አውጥተው ከ600 በላይ ወጣቶችን ያጭበረበሩ እና እያጭበረበሩ ያሉ የከተማችን ማፍያዎች!

መጋቢት 2014 ከ14 አመት በላይ የኖርኩባትን አዲስ አበባን ለቅቄ ወደ ቤተሰቦቼ ክፍለ ሀገር ተመለስኩ። ምክንያቴም ባለኝ የስራ ልምድ እና እውቀት ሰርቼ ራሴን መቀየርም ሆነ ማኖር ስለከበደኝ ነበር። እናም ወደ ክፍለሀገር ተመልሼ እንደነገሩ የግል ስራ ጀምሬ ሁለት ዓመት አካባቢ ሰራሁ። ግን እዚህም አንድም በሰላም እጦቱ(በጦርነቱ) ሲቀጥል ከአካባቢው ሰው(ምንም እንኳን የተወለድኩበት አካባቢ ቢሆንም) ጋር ለመግባባት በመቸገሬ ነገሮች እንዳስብኩት ቀላል አልሆኑልኝም። ከአዲስ አበባ አንፃር ሳየው እዚህ ቢያንስ ስለቤት ኪራይ እናም ስለአስቤዛ ባላስብም ግን ስለነገዬ አለማሰብ አልቻልኩም ነበር እናም ዝም ብሎ መኖር ሲደክመኝ ከአገር ስለመውጣት ማሰብ ጀመርኩ።ወጥቼ
አምስት ስድስት ዓመት ሰርቼ እመለስ እናም እዚህ የተሻለ ኑሮ እኖራለሁ ቢያንስ በምን እኖራለሁ? የሚለውን ጥያቄ በሚገባ እመልሳለሁ በሚል ወደ ውጭ የሚልኩ ኤጀንሲዎችን ማፈላለግ ጀመርኩ። መጀመሪያም ለክትትል እንዲመቸኝ ያለሁበት አካባቢ ነበር ያፈላለኩት ነገር ግን በሰዓቱ እዚህ ያገኘኋቸው ኤጀንሲዎች ላይ እምነት ማሳደር አልቻልኩም ነበር። ምክንያቱም አብዛኞቹ አንድ ጠባብ ክፍል ቢሮ ተከራይተው በዛ ላይ አንድ ሰራተኛ ብቻ ይዘው ነው እየሰሩ የነበረው።እናም ነገ ስመለስ ቢሮው ተዘግቶ ባገኘውስ? በሚል ፍራቻ የዚህን ሀሳብ ዘግቼ ወደ አዲስ አበባ ተመለስኩ። ከዚህ ከመነሳቴ በፊት "የሆነ አሪፍ አማካሪ ድርጅት አለ አሪፍ ነው የድርጅቱ ባለቤት በጣም ሰፊ ኔትወርክ ያላት ናት ። የእነ.....እህትም እዚያው ነው የምትሰራው" ብለው ድርጅቱ ውስጥ የምትሰራ(ሴልስ) እናም የምኖርበት ከተማ ልጅ ስልክ ሰጥተውኝ ነበር እናም ደውዬ ሳናግራት "ብዙ አማራጮች አሉን ቢሮ መጥተህ አናግረን" አለችኝ። ይሄን እንደ አንድ እናም የተሻለ አማራጭ ይዤ ወደ አዲስ አበባ ተመለስኩ። በጊዜው አራት ኪሎ አምባሳደር ህንፃ ወደነበረው ቢሯቸው ስገባም በዓይኔ ያየሁት ነገር ከሴልሶች በላይ የማሳመን ብቃት ነበርው። የቢሯቸውን የውስጥ ዲዛይን ውበት እናም ስፋት ሳይ መቼም የሚዘጋ(ስጋቴ ዘግተው ይጠፋሉ የሚል ስለነበር) መስሎ አልተሰማኝም ነበር። በዛ ላይ የጠቅላይ ሚንስተር ዶ/ር አብይ አህመድን እና የቀድሞ ፕሬዝዳንት የነበሩትን ሳህለወርቅ ዘውዴን ፎቶ በትልልቅ ፍሬም አሰርተው ፊት ለፊት ሰቅለው ነበር ይሄም ለእነሱ አንድ ማሳመኛ መንገድ ነበር። ተሳክቶላቸዋልም። በድርጅቱ ስም አንዳንድ መረጃ ድህረ ገፅ ላይ ስፈልግም ትልልቅ እናም ተፅዕኖ ፈጣሪ አርቲስቶች ሲያስተዋውቁት አየሁ እናም የበለጠ እምነት አደረብኝ። ከምንም በላይ ይሄን ድርጅት እንድመርጥ ያደረገኝ ደግሞ በሰዓቱ በአንዴ ሙሉ ክፍያ ከፍዬ የምሄድበት አቅሙ ስላልነበረኝ እናም እነሱ ጋር በዱቤ በመሆኑ ነበር። "ከ10% እስከ 25% ቅድመ ክፍያ ብቻ ከፍለው ቀሪውን የሚሄዱበት አገር እየሰሩ ይከፍላሉ" ስለተባልኩ በ25% vip አማራጭ 167,750(አንድ መቶ ስልሳ ሰባት ሺ ሰባት መቶ አምሳ) ብር ከፍዬ ውል የተዋዋልኩት። ከዛ በኋላ "የስራ ፍቃድ መጥቶላችኋል እናም ለጊዜው ገንዘብ ስላጠረኝ ነው ፕሮሰሳችሁ ቶሎ እንዲያልቅላችሁ....." እያለች በተለያዬ ጊዜ ከመጀመሪያ ውላችን ውጭ ብዙ ገንዘብ አስከፍላናለች። መክፈል ያልቻለ refound ሞልቶ ገንዙቡ ተመላሽ እንዲሆለት መጠበቅ ጀመረ። ገንዘባቸውን ባያገኙም ቅሉ። በብድርም ሆነ ንብረት ሽጠን መክፈል የቻልን ደግሞ የጠየቀችንን ገንዘብ በሙሉ ብንከፍልም መጨረሻ ላይ "አልተሳካም" አለችን። እኔ በግሌ በaim ultra education consultancy 586,000(አምስት መቶ ሰማንያ ስድስት ሺ) ብር ከፍያለሁ። ምንም ቪዛ ባልተመታበት ሁኔታ የአየር ቲኬት፣ የኮቴ እናም የትራቭል ኢንሹራንስ በሙሉ አስከፍላናለች። ለአንድ ዓመት ያክል ፕሮሰሱን ስከታተል የነበረው ደግሞ ከክፍለ ሀገር በፕሌን(በጦርነት ምክንያት የየብስ ትራንስፖርት ዝግ ስለነበር) እየተመላለስኩ ነበር በዚህም ለፕሌን እናም ለአልጋ ከ120,000(ከአንድ መቶ ሀያ ሺ)ብር በላይ አውጥቻለሁ።ሌሎች ከ600-1000 የሚደርሱ(ትክክለኛ ቁጥሩን ማወቅ ያልቻልኩ) ተበዳዬችም aim ultraን ጨምሮ በተመሳሳይ ግለሰቦች በሚዘወሩ እናም በተለያዩ ድርጅቶች ከ40,000(አርባ ሺ) እስከ 800,000(ስምንት መቶ ሺ) እናም ከዛ በላይ ተበልተዋል። በዚህ የማጭበርበር ተግባር ምክንያት የሰው ህይወት ጠፍቷል፣ ትዳር ፈርሷል፣ ቤተሰብ ተበትኗል የብዙ ወጣቶች ህይወት ሲዖል ሁኗል! እኔ ፕሮሰሱን ስጀምር ቢያንስ 200,000 ብሩ የራሴ ገንዘብ ነበር። ሌላው በተለያዬ መንገድ የተቀበልኩት የቤተሰብ፣ የጓደኛ ፣ብሎም የእቁብ ብር ስለነበር ይሄንን መመለስ ባለመቻሌም ከቤት የመውጣት ሞራል አጣሁ! ስለእውነት አሁን ላይ ሙሉ ገንዘቤን ብትመልስልኝ እንኳን የማልሸፍነው እዳ ውስጥ ገብቻለሁ። ብዙ ነገር አጥቻለሁ። ከቤተሰብ ጋር ተቆራርጫለሁ! ገንዘብ በሰጡኝ ሰዎች ፊት አንገቴን ለመድፋት ተገድጃለሁ! "ከአልጋ ላይም ለመነሳት ተስፋ ያስፈልጋል" እንዲል አዳም ከአልጋ ላይ የምነሳበት ሞራል እያጣሁ ብዙ ቀኖችን አልጋዬ ላይ እያሳለፍኩ አለሁ! ጉዳዩ ከተበላሸ ጀምሮ ንጋትን እየፈራሁ አለሁ! "በሰላም አሳድረኝ" ከሚለው በተቃራኒ እየፀለይኩ ወደ መኝታዬ መግባት ከጀመርኩ ቆየሁ! ሁሉም ነገር ያደክማል! ከማስታወሻዬ ውጭ ለቅርብ ቤተሰቤ እንኳን አውርቼው የማላውቀውን ችግሬን እናም መከፋቴን ሁሉ በዝርዝር ነግሬያት ነበር እንኳንስ አዝና ገንዘቤን ልትመልስልኝ ለመልዕክቴ እንኳን መልስ አልሰጠችኝም። ብቸኛ መፅናኛዬ "እንኳንም እሷን አልሆንኩ ነው"! ለሚያስብ እናም ከህሊናው ላልራቀ ሰው ከመበደል መበደል ይቀላልና! እሷ ግን እንደ ሰው ሀዘን እና ደስታ የሚፈራረቅባት ስለመሆኗም እጠራጠራለሁ! በፈጣሪ በሚያምን ሰው በዚህ ልክ መበደሌ(በደሉ የእኔ ብቻ ባይሆንም) ደግሞ የበለጠ ግራ አጋብቶኛል። "ለስራችን እንደስራችን ዋጋ የሚከፍል አምላክ አለ" ብሎ ከሚያምን ሰው በዚህ ልክ ጭካኔ? ብዙ ነገር እየገባኝ አይደለም። እናም ካልተሳካ ገንዘባችንን መልሽ ስንላትም "ገንዘቡን ሰርቼበታለሁ አሁን ላይ ካሽ የለኝም" ነበር መልሷ። እውነቱ ከእኛ በሰበሰቡት ገንዘብ ሌላ ስራ እየሰሩበት እንጂ ምንም ፕሮሰስ እያደረጉ እንዳልነበር ነው መጨረሻ ላይ የተረዳነው። እኔ የተጭበረበርኩት AIM Ultra Education Consultancy ነው። ይሄ ድርጅት ግን ከአንድ ብዙ አልጋ ካለው ሆቴል ውስጥ አንዱ ክፍል ብቻ ነው። ተመሳሳይ ሰዎች የሚዘውሯቸው ብዙ ድርጅቶች አሉ። ዋናዋ ዘዋሪ ቤተልሄም ታደሰ ይማም ትባላለች። ሴትዮዋን ተከታትሎ ለመያዝም ሆነ ለማስያዝ ከባድ ያደረገው ደግሞ በተለያዩ የቤተሰብ አባል ነው ፍቃድ የምታወጣው እናም ድርጅቶችን የምትከፍተው ። መኖሪያ አድራሻም ስለምትቀያይር ማግኘት አልቻልንም። አንድ ድርጅት ትከፍት እናም መዝረፍ ያለባትን ዘራርፋ እሱን ትዘጋ እና


የጁሙዓህ ኹጥባህ
በሸይኽ ዐብዱ-ስ'ሰላም አንዋር
ርዕስ፦ ስለ ሰላት ግዴታነት
ቦታ –ባዩሽ መስጂድ


Forward from: Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹
ጁሙዓን የት ሃገር፣ የት መስጅድ ሰገዳችሁ? ኹጥባው ስለምን ነበር? ለሌሎችም እንዲጠቅም ከሰማችሁት ውስጥ የኹጥባውን ጭብጥ በአጭር አስፍሩት።


ጁሙዓችንን በሶደቃ ስናደምቀው…

ከላይ በቪድዮው ላይ የተመለከታችኋቸውን የኸይር ሥራ ሂደቶችና የዳዕዋ እንቅስቃሴዎች ይበልጥ በተጠናከረ መልኩ ለማስቀጠል፤ እናንተም አሻራችሁን አሳርፉ።

ያለነው በተከበረው ቀን በጁሙዓህ፣ ያውም በረመዿን ዋዜማ ነው። ኢንሻ አላህ ነፍሳችንን በሶደቃ አፀዳድተን ወደ ረመዿን!

ከታች ካሉት የባንክ አማራጮች በአንዱ አላህ ከሰጣችሁ ላይ ሰድቁ። ሰደቃ ገንዘብን አታጎድልም።


1.ዘምዘም ባንክ..............   (0033239710301)
2.ሒጅራ ባንክ ..................  (100442626002)
3.ንግድ ባንክ ..................... (1000584808137)
4. አቢሲኒያ ባንክ ............... (161161705)
5. ዳሽን ባንክ ..................... (7955764311011)
6. የኦሮሚያ ኅ/ሥራ ባንክ .. (1000094682928)
7. ንብ ባንክ  ....................... (7000050648422)
8. አዋሽ ባንክ  .........(014321240042600)


የምትልኩበትን ደረሰኝ በውስጥ መስመር @Murad_Tadesse ላይ ላኩልኝ። ቡሪክቱም!


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
ዛሬ ጁሙዓህ አይደል? ታዲያ ለምን አንድ የኸይርና የሶደቃ ዝግጅት አልጋብዛችሁም?


የ360 ቀናት የሐኒፍ ጉዞ !

ከቤንሻንጉሉ አሶሳ እስከ ዓፋሩ አዋሽ የተካተቱባቸው ፣  ዲላ ፣ ሚዛን አማን እና ሐረር የደመቁባቸው ከ 10 በላይ የዒልም ኮርስ እና የዳዕዋ መርኃግብሮች! ከ 5 በላይ ልዩ ልዩ ገጠራማ አከባቢዎች የተዘለቁባቸው የዳዕዋ ጉዞዎች! ከ20 በላይ በመዲናችን አዲስ አበባ እና የክልል ከተሞች የተካሄዱ የረመዷን ሙሐደራዎች!

በመንግስት ሆስፒታሎች ፣ በአረጋዊያን መጦሪያ ማህበራት እና በክልል ከተሞች ከ 8,500 በላይ ሰዎች ተጠቃሚ የሆኑበት የኢፍጣር መርኃ ግብር!

105 ኩንታል የፉርኖ ዱቄት ድጋፍ ለተፈናቃዮች የተበረከተበት የዘካተል ፊጥር መርኃ ግብር!

በ 6 የማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች የተሰራጩ  ከ 70 በላይ ፖስተሮች፣ ከ 450 በላይ ቪዲዮዎች ያፈሩዋቸው ከ 100 ሺህ በላይ ተከታታዮች!

ዛሬም እንደትላንቱ በዒልም እና በዳዕዋ በበጎ አድራጎት እና ሚዲያ ዘርፍ ላይ የተሻሉ ስራዎችን ለማበርከት ጥረቶች በአላህ ፍቃድ ተጠናክረው  ይቀጥላሉ!

በሐኒፍ ኢስላማዊ ድርጅት የሚሰሩ ዘርፈ ብዙ የዳዕዋና የኸይር ስራዎች ላይ የብኩልዎን ድጋፍ ለማበርከት የሚከተሉትን የባንክ አካውንቶች ይጠቀሙ!

1.ዘምዘም ባንክ..............   (0033239710301)
2.ሒጅራ ባንክ ..................  (100442626002)
3.ንግድ ባንክ ..................... (1000584808137)
4. አቢሲኒያ ባንክ ............... (161161705)
5. ዳሽን ባንክ ..................... (7955764311011)
6. የኦሮሚያ ኅ/ሥራ ባንክ .. (1000094682928)
7. ንብ ባንክ  ....................... (7000050648422)
8. አዋሽ ባንክ  .........(014321240042600)


"اللهمَّ هَبْ لنا بيتاً آمنًا لا يتسرّب سرّه، ولا ينفذ خيره، ولا يختفى بريقه، ولا يتسلّله جفاء ولا يُثقله بلاء، واجعله يُطعِم الزوار ويُحسن الجوار، اللهمَّ صُبٌ عليه الخير صبًا، ولا تجعل العيش فيه كدّاً وأسعِد من يسكِنه واملأ تفاصيله حُبًا وبَهْجة" 🤲


እያነበባችሁ!

9k 0 34 18 136

ዲፕ ሲክ በጠዋቱ በጁሙዓው አልነጀሰኝም¡

አንተ ዝም ብለህ ኮድህን ኮድኩድ።

አላውቅም ማንን ገደለ!


ወትሮስ ቻይና የነካካው¡

አፈር ብላ ወዳ¡
♠

ኤአይ ሞደሎችን አትመኑ፣ ከማመናችሁ በፊት አጣሩ። Human in the loop መኖር አለበት። ባለፈ አንዷ እነሱን «ፈታዋ መጠየቅ እንደት ይቻላል?» ብላኝ ነበር።

9.4k 0 15 64 290

Forward from: Mizan Tv - ሚዛን ቲቪ 🇪🇹
Video is unavailable for watching
Show in Telegram
የማለዳ ስንቅ ለቀልብዎ❤️

[Part: ②①⑨③]👌


#ቁርኣን


Forward from: Mizan Tv - ሚዛን ቲቪ 🇪🇹
Video is unavailable for watching
Show in Telegram
የምሽት ስንቅ ለቀልብዎ❤️

[Part: ②①⑨②]👌


#ቁርኣን


ሙጦረፍ ቢን ዐብደ-ል'ሏህ እንዲህ ይላል፦

«ጥሩ ጓደኛ ከብቸኝነት ይሻላል። ብቸኝነት ከመጥፎ ጓደኛ ይሻላል።»

[አ-ዝ'ዙህድ ሊ-ኢማም አሕመድ: 1365]

10.8k 0 28 18 148

አንዳንዶች ክፍተት ማፈንፈን እንጂ ጠንካራ ጎን ስለማይታያቸው፤ ይሄንንም እያነበቡ!


ካልሠራህ አትበላም‼
===============
✍ ካልጣርክ፣ ሰበብ ካላደረስክ፣ ካልሠራህ… አትበላም። ዝም ብለህ «ትችላለህ፣ እምቅ አቅም አለህ፣ ህልምህን እውን ማድረግ ትችላለህ፣ በአዕምሮህ ያሰብከውን ሁሉ ታሳካዋለህ፣ ማንም ኃይል አያግድህም፣ በራስህ ተማመን፣ ተመሰጥ፣ የሃሳብህ ውጤት ነህ…» እየተባለ የስበት ህግ (Law of Attraction - LoA) የሚሰበክበት መድረክ አለ።

ÂŤlike attracts like, and that whatever happens to you in your life, you are the one who attracted it to your life, and it was attracted to you because of images stored in your mind, namely the things that you were thinking of. Whatever you think of, you will attract it to you.Âť


የሚያሳዝነው ነገር በዚህ ሰበካ ውስጥ ሙስሊሞች ሳይቀሩ ገብተው፤ ቀስ በቀስ በኔትወርክ እየተሳሳቡ አውቀውም ይሁን ሳያውቁ ከኢስላምም ከሳይንስም ጋር ወደሚጋጭ ክህደት እየጎረፉ ነው። የሚያሳዝነው ደሊላቸው «ይሄው ኒቃቢስቶች አሉ አይደል?፣ ይሄው ጺሙን ያስረዘመውና ሱሪውን ያሳጠረው ልጅ አለ አይደል?…» እየተባባሉ አንዱ አንዱን እየሸለመ በሰፊ አዳራሽ እየተቀወጠ፣ በአጉል ሞራል ወደከፋ ነገር እያመሩ ነው። በዚህ ኔትወርክ ውስጥ ብዙ ተስፋ የቆረጡ ሁሉ መክሊታቸውን ያገኙ መስሏቸው ከውጭ የኢስላምን ፋና ቢያንፀባርቁም በሜዲየሽንና መሰል ፍልስፍና የውስጣቸው ኢማን እየተቦረቦረ ነው።


በምኞት ብቻ ገንዘብ ጠብ አይልም። መርየም የዒሳ እናት ምጥ ላይ ሆና አላህ ከተጠጋችበት ዛፍ የምትመገበው ፍሬ ማውረድ እየቻለ፤ ግን ሰበብ ታደርስ ዘንድ ፍሬው እንዲወርድላት በእጅሽ ዛፉን ወዝውዢው ተባለች። ዝም ብሎ ማውረድ አይችልም ነበር? ይችላል! ግን ሰበብ ማድረስ ያስፈልጋል። ዝም ብለህ ፍራሽህ ላይ ተጋድመህ ስታቃዥ አድረህ፤ ጠዋት ስትነቃ የሚፈጠር ታዕምር ካለ አታስበው።

ገጣሚው እንዲህ እንዲል፦
إذا تمنيتُ بتُّ الليل مغتبطاً *** إن المُنى رأس أموال المفاليسِ!


ለዛም ነው በአጉል ስካመርና ህልም ውስጥ ከመግባት፤ ተምራችሁ ሥሩ የምለው። ሁሉም የየራሱ የተገራለት መክሊት አለው። ትምህርቱ የተገራላችሁ ተማሩ። ሌሎቻችሁ ሌላ ፈልጉ። ትምህርት ብቻ አይደለም ገንዘብ ማግኛ ሰበቡ።
ለዛም ነው Mizan Institute of Technology - MiT ተማሩ የምለው።
ስትማሩ ዝም ብላችሁ ዘው ብላችሁ አትመዝገቡ። መጀመሪያ ከናንተ ጋር የሚሄደውን ዘርፍ ብትችሉ በአካል ቢሯቸው በመሄድ አሊያ በቴሌግራምና በስልክ አማክሩና ከዛ ተመዝገቡ። 3 ቀን ነው የቀራቸው ምዝገባ ሊያቆሙ። ስትማሩም ዝም ብላችሁ እንደ ግቢ ኮርስ ለከፍ ለከፍ ሳይሆን ትኩረት ሰጥታችሁ ተማሩ፤ አሊያ ገንዘብ አታባክኑ።


የኛ ሰው ችግሩ ለፍቶ የሚጠቅመውን ሳይሆን አቋራጭ ፈለገ። ለዛም ነው በስስ ብልቱ ገብተው በባዶ ተስፋና ማነቃቂያ «ትችላለህ» እያሉ ሆዱንና ወኔውን በሳክስ ሲሞሉለት «እችላለሁ!» እያለ በኩፈሳ ተኝቶ በኩፈሳ የሚያነጋው።

The Secret የተሰኘው የአውስትራሊያዊው ጸሐፊ Rhonda Byrne ፍልስፍና ቀስ በቀስ በሂንዱዝምና ቡድሂዝም ነው የሚወስዳችሁ። ዝም ብላችሁ «ይህ ምን ችግር አለው?» እያላችሁ በሚክሯችሁ ላይም አታንጓጡ።

በዚህ ነገር ውስጥ ያላችሁ ወንድምና እህቶች አላህን ፍሩና ከገባችሁበት አዘቅት ውጡ። ሰውም አታጥምሙ፣ ለመጥመማቸው ሰበብ አትሁኑ። በዛ ውስጥ ተጭበርብራችሁ የገባችሁ ኡስታዝ ተብዬም ሆንክ ወጣት ውጣ። በየትኛውም መልኩ ሐራም ከስብ ውስጥ አትግቡ። ሞት ላይቀር ነገር የቱንም ያክል ፈተና ቢበዛ አትሸወዱ፣ ዲናችሁን አትሸርሽሩ።


በዚህ ዘርፍ በቂ ማብራሪያ ከፈለጋችሁ ይህን አንብቡ።

https://islamqa.info/en/answers/112043/the-secret-and-the-law-of-attraction


https://islamqa.info/ar/answers/112043/%D8%AD%D9%88%D9%84-%D9%83%D8%AA%D8%A7%D8%A8-%D8%A7%D9%84%D8%B3%D8%B1-%D9%88%D9%82%D8%A7%D9%86%D9%88%D9%86-%D8%A7%D9%84%D8%AC%D8%B0%D8%A8


||
t.me/MuradTadesse

12.7k 0 73 27 153

ሁላችሁም ተጋብዛችኋል!


እኔና ቤተሰቤ ኢንሻ አላህ እሁድ ከጠዋት ሚሊኒየም አዳራሽ ነን።

እናንተስ?

ትኬት ያልወሰዳችሁ በዚህ ሊንክ ውሰዱ።

http://www.conference.nesiha.tv/




ልብ በሉ! ትኬት በነፃ ነው‼

እናንተ ሂዳችሁ ዳዕዋ ማዳመጥ ነው።

13.5k 0 31 78 135

ኢፍጣር በመስጂደ ነበዊ‼


ያ ረብ! በሰላም አድርሰን።

14.8k 0 16 38 288





Everything is super important.
Until you are sick. Then you realize there was only ever one thing that was important. Your health.

15.8k 0 13 10 106
20 last posts shown.