MILLENNIUM KOMBOLCHA PREPARATORY SCHOOL


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Education


QUALITY EDUCATION FOR ALL

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Education
Statistics
Posts filter


የከተ ሚሊኒየም አጠ/2ኛ ደረጃ ት/ቤት የ1ኛ
ወሠነ ትም/ የወላጆች ውይይት ተካሂዷል :: እየተገነባ ያለውን የ Gተ4 ቤተ መፅሃፍት ፣ አዳራሽና ቢሮዎች ህ/ቡ በነብስ ወከፋ 200ብር ናበላይ እንድሁም በዕውቀት ፣ በጉልበትና በማቴሪያል ድጋፍ እንደሚያደርጉ ቃል ገብተው በሥራው የተደሰቱ መሆኑን ገልፀዋል።








የሚሊኒየም አጠ/2ኛ ደረጃ ት/ቤት የ 2015 ዓ.ም አገር አቀፍ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርስቲ ሲገቡ የሚያሳይ ፎቶ በከፊል ከዚህ በታች ይታያል።


በ 2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍልየ ሚሊንየም ኮምቦልቻ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች አገር አቀፍ ፈተናዎችን ለመፈተን ወደ ወሎ ዩንቨርስቲ ኮምቦልቻ ካምፓስ በጉዞ ላይ 23/11/2015 ዓ.ም. ከቀኑ 9፡00


Forward from: Wollo university Institute of Technology KIoT
የ2015 አ.ም የ2ኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ሰርቲፊኬት ፈተና ክስተት ወ/ሮ ጸሃይ መሃመድ ኡመር እና ሁለቱ ልጆቻቸው፣
ኮምቦልቻ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት 22/11/2015 ዓ.ም
====================
ትምህርት እድሜ እንደማይገድበው ማሳያ የሆኑት ወ/ሮ ጸሃይ መሃመድ ከሁለት ልጆቻችው ጋር የ2ኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ሰርቲፊኬት ፈተናን በጋራ በመውሰድ ለቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቱ የ2015 ዓ.ም የፈተና ወቅት ገጠመኝ መሆን ችለዋል::
የግል ተፈታኝ የሆኑት እናት ከከሚሴ 02 መቶሆሮ አጠ/ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ ከሆነችው ልጃቸው ሲሃም እንድሪስ ጋር የ12 ክፍል አገር አቀፍ ማጠናቀቂያ ፈተናን ለመውሰድ በግቢያችን ቆይታ ያደረጉ ሲሆን፣ ወንድ ልጃቸው ተማሪ ሪድዋን ሁሴን ደግሞ የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኝ በመሆኑ በዛሬው እለት ግቢውን የሚቀላቀል ይሆናል::
ከአንድ ቤት ውስጥ ወላጅ እናትን ጨምሮ ሶስት ተፈታኞች በአንድ ተቋም ውስጥ ለፈተና መቀመጣቸው ድምቀት ከመሆናቸው ባሻገር አስተማሪ ሆኖ አግኝተነዋል ። ተቋማችንም በዚህ አጋጣሚ መልካም ውጤትም ይቀናቸው ዘንድ ይመኛል !!!


Forward from: Wollo university Institute of Technology KIoT
ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች አቀባበል እየተደረገ ነው::
ኮምቦልቻ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት 22/11/2015 ዓ.ም
==================
የማህበራዊ ሳይንስ የ2ኛ ደረጃ መልቀቂያ ሰርቲፊኬት ፈተና ተፈታኞችን አስተናግዶ ሽኝት በማደርግ ላይ የሚገኘው ኮምቦልቻ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በተያዘው የፈተና መርሃ-ግብር መሰረት የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችን  ለማስፈተን ሞቅ ያለ አቀባበል እያደረገላቸው ይገኛል::
ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ ሁለት ቀናት በሚኖረው የተፈታኞች አቀባበል ከሰሜን ሸዋ፣ ከኦሮሞ ብሔረሰብ ልዩ ዞን፣ ከደቡብ ወሎ ፣ ከደሴና ኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ተቋሙ ላይ እንዲፈተኑ የተመደቡ 6141 ተማሪዎች ወደ ግቢው በመግባት ላይ ይገኛሉ ::




Forward from: Wollo university Institute of Technology KIoT
ለማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ሲሰጥ የነበረው የ2ኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ሰርቲፊኬት ፈተና በስኬት ተጠናቀቀ::
ኮምቦልቻ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት 21/11/2015 አ.ም
===================
በኮምቦልቻ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ላለፉት ሶስት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የነበረው የማህበራዊ ሳይንስ የ2ኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ሰርቲፊኬት ፈተና ዛሬ ፍጻሜውን አግኝቷል::
ከደቡብ ወሎ፣ ከሰሜን ወሎ፣ ከሰሜን ሸዋ ፣ ከኦሮሞ ብሔረሰብ ልዩ ዞን ፣ ከደሴ እና ኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደሮች በተቋሙ ለፈተና የተመደቡ ተፈታኞችን ከቅበላ ጀምሮ ሲያስተናግድ የነበረው ኮምቦልቻ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የመጀመሪያውን ዙር የፈተና መርሃ-ግብር በስኬት ማጠናቀቅ ችሏል::
ዛሬ በነበረው የመጨረሻው ቀን የፈተና መርሃ ግብር በጥዋቱ ክፍለ ጊዜ ታሪክ ፣ በከሰአቱ ክፍለ ጊዜ ደግሞ ስነ-ዜጋ ፈተና ተሰጥቶ እጅግ ስርአት ባለው መልኩ የፈተናው መርሃ ግብር እንደተጠናቀቀ የኮምቦልቻ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንትፊክ ዳይሬክተር ዶክተር መላኩ ታመነ ገልፀዋል ። ለዚህ ስኬታማነት ዶክተር መላኩ ታመነ ተፈታኝ ተማሪዎቸን እና በፈተና ሂደቱ ውስጥ ያሉ አካላትን ያመሰገኑ ሲሆን ፤ ለተፈታኝ ተማሪዎች መልካም ውጤት  ይገጥማቸው ዘንድ ተመኝተዋል ። ይህ በእንዲህ እንዳለ በቀጣይ የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞችም ፈተናቸውን በስኬት እንዲያጠናቅቁ የቅድመ ስራዎች በሙሉ እንደተጠናቀቁ አክለው ገልፀዋል !!!


Forward from: Wollo university Institute of Technology KIoT
ሁለተኛ ቀኑን የያዘው የ2ኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ሰርትፍኬት ፈተና በሰላም ተጠናቀቀ !!!
ኮምቦልቻ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት 20/11/2015 ዓ.ም
===================
በኮምቦልቻ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት እየተሰጠ የሚገኝው የ2ኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ሰርትፍኬት ፈተና  በ2ኛ ቀን የተሰጡት የአፕቲትዩድ እና ጆግራፊ ትምህርቶች ፈተና በሰላም ተጠናቋል::
እስካሁን ባለው ሂደት በተቋሙ የተመደቡት የ12 ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በአገር አቀፍ ደረጃ እየተሰጠ የሚገኘው የ2 ኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ሰርቲፊኬት ፈተናን በጥሩ ስነ-ምግባር እየወሰዱ ይገኛሉ::

11 last posts shown.