ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ | ሊቀ-መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ/2/
መከራ ቢገጥመኝ ለበጎ ነው ብዬ አልፋለሁ/2/
አዝ
በሰንሰለት አስረው በወህኒ ቢጥሉኝ
መከራን አብዝተው እጅግ ቢያስጨንቁኝ
ለበጎ ነው ብዬ ተስፋ አድርጌያለሁ ይሁን አንተ ያልከው እገዛልሃለሁ
አዝ
በመከራው ፅናት ጉልበቴ ደከመ
ትካዜ ከቦኛል ተስፋዬም ጨለመ
ነገር ቢሆን ባይሆን አንተን እንዳከብር
አድለኝ በፀጋ ጌታ ያንተን ፍቅር
አዝ
ከሀገር ወጥቼ በዱር መሰደዴ
ከባዕዳን ሀገር እርቄ መሄዴ
ለበጎ ነውና መቼ ይከፋኛል
ፈጽሞ እንዳልጠፋ እጄን ይይዘኛል
አዝ
ትላንትናም ዛሬም አንተ ያው አንተ ነህ
ፍቅርህ አይቀየር ወረትም የለብህ
ስምህን መጥራቴ ሞገስ ሆኖልኛል
ጠላቴ ቢፎክር መች ያሸንፈኛል
@Orthodox_Mezmur_For_All @Orthodox_Mezmur_For_All