"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Religion


🌹«ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን
/አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ።♥ https://t.me/Orthodoxtewahdoc

ሐምሌ 3 በ2014 ዓ°ም ተከፈተ።
📌እግዚአብሔር ቢፈቅድ የቅዱሳኑን ታሪክ እንመማርበታለን ብለን ከፈትነው ቅዱስ እግዚአብሔር ይፍቀድልን አሜን‼
❤የእመ ብርሃን ልጅ🤗

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Religion
Statistics
Posts filter


🥀 ገድሉ ታምራቱ 🥀

ገድሉ ታምራቱ እጅግ ብዙ ነው
ጣዖትን አዋርዶ የተሸለመው
የተዋህዶ ኮከብ ተክለ ሐዋርያ
አባ ተክለሃይማኖት ዘኢትዮጵያ


ዳግማዊ ዩሐንስ ጠፍር የታጠቀ
ፍፁም ባህታዊ ጠላት ያስጨነቀ
የፀጋ ዘአብ ፍሬ ዛፍ ሆኖ በቀለ
በደብረሊባኖስ መናኝ አስከተለ

#አዝ ======
ደካማ መስሏቸው በአንድ እግሩ ቢያዩት
ባለ ስድስት ክንፉ ተክልዬ የእኔ አባት
እርሱስ አንበሳ ነው ይናገር ደብረ አስቦ
ሌጊዮን ሲዋረድ እፍረት ተከናንቦ

#አዝ ======
ከካህናት መካከል ህሩይ ነው ተክልዬ
መጣሁ ከገዳምህ ልሳለምህ ብዬ
ኢትዮጵያዊው ቅዱስ አባ ተክለሃይማኖት
ወልድ ዋህድ ብለህ ምድሪቷን ቀደስካት

#አዝ ======
የባረከው ውሃ የረገጥከው መሬት
ጥላህ ያረፈበት ሆኗል ፀበል እምነት
ኑና ተመልከቱ ድውያን ሲፈቱ
ይሰብካል ተክልዬ ዛሬም እንደ ጥንቱ


እናትነት !🤗

#መንፈሳዊት የልጅ አስተዳደግ

የልጅ አስተዳደግ ማለት በመንፈስ ድኾች የኾኑ የሚያዝኑ የዋሆች ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ልበ ንጹሖች የሚያስተራርቁ ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ በእግዚአብሔር ምክንያት ሲነቀፉና ሲሰደዱ ደስ የሚላቸው ልጆችን ማሳደግ ነው (ማቴ.5፥3-12) ዘላቂውን ግብ በእእምሮ ይዞ ልጆችን ማሳደግ ማለት የሚታገሡ ቸርነትን የሚያደርጉ የማይቀኑ የማይመኩ የማይታብዩ የማይገባውን የማያደርጉ የማይበሳጩ በደልን የማይቈጥሩ ከእውነት ጋር ደስ የሚላቸው በአጭር ቃል ፍቅርን በገቢር ገንዘብ ያደረጉ ልጆችን ማሳደግ ማለት ነው (1ኛ ቆሮ 13፥4-8) የመረሻውን ግብ እያሰቡ ልጆችን ማሳደግ ማለት እንደ እባብ ልባሞች እንደ ርግብ የዋሃን ክፉውን ሳይኾን በጎውን ለማወቅ ትጉሃን የዲያብሎስን ሽንገላ ለማስተዋል ጠቢባን፣ የቅዱሳንን ፋና ለመከተል የቃሉን ወተት የሚጠጡ ንጹሐን አድርጎ ማሳደግ ነው።

ኦርቶዶክሳዊ የሕፃናት አስተዳደግ ማለት ልጆቻችን እኛ አየናቸውም አላየናቸውም በሕሊናቸው ጓዳ በልቡናቸው ሰሌዳ ላይ መንግሥተ እግዚአብሔርን መቅረፅ ነው።

ኦርቶዶክሳዊ የሕፃናት አስተዳደግ ማለት ስንጠራቸው አቤት ስናዛቸው ወዴት የሚሉንን ሳይኾን ትዕግሥትን ቸርነትን በጎነትን እምነትን የውሃትን ራስን መግዛትን በአጭር ቃል የመንፈስ ፍሬዎችን ገንዘብ ያደረጉ ልጆችን ማሳደግ ነው። (ገላ.5፥22-24)

ኦርቶዶክሳዊ የሕፃናት አስተዳደግ ማለት ልጆቻችን የገዛ ክብራቸውን እንዲያውቁና በዚያ መሠረት እንዲያድጉ  ይኸውም የእግዚእብሔር ልጆች ክርስቶስን የሚመስሉ በእግዚእብሔር አርአያና አምሳል ቅዱሳን እንዲኾኑ አድርጎ ማሳደግ ነው። (ዘፍ. 1፥26)

ኦርቶዶክሳዊ የሕፃናት አስተዳደግ ማለት ልጆቻችን የእኛ ንብረት እንዲኾኑ ሳይኾን የእዚአብሔር ልጆች እንዲኾኑ አድርጎ ማሳደግ ው መጥምቁ ዮሐንስ እስራኤላውያንን ለክርስቶስ ያዘጋጃቸው እንደ ነበረ እኛም በዚያ መንገድ ልጆቻችን የእግዚአብሔር ልጆቸ እንዲኾኑ ማዘጋጀት ነው።

ኦርቶዶክሳዊ የሕፃናት አስተዳደግ ማለት የልጆቻችንን መጥፎ ጠባይ ከማራቅና እንዲታዙን ከማድረግ በላይ እግዚአብሔርን በፍጹም ኃይላቸው እንዲወድዱ ማድረግ ነው ቅዱሳንን እንዲያፈቅሩ በቃል ኪዳናቸው ታምነው እርሱን እንዲመስሉ ማድረግ ነው።

ኦርቶዶክሳዊ የሕፃናት እስተዳደግ ማለት ልጆቻችን እንዳይጣሉ ስናደርጋቸው መንፈሳዊ ሕይወትና የቅድስና መንገድ ምን እንደ ኾነ በሚያሳይ መልኩ ማሳደግ ነው መጀመሪያ ላይ ባነሣሁት ምሳሌ ላይ ለምሳሌ ዮሐንስ መጫወቻውን አቀብለኝ ብለውና እያንገራገረም ቢኾን ቢሰጠኝ እኔም ቀጥዬ መጫወቻውን እዚህ አስቀምጠዋለሁ ከእራት በኋላም እንዴት በየተራ እንደምትጫወቱ ስትነግሩኝ ልሰጣችሁ እችላለሁ ብለው ለጊዜው ኹለቱም መፍትሔ ባያመጡም እንደ አሁኑ እንዳልወስድባቸው ለሌላ ጊዜ እንዴት መጫወት እንዳለባቸው ከማሰብ ዝም አሉም።

ኦርቶዶክሳዊ የሕፃናት አስተዳደግ ማለት ልጆቻችን ከላይ ያነሣናቸውን ምግባራት በአንድ ቀን ሊይዙልን እንደማይችሉ ዐውቆ እነዚህን ቀሰ በቀስ እስኪይዟቸው ድረስ ሊማሩ የሚችሉበትን ኸኔታ እያመቻቸን ጊዜ ልንሰጣቸው እንደሚገባን ተረድቶ መታተር ነው ልጅ ማሳደግ የአጭር ጊዜ ሳይኾን የረጅም ጊዜ ኃላፊነት ነውና ልጆቻችን በኹለት ሳምንት ወይም በአንድ ወር እንዲያውቁትና እንዲይዙት የምንፈልገው አንድ ነገር አልያዙም ማለት ሙከራችን ስለማይሠራ ነው ማለት ላይኾን ይችላል ጊዜ የሚፈልግ ይኾናል እንጂ ልጅ ማሳደግ ትዕግሥት ይጠይቃል ልጆቻችን እንዲይዙት የምንፈልገው ነገር ለመዝ እየጣሩ እንደ ኾነ ርግጠኛ እስከ ኾንን ድረስ ዕድል በመስጠት ልንታገሣቸው ይገባናል።"

#ምንጭ፦ትንሿ_ቤተ_ክርስቲያን ገጽ 444.445ገብረ እግዚአብሔር ኪደ

ኦርቶዶክሳዊ የሕፃናት አስተዳደግ ማለት በጎ ቃላትንና ኦርቶዶክሳዊ እሴት ያላቸውን ቃላት በልባቸው ላይ መጻፍ ነው ይህን ለማድረግ ደብተር አስይዞ ክፍለ ጊዜ መድቦ ማድረግ አይኾንም ይህን ማድረግ የምንችለው ሲያጠፉና በዚያች ቅጽበት ፈጠራ የታከለበትን ጥበብ ልናስተምራቸው እንደሚገባን ስናስብ ነው ባለጌ አትኹን" ከማለት ትዕግሥት ራስ ወዳድ አትኹን ከማለት ተሳሰባችሁ ተጫወቱ ኹለተኛ እንደዚህ ብለህ ትናገርና" ከማለት ወንድምህን ይቅርታ ጠይቀው አንተ ለታናሽ ወንድምህ ክፉ ነህ' ከማለት ኦርቶዶክሳዊ ወንድም ለታናሽ ወንድሙ እንደዚህ ይናገራል ጉልበትህን በገዛ እኅትህ ላይ አታሳይ እሺ ከማለት ይልቅ ኦርቶዶክሳዊና ታላቅ ወንድም ለእኅቱ የሚያደርገው ምንድን ነው? ሰነፍ ከማለት ይልቅ መጫወት የምታበዛ ከኾነ የቤት ሥራህን መሥራት ከባድ ነው ደደብ ከማለት ይልቅ አስበህ ወስን ባክህ ኹልጊዜ አትነፋረቅብኝ ከማለት ይልቅ ሳታለቅስ የምትፈልገውን ንገረኝ ማለትና የመሳሰሉ አነጋገሮች ቀላል የሚመስሉ ግን ደግሞ ልጆቻችንን የሚፈውሱ ቃላትና ልምምዶች ናቸው።

እነዚህ አነጋገሮች የሥነ ልቡና ባለሙያዎች እንደሚሉት አዎንታዊ አነጋገሮች አይደሉም የትንሿ ቤተ ክርስቲያን ፈተናዎች በሚለው ምዕራፍ እንደተመለከትነው ተግባቦት ወሳኝ ስለኾነና በኋላ ሲያድጉም በሕይወታቸው ላይ ከፍ ያለ ተጽዕኖ ስላለው ነው እንጂ ስለዚህ የእኛንና የልጆቻችንን ተጋድሎ ለይቶ መሰየምና ማየት ኦርቶዶክሳዊ አነጋገሮችን በዚህ ተጋድሎ ውስጥ ማካተቱ ኹላችንንም የሚያድን ነው።

#ምንጭ ትንሿ_ቤተ_ክርስቲያን ገጽ 468

554 0 13 1 21

አንድ በሥራው ታታሪ የሆነ ዓሳ አጥማጅ ነበር።ይህ አጥማጅ በየቀኑ ዓሳ ያጠምድና አስከሚያልቅ ድረስ ይጠቀማል። ልክ ሲያልቅ ወደ ባህር ዳርቻ በመሄድ ሌላ ያጠምዳል።
ከእለታት አንድ ቀን የዓሳ አጥማጁ ሚስት ባሏ ያመጣላትን ዓሳ በመቆራረጥ ላይ ሳለች አሰገራሚ ነገር ታያለች። ይህች ሰው የተመለከተችው እጅግ የከበረ ሉል ነው ። በጣም እየተገረመች በዓሳ ሆድ ውስጥ ሉል ...? አያለች ባሌ... ባሌ... ባሌ... እያለች ባሏን መጥራት ጀመረች ከዚያም "ምን እንዳገኘሁ ተመልከት ሉል እኮ ነው!! ሉል ... ከዓሳው ሆድ ውስጥ " አለችው ።
እሱም " እንዴት አሰደሳች ሚስት ነሽ እስኪ አቅርቢው ለዛሬ ለቤት ቀለባችን መግዣ ትሆነናለች ..... ከዓሳ ሌላ ምግብ እንበላለን!!" አላት..... ይህ ዓሳ አጥማጅ ሉሉን በመያዝ ወደ ሉል ገዢና ሻጭ በመሄድ ያሳየዋል። ገዢውም "እኔ ይህንን ሉል የመግዛት አቅሙ የለኝም፤ ዋጋው ከፍተኛ ከመሆኑ የተነሳ ይህንን ሱቄንና መኖሪያ ቤቴን ብሸጠው እንኳን ልገዛህ አልችልም። ይልቁንስ እከሌ የሚባል ሀብታም ነጋዴ አለ እርሱ ሊገዛህ ይችላልና ወደርሱ ሂድ። አለው ።
ዓሳ አጥማጁ ሉሉን በመያዝ ወደ ተባለው ሀብታም ሰው በመሄድ ጉዳዩን ነገረው። ይህ ታላቅ ነጋዴም "እኔ አልችልም ይህ የያዝከው ሉል በገንዘብ የሚተመን አይደለምና እኔ መፍትሔ ብዬ የማስበው ወደ ከተማው አስተዳዳሪ ሄደህ ብታሳየው ነው እንደዚህ አይነት ውድ ሉል ከርሱ ውጭ የመግዛት አቅም አለው ብዬ የማስበው ሰው የለም " አለው።
ጉዞውን ወደ ተባለው አስተዳዳሪ በማድረግ ቤቱ እንደደረሰ ወደ ህንፃው ለመግባት ፈቃድ እስኪያገኝ ድረስ መጠበቅ ጀመረ።
(እንደገባም) ለአስተዳዳሪው የያዘውን ሉል ሲያሳየው አጅግ ተገረመ። "እንደዚህ አይነት ሉል ስፈልገው የነበረ ነው…እንዴት ተመኑን እንደምከፍልህ አላውቅም… ነገር ግን ለየት ወዳለው ካዝናዬ እንድትገባ እፈቅድልሃለሁ። እዛ ውስጥም ለስድስት ሰዓታት በመቆየት የቻልከውንና የፈለከውን ንብረት ተሸክመህ መውጣት ትችላለህ። ይህ እንግዲህ የሉልህ ክፍያ ነው።" በማለት ወደ ካዝናው እንዲገባ ጋበዘው።
ዓሳ አጥማጁም "አለቃዬ ሆይ! ስድስት ሰዓት…!! እንደኔ ላለ ዓሳ አጥማጅ በጣም ብዙ ነው እንደው ሁለት ሰዓት ብታደርግልኝ " ሲል ጠየቀው። አስተዳዳሪውም "በጭራሽ አይሆንም ስድስት ሰዓት ሙሉ ከካዝናዬ የፈለከውንና የምትችለውን ያህል ይዘህ መውጣት አለብህ " አለው። ዓሳ አጥማጁ ወደ ካዝናው ሲገባ በጣም የሚያስደንቅ ሁኔታን ተመለከተ። በሦስት የተከፈለ ሰፊ ክፍል
☞ አንደኛው ክፍል በአልማዝ፣ በወርቅና በተለያዩ ጌጣጌጦች የተሞላ ክፍል ነው።
☞ሁለተኛው ክፍል ለመተኛት ምቹ የሆኑ ለየት ያሉ ፍራሾች ያሉበት ክፍል ነው።
☞ ሦስተኛው ክፍል አጠቃላይ በሚፈለጉና ውድ በሆኑ የምግብና የመጠጥ ዓይነቶች የተሞላ ነው።
ዓሳ አጥማጁ ከራሱ ጋር መነጋገር ጀመረ። "ስድስት ሰዓት!! እንደኔ ላለው ድሃ ዓሳ አጥማጅ በጣም ብዙ ነው በዚህ ስድስት ሰዓት ምን ማድረግ አለብኝ? ጥሩ! በሦስተኛው ክፍል ባሉት ምግብና መጠጥ መጀመር አለብኝ ምክንያቱም ብዙ ወርቅ ለመሸከም የሚያስችለኝን ኃይል አገኝበታለሁ። " በማለት ወደ ሦስተኛው ክፍል በመሄድ መብላት ጀመረ። ይበላል… ይበላል… ይጠጣል…
ከስድስቱ ሰዓታት በመብላት ሁለቱን ሰዓት ተጠቀመ። ልክ ሲጨርስ ወርቁንና ጌጣጌጡን ለመሸከም ወደ አንደኛው ክፍል በመሄድ ላይ ሳለ በሁለተኛው ክፍል ያለውን ያማረ ምቹ ፍራሽ ተመለከተና እራሱን ማናገር ጀመረ። "አሁን በጣም ጠግቤያለሁ ለምን ትንሽ በመተኛት በደንብ ለመሸከም የሚያስችለኝን እረፍት አልወስድም? ይህንን እድል ደግሜ አላገኘውምና ለምን
አበላሸዋለሁ?" በማለት ወደ ፍራሹ በመሄድ በጀርባው ተዘረጋ በጣም ጭልጥ ያለ እንቅልፍም ወሰደው።
ከተወሰነ ሰዓታት በኃላ "ተነስ ተነስ ቁም አንተ ጠባብ የሆንክ ዓሳ አጥማጅ ተነስ… ቁም...... ጊዜው አልቋል " አለው። ዓሳ አጥማጁም " እ እ እንዴ ምንድነው...?" አለ። ሰውዬውም " አዎ! ወደ ውጭ ውጣ " አለው። አጥማጁም "ኧረ ምንም በቂ ዕድል አላገኘሁም " አለ። ሰውዬውም "ስድስት ሰዓታት ሙሉ በዚህ ካዝና ውስጥ ሆነህ ጊዜህን ሳትጠቀም ቀርተህ አሁን ትባንናለህ? ከዚያም ሰዓት እንዲጨመርልህ ትጠይቃለህ? እነዚህን አልማዝና ወርቆች በፍጥነት ሰብስበህ በመውጣት የፈለከውን ምግብና መጠጥ እንዲሁም ያሰኘህን አይነት የመኝታ ፍራሽ መግዛት ትችል ነበር። ነገር ግን አንተ ዝንጉና ጠባብ በመሆንህ በዙሪያህ ያለውን እንጂ ሩቅ ያለውን ነገር አታስብም።" በማለት "ወደ ውጭ አስወጡት! " አለ።
አጥማጁም "ኧረ ባካችሁ!! ኧረ!… እባካችሁ አንድ እድል ይሠጠኝ " ቢልም ሊሆንለት አልቻለም።
ታሪካችን አለቀ በውስጡ ያለው ትምህርት ግን አላለቀም......

ልብ በሉ ይህ ሰውዬ እጅግ የከበረ ጸጋ ተሰጥቶት አልተጠቀመበትም ባለችው ጊዜያዊ ምግብና መኝታ ተታሎ እጅግ የበለጠ ጥቅሙን አጣ። የሰው ልጅ ህይወትም እንደዛ ነው። ፀልዩ፣ ንስሃ ግቡ፣ ቁረቡ፣ መንፈሳዊ ስራ ስሩ ስንባል ሁሌ ቀጠሮ። ሁሌ ረጅም ጊዜ ያለን ይመስለንና ቆይ ገና ነኝ እያልን ቀጠሮ እንይዛለን። የሚጠቅሙንን መንፈሳዊ ተግባራት ላይ አስቀድመን ከመሰማራት ይልቅ ሁሌ ስጋዊ ነገሮች ላይ አትኩሮት እየሰጠን የተሰጠን ጊዜ ያልቃል።  መንፈሳዊ ተግባራትን እንደ ትርፍ ወይም ተጨማሪ ነገር አናያቸው። ሰው ከእግዚአብሔር ጋር ከሆነ ሌላው ሁሉ ትርፍ ነው ይጨመርለታል። እግዚአብሔር ይሞላዋል።
እኛም ምድራዊ ነገር አታሎን ጥርስ ማፏጨትና ልቅሶ ወዳለበት ወደ ሲኦል እንዳንጣል በጊዜ ንስሐ ገብተን ተዘጋጅተን ልንኖር ግድ ነው።


ዛሬ ጥር 24 ስባረ ዐጽሙ ለተክለሃይማኖት በዚህ ዕለት አባታችን ተክለ ሃይማኖት ለ22 ዓመታት በጸሎት የቆሙበት ቀኝ እግራቸው መሠበሩንና በአንድ እግራቸው ለ7 ዓመታት ቆመው መጸለያቸውን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታስባለች::

የጻድቁ አባታችንን የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ረድኤት በረከታቸውን  ያሳድርብን። አሜን!
🤲

905 0 18 6 78

🌹መልክአ አቡነ ተክለ ሃይማኖት📚

አቡነ ተክለ ሃይማኖት ሆይ ሰላም እልሃለሁ/፫/

"ተክለ ሃይማኖት ፀሐይ ነፍሴን አደራ በሰማይ"የፃድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ጥበቃ አይለየን ።🤲🌸🌷


✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
✍️"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"📖ምሳ 1፥33☦📚
        
✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
📗ስንክሳር ዘወርኃ ጥር ፳፬/24

ወለተ ሥላሴ ብላችሁ በጸሎታችሁ አስቡኝ
https://t.me/Orthodoxtewahdoc
🌹የያዕቆብ ሌሊት ይሁንልን🕊




"ጌታዬ ሆይ ብቻዬን ብቀር እንኳ ፍፁም የማትለየኝ እስከ እድፌ ሳትፀየፍ በክብር የምታኖረኝ አንተ ብቻ ነህና ተመስገንልኝ🙏🥰


"ተክልዬ❎

"ተክለ ሃይማኖት✅

"እንኳን አደረሳችሁ ሰናይ ሌሊት ይሁንልን የፃድቁ ምልጃ አይለየን🙏♥


ኣንድ ብር ላይ ያለውን የሚስቀውን ልጅ ስመለከት ይገርመኛል፡፡
ኣንድ ላይ ነኝ ብሎ ኣላዘነም፡ የሆነ የተደበቀ ተስፋ ስላለው በተስፋ እና በደስታ ይኖራል ፡፡100 ብር ላይ ማክሮስኮፕ የሚመለከተው ሰውየ በጣም የተጨናነቀ ነው ፡፡100 ላይ ነኝ ብሎ ኣይዝናናም፣ ሌላ 100 ለመጨመር ይጨናነቃል ፡፡የዚህ ዓለም ሰወች ከመቶ ብር የተሳሉት ነን፡፡ በቃኝ የለም፣ ተመስገን የለም፣ በባንኩ በካዝናው ማጠራቀም ጥሎ መሄድ ፡፡መንፈሳዊ ኣባቶቻችን በኣንድ ብሩ ላይ ተስለዋል፡፡ ነዳያን፣የቆሎ ተማሪዎች እና የገዳማት እናቶቻችን እና ኣባቶቻችን ምንም የላቸው፡፡ ነገር ግን ደስተኛ ናቸው። ምክንያቱም ተስፋቸው
ኣምላካቸው ብቻ ስለሆነ ነው፡፡
ውጣውረዱ ወጭ ቀሪው  ኣያሳስባቸውም።

🌷ሰናይ ምሽት ቤተሰብ
🤲


✝✝✝ የአባታችን ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ዋና ዋና ዓመታዊ በዓላት ✝✝✝

1.መጋቢት 24 (ጽንሰታቸው)
2.ታኅሳስ 24 (ልደታቸው)
3.ሚያዝያ 22 (6 ክንፍ የተቀበሉበት)
4.ኅዳር 24 (ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ ጋር ያጠኑበት)
5.ጥር 24 (እግራቸው የተሰበረበት)
6.ነሐሴ 24 (ዕረፍታቸው)
7.ግንቦት 12 (ፍልሰታቸው)

ከጻድቁ በረከት አምላካቸው ይክፈለን


"ጥር 24 የፃድቁ የአባታችን ተክለ አብ ተክለ ወልድ ተክለ መንፈስ ቅዱስ የአቡነ ተክለሃይማኖት ስባረ አፅማቸው ነው ።የአባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖት ፀሎት ምልጃቸው ከፈተና ይጠብቀን ።

🌹የፃድቅ መከራቸው ብዙ ነው ። እግዚአብሔርም ከሁሉ ያድናቸዋል ። መዝሙረ 34 .19


Forward from: "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
🌹#ወር በገባ በ24 #አባ_ኖብ ሰማዕት📕

♨••እንኳን ለአባታችን ለአባ ኖብ ሰማዕት ወርሀዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ በምድረ ግብጽ ከታዩ ታላላቅ ከዋክብት አንዱ ቅዱስ ኖብ በሃገረ ንሒሳ ተወልዶ ያደገ ሲሆን ዘመኑም ዘመነ ሰማዕታት (3ኛው መቶ ክ/ዘመን) ነው:: ወላጆቹ በልጅነቱ ብዙ ሃብት ትተውለት ያርፋሉ:: ወደ ቤተ ክርስቲያን ሔዶ ካህኑ ስለ ምናኔና ሰማዕትነት ሲሰብክ ይሰማዋል::
ገና በአሥራ ሁለት ዓመቱ በቤቱ የነበረውን ሁሉ ለነዳያን አካፍሎ መስቀለ ክርስቶስን ሊሸከም ወደ ዐውደ ስምዕ (የምስክርነት አደባባይ -የክርስቲያኖች መገደያ ቦታ) ተጓዘ:: በዚያም በጉባዔ መካከል ክርስቶስን ሰበከ:: በዚህ ምክንያት በሰብዓዊ አካል ሊሸከሙት የማይችሉትን መከራ በልጅ ገላው ተቀብሏል::
በዚያው ልክም ብዙ ተአምራትን ሰርቷል:: በተአምራቱና በጣዕመ ስብከቱም ከመቶ ዘጠና ሺህ በላይ አሕዛብን ወደ ክርስትና መልሶ ሁሉም ተሰይፈዋል:: በእሳት: በስለት: በሰይፍ: በባሕርና በየብስ መከራን ከተቀበለ በኋላ በዚህች ቀን አክሊለ ክብርን ይቀበል ዘንድ አንገቱን ተከልሏል::
ጌታችን የገባለት ቃል ኪዳኑ ግሩም ነውና ዛሬ በግብጽ በድምቀት ይከበራል:: ምንም በእድሜ ልጅ ቢሆን ቤተ ክርስቲያን አባ (አባታችን) ኖብ ትለዋለች::
የአባኖብ ሰማዕት በረከታቸው ይደርብን፤ጸሎታቸው ይጠብቀን፤ለመንግሥተ ሰማይ መሪ በትር ይሁነን፤ድካማቸው ከጠላት እጅ ያድነን፣የትዕግሥታቸው ሀይል ከእሳት ባሕር ያድነን

አሜን አሜን አሜን

ቤተሰብ ይኹኑ https://t.me/Orthodoxtewahdoc


Forward from: "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
🌹#ቅድስት_ክርስቶስ ሰምራ🌹

☞ወር በገባ በ24 እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ስምህ ናት የእናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ በረከቷ ልመናዋ አማላጅነቷ ይደረግልንና ያደረገችው ተአምር ይህ ነው፡፡
☞በሸዋ ክፍለ ሀገር የሚኖር ጥበበኛ ወይም ዐዋቂ የሆነ ረንድ የንጉሥ ጭፍራ ወይም ወታደር ነበር ሰውየው መካን ነበረና ልጅ ባለመውለዳቸው ከሚስቱ ጋር ለብዙ ጊዜ ሲያዝኑ ኖሩ፡፡

☞ከዕለታት በአንደኛው ቀን በጥቡዕ ልቡና በፍጽም መታመን በእናታችን
በቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ሥዕል ፊት በብዙ ለቅሶ ልጅ ብንወልድ
ለቤተክርስቲያን የሐር መጋረጃና የወርቅ ጃንጥላ መብዓ እናቀርባለን ሲሉ
ብፅዓት አደረጉ፡፡
☞እንዲህምበ ብለው የሎሚ ወይም የለውዝ ፍሬና ከቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
ቅጽረ ቤተ ክርስቲያን ዐፈር ወይም እምነት ይዘው ወይም ወስደው ወደ ሀገራቸው
ተመልሰው ሄዱ፡፡
☞ከጥቂት ዓመታት ወይም ጊዜ በኃላ የዚያ ሰው ሚስት ፀነሰች ወንድ ልጅም
ወለደችና ታላቅ ደስታ አደረጉት እግዚአብሔር አመሰገኑ እናታችን ቅድስት
ክርስቶስ ሠምራን አከበሯት ከፍ ከፍም አደረጓት፡፡
☞አስቀድመው ስለተሳሉት መብዓ የወርቅ ጃንጥላ የቤተ መቅደስ መጋራጃ
ለእናታችን ለቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ቤተክርስቲያን አምጥተው ሰጡ፡፡
☞ከዚያም ከአበ ምኔቱ ወይም ከገዳሙ አስተዳደር ከአባ ዘመንፈስ ቅዱስ
ቡራኬና ታላቅ በረከት ተቀብለው እግዚአብሔንና ኤናታችን ክርስቶስ ሠምራን
እያመሰገኑ በሰላም በታላቅ ደስታ ወደቤታቸው ሄዱ፡፡
☞የእናታችን የቅድስት ክርስቶስ ሰምራ አማላጅነቷ ለሁላችን ይደረግልን
ለዘለዓለሙ አሜን፡፡
☞(ገድለ ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ)
☞ሲራክ ተክለጻድቅ የተዋህዶ ልጅ




Forward from: "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
☞ ወር በገባ በ 24 ቀን የሙሴ ጸሌም ወርሐዊ መታሰቢያ ነው፡፡☞ብዙ መነኮሳት ወደ አቡነ ሙሴ እየመጡ የሕይወት ትምህርትን ይማሩ ነበር፡ ከነዚህ የሕይወት ትምሕርታቸው መካከል በጥቂቱ እንመልከት፡፡

☞1ኛ☞አባ ሙሴ በገዳመ አስቄጠስ እያለ ከገዳማውያን አንዱ ጥፋት ሠራና
ማኅበሩ ለፍርድ ተሰበሰበ፡፡ አባ ሙሴ ግን በጉባኤ ላይ አልነበረም፡፡ ስለዚህ
ካህኑ ተልኮ ና ሁላችንም አንተን እየጠበቅን ነው አለወ፡፡ አባ ሙሴም በሚያፈስስ
ከረጢት አሸዋ ሞልቶ ያንንም በጀርባው ተሸክሞ ከኀላው እያፈሰሰ ወደ ጉባኤው
አመራ፡፡ ጉባኤተኞቹ ተገርመው ለምን እንደዚህ እንዳደረገ ጠየቁት፡፡ እርሱም
የእኔ ኃጢአቶች በኀላዬ እንደዚህ አሸዋ በዝተው ይፈሳሉ ነገር ግን ላያቸው
አልቻልኩም ዛሬ ግን በሌላው ላይ ለመፍረድ መጥቻለሁ አላቸው፡፡ ይህን ሲሰሙ
ዝም አሉ፡፡ ያን ወንድምም በይቅርታ አለፋት፡፡
☞2ኛ☞በሌላ ጊዜ በገዳመ አስቄጠስ ያሉ መነኮሳት ተሰብስበው የአባ ሙሴን
ትዕግሥት ለመፈተን ሲሉ ይህ ጥቁር መነኩሴ ለምን እዚህ መጣ ብለው
ተናገሩት፡፡ እርሱም ዝም አለ፡፡ ጉባኤው ሲበተን አባ ክፋ ስንናገርህ ምንም ሐዘን
አልተሰማህም ነበርን? ሱሉ ጠየቁት፡፡ እሱም ተሰምቶኝ ነበር ግን እንዳልናገረው
አንደበቴን ተቆጣጠርኩት አላቸው፡፡
☞3ኛ☞አንድ ጊዜ የአካባቢው ገዥ ሰለ አባ ሙሴ ዝና ሰምቶ ያየው ዘንድ ወደ
ገዳመአስቄጠስ መጣ፡፡ ይህን የሰማው አባ ሙሴ ሸሽቶ ወደ ጫካ ገባ፡፡
በመንገድም ላይ የገዥው መልእክተኞች አገኙትና እባክህን አባ ሙሴ የት
እንዳለ በኣቱን አሳየን አሉት፡፡ ከርሱ ምን ትሻላችሁ እርሱ ኮ ቂላቅል ነው
አላቸው፡፡
☞ይህን የሰማው የአካባቢው ገዥ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ መጣና የሆነውን ሁሉ
ለአገልጋዮቹ ነገራቸው፡፡ ብዙ ሰዎች ስለ አባ ሙሴ ሲያወሩ ሰምቼ ለማግኘት
መጥቼ ነበር በመንገድ ላይ ያገኘነው አንድ አረጋዊ ሰው ግን የአባ ሙሴ በኣት
የት እንደሆነ ስንጠይቀው ከእርሱ ምን ትሻለችሁ እርሱ ኮ ቂላቅል ነው አለን
ብለው ነገራቸው፡፡
☞አገልጋዮቹም በጣም ተናደዱና ምን ዓይነት ሰው ነው ስለ ቅዱሱ ይህን
የሚናገር ብለው ጠየቁት፡፡
☞ትልቅ ጠቆር ያለ አሮጌ ልብስ የለበሰ ነው፡፡ አላቸው፡፡ አገልጋዮቹም
ተገርመው ይህማ ራሱ አባ ሙሴ ነው ይህን ያለህ ሊያገኝህ ስላልፈለገ ነው
አሉት፡፡ የአካባቢው ገዥም ከአባ ሙሴ ሁኔታ ከንቱ ውዳሴን ስለ መሸሽ ትልቅ
ትምህርት ተምር ተመለሰ፡፡
☞4ኛአባ ሙሴ በኣት ሠርቶ ወደ ጴጥራ ሲሔድ በአካባቢው ውኃ ሰላልነበረ
ተጨንቆ ነበር፡፡ አንድ ድምፅ ሒድ ስለምን ነገር አትጨነቅ አለው፡፡ ሰለዚህም
በዚያ መኖር ጀመረ፡፡ አንድ ቀን በጴጥራ እያለ አበው ሊጎበኙት መጡ
የነበራቸውን ውኃ ጥቂት ነበረችና በርሷ ምግባቸውን አበሰለ፡፡ የሚያጠጣቸው
ግን አላገኘም፡፡ ስለዚህ ወደ ውጭ እየወጣ ውኃ ይሰጠው ዘንድ እግዚአብሔርን
ይለምን ነበር፡፡ በመጨረሻም ዝናብ ዘነበና የውኃ ማጠራቀሚያዎቹን ሁሉ ሞላ፡፡
☞እነዚያም አባቶች ትወጣና ትገባ የነበረው ለምን እንደሆነ እባክህ ንገረን
አሉት፡፡ እናንተ በእግድነት ስትመጡ ውኃ አልነበረኝም ስለዚህ ያንተን አገልጋዮች
ወደ እኔ ልከሃቸዋል ነገር ግን ውኃ የለኝም ስለዚህ እባክህ ውኃ ስጠኝ እያልኩ
እግዚአብሔርን ለመለመን ነበር አላቸው፡፡
☞5ኛ☞በአንድ ወቅት በገዳመ አስቄጠስ ጾም ታወጀ፡፡ በዚያም ሳምንት አባ
ሙሴን ለማየት ከግብፅ ወንድሞቹ መጡ፡፡ አባ ሙሴም በእንግድነት
ተቀበላቸውና ምግብ ያበስልላቸው ጀመር፡፡ የእሳቱን ጢስ የተመለከቱ ጉረቤቶቹ
አባ ሙሴ ትእዛዝ አፍርሶ ምግብ ያበስላል ብለው ለገዳሙ ሓላፊዎች ተናገሩት፡፡
ሓላፊዎችም አሁን ተውት ሲመጣ እኛው ራሳችን እናናግረዋለን አሏቸው፡፡
☞ሓላፊዎችም አባ ሙሴን ጠርተው ለምን ምግብን እንዳበሰለ ተረዱ፡፡
በቀዳሚ ሰንበት ማኅበሩ ሁሉ ወደ ቤተክርስቲያን ሲጣ በዐደባባይ አባ ሙሴ
ሆይ የሰውን ትእዛዝ አልጠበቅም የእግዚአብሔር ትእዛዝ /እንግዳ ሆኜ መጥቼ
ተቀብላችሁኛል የሚለውን ግን ጠብቀሃል ብለው አመሰገኑት፡፡
☞የጻድቁ አባታችን የአቡነ ሙሴ ጸሊም የሕይወት ትምህርቶች ከብዙ በጥቂቱ
በእኔ በሀጥያተኛው ለበረከት ያክል ይቺን ጻፍኩላችሁ፡፡
☞የጹሁፍ ምንጭ(በዲያቆን ዳንኤል ክብረት ከተጻፈው "በበረሓ ጉያ
ውስጥ"ከተሰኘው መጽሐፍ የተወሰደ)
☞ከጻድቁ አባታችን ከአባ ሙሴ ጸሊም የሕይወት ትምህርት ተምረን ፍሬ
ለማፍራት ፈጣሪ ማስተዋሉን ያድለን፡፡
☞የጻድቁ አባ ሙሴ ጸሊም በረከታቸው ይደርብን፡፡
☞ሲራክ ተክለጻዲቅ የተዋህዶ ልጅ




Forward from: "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
➠✝️ወር በገባ በ 24  ሁሌም የምናስባቸው ሃያ አራቱ  ካሕናተ ሰማይ  የሰውን ልጆች ከመከራ ስጋ ከመከራ ነፍስ ይታደጉን🌹

♨የ24ቱ ካህናተ ሰማይ(ሱራፌል) ስማቸው የሚከተሉት ናቸው።➻
❶,ቅዱስ አካኤል
❷ ,ቅዱስ ፋኑኤል
❸ ,ቅዱስ ጋኑኤል
❹ ,ቅዱስ ታድኤል
❺ ,ቅዱስ አፍድኤል
❻ ,ቅዱስ ዘራኤል
❼ ,ቅዱስ ኤልኤል
❽ ,ቅዱስ ተዳኤል
❾ ,ቅዱስ ዮካኤል
❿,ቅዱስ  ገርድኤል
❶❶,ቅዱስ  ልፍድኤል
❶❷ ,ቅዱስ መርዋኤል
❶❸,ቅዱስ  ኑራኤል
❶❹,ቅዱስ  ክስልቱኤል
❶❺,ቅዱስ  ዑራኤል
❶❻,ቅዱስ  ባቱኤል
❶❼,ቅዱስ  ሩፋኤል
❶❽,ቅዱስ  ሰላትኤል
❶❾,ቅዱስ  ጣርኤል
❷○ቅዱስ  እምኑኤል
❷❶'ቅዱስ ፔላልኤል
❷❷ ,ቅዱስ ታልዲኤል
❷❸,ቅዱስ ፐሰልዲኤል
❷❹ ,ቅዱስ አሌቲኤል
የ ካህናተ ሰማይ በረከት ረድኤት አማላጅነት አይለየን በጸሎታቸው ይማረን

ቤተሰብ ይሁኑ

https://t.me/Orthodoxtewahdoc




Forward from: "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
†✝† እንኳን ለቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †✝†

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ሐዋርያዊ †††

††† ልደት †††

††† መልካም ዛፍ መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን
የወለዱት ደጋጉ: ጸጋ ዘአብ ካህኑና እግዚእ ኃረያ ናቸው::
እርሱ በክህነቱ: እርሷ በደግነቷ: በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ
እግዚአብሔር ጣፋጭ ፍሬን ሰጥቷቸዋል::

በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ ቢደርስባቸው ቅዱስ
ሚካኤል: ጸጋ ዘአብን ከሞት: እግዚእ ኃረያን ከትድምርተ
አረሚ (ከአረማዊ ጋብቻ) አድኗቸዋል:: በኋላም የቅዱሱን
መወለድ አብስሯቸዋል::

ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የተጸነሱት መጋቢት 24 ቀን
በ1206 ዓ/ም ሲሆን የተወለዱት ደግሞ ታኅሣሥ 24 ቀን
በ1207 ዓ/ም ነው:: በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት
ተገልጸዋል:: ቤታቸውም በበረከት ሞልቷል::

††† ዕድገት †††

የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው "ፍሥሃ ጽዮን" ይሰኛል::
ይሕንን ስም ይዘው: አባታቸው ጸጋ ዘአብን ተከትለው
አድገዋል:: በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን (ብሉያት:
ሐዲሳትን) ተምረዋል:: በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ አዳኝ
እንደ ነበሩ ይነገራል:: ዲቁናም ከወቅቱ ጳጳስ አባ ጌርሎስ
ተቀብለዋል::

††† መጠራት †††

አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮን ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት
ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ ተሰማ:: የክብር ባለቤት
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክት እያመሰገኑት
በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ::

የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ:: "ከዛሬ
ጀምሮ ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን::
ከዚህ በኋላ አራዊትን ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ:: ዘወትር
ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ በግርማ ዐረገ:: ቅዱስ ተክለ
ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በኋላ ሰዓትን አላጠፉም::
ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ ይዘው ቤታቸው
እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ::

††† አገልግሎት †††

ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከጳጳሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል
አገልግሎትን ጀመሩ:: በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው
ሽዋ (ጽላልሽ) አካባቢ ብቻ በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን
አሳምነው አጠመቁ:: ያን ጊዜ ኢትዮጵያ 2 መልክ ነበራት::

1ኛ. ዮዲት (ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች
ተጽዕኖ ወደ ደቡብ አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን
ክዷል: ወይም በባዕድ አምልኮ ተጠምዷል::
2ኛው ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት ክርስትናና ምናኔ
ተነቃቅቶ ነበር::

ግማሹ ሃገር በጨለመበት ወቅት የደረሱት ሐዲስ ሐዋርያ
አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት ጉልበታቸውና በኃይለ
መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ:: ሕዝቡን:
መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው: ማርያኖችን
(ጠንቋዮችን) አጥፍተዋል::

††† ገዳማዊ ሕይወት †††

††† ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮጵያን
ከማብራታቸው ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል::
እርሳቸው ከሁሉ የተሻሉ ሳሉም በ3 ገዳማት በረድዕነት
አገልግለዋል::

እነዚህም በአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ለ12 ዓመታት:
በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ ገዳም ለ7 ዓመታት: በደብረ
ዳሞ ከአቡነ ዮሐኒ ጋር ለ7 ዓመታት: በአጠቃላይ ለ26
ዓመታት አገልግለዋል::

በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ በኋላም ወደ ምድረ ሽዋ
(ዞረሬ) ተመልሰው በአንዲት በዓት ውስጥ ለ22 ዓመታት
ቆመው ጸልየዋል:: በተሰበረ እግራቸውም 6 ጦሮችን
በግራና በቀኝ ተክለው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል::

††† ስድስት ክንፍ †††

ኢትዮጵያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት
ከኢትዮጵያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት መካናት
ተባርከዋል:: ጻድቁ ምድረ እሥራኤል የገቡት በየመንገዱ
መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ ነበር::

ከወቅቱ ሊቀ ጳጳሳት አባ ሚካኤል ጋርም ተገናኝተው
ቡራኬን ተሰጣጥተዋል:: ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ በኋላ
ነው:: ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ
ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም
ተደሞ እንባቸው ይፈስ ነበር::

ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው ተክለ ሃይማኖት
የሚያዩት ቦታውን አልነበረም:: በገሃድ:-
*በቤተ መቅደስ ብስራቱን
*በቤተ ልሔም ልደቱን
*በቤተ ዮሴፍ ግዝረቱን
*በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን
*በቤተ አልዓዛር ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር::

የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል ወደ ሆነው ቀራንዮ
ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ ቢመለከቱት
ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን ቀየረና
ዓይናቸው ጠፋ::

በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ እመቤታችን ድንግል
ማርያም ፈጥና ደርሳ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን ወደ ሰማይ
አሳረገቻቸው::

††† በዚያም:-
*የብርሃን ዐይን ተቀብለው
*6 ክንፍ አብቅለው
*የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው
*ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው
*ከ24ቱ ካህናተ ሰማይም ተደምረው
*ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው
*"ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ
ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል::

††† ተአምራት †††

የቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት
የበዛ ነው::
*ሙት አንስተዋል
*ድውያንን ፈውሰዋል
*አጋንንትን አሳደዋል
*እሳትን ጨብጠዋል
*በክንፍ በረዋል
*ደመናን ዙፋን አድርገዋል::

ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን
መሥርተዋል:: በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ
ሕጻናት አብረው ኑረዋል:: በዘመናቸው ሰይጣን
ታሥሯልና::

††† ዕረፍት †††

††† ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን
ሆነው: መከራን በብዙ ተቀብለው: እልፍ አእላፍ ፍሬን
አፍርተው: በተወለዱ በ99 ዓመት: ከ8 ወር: ከ1 ቀናቸው
ነሐሴ 24 ቀን በ1306 ዓ/ም ዐርፈዋል:: ጌታ: ድንግል
ማርያምና ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል:: 10
ትውልድ የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል::

††† በዚህ ዕለት አባታችን ተክለ ሃይማኖት ለ22 ዓመታት
የቆሙበት ቀኝ እግራቸው መሠበሩንና በአንድ እግራቸው
ለ7 ዓመታት ቆመው መጸለያቸውን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን
ታስባለች::

††† ጥር 24 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1አቡነ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት
2.ቅድስት ማርያ ግብጻዊት
3.ታላቁ አባ ቢፋ
4.አባ አብሳዲ ቀሲስ
5.ቅዱሳን ጻድቃነ ሐውዚን

††† ወርኀዊ በዓላት
1.አቡነ ዘዮሐንስ (ዘክብራን ገብርኤል-ጣና)
2.ቅድስት እናታችን ክርስቶስ ሠምራ
3.ቅዱስ ቶማስ ዘመርዓስ
4.ቅዱስ ሙሴ ጸሊም
5.ቅዱስ አጋቢጦስ
6.ሃያ አራቱ ካህናተ ሠማይ

††† "በድካም : አብዝቼ በመገረፍ : አብዝቼ በመታሠር :
አትርፌ በመሞት ብዙ ጊዜ ሆንሁ:: በድካምና በጥረት :
ብዙ ጊዜም እንቅልፍ በማጣት : በራብና በጥም : ብዙ
ጊዜም በመጦም : በብርድና በራቁትነት ነበርሁ . . .
የቀረውን ነገር ሳልቆጥር ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ
የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው::" †††
(፪ቆሮ ፲፩፥፳፫)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††

20 last posts shown.