30/07/2017 ዓ.ም
ከአማራ ፋኖ በሸዋ የተሠጠ መግለጫ
የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት በደ/ወሎ ዳውንት ላይ ከብልፅግና ጋር ባደረጉት ድርድርና ስምምነት መሠረት የአማራ
ፋኖ አደረጃጀትን በጋራ ለመዋጋት የተስማሙበትን አክብረዋል።
ለህዝባችን የሚያሳዝን ቢሆንም ተገደን ድርጅታችንን እና ትግሉን መጠበቅ ስላለብን የአፋሕድ ገረድ ቅጠረኛ ከነሹም አብዴታ ጋር በመሆን ድርጅታችን ላይ ወረራ ፈፅሟል በዚህ ወረራ በርካታ ሀይል ሲደመሰስ በርካቶች እጅ ሰጥተዋል። ለዚህ ድርጊታቸው እኛ ላይ ለፈፀሙት ሳይሆን ታጋዩ ላይ ለወሰድነው እርምጃ የአፋሕድ እና የአማራ ፋኖ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አመራሮችን ይቅር የማንላቸው መሆኑን እና የትግሉ ጠላፊዎች እነሱ መሆናቸው እንዲታወቅልን እንወዳለን።
የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ እና የአገዛዙ ሃይል በጥምረት በአማራ ፋኖ በሸዋ ላይ እኩይ ድንገተኛ ጥቃት መሰንዘራቸውን እያሳወቅን።
በተደረገበት ድንገተኛ ጥቃት የአማራ ፋኖ በሸዋ በድል ለመወጣት ተችሏል።
እንደሚታወቀው የአማራ ፋኖ በሸዋ በታሕሳስ ወር በ2017 ዓ.ም ለአማራ ሕዝብ ይጠቅማል ይበጃል ያልንውን አማራጭ በሙሉ በስራ አስፈፃሚዎች የወሰነና የነበረን ልዩነት በውይይትና በንግግር ይፈታል ብሎ በማመን በጥር ወር ለ14 ቀን የአንድነት መርሃ-ግብር አዘጋጅተን መነጋገራችንን በውስጥም በውጭም ያላችሁ አካላት የትግሉ ደጋፊዎች ታውቃላችሁ።
ሆኖም ግን ይህንን የሠላም አማራጮች በመግፋትና የአማራን ሕዝብ ሠላም እና የሕዝባችንን የትግል ግብ አሳልፎ ለጠላት በመስጠት በድጋሜ የሕዝባችንን ሰቆቃ ለማስረዘም በአማራ ፋኖ በሸዋ ላይ በሰኔ 23/2016 ዓ.ም እንዳደረጉት ወረራ ዘረፋ ዘለፋና ግድያ ድጋሜ በዛሬዋ ዕለት ማለትም 30/07/2017 ዓ.ም ከለሊቱ 10:00 ሰዓት ጀምረው ከአገዛዙ ሃይል ጋር በጥምረት በአማራ ፋኖ በሸዋ ላይ ጥቃት ፈፅመዋል።
የአማራ ፋኖ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ መነሻውን ከሞጃናወደራ ወረዳ በአራዳ ጎጥ በኩል ወደ በዞ ቀበሌ; በአይዞሽ አሞራ ወደ ጊፍት ቀበሌ ወረራ ያረጉ ሲሆን :-ሌላኛው የአገዛዙ ሃይል ለጠቅላይ ግዛቱ በማገዝ ከደ/ብርሃን ወደ ዘንደጉር ውጊያ በማቅናት ጦርነት ከፍቷል።
ይሕንን ጥቃት የአማራ ፋኖ በሸዋ እንደ አመጣጡ ያለምንም ኪሳራ በማጥቃት በመደምሰስ ና ግብዓት በማግኘት ግስጋሴውን ወደፊት አድርጓል።
የጠቅላይ ግዛቱ ሴራ ይህ ብቻ አይደለም ነፃ ያወጧቸውን ቀጠናዎች አገዛዙን ከመፋለም ወንድሙን ለመውጋት ጥሎ በመንቀሳቀስ ለአገዛዙ ሃይል ምቹ መደላድልን በመፍጠር ዓፄ-ይኩኑ አምላክ ክ/ጦር ና 7/70 ክ/ጦር ለማገዝ እንዳይቀሳቀሱ ከሰንበቴ ወደ አላላ ሃይል እንዲጨምር ና የኤፍራታ ግድም ወረዳን አገዛዙ እንዲቆጣጠረው አድርገዋል።
በተጨማሪ የከሠም ክ/ጦር ለእገዛ እንዳይቀሳቀሱ ና እንዳይተባበር ለማድረግ ደ/ብርሃን ያለውን የአገዛዙን ሃይል ጋብዘዋል።
ይህ ማለት ሰሞኑን 'አቶ ሽመልስ አብዲሳ 'የኦሮሚያ ክልል ፕ/ት የተናገረውን እና ያዘጋጁትን የሴራ ፖለቲካ ከጠላት ጋር በመተባበር በግልፅ አሳይተዋል።
" የአማራ ትግል ይጠራል እንጂ አይደፈርስም "
የአማራ ህዝብና የፋኖ ሰራዊት እንዲረዱን የምንፈልገው ለሰላም እጃችንን ዘርግተን እያለ በሴራ ከዋናው የአማራ ህዝብ ጠላት ጋር በመጣመር በጦርነትም ይሁን በፖለቲካ ለሚዘምትብን በሙሉ እጃችንን እና እግራችንን አጣጥፈን የማንቀመጥ መሆናችንን ለማሳወቅ እንወዳለን ።
በዚህ አጋጣሚ በሴረኞች እና በጥቅመኞች ተታላችሁም ይሁን ተገዳችሁ ወደ እርስበርስ ጦርነት የገባችሁ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን በሙሉ በሰላም ወደ አማራ ፋኖ በሸዋ መቀላቀል ለምትፈልጉ ያለምንም ጦርነት መቀላቀል ትችላላችሁ ።
ክብር ለተሰውት !
ድል ለአማራ ህዝብ !
የአማራ ፋኖ በሸዋ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ክፍል
@Showapress