Shewa press


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


ማንቻውንም አይነት ጥቆማ እና አስተያየቶችን ለማድረስ 👉 @Natuu8

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


30/07/2017 ዓ.ም
ከአማራ ፋኖ በሸዋ የተሠጠ መግለጫ

የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት በደ/ወሎ ዳውንት ላይ ከብልፅግና ጋር ባደረጉት ድርድርና ስምምነት መሠረት የአማራ
ፋኖ አደረጃጀትን በጋራ ለመዋጋት የተስማሙበትን አክብረዋል።

ለህዝባችን የሚያሳዝን ቢሆንም ተገደን ድርጅታችንን እና ትግሉን መጠበቅ ስላለብን የአፋሕድ ገረድ ቅጠረኛ ከነሹም አብዴታ ጋር በመሆን ድርጅታችን ላይ ወረራ ፈፅሟል በዚህ ወረራ በርካታ ሀይል ሲደመሰስ በርካቶች እጅ ሰጥተዋል። ለዚህ ድርጊታቸው እኛ ላይ ለፈፀሙት ሳይሆን ታጋዩ ላይ ለወሰድነው እርምጃ የአፋሕድ እና የአማራ ፋኖ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አመራሮችን ይቅር የማንላቸው መሆኑን እና የትግሉ ጠላፊዎች እነሱ መሆናቸው እንዲታወቅልን እንወዳለን።
የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ እና የአገዛዙ ሃይል በጥምረት በአማራ ፋኖ በሸዋ ላይ እኩይ ድንገተኛ ጥቃት መሰንዘራቸውን እያሳወቅን።

በተደረገበት ድንገተኛ ጥቃት የአማራ ፋኖ በሸዋ በድል ለመወጣት ተችሏል።
እንደሚታወቀው የአማራ ፋኖ በሸዋ በታሕሳስ ወር በ2017 ዓ.ም ለአማራ ሕዝብ ይጠቅማል ይበጃል ያልንውን አማራጭ በሙሉ በስራ አስፈፃሚዎች የወሰነና የነበረን ልዩነት በውይይትና በንግግር ይፈታል ብሎ በማመን በጥር ወር ለ14 ቀን የአንድነት መርሃ-ግብር አዘጋጅተን መነጋገራችንን በውስጥም በውጭም ያላችሁ አካላት የትግሉ ደጋፊዎች ታውቃላችሁ።

ሆኖም ግን ይህንን የሠላም አማራጮች በመግፋትና የአማራን ሕዝብ ሠላም እና የሕዝባችንን የትግል ግብ አሳልፎ ለጠላት በመስጠት በድጋሜ የሕዝባችንን ሰቆቃ ለማስረዘም በአማራ ፋኖ በሸዋ ላይ በሰኔ 23/2016 ዓ.ም እንዳደረጉት ወረራ ዘረፋ ዘለፋና ግድያ ድጋሜ በዛሬዋ ዕለት ማለትም 30/07/2017 ዓ.ም ከለሊቱ 10:00 ሰዓት ጀምረው ከአገዛዙ ሃይል ጋር በጥምረት በአማራ ፋኖ በሸዋ ላይ ጥቃት ፈፅመዋል።

የአማራ ፋኖ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ መነሻውን ከሞጃናወደራ ወረዳ በአራዳ ጎጥ በኩል ወደ በዞ ቀበሌ; በአይዞሽ አሞራ ወደ ጊፍት ቀበሌ ወረራ ያረጉ ሲሆን :-ሌላኛው የአገዛዙ ሃይል ለጠቅላይ ግዛቱ በማገዝ ከደ/ብርሃን ወደ ዘንደጉር ውጊያ በማቅናት ጦርነት ከፍቷል።

ይሕንን ጥቃት የአማራ ፋኖ በሸዋ እንደ አመጣጡ ያለምንም ኪሳራ በማጥቃት በመደምሰስ ና ግብዓት በማግኘት ግስጋሴውን ወደፊት አድርጓል።
የጠቅላይ ግዛቱ ሴራ ይህ ብቻ አይደለም ነፃ ያወጧቸውን ቀጠናዎች አገዛዙን ከመፋለም ወንድሙን ለመውጋት ጥሎ በመንቀሳቀስ ለአገዛዙ ሃይል ምቹ መደላድልን በመፍጠር ዓፄ-ይኩኑ አምላክ ክ/ጦር ና 7/70 ክ/ጦር ለማገዝ እንዳይቀሳቀሱ ከሰንበቴ ወደ አላላ ሃይል እንዲጨምር ና የኤፍራታ ግድም ወረዳን አገዛዙ እንዲቆጣጠረው አድርገዋል።
በተጨማሪ የከሠም ክ/ጦር ለእገዛ እንዳይቀሳቀሱ ና እንዳይተባበር ለማድረግ ደ/ብርሃን ያለውን የአገዛዙን ሃይል ጋብዘዋል።
ይህ ማለት ሰሞኑን 'አቶ ሽመልስ አብዲሳ 'የኦሮሚያ ክልል ፕ/ት የተናገረውን እና ያዘጋጁትን የሴራ ፖለቲካ ከጠላት ጋር በመተባበር በግልፅ አሳይተዋል።

" የአማራ ትግል ይጠራል እንጂ አይደፈርስም "

የአማራ ህዝብና የፋኖ ሰራዊት እንዲረዱን የምንፈልገው ለሰላም እጃችንን ዘርግተን እያለ በሴራ ከዋናው የአማራ ህዝብ ጠላት ጋር በመጣመር በጦርነትም ይሁን በፖለቲካ ለሚዘምትብን በሙሉ እጃችንን እና እግራችንን አጣጥፈን የማንቀመጥ መሆናችንን ለማሳወቅ እንወዳለን ።

በዚህ አጋጣሚ በሴረኞች እና በጥቅመኞች ተታላችሁም ይሁን ተገዳችሁ ወደ እርስበርስ ጦርነት የገባችሁ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን በሙሉ በሰላም ወደ አማራ ፋኖ በሸዋ መቀላቀል ለምትፈልጉ ያለምንም ጦርነት መቀላቀል ትችላላችሁ ።

ክብር ለተሰውት !
ድል ለአማራ ህዝብ !

የአማራ ፋኖ በሸዋ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ክፍል

@Showapress


በለጠ ሞላ በህዝብ ተመርጦ ፓርላማ የገባውን ደሳለኝ ጫኔን ለመዝለፍ መሞከሩ ፈገግ ያሰኛል¡

ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ ማለት በ ህይወቱ ተወራርዶ ለወጣበት ህዝብ በፓርላማ ድምፅ የሆነ ብቸኛው እንቁ የ አማራ ጀግና ነው።

@showapress


አብን ከዚህ በኋላ ከመኖሩ ይልቅ ባለመኖሩ የአማራን ሕዝብ የሚጠቅም ፓርቲ ነው''

ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ

@showapress


ከአራቱም ግዛቶች የተሰጠ የጋራ አቋም።

@showapress


ሰከላ ከተማን የአማራ ፋኖ በጎጃም በዚህ ሰዓት ተቆጣጥሯል።

#ዘመቻአንድነት
@showapress


በሰሜን ሸዋ የቀጠለዉ እገታና አንድምታዉ ዝምታዉ ለምን?
(ታዬ ደንደአ )
➖➖➖
ሰሜን ሸዋ ኦሮሚያ ክልል... እጅግ አደገኛ የእገታ ወንጀል ለዓመታት ቀጥሏል። የዞኑ ነዋሪዎች በየተራ ከከተማና ከገጠር ይታገታሉ። እገታዉ በተመሳሳይ በመንገደኞች ላይም ሲፈፀም ዛሬ ደርሷል። ለታጋቾች ማስለቀቂያ በሚሊየኖችና በመቶ ሺዎች ይጠየቃል። የቻለ ጥሪቱን ሽጦ ወይም ዘመድ አዝማድ አስቸግሮ በመክፈል ይለቀቃል። ከፍያዉ ደግሞ ከካሽ ባሻገር በባንኮች ጭምር እንደሚፈፀም ኢሰመኮም አረጋግጧል። መክፈል ያልቸለዉ እንደሚገደልም ታዉቋል። በዚህ ምክንያት ብዙዎች ጥሪታቸዉን በመነጠቅ ለከባድ ችጋር ተጋልጧል። በርካቶችም ህይወታቸዉን አጥቷል።

ትላንትም በሰሜን ሸዋ ወረ-ጃርሶ ወረዳ የተለመደዉ አሳዛኝ የእገታ ወንጀል መፈፀሙን ሰምተናል። አንድ የመንገደኞች አዉቶቢስ ላይ ተኩስ ተከፍቶ በርካቶች ሲቆስሉ ከአስር በላይ ንፁኃን ዜጎች መገደላቸዉ ተዘግቧል። ታፍነዉ የተወሰዱ ስለመኖራቸዉም ይነገራል። ዜጎች በዚህ ሁኔታ መንገድ ላይ መቅረታቸዉ እጅግ ያሳዝናል። የዜጎችን ደህንነት የመጠበቅ ኃላፊነት ያለበት አካል ግን የፓርክና የሪዞርት ግንባታ ላይ አተኩሯል።

ከሁለት ቀን በፊት አንድ የፖሊስ ኢንስፔክተር ሁለት መቶ ብር ጉቦ መቀበሉ ትልቅ ዜና ነበር። ኢቲቪና ፋናም "ሌብነት ላይ ለተጀመረዉ ትግል አበረታች እርምጃ" ብለዉታል። ከሳምንት በፊትም "ሀሰተኛ መረጃን ለማጋለጥ" ጥረዋል። ጉዳዩ የማይመለከታቸዉ ባለስልጣናት ጭምር በየተራ ወጥተዉ የብርቱካን ድራማ "ኢትዮጵያን ለመግደል የተሸረበ ሴራ ነዉ" ብለዉናል። የበርካታ ዜጎችን ህይወት የቀጠፈዉና አካል ያጎደለዉ የትላንቱ ወንጀል ግን ዝም ተብሏል። የሁለት መቶ ብር ጉቦ ያንበገባቸዉ ኢቲቪና ፋና በሚሊዬኖች እየዘረፈ ብዙ ዜጎችን ለመከራ ያጋለጠዉ ተደጋጋሚ የእገታ ወንጀል ምንም ያልመሰላቸዉ ለምን ይሆን? የኢትዮጵያ ህዝብ በሀሰተኛ መረጃ እንዳይጎዳ በዚያ ልክ የተረባረቡት ሚዲያዎችና ባለስልጣናት ንፁኃን ዜጎች በየግዜዉ በመታገት ሲገደሉና አካላቸዉን ሲያጡ ለምን አያማቸዉም? በድራማዉ የታሰበለት የኢትዮጵያ ህዝብ የትላንቱን ተጎጂዎች አያጠቃልልም እንዴ?

ተጨማሪ ጥያቄዎችም አሉ። መጠኑ ቢለያይም በኦሮሚያ የነዋሪዎች እገታ በየቦታዉ ተለምዷል። በሰላም ወጥቶ መግባት በአብዛኛዉ ቅንጦት ሆኗል። ሰላም ሳይረጋገጥ ስለብልፅግና መስበክም ቀልድ ይሆናል። ይሁንና በዚህ ሁሉም ይመሳሰላል። በመንገደኞች እገታ ላይ ግን ግልፅ ልዩነት ይታያል። ከመንገዶች ሁሉ የጎጃም መስመር በዋናነት ተደጋጋሚ ጥቃቶችን አስተናግዷል። የዚህ መስመር ላይ ብዙዎች ተዘርፈዉ ለመከራ ሲጋለጡ በርካቶች ህይወታቸዉንና አካላቸዉን አጥተዋል። ሚስጢሩ ምንድ ነዉ? አጋቹስ በትክክል ማን ይሆን? ተመሳሳይ ወንጀል በተደጋጋሚ ተመሳሳይ ቦታ ላይ ለምን ይፈፀማል? ኃላፊነት ያለበት አካልስ ለምን ዝም ይላል? ይህ አደገኛ ወንጀል በመንግስት ሚዲያ የማይዘገበዉስ ለምንድነው? በርግጥ የእገታዉ ዓላማ ገንዘብ ማግኘት ብቻ ነዉ ወይስ የፖለቲካ ቁማር አለበት? ምናልባት የፖለቲካ ቁማር ኖሮበት ዓላማዉ ኦሮሞንና አማራን ለማጣላት ከሆነ ውጤቱ ማንን ይጠቅማል? ኢቲቪና ፋና ልክ እንደብርቱካን "ድራማ" ተረባርበዉ ቢያጋልጡትስ?

ለሟች ወገኖቻችን እጅግ አዝኛለሁ! የቆሰሉትም ፈጥነዉ ይድኑ ዘንድ እመኛለሁ! ዋናዉ ጉዳይ ግን የፖለቲካ ቀዉሱንና እንቆቅልሹን መፍታት መሆኑን ልብ እንበል እላለሁ!

@showapress


(ዘመቻ አንድነት በጎጃም ግንባር|፲፱ኛ ቀን)

፩. 5ኛ ክፍለጦር ወርቅ አባይ ብርጌድ 83 የሚሊሺያ አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ፋኖን ተቀላቅለዋል።

፪. ባህርዳር ላይ!

ሀ- የአማራ ፋኖ በጎጃም ፩ኛ ክፍለ ጦር በሰጠው ልዩ ኦፕሬሽን ባህርዳር ብርጌድ የቦንብ እና የሞርተር ጥቃት ተፈፅሟል። በቦንብ ጥቃቱ ቀበሌ 16 ስታዲየም አካባቢ ጥበቃ ላይ የነበሩ የአገዛዙ ጭፍሮች ሙትና ቁስለኛ ሁነዋል።

ለ- ዘሪሁን 13 በመጠቀም ቆላ ፅዮን ማርያም ቀበሌ 11 ስራ አመራር መሰብሰቢያ አካባቢ ሊሰበሰብ የነበረው ካድሬ እንዲፈረጥጥ ተደርጓል።

ሐ- በሰባታሚት በኩል ደግሞ የሞርተር ጥቃት በመፈፀም በአገዛዙ ሊሰራ የታሰበው ፖለቲካዊ ፕሮፓጋንዳ እንዲከሽፍ ተደርጓል።

የቦንብ ጥቃቱ ከትላንት ምሽት ጀምሮ ነው የተፈፀመው።

[አማራ ፋኖ በጎጃም]
መጋቢት 28/2017 ዓም

@Showapress


መከላከያ ደምስሸዋለሁ ያለውን የሽኔ አመራር የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በፀጥታ ዘርፍ ሹመት ሰጥቶታል።

@showapress


"ይህ የመጨረሻው የሚያነባ የአማራ ትውልድ ይሆናል"

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ መግለጫ!

ባለፉት 500 ዓመታት ለነጋሪም፣ ለሰሚም ለፀሐፊም ያስቸገሩ ለታሪክ ገፆች የከበዱ ፍጅቶች በአማራ ህዝብ ላይ ተፈፅመዋል። በተለይ ባለፉት ሰማንያ ዓመታት ውስጥ ጠላቶቻችን አማራ አልቦ ምድር ሊፈጥሩ ጥረዋል። የጠላቶቻችን የጦር መኳንንት አማራ የሌለባት ኢትዮጵያን ለአለቆቻቸው ሊያስረክቡ ቃል ገብተው ሊፈፀሙት ተንቀሳቅሰዋል። በመሆኑም ሚሊዮን አማራዎች በዚህ እቅድ የተነሳ አልቀዋል። ይህንን ግፍ ለማስቆም ቀደምቶቻችን በተለያየ ጊዜ የተሳካም ያልተሳካም የጀግንነትና የአርበኝነት ስራ ሰርተዋል። በነዚህ ሰማንያ ዓመታት ውስጥ አንድ የአማራ ጭንቅላት ተቆርጦ ሰላሳ ብር ተሽጧል። የአማራን አንገትበላይ በብዛት ያመጣ ባንዳ ለስኬቱ ተሸልሟል። አካላችንም መሬታችንም እየተቆራረጠ ተጥሏል፤ ተሸጧልም። በዚህ ሁሉ ረጅም ዘመን ውስጥ አማራ ፈጅ ጥፋቶችና ክፋቶች ምንጫቸው አንድ በመሆኑ የዚሁ ተቀጥላና ዲቃላ ሕዝብ አውዳሚ መንፈስ የወለደው የአብይ አህመድ የጥፋት ዘመን ዛሬ መጋቢት 24 ቀን 2017 ዓ/ም ሰባተኛ ዓመቱን አስቆጥሯል::

አማራም ከአምስት መቶ ዓመት የውድቀትና የውርደት ዘመን በኋላ በዚህኛው ትውልድ ጊዜ ነቅቶ ተደራጅቶ ታጥቆና የመከራ መሻገሪያ ርዕዮቱን ሰንቆ የተነሳ ሲሆን ከሰባት መቶ ዓመታት በላይ የከበዱ ሰባት ዓመታት እያሳለፈ ይገኛል። አብይ አህመድ የአማራ ህዝብ አንድ አንገት ኖሮት በአንድ ጊዜ በአንድ ቅፅበት በአንዳች ሰይፍ ቆርጦ ጥሎት ቢገላገል ደስታውን መሸከም የማይችል የ21ኛው ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያዊ ካሊጉላ ነው። በአማራ ህዝብ የሺህ ዓመታት ታሪክ ጉዞ በተለያየ ጊዜ ብቅ እያለ ሲያደማንና ሲያወድመን የኖረ መንፈስ አሁንም በአብይ አህመድ ዘመን አብይን ፈጥሮ በአብይ አህመድ በኩል እየወጋንና እየጨፈጨፈን ይገኛል።

ጉዳዩ ተራ ፖለቲካዊ ግብግብ አይደለም። የአማራ ህዝብ እየተከላከለ ያለው ጦርነት ጥልቅ የማንነት የታሪክና የእሴት ጦርነት ነው። ከፖለቲካ ትግል አለፍ ያለ ውስብስብ ጦርነት ነው። ጠላቶቻችን አማራ አልባ ኢትዮጵያን ሊፈጥሩ ለራሳቸው ቃል እንደገቡት ሁሉ ተመሳሳይና አንድ መንፈስ የወለደው አብይ አህመድና ዘመኑ አማራ የሌለባት ኢትዮጵያን ሊፈጥሩ አየተጉ ይገኛሉ። ይህ የጥፋት ፕሮጀክት ነው ዛሬ መጋቢት 24/2017 ዓ/ም ሰባት ዓመት የሞላው!

ሰባት የውድመትና የመንቃት፣ የደምና የድል፣ የመውደቅና የመነሳት፣ የእልቂትና ጠላትን በኩራትና በጀግንነት የመጋፈጥ ተጋፍጦም የማሸነፍ አስገራሚ አመታት!

ሰባት በደምና በድል የተነከርንባቸው፣ በእንባና ሳቅ የታጠብንባቸው፣ ከሞት ውቅያኖስ ተስፋ፣ ከእልቂት ባህር ድል የቀዳንባቸው ግራጫ አመታት!

አሁን የአማራ ልጆች ተነስተናል ነቅተናል ተደራጅተናል ታጥቀናል ድልን ለምደናል። ህልውናችንን የምናረጋግጥበት ዘመን እሩቅ እንደማይሆን ከተረዳንም ውለን አድረናል። እንደ ህዝብ ለእልቂት ሳይሆን ለድል መፈጠራችንን አምነናል። ውስጣዊ አማራዊ አንድነታችን በመዋቅር ደረጃ ማረጋገጥ ብቻ ይቀረናል። ይህም በቅርቡ እውን ይሆናል። ከዛማ ማን ከፊታችን ይቆማል? ማንም። ተራሮች እንኳን ቀና ብለው አያዩንም። ውሃው ይጎድልልናል፤ ነፋስም ይታዘዘናል።

ይህ የመጨረሻው የሚያነባ ትውልድ ይሆናል።

ክብር ለትግሉ ሰማዕታት !
ድላችን በተባበረ ክንዳችን

የአማራ ፋኖ በሸዋ
የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር
የአማራ ፋኖ በወሎ(ቤተ-አማራ)
የአማራ ፋኖ በጎጃም

ዘመቻ አንድነት ግለቱን ጠብቆ ይቀጥላል

መጋቢት 24/2017 ዓ/ም

@showapress


አሳዛኝ ጭፍጨፋ ሰሜን ሜጫ ወረዳ ብራቃት ከተማ

በሰሜን ጎጃም ዞን ሰሜን ሜጫ ወረዳ ብራቃት ከተማ ከትናንት መጋቢት 22/07/2017 ዓ.ም ጀምሮ በአብይ አህመድ ብልፅግና ቡድን አገልጋይ በሆኑት አድማ ብተና እና መከላከያ መካከል ከባድ የሆነ የእርስ በእርስ ውጊያ ተካሂዷል። እርስ በእርሳቸው በፈጠሩት የተኩስ ልውውጥ የብራቃት ከተማ ነዋሪዎችን በየሰፈሩ እየዞሩ ህፃናትና አረጋውያንን ጨምሮ ያገኛቸውን ንፁሃኖችን በአሰቃቂ ሁኔታ ጨፍጭፈዋል።

ከሟቾቹ መካከል የፍጣ ሚካኤል ቤተክርስቲያንን አስተዳዳሪን ጨምሮ ከወፍጮ ሲመለሱ የነበሩ እናቶችን እንዲሁም ቤት ለቤት እየዞሩ በር እየገነጠሉ ጭምር በመግባት ንፁሃኖችን ያለ ርህራሄ በአሰቃቂ ሁኔታ ገድለዋቸዋል።

እስካሁን አስከሬናቸው ያልተነሱ ንፁሃን እንዳሉ ሁኖ አስከሬናቸው የተነሳ የንፁሃን ሟቾች ስም ዝርዝር፦

ተ.ቁ ስም ዕድሜ
1. ገረም ይመኑ 65
2. ቻይና ይመኑ 40
3. ዋለ አለም 50
4. አየነው ሙላት 35
5. ዘላለም ጊዜው 25
6. ጊዜው ደለለ 36
7. አዳነ አርያ 40
8. ጀምበር ፀጋሁን 12
9. ልቦናው እንደሻው 27
10. ሙሉቀን ስሜ 46
11. ሙሉጌታ አለሙ 25
12. ቄ/ዋሴ ይግዛው 45
13. ፈንቴ አለልኝ 20
14. እንየው ጎለም 15
15. በለጠ ጊዜው 36
16. ታደለ ሙሉጌታ 28
17. ጋሻው አዳሙ 35
18. ጠና በላይ 42
19. ማንጠግቦሽ አበጀ 48
20. ጠጅቱ አላምር 33
21. ታደለ ሙሉየ 19
22. በለጠ ስንቴ 13
23. አበባው አዳነ 10
24. አለልኝ ዋለ 29
25. ታደለ ዋለ 36
26. ልቦናው ተሻገር 13
27. በውቀት ጎበዜ 10
28. ገሰሰ ጥላሁን 71
29. አበዋ ምኒችል 27
30. ታደሰ ጥሌ 33
31. አንችናሉ አጥናፉ 56
32. ባለው ጌቴ የአእምሮ በሽተኛ
33. ጥሩድል ሙሉ 19
34. በላይነሽ ደሴ 26
35. ሞገስ ሽቴ 43
36. አቡሽ ታረቀኝ
37. ወለላ ጌጡ 40
38. ምትኩ ዋለ
39. ፈቃዱ ፀጋዬ
40. ዋለ ንጉስ
41. አበባው መንግስት 10
42. ትዜ ገብሬ
43. ጋሹ
44. ሙሉጌታ
45. ፀና በላይ
46. ታደለ ሙንየ

ናቸው።

የሰማእታቱን ነብስ ይማርልን!

@Showapress


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
አገዛዙ አቅም አጥቶ ነው እንጅ ሰሜንን ለማጥፋት ነው የተነሳው እስካሁን ከ ከትግራይ እና ከ ኤርትራ ሀይሎች ጋር ምንም ግንኙነት አልነበረንም ወደፊት ግን ይኖረናል……ጀነራል ተፈራ ማሞ ከተናገረው።

@showapress


አማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ራንቦ ክፍለጦር ከድል መልስ ሚዳመራኛ ሬማ !!

@Showapress


የአማራ ፋኖ በሸዋ ከሰም ክፍለጦር ተስፋ ብርጌድ ረዘም ላለ ግዜ ያሰለጠናቸውን እስፔሻል ኮማዶ አስመረቀ።

@Showapress


የሸዋል ወር ጨረቃ ዛሬ በመታየቷ 1 ሺህ 446ኛው የዒድ አል-ፈጥር በዓል ነገ እሁድ መጋቢት 21 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚከበር ተገልጿል።
ለሙስሊም ወገኖቻችን በሙሉ መልካም በዓል ይሁንላችሁ‼️
ዒድ_ሙባረክ

@showapress


"በዘመቻ አንድነት" በባህርዳር የሚገኘው ራሱን የአማራ ክልል የፀጥታ መዋቅር ብሎ የሚጠራ ተቋም በይፋ ፈረሰ!

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የሕዝብ ግንኘነት መምሪያ የተሰጠ ወቅታዊ ማብራሪያ

እንደሚታወቀው አገዛዙ የአማራን ህዝብ ከምድረ-ገፅ እና ከታሪክ ማህደር ለማጥፋት እና ለመፋቅ ሀገሪቱ አለኝ የሚለውንለውን የአየር ኃይል፣ ሜካናይዝድ፣ እግረኛ እና በሀገሪቱ በመሰራት ላይ የነበሩ ሜጋ ፕሮጀክቶችን ጭምር በማጠፍ የሀገሪቱን በጀት ሙሉ በሙሉ ለጦርነቱ በመመደብና በመጠቀም በሕዝባችን ላይ ይፋዊ ጦርነት አውጆ ሲንቀሳቀስ ሁለት ዓመት ሞልቶታል።

ህዝባችንም ከራሱ ከአብራኩ በወጡ ሀቀኛ ልጆቹ በፋኖ አደረጃጀት እየተመራ ያለ አንዳች ድካምና መሰላቸት በመፋለም በክልሉ የአማራ ህዝብ ታሪካዊ ጠላት የሆነውን የብልፅግና መዋቅር፣ የፓርቲው አሽከር የሆነውን የፀጥታ መዋቅር (የፖሊስ የሚሊሻ የሰላም አስከባሪና እና ሌሎችም የፀጥታ ተቋማትን እንዲሁም አገዛዙን ስልታዊ በሆነ መንገድ ሲያገለግል የነበረውን የስም መንግስታዊ መዋቅር ሙሉ ለሙሉ በማፍረስ አገዛዙን ከአማራ ህዝብ ጋር ያለውን ግንኘነት ተመልሶ መቀጠል እንዳይችል አድርገን ቆርጠነዋል፤ የክልሉን 90% በላይ የሚሆንን መዋቅር በመቆጣጠር የማስተዳደር ስራው እየተፈፀመ ይገኛል።

እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ አገዛዙ የአማራን ክልል ከፋኖ ነጠክሁ፤ ሰላም ነው ፤ አሸነፍኩ እያለ በውሸት ማደንቆሪያ ማሽኖች በሆኑት የመገናኛ ዘዴዎቹ ኢትዮጵያዊያንን እና ዓለም አቀፍ ማህበረሰቡን እያወናበደ ይገኛል።

ከሰሞኑም የአማራ ፋኖ አደረጃቶች ማለትም የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አማራ)፣ የአማራ ፋኖ በጎጃም፣ የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር እና የአማራ ፋኖ በሸዋ የአገዛዙን የውሸት ካፕ ቀዳዶ እርቃኑን በማስቀረት ለኢትዮጵያውያን እና ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማሳየት የመጨረሻው ጠርዝ ላይ መሆኑን ግልፅ ለማድረግ "ዘመቻ አንድነትን" በማወጅ አገዛዙን በበርካታ የስርዓቱ አገልጋዮች ላይ እርምጃ እየወሰድን እንገኛለን።

አገዛዙ “የፀጥታ ኃይላችን ከመቸውም ጊዜ በላይ ጠንክሯል፣ ፋኖ ተበትኗል” የሚለው የሀሰት ፕሮፖጋንዳ "በዘመቻ አንድነት" ውሃ በልቶታል፤ የአማራ ክልል የፀጥታ መዋቅር ሙሉ ለሙሉ ፈርሷል፤ የአገዛዙ የጀርባ አጥንት የሚባሉት የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ የነበረውን ደሳለኝ ጣሰውን ጨምሮ በርካቶችን ከሕዝባቸው በላይ ከሚሞቱለት ስልጣን አንስቶ የቁም እስረኛ አድርጓል። የክልሉ የፖሊስ ኮምሽን ኮምሽነር የነበረውን ደስየ ደጀንን ከኃላፊነት አንስቶ አባሮ የቁም አስረኛ አደርጓል። የክልሉ የሚሊሻ ፅ/ቤት ኃላፊ የነበረውን ኮ/ል ባምላኩ አባይን ከስልጣን አንስቶ የቁም እስረኛ አድርጓል። በአገዛዙ ቤት የሸብር መንፈስ ብቻ ሳይሆን እርስ በእርስ መወነጃጀሉ በዝቷል። አበባው ታደሰ የተባለ የጨፍጫፊው ቡድን መሪ በብስጭት “ካላገዛችሁን ክልሉን ለቀን እንወጣለን” በማለት መዛቱን በመረጃና ደህንነት መዋቅራችን አረጋግጠናል።

ይህ ሁሉ ተዓምር እየተፈጠረ ያለው "ዘመቻ አንድነትን" የአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች አውጀው ካላቸው አቅም ላይ ከግማሽ በታች እየተጠቀሙ ባለበት ወቅት መሆኑ ድሉን እጥፍ ድርብ ያደርገዋል።

ክብር ለትግሉ ሰማዕታት
ድላችን በተባበረ ክንዳችን

የአማራ ፋኖ በወሎ(ቤተ-አማራ)
የአማራ ፋኖ በጎጃም
የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር
የአማራ ፋኖ በሸዋ

ዘመቻ አንድነት ግለቱን ጠብቆ ይቀጥላል!

መጋቢት 20 ቀን 2017 ዓ/ም

@Showapress


አምስተኛዉ እጅግ መሠረታዊ የጋራ ችግሮች እያሉብን መከፋፈላችንን ይመለከታል። ከብልፅግና አዉሮፕላን ውጭ ያለን ሰዎች በዋጋ ግሽበቱ ምክንያት መኖር ቸግሮናል። ባለፈዉ ሳምንት ብቻ ነዳጅ በሊትር 11 ብር ገደማ ጨምሯል። ይህ ችግር አማራ-ኦሮሞ፣ ትግራዋይ-ሲዳማ፣ ሶማሌ-አፋር፣ ወላይታ-ጋሞ ወይም ሙስሊም-ክርስቲያን ብሎ ሳይለይ ሁላችንንም ይጎዳል። የሰላም መደፍረሱም በተመሳሳይ የሁላችንን ህይወት ይነካል። ለስድስት ዓመታት የቀጠለዉ የወንድማማች ጦርነት በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ልጆቻችንን፣ ወንድሞቻችንንና እህቶቻችንን በልቷል። ሀብታችንም በትሪሊዬኖች ባልተገባ ጦርነት ወድሟል። በተለያዩ ቦታዎች በኮሪደር ስም አያሌ ዜጎች ያለምንም ካሳ ከይዞታቸዉ ተፈናቅሏል። የቀይ ባህር ዓሳ በየግዜዉ ችጋርን ለመሸሽ የሚሰደዱ ልጆቻችንን ይመገባል። በእዉነቱ ከሆነ እነዚህ ጉዳዮች -እነፋናን ባያሳስቡም- ሁላችንንም ያለልዩነት ሊያንገበግቡን ይገባል። ይሁንና በትናንሽ አጀንዳዎች ስንጨቃጨቅ ይታያል። ለምን እንደዚህ ይሆናል? ሊያስተባብሩን የሚገቡ ትላልቅ የጋራ አጀንዳዎችና ችግሮች እያሉን ምን ይከፋፍለናል? አሰቀድመዉ አንደነገሩን ፖለቲካ ቁማር ከሆነ እንደህዝብና እንደሀገር እንዳንበላ ራሳችንን ፈትሸን ማረም ይኖርብናል!

©ታየ ደዳዓ

@Showapress


የትወናዉና የዶክመንተሪዉ ወግ
ማጣሪያ ጥያቄዎች...(በ አቶ ታዬ ደዳ)

በቀድሚያ እንኳን ለፊቼ ጨምበላላ በዓል አደረሰን! ሲቀጥል ፋና ብሮድካስቲንግ በብርቱካንና በኢ.ቢ.ኤስ ጉዳይ ላይ የሠራዉን ዶክመንተሪ አይቻለሁ። በሌሎች ቻናሎችም ተላልፎ ሊሆን ይችላል። ዓላማዉ ህዝብ በሀሰተኛ መረጃ እንዳይደናገር እዉነትን የማዉጣት ጥረት እንደሆነ ተገልጿል። የተባለዉ ከልብ ከሆነ ለህዝብና ለእዉነት በዚህ ፍጥነትና ጥልቀት መቆርቆር የጀግንነት ኒሻን ይገባዉ ይሆናል። ችግሩ የማጣሪያ ጥያቄዎች መኖራቸዉ ነዉ። በዚህ ጉዳይ እንደግልም እንደህዝብመ ብዙ ማለት ይቻላል። ለአሁኑ ጰአምስት ነጥቦችን ብቻ እንመልከት።

መጀመሪያ የጎደሉ የዶክመንተሪዉ ክፍሎችን መፈተሽ ነዉ። ብርቱካን ተመስገን ህዝብን ለማሳሳት በሴረኞች ተመልምላ የሀሰት ድራማ መተወኗን ከዶክመንተሪዉ ሰምተናል። ፖለቲካ ቁማር መሆኑ በግልፅ የተነገረዉ ህዝብ ነገሩን በቀጥታ ለማመን የሚቸገር ቢሆንም ሴራዉን ሸርቧል የተባሉ ሰዎችም ተጠቀሷል። ሊመለሱ የሚገባቸዉ ጥያቄዎች ግን አሉን። በሀገራችን ነባራዊ ሁኔታ በተጨባጭ ተደፍረዉ ከህይወት ጎዳና የወጡ በርካታ ሴቶች እያሉ "ሴረኞቹ" ድራማ መስራት ለምን አስፈለጋቸዉ? ድራማ ቢያስፈልግስ በተለያዬ ምክንያት ህይወት ተበላሽቶባቸዉ በጎዳና የሚኖሩ ብዙ የመከራ ሰላባ ሴቶች እያሉ ባለትዳር፣ የልጅ እናትና የተመቸ ኑሮ የነበራት ብርቱካን ለትወናዉ በምን መስፈርት ተመረጠች? የኢ.ቢ.ኤስ ጋዘጠኞች የድራማዉ አካል ከሆኑ ቢያንስ ብርቱካን ከአዲስ አበባ ሳትወጣ ድራማዉን ለምን በአየር ላይ አዋሉ?

ሌሎች ጥያቄዎች! ብርቱካን ድራማዉን በትክክለኛ ስሟን ከመተወን ፈንታ ከደምቢዶሎ ዩንቨርሲቲ መታገታቸዉ ከተነገረላቸዉ ተማሪዎች የአንዷን ስም ለምን አልተጠቀመችም? ከትወናዉ በፊት የብርቱካን ስልክ ተጠልፎ ከሆነ ለምን? ድራማዉ ከተጋለጠ በኋላስ የብርቱካን ስልክ እንደሚጠለፍ እየታወቀ "ሴረኞቹ" እንዴት በቀጥታ ደወለዉ ድምፃቸዉን አስቀዱ? ይህን ቀላል ነገር መገመት አቅቷቸዉ ነዉወይስ ለዶክመንተሪዉ ግበዓት ለመጨመር ይሆን? ብርቱካን ህይወቷ አደጋ ላይ መሆኑ ተነግሯት ስልኳን ጥላ ፋኖዎች ወዳሉበት እንድትሸሽ ሲነገራት ምንን ተማምና ሳትሸሽ ቀረች? የአካዉንቲንግና የፋይናስ ድግሪ ያላት ብልህ ሴት ማምለጥ አቅቷት ይሆን? የተከበረ ትዳርና የተመቻቸ ኑሮ የነበራት ብልጧ ብርቱካን ለትራንስፖርት የሚሆን አምስት ሺህ ብር እንኳን ሳትቀበል ህይወቷን ለምን ለአደጋና ለዉርደት አጋለጠች? እነመዓዛ መሀመድ ሲደውሉላት ድምጿ እጅግ መደንገጧን የሚያሳብቅባት ብርቱካን ዶክመንተሪዉ ላይ እንዴት ተረጋጋች? በፍቷ ላይ ሀፍረትና ፀፀት የማይታይባት ለምን ይሆን? የነብርቱካን ቤት ውስጡ በዶክመንተሪዉ ታይቷል? ትወናዉንና ዶክመነተሪዉን በአግባቡ ለመረዳት እነዚህ ቁልፍ ጥያቄዎች መመለስ ያለባቸዉ ይመስለኛል። ጥያቄዎቹን በትክክል መመለስ ማን ለምን ትወናዉን እንደሰራ ጥቆማ ይሰጣል። አደናጋሪዉና የድራማዉ ባለቤትም ይታወቃል:: ጥያቄዎቹ ካልተመለሱ ግን ዶክመንተሪዉ ከትወናዉ በላይ ህዝብን ያደናግራል። በተለይም በሀገራችን የተንሰራፋዉን አሰቃቂ የሴቶች ጥቃትን ለመሸፈን የታሰበ ድብቅ ነገር ሊኖርም ይችላል። ይህ ከሆነ ደግሞ በትወናዉ ሂደት ላይ የሚና መለዋወጥ ይኖር ይሆናል።

ሁለተኛዉ ወንጀልን መርምሮ ተጠያቂነት ለማስፈን የተደረገዉ ጥረትን ይመለከታል። በማንም ላይ የትኛዉም ዓይነት ወንጀል ቢፈፃም በፍጥነት መርምሮ ተጠያቂነትን በማረጋገጥ ውጤቱን ለህዝብ ይፋ ማድረግ ይገባል። ከዚህ አንፃር ፖሊስና ፋና የሠሩት ይበረታታል። ውስጡን ለቄስ ብለን ብርቱካና ኢ.ቢ.ኤስ ሀሰተኛ መረጃን አሠራጭተዉ ከሆነ በልኩ ሊጠየቁ ግድ ይላል። ዋናዉ ጥያቄ ግን ህዝብ እንዳይደናገር አስቦ የብርቱካንንና የኢ.ቢ.ኤስን ጉዳይ መርምሮ እዉነቱን ለማዉጣት ከብርሃን በላይ የፈጠነዉ ፖሊስና ሚዲያ በከረዩ አባገዳዎች ላይ በመንግስት የተፈፀመዉን የጦር ወንጀል መርምረዉ እዉነቱን ለህዝብ ማሳወቅ ለምን አቃታቸዉ? በነገራችን ላይ ፋና በከፍተኛ ግፍ ሰለተረሸኑት የከረዩ አባገዳዎች ዜና ሰርቶ ያዉቃል? በሜታ ወልቂጤ ተደፍራና ተገድላ የተሰቀለችዉ ህፃን ስምቦ ብርሃኑ ጉዳይ ተመርምሮ ጉዳዩ ለህዝብ ተገልጿል? ወይዘሪት አያንቱ ተስፋሁን በቅርቡ በነቀምት ከተማ ተገድላ መገኘቷ የምርመራና የሚዲያ አጀንዳ ሆኗል? ፖለስና ፋና በሰምቦ ብርሃኑና በአያንቱ ተስፋሁን ጉዳይ ያልፈጠኑት ለምን ይሆን? ሀሰተኛ መረጃን ከማሰራጨት በላይ እጅግ የከፉ ወንጀሎች ተድበስብሰዉ አልቀሩም? የብርቱካንና የኢ.ቢ.ኤስ ጉዳይ በዚህ ልክ ፍጥነትና ግልፅነት ያገኘዉ ለምን ይሆን? ለኛ ያልተገለፀ ሌላ እዉነት ሊኖር እንደሚችል መገመት አይከፋም ለማለት ነዉ።

ሶስተኛዉ መታገትና መደፈር ለኢትዮጵያውያን ሴቶች አሁን ላይ እንግዳ አለመሆኑ ነዉ። በቅርቡ እንኳን በሰሜን ሸዋ አሊዶሮ አከባቢ ሴቶች የሚገኙበት አንድ አዉቶቢስ ሙሉ ዜጎች መታገታቸዉ በBBC ሳይቀር ተዘግቧል። እነዚህ ዜጎች ያሉበት አይታወቅም። እየተደፈሩም ሊሆን ይችላል። ለፋናና ለፖሊስ ግን የምርመራ አጀንዳ አልሆነም። ከዚህ ቀደምም በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በትግራይ፣ በደቡብና በሌሎች ቦታዎችም በእህቶቻችን ላይ ዘግናኝ የመድፈር ወንጀሎች ሲፈፀሙ ነበር። በኢ.ቢ.ኤስ የቀረበዉ የብርቱካን ታሪክ እንደተባለዉ ትወና እንኳን ቢሆን እንደሀገር አሁን ካለንበት ተጨባጭ ሁኔታ አንፃር ከእዉነት የራቀ አይደለም። ከዚያ የባሱ ከባባድ ወንጀሎች በፀጥታ አካላት ሳይቀር ሲፈፀሙ አይተናል። እንዲህ ዓይነት ኢ-ሰበዓዊና አስነዋሪ ወንጀሎችን ስንመለከት እንደህዝብ መተባበር ሲገባን በብሔር ወይም በሌላ ምክንያት ከፋፍሎ ምን ያነታርከናል? የአንዳችን ቁስል እንዴት ለሌላችን መዝናኛ ይሆናል? ደግሞ ግለሰብ ወይም ወንጀለኛ ቡድን በጭካኔ ለሚፈፅመዉ ጥፋት ብሔር በምን ሂሳብ ይጠየቃል? ከህግ አኳያ አንድ ሰዉ የሚፈፅመዉ ወንጀል ወንድሙን እንኳን እንደማይመለከት ይታወቃል። እንደህዝብ የጅምላ ፍረጃ ላይ ራሳችንን መፈተሽ ያለብን ይመስለኛል። ባልተገባ ጉዳይ መፈራረጃችንና መነታረካችን በኪሳራችን ለሚያተርፉ ቁማርተኞች ብቻ ይጠቅማል።

አራተኛዉ ፋና ብሮድካስቲንግ በሀሰተኛ መረጃ ላይ የያዘዉን አቋም ይመለከታል። በብርቱካን ጉዳይ ዶክመንተሪ የተሰረዉ ህዝብ በሀሰተኛ መረጃ እንዳይደናገር መሆኑ ተነግሮናል። በእዉነቱ ይህ ግልፅነት የመፍጠር ተግባር እንደፋና ካሉ ሚዲያዎች ይጠበቃል። ይሁንና ታህሳስ 01/2016 ሌሊት ከታሰርኩ በኋላ ፋና "አቶ ታዬ ደንደአ ኦነግ ሸኔን በቤቱ በመሸሸግ ሰዎችን ሲያሳግት ነበር" የሚል ሀሰተኛ መረጃን ለህዝብ አስተላልፏል። ይህ ዉሸት እንደህዝብ ተወካይነቴ ስሜን ከማጠልሸቱ ባሻገር ህዝቡን አደናግሯል። ፋና በኋላ በሰበዓዊ መብቶች ኮሚሽን ሲጠየቅ "ከፀጥታ ግብረኃይል ተዘጋጅቶ የመጣዉን አነበብኩ እንጂ ሀሰተኛ መረጃዉን እኔ አላዘጋጀሁትም " ብሏል። እዉነቱ ከታወቀ ወድህም ማስተባበል ቸግሮታል::: ያኔ ሆን ብሎ ህዝብን ለማደናገር ሀሰተኛ መረጃን ሳያጣራ ተቀብሎ ያሰራጨዉና በኋላ እንኳን ስህተቱን ለማስተባበል የተቸገረዉ ፋና ዛሬ ህዝቡ እንዳይደናገር ሀሰተኛ መረጃን ለመከላከልና ኢ.ቢ.ኤስን ለማጋለጥ በብርሃን ፍጥነት ረጅምና ረቂቅ ዶክመንተሪ የሰራዉ በምን ፎርሙላ ነዉ? የራሷ አሮባት ያስብላል!



18 last posts shown.