Ministry of Education


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Telegram



Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Telegram
Statistics
Posts filter


የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ የ6ኛ እና 8 ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና የሚሰጥባቸውን ቀናት ይፋ አደርጓል።

የ8ኛ ክፍል ፈተና ሰኔ 19 እና 20 እንዲሁም የ6ኛ ክፍል ፈተና ሰኔ 26 እና 27 እንደሚሰጥ ተገልጿል።

ቢሮው ከተማ አቀፍ ፈተናዎቹን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመስጠት ከፍተኛ ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱን የገለፀ ዲሆን ትምህርት ቤቶች ተማሪዎቹን የበለጠ ማዘጋጀት እንዲችሉ ከከተማና ክፍለ ከተሞች ጋር በጋራ በመሆን የሞዴል ፈተናዎችን እንዲሰጡ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

በ2015 ዓ.ም 75,100 የ8ኛ እንዲሁም 75,078 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ከተማ አቀፍ ፈተናውን ይወስዳሉ።
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister


በመዲናዋ የስድስተኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ሰኔ 22 እና 23/2015 ዓ.ም ይሰጣል:-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ

አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ(ኤ ኤም ኤን) ሚያዚያ 19/2015 ዓም

በመዲናዋ የስድስተኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ሰኔ 22 እና 23 ቀን 2015 ዓ.ም እንደሚሰጥ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ገለጸ፡፡

በ2015 የትምህርት ዘመን ተግባራዊ በሆነው አዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሰረት የስድስተኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና እንደሚሰጥ ይታወቃል፡፡

የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ፈተናውን ለመስጠት የሚያስችለውን ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ገልጿል፡፡

የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ቢሮው ፈተናውን ለመስጠት የሚያስችል ዝግጅት እያደረገ ነው፡፡

ተፈታኝ ተማሪዎችን በስነ-ልቦና ከማዘጋጀት ባሻገር በትምህርት ቤቶች ቅዳሜና ከመደበኛ ትምህርት ውጭ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም የተማሪዎችን ስነ-ልቦና ለማዘጋጀት የሚያግዝ የሞዴል ፈተና መሰጠቱን ጠቅሰው፤ በፈተናው አበረታች ውጤት ተገኝቷል ነው ያሉት፡፡

በቀጣይም ተጨማሪ የሞዴል ፈተና ለመስጠት ዝግጅት መጠናቀቁን ነው የተናገሩት፡፡

ይህን ተከትሎ ሰኔ 22 እና 23 ቀን 2015 ዓ.ም የስድስተኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና እንደሚሰጥ ዶክተር ዘላለም የገለጹት።

የስድስተኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ለመውሰድ 75ሺህ 102 ተማሪዎች የኦንላይን ምዝገባ ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡፡

በፈተና ወቅት ኩረጃ እንዳይኖር በቂ ዝግጅት መደረጉን  ገልጸው በመጀመሪያ ዙር የሞዴል ፈተና ወቅት ኩረጃ እንዳይኖር የሚያስቸሉ ተግባራት መከናወናቸውን አስረድተዋል።

በተመሳሳይ የስምንተኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ሰኔ 19 እና 20 ቀን 2015 ዓ.ም በከተማ ደረጃ የሚሰጥ ሲሆን፤ 78ሺህ 78 ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚወስዱ ከአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister


" የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና ሃምሌ ወር ላይ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ይሰጣል " - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ከዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶችና  ከክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎችጋር ውይይት አካሄደ፡፡

የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና ሃምሌ ወር ላይ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንደሚካሄድ ገልጸዋል፡፡

ፈተናው ልክ እንደባለፈው አመት በሁለት ዙር የሚሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በመጀመሪያው ዙር የነበሩ የፈተና ችግሮችን ዘርዝረው ለቀጣዩ የመፍትሄ አቅጣጫ ማስቀመጥና ቅድመ ዝግጅት ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን በአጽንኦት አሳስበዋል፡፡

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) በበኩላቸው የ2015 ዓ.ም ፈተናን ለማስፈፀም ልዩ ልዩ መመሪያዎች እየተዘጋጁ መሆኑንና የተፈታኞች መረጃ በአግባቡ እየተደራጀ መሆኑን  አብራርተዋል።

ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) የህብረተሰቡን ችግር ለመቅረፍና አመለካከቱን ለመቀየር፣ ብቁና አገር ተረካቢ ትዉልድ ለመፍጠር አሁን ያለው ባለድርሻ አካል ሚናውን ሊወጣ ይገባል ሲሉ በአንክሮ ተናግረዋል፡፡

በመጨረሻም በ2016 ዓ.ም የሚካሄደው ፈተና እንደአካባቢው ሁኔታ ኦን ላይን እንደሚሆን ገልጸው የእለቱ ውይይት ተጠናቋል፡፡
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister


በትግራይ ክልል መደበኛ ትምህርት ሚያዝያ 23/2015 ዓ.ም ይጀመራል።

በትግራይ ክልል ከ1ኛ እስከ 12ኛ ክፍል መደበኛ ትምህርት ሚያዝያ 23/2015 ዓ.ም እንደሚጀመር የጊዜያዊ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ አስታውቋል።

የጊዜያዊ መንግስት በተቋቋመባቸው የክልሉ አካባቢዎች መደበኛ የመማር ማስተማር ሂደቱ እንደሚጀመር የቢሮው ኃላፊ ኪሮስ ጉኡሽ (ዶ/ር) ተናግረዋል።

"በክልሉ ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ 2.4 ሚሊዮን ተማሪዎችን ወደ ትምህርታቸው ለመመለስ ምዝገባ እንደሚደረግ" ኃላፊው ገልጸዋል።
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister


በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስዳችሁ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገባችሁና በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ መንግስት የተሰጠውን ነፃ የትምህርት ዕድል (ስኮላርሺፕ) እየተጠባበቃችሁ ያላችሁ ተማሪዎች በተከታዩ ሊንክ አማካይነት የማመልከቻ ፎርሙን መሙላት ትችላላችሁ፦

http://survey.ethernet.edu.et/index.php/518562?lang=en

የማመልከቻ ፎርሙን መሙላት የሚቻለው ከዛሬ ሚያዝያ 09 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ አምስት ቀናት ብቻ መሆኑ ተገልጿል።

በማመልከቻ ፎርሙ ልትሞሏቸው የሚገቡ፦

➧ የ12ኛ ክፍል ውጤት ኮፒ፣
➧ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ኮፒ፣
➧ ግለ ታሪክ (CV) ኮፒ፣
➧ የልደት የምስክር ወረቀት ኮፒ እና
➧ ሌሎች በፎርሙ የተጠቀሱ መረጃዎች።

መረጃዎቹ ተጣርተው ለፈተና የሚቀረቡ ተማሪዎችን ዝርዝር በቀጣይ እንደሚያሳውቅ የትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister


#MoE

የዲጂታል ትምህርት ስትራቴጂ እየተነደፈ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡

ስትራቴጂው በቴክኖሎጂ የተደገፈ ትምህርት በመላ ሀገሪቱ ለመስጠት እንደሚያስችል በሚኒስቴሩ የአይሲቲና ዲጂታል ትምህርት ዋና ሥራ አስኪያጅ ዘላለም አሰፋ (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡

ዓለም አቀፉ ኩባንያ 'ህዋዌ ቴክኖሎጂ' በኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የአይሲቲ አካዳሚ መክፈት መጀመሩ ብዙ የአይሲቲ ባለሙያዎችን ለማፍራት እንደሚያስችል ኃላፊው ተናግረዋል፡፡

የትምህርት ዘርፉ በቴክኖሎጂ የታገዘ መሆኑ ተማሪዎች ዓለም አቀፋዊ ዕውቀትን እንዲያገኙ የሚያስችል እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡

ምስል፦ የሁዋዌ አይሲቲ አካዳሚ በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ሲከፈት
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister


መቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ ዘንድሮ ለሚመረቁ የ4ኛ ዓመት ተማሪዎች ሞዴል የመውጫ ፈተና በኦንላይን ሰጥቷል።

በዩኒቨርሲቲው የተዘጋጀና ለአጠቃቀም ቀላል የሆነ ሶፍትዌር፤ ሞዴል ፈተናውን ለመስጠት ጥቅም ላይ ውሏል።

ፈተናው ተማሪዎች ቴክኖሎጂውን እንዲለማመዱ፣ ቅድመ ዝግጅታቸውን እንዲፈትሹ እና ክፍተቶችን ለመለየት የሚያስችል መሆኑን የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት ካሳ ሻውል (ዶ/ር) ገልጸዋል።

በዚህ ዓመት መጨረሻ ለመጀመሪያ ጊዜ በሚሰጠው የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና፤ 250 ሺህ የሚጠጉ የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች ፈተናውን በኦንላይን እንደሚወስዱ መንግስት መግለጹ ይታወሳል፡፡
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የሞዴል ፈተና ለ6ኛ፣ 8ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች በቀጣይ ሳምንት ይሰጣል።

ሞዴል ፈተናው ከመጋቢት 27 እስከ 29/2015 ዓ.ም ድረስ ይሰጣል፡፡

ሞዴል ፈተናው ስታንዳርዱን ጠብቆ በቢሮው መዘጋጀቱን የቢሮው የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክተር ዲናኦል ጫላ ገልጸዋል።

ፈተናው ተማሪዎች ራሳቸውን ለዋናው ፈተና ዝግጁ ማድረግ እንዲችሉ የተዘጋጀ ነው ብለዋል።
@TIMIHIRT_MINISTER
@TIMIHIRT_MINISTER


#AddisAbaba

" ከ75 ሺ በላይ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎችን የሚኒስትሪ ፈተና ለማስፈተን ዝግጅት እየተደረገ ነው " - የአ/አ ትምህርት ቢሮ

ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ በሚሰጠውን የ6ኛ ክፍል የሚኒስትሪ ፈተና ተማሪዎችን ለማስፈተን የዝግጅት ሥራዎችን እየሠራ መሆኑን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አስታውቋቃ።

የቢሮው የፈተና ዝግጅት እና አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ዲናኦል ጫላ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የሠጡት ቃል ፦

- በአዲስ አበባ ከተማ በግል እና በመንግሥት ትምህርት ቤቶች በትምህርት ገበታ ላይ የሚገኙ ከ75 ሺህ በላይ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎችን ለማስፈተን ዝግጅት እየተደረገ ነው።

- ከቢሮ እስከ ትምህርት ቤቶች ድረስ ተማሪዎቹን ለፈተና የማዘጋጀት ሥራ እየተሠራ ይገኛል።

- ተማሪዎች የሚኒስትሪ ፈተና ከመፈተናቸው አስቀድሞ የተለያዩ ደረጃቸውን የጠበቁ ሞዴል ፈተናዎችን በማዘጋጀት በወሩ እንዲወስዱ ተደርጓል። ለፈተናው የተለያዩ አጋዥ መጽሐፍትንም አንብበው እንዲዘጋጁ እና እንዲፈተኑ እየተደረገ ነው።

- በአማርኛ ቋንቋ የሚፈተኑ አራት እንዲሁም በአፋን ኦሮሞ የሚፈተኑ አምስት የትምህርት ዓይነት ፈተናዎች የሚወስዱ ይሆናል። በዚህ መሠረትም ፦
👉 የሒሳብ፣
👉 የአካባቢ ሳይንስ፣
👉 አማርኛ፣
👉 አፋን ኦሮሞ እና እንግሊዝኛ የትምህርት ዓይነቶች ይሰጣሉ።

- ምዝገባው የሚካሄደው በኦንላይን ሲሆን የተመዘገቡ ተማሪዎች የተመዘገቡበትን የስም እና ዕድሜ ስህተት እንዳይኖር ማረጋገጥ እና ማስተካከል ይችላሉ።

- በየክላስተሩ ላሉ ትምህርት ቤቶች ወጥ በሆነ መልኩ ስልጠና በመስጠት ትምህርት ቤቶች ራሳቸው ፈተናዎችን እንዲያወጡ እና እንዲፈተኑ ይደርጋል።

- በአዲሱ ሥርዓት ትምህርት በየምዕራፉ ማጠናቀቂያ ላይ ለተማሪዎች ፈተና ይሰጣል። ለዚህም አንደኛ ምዕራፍ የሚባለው ከአንደኛ እስከ ስድስተኛ ክፍል ያለው የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ሲሆን ሁለተኛ ምዕራፍ የሚባለው ከሰባት እስከ ስምንተኛ ክፍል ነው።

- የመጀመሪያ ምዕራፍ የአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች የሚያጠናቅቁት ስድስተኛ ክፍል ላይ ስለሆነ የሚኒስትሪ ፈተናው ተማሪዎች ከታች ጀምረው ራሳቸውን እያነጹ እንዲመጡ የሚያደርግ ነው። የትምህርት ጥራትን ከማረጋገጥ አንጻር ከፍተኛ ጥቅም አለው።

- የመማሪያ መጽሐፍት በሚፈለገው ልክ ሀገር ውስጥ አለመገኘት እና በውጭ ምንዛሪ እጥረት ምክንያት ከውጭ የሚመጡ መጽሐፍት የመዘግየት ሁኔታ አለ።

- የሚኒስትሪ ፈተና የሚሰጥበት ቀናት የሚወሰነው በአገር አቀፍ ደረጃ ቢሆንም እንደ ቢሮ #ከሰኔ አጋማሽ በኋላ ለመስጠት ዝግጁ ነን።
@TIMIHIRT_MINISTER
@TIMIHIRT_MINISTER


#MoE

250 ሺህ ለሚጠጉ የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

በመጪው ሐምሌ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ለሚመረቁ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት እየተጠናቀቅ እንደሚገኝ በሚኒስቴሩ የከፍተኛ ትምህርት ጥራትና ብቃት ማሻሻያ ዴስክ ኃላፊ ሰይድ መሐመድ ለኢፕድ ተናግረዋል፡፡

ሚኒስቴሩ የመውጫ ፈተናውን በተሳካ ሁኔታ ለመስጠት ከመንግሥት እና ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በቅርበት እየሠራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

የመውጫ ፈተናውን ወስደው ማለፍ ያልቻሉ ተማሪዎች ደጋግመው መፈተን የሚችሉበት ዕድል መኖሩን ኃላፊው አመልክተዋል።

ፈተናውን በተደጋጋሚ ወስዶ ማለፍ ያልቻለ ተማሪ ከዲግሪ በታች ባሉ ደረጃዎች ምዘና እንዲወስድ የሚያደርግ የብቃት ማረጋገጫ ማዕቀፍ በትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን በመዘጋጀት ላይ ይገኛል ብለዋል።

ይሁን እንጂ ተፈታኙ ለዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ዝግጁ ነኝ ብሎ ባሰበ ጊዜ ፈተናውን መውሰድና ማለፍ ከቻለ የዲግሪ ማረጋገጫ ማግኘት እንደሚችል ገልጸዋል።

የመውጫ ፈተናው በኦንላይን እንደሚሰጥ ያመለከቱት ኃላፊው፤ ተማሪዎች ዋናውን ፈተና ከመፈተናቸው በፊት ሞዴል ፈተናዎች እንደሚወስዱ ጠቅሰዋል፡፡ 
@TIMIHIRT_MINISTER
@TIMIHIRT_MINISTER


የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት የጠራው ምንም አይነት ሰላማዊ ሰልፍ አለመኖሩን አሳውቋል።

በዚህ ዓመት ሊሰጥ በታሰበው የመውጫ ፈተና ዙሪያ በስሙ የተሰራጨው መረጃ ህብረቱን የማይወክል መሆኑንም ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ አረጋግጧል።

በዚህ ዓመት እንዲሰጥ በተወሰነው የመውጫ ፈተና ላይ ተማሪዎች በሚያነሷቸው ስጋቶችና ቅሬታዎች ላይ ከትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮችና ከሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይቶች መደረጋቸውን ወደፊትም እንደሚደረጉ ህብረቱ ገልጿል።

በውይይቶቹ የተነሱ ሀሳቦች ገሚሶቹ ምላሽ ያገኙ ሲሆን በቀጣይ የሚስተካከሉ መረጃዎችን የሚያሳወቅ መሆኑንም ህብረቱ ጠቁሟል።

ፈተናው የተማሪዎችን ብቃት የሚመዝንና የትምህርት ጥራት ሊያስጠብቅ በሚችልበት ሁኔታ ላይ አሁንም በጋራ እየሠራ መሆኑን ህብረቱ አስታውሷል።

ተማሪዎች በፈተናው እና ተዛማጅ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ሀሳብ በግቢያቸው ለሚገኙ የተማሪዎች ህብረት እያቀረቡ በኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት አማካይነት ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመወያየት ምላሽ የሚሰጥበት መሆኑንም ገልጿል።

በቅርቡ የተሰራጨው መረጃ ህብረቱን የማይወክልና ተቀባይነት የሌለው መሆኑን የገለጸው ህብረቱ፤ በህብረቱ የተጠራ ምንም አይነት ሰላማዊ ሰልፍ አለመኖሩን ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ አረጋግጧል።

ተመራቂ ተማሪዎች በተቋሞቻቸውና በተማሪዎች ህብረት አማካይነት የሚሰጡ የድጋፍ ትምህርቶችን በመከታተል ለመውጫ ፈተናው ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ ህብረቱ ጥሪ አድርጓል።

ሐሰተኛና የተዛባ መረጃ የሚያሰራጩ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡም ህብረቱ አሳስቧል።
@TIMIHIRT_MINISTER
@TIMIHIRT_MINISTER


ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ተማሪዎችን በመቀበል ላይ ይገኛል።

ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ከ1 ሺህ 400 በላይ የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ተማሪዎች በትምህርት ሚኒስቴር ተመድበውለታል።

@TIMIHIRT_MINISTER
@TIMIHIRT_MINISTER


#GambellaUniversity

በ2015 ዓ.ም በጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ የአቅም ማሻሻያ ሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች መግቢያ ጊዜ መጋቢት 08 እና 09/2015 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትሄዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

➧ የትምህርት ማስረጃዎች ዋናውና ኮፒው፣
➧ አራት ጉርድ ፎቶግራፍ፣
➧ የሌሊት አልባሳት፣
➧ የስፖርት ትጥቅ፡፡

ከተጠቀሱት ቀናት ውጪ የሚመጡ ተማሪዎችን የማያስተናግድ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።


በ2015 ዓ.ም የቅድመ ምረቃ መደበኛ እና የአቅም ማሻሻያ ሪሚዲያል የመግቢያ ቀን ያሳወቁ ዩኒቨርሲቲዎች

¤ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ - መጋቢት 11 እና 12

¤ ደብረ ብርሀን ዩኒቨርሲቲ መጋቢት 16 እና 17

¤ አምቦ ዩኒቨረሲቲ መጋቢት 7 እና 8

¤  መቅደላ አምባ ዩኒቨረሲቲ መጋቢት 7 እና 8

¤ ቡሌ ሆራ ዩኒቨረሲቲ መጋቢት 4 እና 5

¤ ጂንካ ዩኒቨረሲቲ መጋቢት 4 እና 5

¤ መዳ ወላቡ ዩኒቨረሲቲ መጋቢት 7 እና 8

¤ ወለጋ ዩኒቨረሲቲ መጋቢት 7 እና 8

¤ ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨረሲቲ መጋቢት 4 እና 5

¤ ኢንጂባራ ዩኒቨረሲቲ መጋቢት 4 እና 5

¤ ደባርቅ ዩኒቨረሲቲ መጋቢት 5 እና 6

¤ አሶሳ ዩኒቨረሲቲ መጋቢት 11 እና 12

¤ ወሎ ዩኒቨረሲቲ መጋቢት 4 እና 5

¤ ቦረና ዩኒቨረሲቲ መጋቢት 11 እና 12

¤ ሚዛን ቴፒ ዩኒቨረሲቲ መጋቢት 8 እና 9

Share  @Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister


ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ለአቅም ማሻሻያ Remedial ፕሮግራም የተመደቡ ተማሪዎችን መቀበል ጀምሯል።

ዩኒቨርሲቲው የሪሚዲያል ተማሪዎችን በነገው ዕለትም መቀበሉን ይቀጥላል።
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister


ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ለአቅም ማሻሻያ Remedial ፕሮግራም የተመደቡ ተማሪዎችን መቀበል ጀምሯል።

ዩኒቨርሲቲው የሪሚዲያል ተማሪዎችን በነገው ዕለትም መቀበሉን ይቀጥላል።
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister


#MizanTepiUniversity

በ2015 ዓ.ም በሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ የአቅም ማሻሻያ ሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ምዝገባ መጋቢት 8 እና 9/2015 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

የምዝገባ ቦታ፡-

➧ የማህበራዊ ሳይንስ መስክ ተማሪዎች በሚዛን አማን ዋናው ግቢ
➧ የተፈጥሮ ሳይንስ መስክ ተማሪዎች በቴፒ ግቢ

ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትሄዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

➧ የ10ኛ እና የ12ኛ ክፍል ውጤት ዋናውና ኮፒው፣
➧ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
➧ አምስት 3×4 ፎቶግራፍ፣
➧ የሌሊት አልባሳት፡፡

ከተጠቀሱት ቀናት ውጪ የሚመጡ ተማሪዎችን የማያስተናግድ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል።
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister


በ2015 ዓ.ም በቦረና ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ የአቅም ማሻሻያ ሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ምዝገባ መጋቢት 11 እና 12/2015 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትሄዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

➧ የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ሰርተፊኬት ዋናውና ኮፒው፣
➧ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
➧ ስምንት 3×4 ፎቶግራፍ፣
➧ የሌሊት አልባሳት፡፡

ከተጠቀሱት ቀናት ውጪ የሚመጡ ተማሪዎችን የማያስተናግድ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል።
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister


በ2015 ዓ.ም በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ ገቢ የቅድመ ምረቃ መደበኛ እና የአቅም ማሻሻያ ሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች መግቢያ ጊዜ መጋቢት 11 እና 12/2015 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትሄዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

➧ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
➧ የ10 እና የ12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
➧ አራት ፓስፖርት መጠን ፎቶግራፍ፣
➧ የሌሊት አልባሳት፣
➧ የስፖርት ትጥቅ፡፡

ከተጠቀሱት ቀናት ውጪ የሚመጡ ተማሪዎችን የማያስተናግድ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል።

(ተጨማሪ ከላይ ተያይዟል።)
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister


#BahirDarUniversity

በ2015 ዓ.ም በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ የካቲት 29 እና 30/2015 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

የምዝገባ ቦታ ➧
በሰላም ካምፓስ እና በቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ካምፓስ

ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትሄዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

➧የ8ኛ ክፍል ካርድ፣
➧ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
➧ የ12ኛ ክፍል ሰርተፊኬት ዋናውና ኮፒው፣
➧ አራት ጉርድ ፎቶግራፍ፣
➧ የሌሊት አልባሳት፣
➧ የስፖርት ትጥቅ፡፡

(ተጨማሪ ከላይ ተያይዟል።)
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister

20 last posts shown.

24 540

subscribers
Channel statistics