Tikvah-University


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Education



Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Education
Statistics
Posts filter


ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ጋር በመተባበር ዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ለሚወስዱ ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት መስጠት ሊጀምር ነው፡፡

የማጠናከሪያ ትምህርቱ በሀዲያ ዞን፣ በከምባታ ዞን እና በጠምባሮ ልዩ ወረዳ ለሚገኙና ዘንድሮ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለሚወሰዱ ተማሪዎች እንደሚሰጥ ተገልጿል፡፡

ከዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ እና ከሁለቱም ዞኖች ከሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተመረጡ 432 መምህራን በ54 ማዕከላት ከመጪው ቅዳሜ ጀምሮ ለተከታታይ ስምንት ሳምንታት የማጠናከሪያ ትምህርቱን ይሰጣሉ ተብሏል፡፡

የማጠናከሪያ ትምህርቱ የተፈታኝ ተማሪዎችን የማለፍ ምጣኔ ለማሳደግ እንደሚያስችል ታምኖበታል፡፡

@tikvahuniversity

20.9k 0 36 29 182

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ለተመደቡ ሬዚደንት ሐኪሞች ዛሬ ሊሰጠው የነበረውን ኦረንቴሽን ወደ መጪው ሰኞ አስተላለልፏል፡፡

ገለፃው ሰኞ መጋቢት 23/2016 ዓ.ም ጠዋት 2፡00 ሰዓት ይሰጣል ተብሏል፡፡

@tikvahuniversity


#የካቲት_12_ሆስፒታል_ሜዲካል_ኮሌጅ

በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በ Post Basic Neonatal nursing, Post Basic ECCN nursing, Post Basic BSc in Medical Laboratory Science እና Post Basic Comprehensive nursing በመጀመሪያ ዲግሪ ለመማር ስም ዝርዝራችሁ ከጤና ቢሮ የተላከ በሙሉ የፈተና ቀን መጋቢት 25/2016 ዓ.ም መሆኑን ኮሌጁ አሳውቋል፡፡

ምዝገባ፦ መጋቢት 30 እና ሚያዚያ 1/2016 ዓ.ም
ትምህርት የሚጀምረው፦ ሚያዚያ 2/2016 ዓ.ም

@tikvahuniversity


#የሥራ_ቅጥር_ጥቆማ

ቦረና ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የሙያ መስኮች ባለሙያዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።

➤ የሥራ መደብ፦ በተለያዩ የሙያ መስኮች
➤ ተፈላጊ ባለሙያዎች ብዛት፦ 44
➤ የትምህርት ደረጃ፦ ከመጀመሪያ ዲግሪ ጀምሮ
➤ የሥራ ልምድ፦ ከዜሮ ዓመት ጀምሮ
➤ የሥራ ቦታ፦ ቦረና ዩኒቨርሲቲ
➤ የማመልከቻ ጊዜ፦ ከዛሬ መጋቢት 18/2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት

የማመልከቻ አማራጮች፦

ቦረና ዩኒቨርሲቲ የሰው ሀብት አስተዳደርና ልማት ዳይሬክቶሬት በአካል በመገኘት ወይም አዲስ አበባ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ወኪል ቢሮ፣ አራት ኪሎ፣ የቀድሞው የጀርመን ባህል ኢንስቲትዩት ህንፃ ቢሮ ቁ. 15 የማመልከቻ ደብዳቤ፣ ሲቪ እና የትምህርት ማስረጃዎች ዋናውና ኮፒውን ማስገባት ይጠበቅባችኋል፡፡

@tikvahuniversity

31.7k 0 95 10 125

የፊታችን ቅዳሜ መጋቢት 21/2016 ዓ.ም 7ኛ ዙር የኮምፒውተር ፕሮግራሚንግ (Computer Programming) ስልጠና ይጀምራል።

🔔  ቀድመው ይመዝገቡ!

👉 100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና
👉 መሠረታዊ የኮምፒውተር ትምህርትን አካቶ የሚሰጥ
👉 C++, Java እና Python ፕሮግራሞች ከፍ ባለ ደረጃ (Advanced Level) በጋራ የሚሰጡበት

☎️    0906777799 / 0906777755

አድራሻ፦ ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ

የበለጠ ይጠብቁ ...
💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥


Facebook | Telegram | Instagram | LinkedIn


በአክሱም ዩኒቨርሲቲ በ Post Basic Nursing ለመማር የመግቢያ ፈተና ያለፋችሁ አመልካቾች ምዝገባ መጋቢት 25 እና 26/2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

የምዝገባ ቦታ፦ በአክሱም ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ

@tikvahuniversity


የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ኅብረት የሥራ አስፈጻሚዎች ምርጫ በመቐለ ዩኒቨርሲቲ አካሒዷል፡፡

የመቐለ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ኅብረት ፕሬዝዳንት ሐየሎም ስዩም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ኅብረት ፕሬዝዳንት ሆኖ ተመርጧል፡፡

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ኅብረት ፕሬዝዳንት ምክትል ፕሬዝዳንት እንዲሁም የጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ኅብረት ፕሬዝዳንት ጸሐፊ ሆነው የተመረጡ ሲሆን ሌሎች ዘጠኝ የሥራ አስፈጻሚዎች ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች መመረጣቸውም ታውቋል።

አዲሶቹ አመራሮች ኅብረቱን ለቀጣይ ሁለት ዓመታት እንደሚያገለግሉ ተገልጿል።

@tikvahuniversity

38k 0 19 17 195

መቐለ ዩኒቨርሲቲ የሁለተኛ እና የሦስተኛ ዲግሪ ፕሮግራም የመማር ማስተማር ሒደትን በድጋሜ ለማስጀመር በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ገለፀ።

የቅድመ ምረቃ ፕሮግራም ትምህርት እየተሰጠ እንደሚገኝ የጠቆሙት የተቋሙ የአካዳሚክ ም/ፕሬዝዳንት አብዱልቃድር ከሪም (ዶ/ር) ፤ ዩኒቨርሲቲው በአሁኑ ወቅት ከ11 ሺህ በላይ ተማሪዎች እያስተማረ ይገኛል ብለዋል።

ዩኒቨርሲቲው ያጋጠመውን የበጀት እጥረት ተቋቁሞ በቅርቡ 2,035 ተማሪዎች ማስመረቁንም አስታውሰዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው በቀጣይ በተለይ የምርምር እና የመዋቅር ሪፎርም ሥራዎች ላይ ትኩረት በማድረግ ወደ ተግባር እንደሚገባ ምክትል ፕሬዝዳንቱ ለኢፕድ ተናግረዋል፡፡

@tikvahuniversity

45.2k 0 11 19 156

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም አዲስ የተመደቡ መደበኛ እና የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎችን በመቀበል ላይ ይገኛል።

ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎቹን ተቀብሎ ለማስተማር ለመጋቢት 16 እና 17/2016 ዓ.ም ጥሪ ማድረጉ ይታወቃል።

@tikvahuniversity

46k 0 23 16 106

#AdigratUniversity

በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ትምህርታችሁን ስትከታተሉ የነበራችሁና በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት በ2014 ዓ.ም ወደ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተመድባችሁ መማራችሁ ይታወቃል።

ይሁን እንጂ በ2013 ዓ.ም ከዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ስትወጡ ያልጨረሳችሁት የተወሰኑ የትምህርት ዓይነቶች መኖራቸውን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

በመሆኑም ከዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ስትወጡ ያላጠናቀቃችሁት ትምህርት ያላችሁ ተማሪዎች በዚህ ሴሚስተር እንድታጠናቅቁ ከመጋቢት 28 እስከ 30/2016 ዓ.ም ባለው ግዜ መመዘገብ ትችላላችሁ ተብሏል።

@tikvahuniversity

48.5k 0 53 48 123

#BahirDarUniversity

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለዘጠኝ ምሁራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቷል።

የዩኒቨርሲቲው ሥራ አመራር ቦርድ ምሁራኑ በየመስኳቸው የነበራቸውን ልዩ አበርክቶ በመገምገም የፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቷቸዋል።

የፕሮፌሰርነት ማዕረግ የተሰጣቸው ምሁራን፦

1. ሙሉጌታ አድማሱ ደለለ (Bio Systems Engineering)
2. ታምራት ተስፋዬ ይመር (Biorefinery Engineering)
3. አስማማው ጣሰው ወልዴ (Animal Production)
4. መላኩ አለማየሁ ወርቄ (Horticulture)
5. የሻምበል መኩሪያው ቸከኮል (Animal Nutrition)
6. አቻምየለህ ጋሹ አዳም (Land Governance)
7. ምርኩዝ አበራ አድማሱ (Plant Pathology)
8. ታደሠ መለሠ መራዊ (Curriculum and Instruction)
9. አስራት ዳኘው ከልካይ (Curriculum and Instruction)

ቦርዱ የምሁራኑን የማስተማር ሥራ፣ የምርምር ተሳትፎ፣ የማህበረሰብ አገልግሎት እና በተቋማዊ ጉዳይ ያላቸውን አስተዋፆ በመገምገም የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ማፅደቁን ከተቋሙ የተገኘ መረጃ ያሳያል።

@tikvahuniversity


የፊታችን ማክሰኞ መጋቢት 17/2016 ዓ.ም 9ኛ ዙር ሙሉ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ (Modern Accountancy and Auditing) ስልጠና ይጀምራል።

👉 100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና
👉 መሠረታዊ አካውንቲንግ እና ኦዲት አሰራር፣
👉 ሙሉ የአካውንቲንግ ሒሳብ አሰራር በፒስቺሪ ተደግፎና የግብር አያያዝ ትምህርቶችን አካቶ የሚሰጥ
👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት

☎️    0906777799 / 0906777755

አድራሻ፦ ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ

የበለጠ ይጠብቁ ...
💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥


Facebook | Telegram | Instagram | LinkedIn


#BahirDarUniversity

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም አዲስ ለተመደቡ እና በ2015 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ለተከታተሉ ተማሪዎች ጥሪ አድርጓል።

በዚህም በ2016 ዓ.ም አዲስ የተመደባችሁ Freshman ተማሪዎች እና በ2015 ዓ.ም በሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸሁን በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስትከታተሉ ቆይታችሁ የማለፊያ ውጤት በማምጣት በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሔደው ከመጋቢት 26 እስከ 28/2016 ዓ.ም መሆኑን ተቋሙ አሳውቋል።

የምዝገባ ቦታ፦
➤ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በሰላም ግቢ
➤ የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በግሽ አባይ ግቢ

በተለያዩ ምክንያቶች ትምህርታችሁን አቋርጣችሁ ለአንደኛ ዓመት የመጀመሪያ ሴሚስተር ለመልሶ ቅበላ የሚያበቃ ውጤት ያላችሁና የመልሶ ቅበላ ፎርም የሞላችሁ ተማሪዎች ምዝገባ መጋቢት 30/2016 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል።

(ተጨማሪ መረጃ ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity

51.2k 0 387 71 266

አሶሳ ዩኒቨርሲቲ ከፍትህ እና ሕግ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር 8ኛውን ሀገር ዓቀፍ የአምሳለ ችሎት ውድድር ያካሒዳል።

በሀገሪቱ የሚገኙ የሕግ ትምህርት ቤቶችን በመወከል ያለፉ ተማሪዎች ከመጋቢት 20 እስከ 22/2016 ዓ.ም በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ በሚካሔደው ውድድር ይሳተፋሉ።

@tikvahuniversity


ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት አዳዲስ የአጭር ጊዜ ስልጠናዎች ለመስጠት ስርዓተ ትምህርት አዘጋጅቷል።

ኢንስቲትዩተ የሁለት መደበኛ ስልጠና ስርዓተ ትምህርት ክለሳም አድርጓል።

12 ሙያዎች ፍላጎትን መሰረት ያደረገ የአጭር ጊዜ ስልጠናዎች ለመስጠት አዲስ ስርዓተ ትምህርት መዘጋጀቱን የኢንስቲትዩቱ ስልጠናና አቅም ግንባታ ዘርፍ ም/ዋ/ዳይሬክተር ሀብታሙ ክብረት ገልጸዋል፡፡

ኢንስቲትዩቱ በዓለም ባንክ EASTRIP ፕሮጀክት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ያካሔደውን የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት መሰረት በማድረግ የስርዓተ ትምህርት እና የመማሪያ ሰነድ ማዘጋጀቱን ጠቁመዋል።

ስርዓተ ትምህርት ከተዘጋጀላቸው ሙያዎች መካከል፦

- የውጭ ቋንቋዎች ስልጠና (እንግሊዘኛ፣ አረብኛ እና ፈረንሳይኛ)
- የትኩስ መጠጥ አገልግሎት (Bartender Service)፣
- የመጠጥ አግልግሎት (Barista Service)፣
- የሥጋ ቤት አገልግሎት (Butchery)፣
- ጤናና ውበት (Wellness and Spa Service) ይገኙበታል፡፡

@tikvahuniversity


#Update

የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሰኔ ወር እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

በዚህ ዓመት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ ከ670 ሺህ በላይ ተማሪዎች ምዝገባ ማድረጋቸውን የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) በቅርቡ መግለፃቸው ይታወሳል፡፡

የፀጥታ ችግር ካለባቸው አካባቢዎች በስተቀር በአብዛኛው የአገሪቱ አካባቢዎች የተማሪዎች ምዝገባ መጠናቀቁም ተገልጿል።

የፈተናው ሕትመት በቀጣይ ቀናት እንደሚጀመር ለኢሳት የገለፁት ዋና ዳይሬክተሩ፤ የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በሰኔ ወር እንደሚሰጥም አረጋግጠዋል፡፡

ለ3ኛ ጊዜ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚሰጠው ብሔራዊ ፈተናው፤ ዘንድሮ ለተፈጥሮ ሳይንስ እና ማኅበራዊ ሳይንስ የትምህርት መስኮች ለእያንዳንዳቸው በስድስት የትምህርት አይነቶች እንዲሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር መወሰኑ አይዘነጋም፡፡

@tikvahuniversity

76.4k 0 1.5k 87 489

#HawassaUniversity

በ2016 ዓ.ም ለስፔሻሊቲ ስልጠና በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ ሬዚደንት ሐኪሞች ምዝገባ መጋቢት 18 እና 19/2016 ዓ.ም እንደሚከናወን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ምዝገባ ለማድረግ ኦፊሺያል ትራንስክሪፕት በኢሜይል registrar@hu.edu.et ወይም በፖ.ሳ.ቁ. 05 አስቀድሞ ማስላክ ይጠበቅባችኋል።

የምዝገባ ቦታ፦
በህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ሬጅስትራር ቢሮ

ተመዝጋቢዎች ከዩኒቨርሲቲው ዋናው ግቢ ሬጅስትራር እና ድኅረ ምረቃ ትምህርት ቤት “Admission” እና “Acceptance” ደብዳቤ መያዝ ይኖርባችሀኋል።

ማንኛውም ተመዝጋቢ አስቀድሞ ይሠራበት ከነበረ ተቋም ክሊራንስ ማቅረብ ይጠበቅበታል።

ኦረንቴሽን መጋቢት 20/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

@tilvahuniversity


#ጥቆማ

ቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የሙያ መስኮች መምህራንን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።

➤ የሥራ መደብ፦ በተለያዩ ሙያ መስኮች
➤ ተፈላጊ ባለሙያዎች ብዛት፦ 23
➤ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፦ 2ኛ ዲግሪ
➤ የሥራ ቦታ፦ ቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲ
➤ የማመልከቻ ጊዜ፦ ማስታወቂያው ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ባሉት አምስት ተከታታይ የሥራ ቀናት

አመልካቾች ስትመዘገቡ የትምህርት እና የሥራ ልምድ ማስረጃ ዋናውና የማይመለስ ኮፒ ማቅረብ ይጠበቅባችኋል፡፡

በኢሜይል ለመመዝገብ፦ 𝘒𝘥𝘶𝘩𝘳𝘥@𝘬𝘥𝘶.𝘦𝘥𝘶.𝘦𝘵

ለተጨማሪ መረጃ፦ +251252401076

@tikvahuniversity

55.3k 0 38 14 103

#AddisAbabaUniversity

በ2016 ዓ.ም ለስፔሻሊቲ ስልጠና አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የተመደባችሁ ሬዚደንት ሐኪሞች የድኅረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (GAT) ማክሰኞ መጋቢት 17/2016 ዓ.ም ይሰጣል፡፡

ምዝገባ እስከ ሰኞ መጋቢት 16/2016 ዓ.ም ቀን 6፡00 ሰዓት በኦንላይን https://portal.aau.edu.et. እንደሚከናወን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

@tikvahuniversity


በቱኒዚያ በተካሔደው የሁዋዌ አይ.ሲ.ቲ. ውድድር ሦስተኛ ደረጃን ይዘው ያጠናቀቁት ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች በቻይና በሚካሔደው የፍፃሜ ውድድር ይሳተፋሉ፡፡

ባለፈው ሳምንት በቱኒዚያ በተካሔደው ክፍለ አኅጉራዊ የፍፃሜ ውድድር ኢትዮጵያን ወክለው ከተወዳደሩት ዘጠኝ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መካከል በኮምፒውቲንግ ትራክ የተወዳደሩት የሦስት ተማሪዎች ቡድን በሦስተኛ ደረጃ ማጠናቀቁ ይታወቃል፡፡ ሁለቱ ተማሪዎች የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፤ አንዱ ደግሞ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ናቸው።

ሞሮኮ እና ቱኒዚያን ተከትለው ሦስተኛ ደረጃን ያገኙት ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች፤ ዘመናዊ የሁዋዌን ስልክ የተሸለሙ ሲሆን የተቀሩት ስድስት ተማሪዎች ለተሳትፏቸው የሁዋዌ ታብሌቶችን ተሸልመዋል።

አሸናፊዎቹ ተማሪዎች በ2024 በቻይና በሚካሔደውና ከ500 ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ ከ20 ሺህ በላይ ተማሪዎች በሚሳተፉበት የመጨረሻው ምዕራፍ ውድድር እንደሚሳተፉ የሁዋዌ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ሊሚንግ ዬ ገልፀዋል። #ሪፖርተር

@tikvahuniversity

56.8k 0 25 13 315
20 last posts shown.