Tikvah-University


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Education


Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Education
Statistics
Posts filter


#UniversityOfGondar

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ለቅድመ-ምረቃ እና ድኅረ-ምረቃ ፕሮግራም መደበኛ እና ተከታታይ መርሐግብር ተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል፡፡

በዚህም የቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች የ2017 ትምህርት ዘመን የምዝገባ ቀናት ጥቅምት 21 እና 22/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

በተመሳሳይ የነባር እና አዲስ ገቢ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራም መደበኛ እና ተከታታይ መርሐግብር ተማሪዎች ጥቅምት 21 እና 22/2017 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል፡፡

በ2017 ዓ.ም ጎንደር ዩኒቨርሲቲ አዲስ የምትመደቡ ተማሪዎች እና በ2016 ዓ.ም በሪሚዲያል መርሐግብር ትምህርታችሁን ስትከታተሉ ቆይታችሁ የማለፊያ ነጥብ ያመጣችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ቀናት ወደፊት ይገለፃል ተብሏል፡፡

@tikvahuniversity

22.4k 0 144 75 213

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመምህራን ደመወዝ በመቋረጡ የ2017 ትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሥራ በተለያዩ ዞኖች በአግባቡ አለመጀመሩ ተገለፀ፡፡

በክልሉ የተለያዩ ዞኖች የመምህራን ደመወዝ በመቋረጡ የተነሳ እስካሁን በአንዳንድ ትምህር ቤቶች ትምህርት አለመጀመሩ ተሰምቷል፡፡

ከግል እና ከጥቂት የመንግሥት ትምህርት ቤቶች ውጪ አብዛኞቹ ትምህርት ቤቶች እንዳልተከፈቱ፣ ቢከፈቱም ከሁለት በላይ መመህራን ስለማይገቡ ትምህርት አለመጀመሩን አስተያየታቸውን ለቮኦኤ የሰጡ ወላጆች ስጋታቸውን ገልፀዋል።

በወላይታ ዞን፣ በጋሞ ዞን፣ በኮንሶ ዞን እና በጎፋ ዞን በሚገኙ 28 ወረዳዎች የሚያስተምሩ በሺዎች የሚቆጠሩ መምህራን ደመወዝ በወቅቱ እንደማይከፈል የክልሉ መምህራን ማኅበር ገልጿል።

በዞኖቹ ከሁለት እስከ ሦስት ወራት ደመወዝ ያልተከፈላቸው መምህራን መኖራቸውን የገለፁት የማኅበሩ ፕሬዝዳንት አማኑኤል ጳውሎስ፤ መምህራኑ በጣም በመቸገራቸው ኑሯቸውን ለመደጎም የቀን ሥራ ጭምር እየሠሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡

መምህራኑ የደመወዝ ይከፈለን ጥያቄ ሲያቀርቡ ዛቻ፣ ማስፈራሪያ እና እስራት እየተፈፀመባቸው እንደሆነም ወላጆች እና መምህራን ገልፀዋል፡፡

በአንዳንድ ክልሎች የመምህራን ደመወዝ በጊዜ አለመከፈል ብሎም እየተቆራረጠ በፐርሰንት መከፈል፣ ያለመምህራን ዕውቅናና ፈቃድ በተለያዩ ምክንያቶች የደመወዝ መቆረጥ፤ ይሄንን የሚቃወሙትን ደግሞ ማዋከብና ማንገላታት እንደሚፈፀም የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ባለፈው ሳምንት ባወጣው መግለጫ መግለፁ ይታወሳል፡፡

የቪኦኤን ዘለግ ያለ ዘገባ ያድምጡ  👇
https://amharic.voanews.com/a/south-ethiopia-school-disruption/7836277.html

@tikvahuniversity


#ሎርካን_ሜዲካል_ኮሌጅ

🔔 የበርካታ ዓመታት ልምድ ባላቸው ሐኪሞችና ምሁራን ባለቤትነት የሚመራው ሎርካን ሜዲካል ኮሌጅ ምዝገባ ጀምሯል❗️

BSc fields of study:
→ Doctor of Medicine
→ Doctor of Dental Medicine
→ Bachelor of Dental Science
→ Nursing

TVET Programs:
→ Dental Therapy
→ Nursing
→ Medical Laboratory
→ Pharmacy
→ Radiography

የ CPD ማዕከል አገልግሎት!

☎️ 0913398780 / 0911596059

አድራሻ፦
CMC አደባባይ ከፀሐይ ሪል እስቴት ጀርባ ከ ICMC ጠቅላላ ሆስፒታል አጠገብ
Addis Ababa, CMC Square, behind Tsehay Real Estate, next to ICMC General Hospital.
Facebook: https://www.facebook.com/Lorcanmedicalcollege


ኢንዲያን ዓለም አቀፍ ትምህርት ቤት እና አንድነት ዓለም አቀፍ ትምህርት ቤት የማስተማር ፈቃዳቸው እንዳልታደሰላቸው የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን አሳውቋል፡፡

በ2017 ትምህርት ዘመን በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች ፈቃድ ያላቸው፣ የሌላቸው እና የፈቃድ ዕድሳት ጥያቂያቸው በሒደት ላይ የሆኑ ዓለም አቀፍ እና የማኅበረሰብ ትምህርት ቤቶች ዝርዝርን ባለሥልጣኑ ይፋ አድረጓል፡፡

በዚህም ከኬጂ እስከ 12ኛ ክፍል የሚያስተምሩት ኢንዲያን ዓለም አቀፍ ትምህርት ቤት እና አንድነት ዓለም አቀፍ ትምህርት ቤት የማስተማር ፈቃዳቸው ያልታደሰላቸው መሆኑ ተገልጿል፡፡

የፈቃድ ዕድሳት ጥያቄ አቅርበው በሒደት ላይ የሚገኙ ተቋማት፦
▪️ብሪቲሽ ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤት
▪️ላየን ኸርት አካዳሚ
▪️ሄለኒክ ግሪክ ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤት

የፈቃድ ጥያቄ አቅርበው በሒደት ላይ የሚገኙ ተቋማት፦
▪️ትራንሴንድ አካዳሚ
▪️ማህሪፍ ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤት

ሌሎች 23 ዓለም አቀፍ እና የማኅበረሰብ ትምህርት ቤቶች ፈቃድ የተሰጣቸው እና ፈቃዳቸው የተሰጣቸው መሆኑንም የባለስልጣኑ መረጃ ያሳያል፡፡

(ባለሥልጣኑ ያወጣው ዝርዝር ከላይ ተያይዟል፡፡)

@tikvahuniversity

22k 0 9 35 74

3ኛ ዙር የፋይናንስ እና ካፒታል ማርኬት ስልጠና ሰኞ ጥቅምት 18/2017 ዓ.ም ይጀምራል!

👉 ፈጥነው ይመዝገቡ!

የካፒታል ማርኬት ገበያ በኢትዮጵያ ሊጀመር ነው፡፡ በኢንስቲትዩታችን የሚሰጠውን የፋይናንስና ካፒታል ማርኬት ስልጠና በመውሰድ ራስዎን ለትግበራው ያዘጋጁ፡፡

ስልጠናው ከመሰረታዊ የካፒታል ገበያ ምንነት አንስቶ እንዴት አንድ ግለሰብ ወይም ተቋም ከስጋት ነፃ በሆነ መንገድ በገበያው ላይ መሳተፍ እንደሚችል ግልፅ ያደርጋል፡፡ ስልጠናውን ይውሰዱና ትግበራውን ይጠባበቁ!

☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦
ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ

Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
TikTok: @sage_training_institute' rel='nofollow'>https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute


በጦርነት ምክንያት ሥራ ያቆሙ መምህራንን ማዘዋወር ካልተቻለ ወደ ሥራቸው እስኪመለሱ ባሉበት ደመወዛቸው እንዲከፈላቸው የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር ጠየቀ፡፡

"መምህራን የኑሮ ውድነት በከፍተኛ መጠን እየፈተናቸው እንደሚገኙ፣ የረዥም ጊዜ አገልግሎት ያላቸው መምህራን የደረጃ ዕድገት ወይም ዕርከን እያገኙ አለመሆናቸው፣ በአንዳንድ ክልሎች የመምህራን ደመወዝ በጊዜ አለመከፈልና በፐርሰንት መቆራረጥ፣ ያለ መምህራን ፈቃድ በተለያዩ ምክንያቶች የደመወዝ መቆረጥና ይህንን ድርጊት የሚቃወሙትን ደግሞ ማዋከብና ማንገላታት እንዳለ" 37ኛ መደበኛ ጉባኤውን በቅርቡ ያካሔደው ማኅበሩ አሳውቋል፡፡

በተጨማሪም ከዓመታት በፊት የተጀመረው የመምህራን የመኖሪያ ቤትና የመሥሪያ ቦታ በሚፈለገው ፍጥነት እየተከናወነ አለመሆኑን፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን ደግሞ ጭራሽ አለመጀመሩን፣ በትርፍ ሰዓት ክፍያ ላይ ተደራራቢ ግብር መቆረጥ፣ የመጻሕፍትና ሌሎች ግብዓቶች እጥረት፣ የክረምት መምህራን ሥልጠናና ያጋጠሙ ችግሮች ማኅበሩ ባወጣው መግለጫ ተዳሰዋል፡፡

"መምህራን ክፍል ውስጥ ገብተው ማስተማር ባልቻሉበት ወቅት፣ አላሰተማሩም ተብሎ ደመወዛቸው ሊቆረጥባቸው አይገባም" ሲሉ የማኅበሩ ፕሬዝዳንት ዮሐንስ በንቲ (ዶ/ር) ለሪፖርተር ተናግረዋል።

ከወራት በፊት የ18 ወራት ውዝፍ ደመወዝ ስላልተከፈላቸው ለችግር መጋለጣቸውን የትግራይ ክልል መምህራን መጠየቃቸው ይታወሳል፡፡ በዚህም በቅርቡ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የአምስት ወራት ደመወዝ ለመምህራኑ እንደሚከፍል ቢናገርም፣ የቀሪው የአንድ ዓመት ውዝፍ ክፍያ ግን አሁንም መፍትሔ እንደሚፈልግ የማኅበሩ ፕሬዝዳንት ገልፀዋል፡፡

በጦርነት ምክንያት ሥራ ያቆሙ መምህራንን ማዘዋወር ካልተቻለ ወደ ሥራቸው እስኪመለሱ ባሉበት ደመወዛቸው እንዲከፈላቸው የጠየቁት የማኅበሩ ፕሬዝዳንት፤ መንግሥትም ሆነ ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት የመምህራኑን ችግር ሊረዱና መፍትሔ ሊሰጡት ይገባል ብለዋል፡፡

ከትግራይ ክልል በስተቀር በሌሎች ክልሎች እስከ ሦስት ወራት ደመወዝ ያልተለከፈላቸው በተለይም በቀድሞው ደቡብ ክልል ውስጥ የነበሩ ትምህርት ተቋማትም እንደሚገኙ የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፤ በአማራ ክልል በሚካሄደው ጦርነት ደመወዝ ያልተከፈላቸውና ሥራ ያቆሙ መምህራን መረጃ ተጠናቅሮ አልደረሰም ብለዋል። #ሪፖርተር

@tikvahuniversity

47.3k 0 21 57 358

#የሥራ_ቅጥር_ጥቆማ

ወራቤ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች መምህራንና ቴክኒካል ረዳቶችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።

➤ የሥራ መደብ፦ በተለያዩ የሙያ መስኮች
➤ ተፈላጊ ባለሙያዎች ብዛት፦ 18
➤ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፦ ከመጀመሪያ ዲግሪ ጀምሮ
➤ የሥራ ልምድ፦ ዜሮ ዓመት
➤ የሥራ ቦታ፦ ወራቤ ዩኒቨርሲቲ
➤ የማመልከቻ ጊዜ፦ ከጥቅምት 11/2017 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ አስር (10) የሥራ ቀናት

አመልካቾች ሙሉ የህይወት ታሪካችሁን (CV) እና ሙሉ የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውና የማይመለስ ኮፒ በመያዝ በዩኒቨርሲቲው የሰው ሃብት አስተዳዳርና ልማት ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁ. ዐ3 በመገኘት መመዝገብ ትችላላችሁ ተብሏል፡፡

ለበለጠ መረጃ፡- 0463299124

(ዩኒቨርሲቲው ያወጣው የቅጥር ማስታወቂያ ከላይ ተያይዟል፡፡)

@tikvahuniversity

48.2k 0 101 30 114

#ጥቆማ

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የድኅረ-ምረቃ ትምህርት አመልካቾች ምዝገባ ከዛሬ ጥቅምት 13 እስከ 19/2017 ዓ.ም ያከናውናል፡፡

ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ትምህርት የመግቢያ ፈተና (NGAT) ወስደው የማለፊያ ነጥብ በማምጣት ካመለከቱ መካከል፣ በቂ አመልካች ቁጥር የተገኘባቸውና በ2017 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲው ዋናው ግቢ የሚከፈቱ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች፦
▪️ Nutrition (መደበኛ)
▪️ Reproductive Health (መደበኛ)
▪️ MBA (መደበኛ እና ኤክስቴንሽን)

በሌሎች የትምህርት ክፍሎች ያመለከታቸሁ፣ በቂ የአመልካች ቁጥር ባለመገኘቱ የትምህርት ዝግጅታችሁ በሚያሳትፋችሁ በተከፈቱ ትምህርት ክፍሎች ላይ እንድትመዘገቡ ዩኒቨርሲቲው ጠቁሟል፡፡

በኦንላይን የተመዘገባችሁ ለምዝገባ ስትሔዱ ለማመልከት የተጠየቁትን መረጃዎች ይዛችሁ መቅረብ ይኖርባችኋል፡፡

@tikvahuniversity


የኢንቴሪየር ዲዛይን (Interior Design) ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን! 

👉 Sketch-Up, Revit, Rhino, 3D Max እና Lumion ሶፍትዌሮችን በአንድ ላይ
👉 ከንድፈ ሀሳብ እና ሶፍትዌር ስልጠና በተጨማሪ በተግባር በወርክሾፕም የሚሰለጥኑበት

☎️    0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦
ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ

Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
TikTok: @sage_training_institute' rel='nofollow'>https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute


ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ነባር መደበኛ ተማሪዎቹን በመቀበል ላይ ይገኛል።

ዩኒቨርሲቲው ለነባር መደበኛ እና የ2016 ሪሚዲያል ተማሪዎቹ ለጥቅምት 11 እና 12/2017 ዓ.ም ጥሪ ማድረጉ ይታወሳል።

@tikvahuniversity

50.2k 0 162 137 298

ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም በተቋሙ የሪሚዲያል ተማሪዎች የነበራችሁና የማለፊያ ነጥብ ያሰመዘገባችሁ እንዲሁም በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስዳችሁ በሰላሌ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሔደው ጥቅምት 21 እና 22/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

ለምዝገባ ስትሔዱ መያዝ የሚኖርባችሁ፦
▪️ ብርድ ልብስ፣ አንሶላ፣ ትራስ ጨርቅ
▪️ አራት 3x 4 ጉርድ ፎቶግራፍ

የምዝገባ ቦታ፦
ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ጀኔራል ታደሰ ብሩ ከምፓስ

@tikvahuniversity

59.7k 0 934 268 521

#ጥቆማ

የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ለ2017 ትምህርት ዘመን በመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራም ሰልጣኞችን መመዝገብ ጀምሯል፡፡

መስፈርቶች
▪️የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ የሆነ/የሆነች፣
▪️በ2015/16 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና የማለፊያ ውጤት (50%) ያለው/ያላት፣
▪️በ2014/15 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ተከታትለው ያጠናቀቁ

ስልጠናው በአዲስ አበባ ላምበረት መናኸሪያ አካባቢ በሚገኘው የኢንስቲትዩቱ ግቢ የሚሰጥ ሲሆን፤ በተጨማሪም የቻይንኛ እና ኮሪያኛ ስልጠናዎች ይሰጣሉ፡፡ ኢንስቲትዩቱ የምግብ እና የዶርም አገልግሎቶች ያቀርባል፡፡

የምዝገባ ጊዜ፦
ጥቅምት 11-15/2017 ዓ.ም
የመግቢያ ፈተና የሚሰጥበት ጊዜ፦
ጥቅምት 19/2017 ዓ.ም
ትምህርት የሚጀምረው፦
ኅዳር 2/2017 ዓ.ም

አስፈላጊ ሰነዶች
▪️ የ11ኛ እና የ12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት
▪️ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ሰርተፊኬት
▪️ የሪሚዲያል ፕሮግራም ሰርተፊኬት

@tikvahuniversity

56.6k 0 349 109 196

#DebreTaborUniversity

ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ለነባር መደበኛ የቅድመ-ምረቃ ተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል፡፡

በዚህም በ2016 ዓ.ም አንደኛ ዓመትና ከዚያ በላይ የነበራችሁ የደብረ ታቦር ዩንቨርሲቲ ተማሪዎች የ2017 ዓ.ም ትምህርት የምዝገባ ጊዜ ጥቅምት 25 እና 26/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

በ2016 ዓ.ም በተለያዩ ምክንያቶች ወደ ተቋሙ መሔድ ያልቻለችሁና ዊዝድሮዋል መሙላት ሳትችሉ የቀራችሁ ተማሪዎች በዚህ ዓመት ትምህርታችሁን ከቀጣይ ባች ጋር መቀጠል እንድትችሉ ዩኒቨርሲቲው ስለፈቀደ ከላይ በተጠቀሱት ቀናት ማመልከት ትችላላችሁ ተብሏል፡፡

በ2017 ዓ.ም የመጀመሪያ ዓመት የምትቀላቀሉ (2016 ዓ.ም ሪሚዲያል የነበራችሁ እና አዲስ የምትመደቡ) ተማሪዎች በሌላ ማስታዎቂያ ጥሪ ይደረግላችኋል ተብሏል፡፡

@tikvahuniversity

50.8k 0 111 54 138

💫 ከዳር እስከ ዳር በፈጣኑ የሳፋሪኮም ኢንተርኔት! እንገናኝ! ✨ የተመቸንን ሼር እናድርግ! 👍 ከወደድነው ጋር እንደልብ እንገናኝ!

አስተማማኙን ኔትወርክ ዛሬውኑ እንቀላቀል!

የቴሌግራም ቦታችንን https://t.me/official_safaricomet_bot በመጠቀም የአየር ሰዓት ወይም ልዩ ልዩ ጥቅሎችን እንግዛ!

#MPESASafaricom #SafaricomEthiopia #1Wedefit
#Furtheraheadtogether


#የሥራ_ቅጥር_ጥቆማ

ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የሙያ መስኮች አመልካቾችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።

➤ የሥራ መደብ፦ በተለያዩ የሙያ መስኮች
➤ ተፈላጊ ባለሙያዎች ብዛት፦ 71
➤ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፦ ከ2ኛ ዲግሪ ጀምሮ
➤ የሥራ ልምድ፦ አይጠይቅም
➤ የሥራ ቦታ፦ ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ
➤ የማመልከቻ ጊዜ፦ ከጥቅምት 6/2017 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ሰባት (7) ተከታታይ የሥራ ቀናት

የምዝገባ ቦታ፦
ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ (በሁሉም ግቢዎች) የብቃትና ሰው ሃብት አስተዳደር ሥራ አስፈፃሚ ቢሮ

ለበለጠ መረጃ፦ 0471350151 / 0473360159

(ዩኒቨርሲቲው ያወጣው የቅጥር ማስታወቂያ ከላይ ተያይዟል፡፡)

@tikvahuniversity

52.9k 0 83 47 183

#MoE

በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ወስደው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች ምደባ በቅርቡ እንደሚገለፅ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡

የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች፣ ምደባው ይፋ እስከሚደረግ በትዕግስት እንዲጠብቁ ሚኒስቴሩ ጠይቋል፡፡

@tikvahuniversity

60.3k 0 762 496 619

የ2017 ስልጠና ዘመን የቴክኒክና ሙያ የመደበኛ ስልጠና የመቁረጫ ነጥብ:

የተፈጥሮ ሳይንስ የመግቢያ ውጤት

የስልጠና ደረጃ 1 እና 2
▪️ ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥብ 141 እና ከዚያ በታች፣
▪️ ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥብ 137 እና ከዚያ በታች፣
▪️ ሴቶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥብ 138 እና ከዚያ በታች፣
▪️ ሴቶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥብ 134 እና ከዚያ በታች፣
▪️ ለሁሉም የአካል ጉዳተኞች የመቁረጫ ነጥብ 124 እና ከዚያ በታች፡፡

የስልጠና ደረጀ 3 እና 4
▪️ ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥብ 142 ከዚያ በላይ፣
▪️ ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥብ 138 እና ከዚያ በላይ፣
▪️ ሴቶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥብ 139 እና ከዚያ በላይ፣
▪️ ሴቶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥብ 135 እና ከዚያ በላይ፣
▪️ ለሁሉም የአካል ጉዳተኞች የመቁረጫ ነጥብ 125 እና ከዚያ በላይ፡፡

የስልጠና ደረጀ 5
▪️ ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥብ 179 ከዚያ በላይ፣
▪️ ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥብ 167 እና ከዚያ በላይ፣
▪️ ሴቶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥብ 170 እና ከዚያ በላይ፣
▪️ ሴቶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 162 እና ከዚያ በላይ፣
▪️ ለሁሉም የአካል ጉዳተኞች የመቁረጫ ነጥብ 154 እና ከዚያ በላይ፡፡


የማህበራዊ ሳይንስ የመግቢያ ውጤት

የስልጠና ደረጃ 1 እና 2
▪️ ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 139 ከዚያ በታች፣
▪️ ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥብ 135 እና ከዚያ በታች፣
▪️ ሴቶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥብ 134 እና ከዚያ በታች፣
▪️ ሴቶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥብ 124 እና ከዚያ በታች፣
▪️ ለሁሉም የአካል ጉዳተኞች የመቁረጫ ነጥብ 124 እና ከዚያ በታች፡፡

የስልጠና ደረጀ 3 እና 4
▪️ ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥብ 140 ከዚያ በላይ፣
▪️ ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥብ 136 እና ከዚያ በላይ፣
▪️ ሴቶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥብ 135 እና እና ከዚያ በላይ፣
▪️ ሴቶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥብ 125 እና ከዚያ በላይ፣
▪️ ለሁሉም የአካል ጉዳተኞች የመቁረጫ ነጥብ 125 እና ከዚያ በላይ፡፡

የስልጠና ደረጀ 5
▪️ ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥብ 172 ከዚያ በላይ፣
▪️ ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥብ 164 እና ከዚያ በላይ፣
▪️ ሴቶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥብ 165 እና እና ከዚያ በላይ፣
▪️ ሴቶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥብ 160 እና ከዚያ በላይ፣
▪️ ለሁሉም የአካል ጉዳተኞች የመቁረጫ ነጥብ 154 እና ከዚያ በላይ፡፡

@tikvahuniversity

56.9k 0 232 54 155

Forward from: TIKVAH-ETHIOPIA
የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ተደረገ።

የ2017 የቴክኒክና ሙያ የመደበኛ ስልጠና ዘመን መቁረጫ ነጥብ ዛሬ ይፋ ተደርጓል።

የመቁረጫ ነጥቡ ዝርዝር ከላይ ተያይዟል።

@tikvahethiopia

18 last posts shown.