Posts filter


"የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ሁሉም ተማሪዎች በተማሩበት ስርዓተ ትምህርት ይዘት ይዘጋጃል፡፡" - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

የ2017 ዓ.ም ተፈታኝ ተማሪዎች ከ9ኛ-10ኛ በነባሩ ስርዓተ ትምህርት፣ ከ11ኛ-12ኛ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት እንዲሁም ለስርዓተ ትምህርት የሙከራ ትግበራ በናሙናነት ተመርጠው የተሳተፉ ትምህርት ቤቶች ላይ የነበሩ ተማሪዎች 10ኛ ከፍልን በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት የተማሩ መሆናቸውን አገልግሎቱ ገልጿል፡፡

በአማራ ክልል በፀጥታ ችግር ምክንያት በ2016 ዓ.ም ሳይፈተኑ የቀሩና የ11ኛ ክፍልን በነባሩ ስርዓተ ትምህርት የተማሩ ትምህርት ቤቶች ላይ የነበሩ ተማሪዎች በ2017 ዓ.ም የሚፈተኑም አሉ፡፡

በመሆኑም የ2017 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና "ከላይ የተገለፁትን ነባራዊ ሁኔታዎች ከግምት ውስጥ ባስገባና ሁሉንም ተፈታኝ ተማሪዎች በማከለ መንገድ ስታንዳርዱን፣ ደህንነቱንና ሚስጢራዊነቱን ጠብቆ በመዘጋጀት ላይ ይገኛል" ብሏል አገልግሎቱ።

የፈተና ዝግጅቱ ምን ያካትታል?

➫ ከ9ኛ ከፍል ሙሉ በሙሉ ከነባሩ ስርዓተ ትምህርት፣
➫ ከ10ኛ ክፍል በነባሩ እና በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ተመሳሳይ ይዘቶች፣
➫ ከ11ኛ ከፍል በነባሩ እና በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ተመሳሳይ ይዘቶች፣
➫ ከ12ኛ ከፍል ሙሉ በሙሉ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሰረት የሚዘጋጅ ይሆናል።

የኢኮኖሚክስ የትምህርት ዓይነት በስርዓተ ትምህርቱ አዲስ የተጀመረ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በ12ኛ ክፍል ይዘት ላይ ብቻ ተመስርቶ ይዘጋጃል ተብሏል።

@tikvahuniversity

28.1k 0 337 80 220

Artificial Intelligence and Data Science ስልጠና በፒያሣ እና በመገናኛ ካምፓስ ምዝገባ ላይ ነን!

👉 ከፍተኛ ልምድ ባላቸው መምህራን የሚሰጥ
👉 ንድፈ ሀሳብን ከተግባር ጋር በማዛመድ የሚሰጥ ስልጠና

☎️   0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦
ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ

Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute


"በ2017 ዓ.ም 150 ሺህ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን በበይነ መረብ ለመፈተን ዝግጅት እየተደረገ ነው።" - ትምህርት ሚኒስቴር

ትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የምክክር መድረክ በማካሔድ ላይ ይገኛል።

በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) "በዚህ ዓመት 150 ሺህ የሚደርሱ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናቸውን በበይነ መረብ እንዲወስዱ ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል" ብለዋል።

በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በወረቀት እና በኦንላይን ድብልቅ በሆነ መልኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰጠ ሲሆን፤ 30 ሺህ የሚጠጉ ተማሪዎች ፈተናቸውን በኦንላይን መውሰዳቸው ይታወሳል።

@tikvahuniversity

38.5k 0 48 108 228

#ጥቆማ
#BongaUniversity

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የጤና ሙያ መስኮች ባለሙያዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡

➤ የሥራ መደብ፦ በጤና መስኮች
➤ ተፈላጊ ባለሙያዎች ብዛት፦ 37
➤ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፦ ከመጀመሪያ ዲግሪ ጀምሮ
➤ የሥራ ቦታ፦ ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ

መስፈርቱን የምታሟሉ ባለሙያዎች ከዛሬ የካቲት 13/2017 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ አስር የሥራ ቀናት በዩኒቨርሲቲው የብቃትና ሰው ሃብት አስተዳደር ሥራ አስፈጻሚ ቢሮ ወይም አዲስ አበባ ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ወኪል ቢሮ ሽሮሜዳ ከአሜሪካ ኤምባሲ ፊት ለፊት በመገኘት ማመልከት ትችላላችሁ ተብሏል፡፡

የፈተና ጊዜ በቀጣይ ይገለጻል፡፡ (ዝርዝር የሥራ ማስታወቂያው ከላይ ተያይዟል፡፡)

ለተጨማሪ መረጃ፦
0111561725 / 0911102250

@tikvahuniversity

37.8k 0 104 25 95

💨⚡️ ለብዙ ሰዓት ከምትወዱት/ከምትወዷት ጋር እንድታወሩ የሚያስችላችሁን 3000 mah የባትሪ አቅም ያለውና አዳዲስ የቴክኖሎጂ ትሩፋቶችን ይዞ በአንዴ እስከ 8 ሰው ድረስ የሚያስጠቅመውን ልዩ ቅመም MIFIን ገዝተን ፈጣን 4G ኢንተርኔት እንጠቀም! ለ30 ቀን ከሚቆይ ነጻ 30ጊባ ዳታ ጉርሻ ጋር 😋

ከሳፋሪኮም ጋር አንድ ወደፊት ⚡️

🔗 የ M-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያን በዚህ ሊንክ እናውርድ፦ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

#SafaricomEthiopia


አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ 85 የሕክምና ዶክተሮች እና 160 የጤና ሳይንስ ተማሪዎችን ቅዳሜ የካቲት 15/2017 ዓ.ም ያስመርቃል፡፡

መቱ እና ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲዎችን ጨምሮ በርካታ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሳምንቱ መጨረሻ ተማሪዎቻቸውን ያስመርቃሉ።

@tikvahuniversity

39.8k 0 13 40 120

#ጥቆማ

የወለጋ ዩኒቨርሲቲ ሪፌራል ሆስፒታል በተለያዩ ክፍት የሥራ መደቦች ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል።

የምዝገባ ጊዜ፦
እስከ ሰኞ የካቲት 17/2017 ዓ.ም

የምዝገባ ቦታ፡-
ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ሪፌራል ሆስፒታል የሰው ሀብት አስተዳደርና ልማት የሥራ ሂደት ቢሮ ቁ. 85

➫ አመልካቾች የምታቀርቡት የሥራ ልምድ ከሥራ መደቡ ጋር ቀጥታ ግንኙነት ያለው መሆን እንዲሁም ደመወዝና ከመቼ እስከ መቼ እንዳገለገሉ የሚገልጽ መሆን አለበት።

➫ አመልካቾች የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውና የማይመለስ አንድ ኮፒ ማቅረብ ይጠበቅባችኋል፡፡

➫ አመልካቾች የምታቀርቡት የሥራ ልምድ ማስረጃ የመንግሥታዊ መስሪያ ቤት ካልሆነ የገቢ ግብር መክፈላችሁን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባችኋል፡፡

➫ ዜሮ ዓመት ለሚጠይቁ የሥራ መደቦች የምትወዳደሩ አመልካቾች የሥራ-አጥ ካርድ ማቅረብ ይጠበቅባችኋል።

አስፈላጊውን መስፈርት የምታሟሉ አመልካቾች መወዳደር ትችላላችሁ የተባለ ሲሆን፤ የፈተና ቀን በውስጥ ማስታወቂያ ይገለጻል ተብሏል።

@tikvahuniversity


2ኛ ዙር የፎቶግራፊ፣ ቪዲዮግራፊ፣ ግራፊክ ዲዛይን እና ቪዲዮ ኤዲቲንግ ስልጠና በመገናኛ ካምፓስ ምዝገባ ላይ ነን። 

👉 ተግባርን ከንድፈ ሀሳብ ያስተሳሰረ ስልጠና
👉 Photography, Cinematography, Videography, Graphic Design and Video Editing በአንድ ላይ
👉 ፕሮጀክቶችን በስቱዲዮ እና በመስክ በመስራት የሚሰጥ

☎️   0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦
ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ

Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute


የተለያዩ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በልዩ ልዩ የትምህርት መስኮች ያስተማሯቸውን ተማሪዎች የካቲት 15 እና 16/2017 ዓ.ም ያስመርቃሉ።

አምቦ ዩኒቨርሲቲ፣ ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ፣ ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ፣ እና ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በሳምንቱ መጨረሻ ተማሪዎቻቸውን ከሚያስመርቁ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መካከል ይገኙበታል፡፡

ተቋማቱ በቅድመ-ምረቃ እና በድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች ያስተምሯቸውን ተማሪዎች ያስመርቃሉ።

@tikvahuniversity

50.6k 0 18 111 218

ሚዛን ኢንስቲትዩት ኦፍ ቴክኖሎጂ በሦስት ዙር ቴክኖሎጂ ነክ በሆኑ ኮርሶች ያሰለጠናቸውን 127 ተማሪዎች አስመርቋል።

ተመራቂዎቹ በዌብ ዲቨሎፕመንት፣ በሞባይል አፕ ዲቨሎፕመንት፣ በግራፊክስ ዲዛይን፣ በዲጂታል ማርኬቲንግ፣ በቪዲዮ ኤዲቲንግ፣ በቤዚክ ኮምፒውተር ስኪል እና በዳታ ሳይንስ መስኮች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

ተማሪዎቹም በመደበኛ፣ በማታ እና በእረፍት ቀናት በአካል እና በኦንላይን ትምህርታቸውን መከታተላቸውን የኢንስቲትዩቱ ሥራ አስኪያጅ አህመድ ሙሀመድ ገልፀዋል።

በ2014 ዓ.ም የተቋቋመው ኢንስቲትዩቱ እስካሁን ከ300 በላይ ተማሪዎችን ከ 2-9 ወር በሚሰጡ ኮርሶች በሰባት ዙር ማስመረቁን ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል።

@tikvahuniversity


20ኛ ዙር የድረ-ገጽ እና ሞባይል መተግበሪያ ማበልፀግ (Full-Stack Website and Mobile Application Development) ስልጠና በፒያሣ እና በመገናኛ ካምፓስ በምዝገባ ላይ ነን።   

👉 ተግባርን ከንድፈ ሀሳብ ያስተሳሰረ ስልጠና
👉 ፕሮግራሚንግ ትምህርቶችን አካቶ የሚሰጥ
👉 Front-end እና Back-end በአንድ ላይ እስከ Deployment ያካተተ
👉 በተግባር ድረ-ገጾች እና ሞባይል መተግበሪያዎችን እያበለፀጉ የሚሰለጥኑበት
👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት

☎️   0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦
ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ

Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute


የመውጫ ፈተና ውጤት መለቀቅን ተከትሎ በርካታ የኮምፕርሄንሲቭ ነርሲንግ ተፈታኞች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ልከዋል፡፡

"ፈተናው ከብሉ ፕሪንት ውጪ ነው የመጣው" የሚሉት ተፈታኞቹ፤ እርማቱ በድጋሜ ሊታይ ይገባል ሲሉ ይጠይቃሉ፡፡

በጉዳዩ ላይ ትምህርት ሚኒስቴርን ያነጋገርን ሲሆን፤ ከኮምፕርሄንሲቭ ነርሲንግ ፈተና ጋር የተያያዘ ምንም አይነት ቅሬታ ለተቋሙ #አለመድረሱን ሚኒስቴሩ ጠቁሟል፡፡

በውጤታቸው ላይ ቅሬታ ያላቸው ተፈታኞች በትምህርት ሚኒስቴር ውስጥ ለሚገኘው የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ ማቅረብ እንደሚችሉም ተቋሙ ገልጿል፡፡

በሌላ በኩል ውጤታቸውን ለማየት የተቸገሩ የግል (በድጋሜ) ተፈታኞች፣ ውጤታቸው ወደተፈተኑበት ተቋም የተላከ በመሆኑ ወደተቋማቱ በመሔድ ውጤታቸውን ማየት እንደሚችሉ ሚኒስቴሩ አስረድቷል፡፡

@tikvahuniversity

60.9k 0 168 287 343

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በቅድመ-ምረቃ እና በድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች ያስተማራቸውን 343 ተማሪዎች ዛሬ ያስመርቃል፡፡

ከተመራቂዎቹ 76ቱ በድኅረ-ምረቃ ፕሮግራም ትሀምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቀቁ ናቸው፡፡

@tikvahuniversity


የተባበሩት መንግሥታት የዘላቂ ልማት መፍትሔ ጥምረት (SDSN) የአፍሪካ ማዕከል በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከፍቷል፡፡

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተከፈተው የጥምረቱ ማዕከል የጥናትና ምርምር ሥራዎችን በማከናወን ለፖሊሲ አውጪዎች ግብዓት የሚሆኑ ሳይንሳዊ መፍትሔዎችን ያቀርባል ተብሏል።

የማዕከሉ መከፈት ተጨማሪ አቅም እንደሚፈጥር እና በትብብር ለአፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄዎችን ለመቅረፅ የራሱን አበርክቶ እንደሚወጣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተ/ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡

@tikvahuniversity


41ኛ ዙር የግራፊክ ዲዛይን፣ ቪዲዮ ኤዲቲንግ፣ ሞሽን ግራፊክ እና ዲጂታል ማርኬቲንግ ስልጠና በፒያሣ እና በመገናኛ ካምፓስ በምዝገባ ላይ ነን!

👉 ተግባርን ከንድፈ ሀሳብ ያስተሳሰረ ስልጠና
👉 Advanced Graphic + Video Editing + Motion Graphic + Digital Marketing በአንድ ላይ
👉 ከ50 በላይ ፕሮጀክቶች ያሉት
👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት

☎️   0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦
ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ

Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute


#Exit_Exam_Result

የ2017 አጋማሽ ዓመት የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ውጤት ኦንላይን የመመልከቻ ሊንክ መስራት ጀምሯል።

https//:result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት ExitExam የሚለውን በመምረጥና የራስዎን User Name በማስገባት ውጤትዎን መመልከት ይችላሉ።

@tikvahuniversity

72.9k 2 1.6k 662 439

የወለጋ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኢንስቲትዩት የመውጫ ፈተና ያስፈተናቸው ተማሪዎቹ ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገባቸውን አሳውቋል፡፡

በዚህም ኢንስቲትዩቱ ያስፈተናቸው የአንስቴዥያ፣ ሚድዋይፈሪ፣ ሜዲካል ላብራቶሪ ሳይንስ እና ፋርማሲ ተፈታኞች በሙሉ የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸውን ግልጿል፡፡

@tikvahuniversity


ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በቅርቡ ሥራ ያስጀመረው የመሀል-ሜዳ ካምፓስ ትምህርት መስጠት ጀምሯል፡፡

በቅርቡ ተማሪዎችን የተቀበለው ካምፓሱ፤ የመጀመሪያ ቀን የመጀመሪያ የትምህርት ክፍለ-ጊዜ ዛሬ አካሒዷል።

@tikvahuniversity


ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሜዲካል ኮሌጅ በ2017 አጋማሽ ዓመት የመውጫ ፈተና ካስፈተናቸው የሕክምና ተማሪዎች መካከል 98 በመቶ ተፈታኞች የማለፊይ ውጤት ማምጣታቸውን ገልጿል።

@tikvahuniversity

57.2k 0 15 143 206

#TVTI_Exit_Exam

የመውጫ ፈተና የምትወስዱ የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ሰልጣኞች በኦንላይን የምዝገባ ጊዜ ዛሬ ያበቃል።

ተከታዩን ማስፈንጠሪያ በመጫን የምታገኙትን ቅፅ በመሙላት ምዝገባ ያድርጉ 👇
https://forms.office.com/r/3KgnK1esuc

ኦንላይን መመዝገብ የማትችሉ አመልካቾች በኢንስቲትዩቱ ዋናው ግቢ በመገኘት በየትምህርት ክፍላችሁ መመዝገብ ትችላላችሁ ተብሏል።

🔔 የምዝገባ ጊዜው ዛሬ የካቲት 10/2017 ዓ.ም ያበቃል።

የመውጫ ፈተናውን #በድጋሜ ለምትወስዱ ተፈታኞች ፈተናው በኢንስቲትዩቱ ዋና ግቢ እና በአዲስ አበባ በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ይሰጣል።

የመዝገባ ብር 500 በኢንስቲትዩቱ የንግድ ባንክ አካውንት በማስገባት ክፍያ በመፈፀም ደረሰኝ መያዝ ይጠበቅባችኋል።

✍ የምዝገባ ጥሪው በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የጋርመንት ቴክኖሎጂ ሰልጣኞችንም ይመለከታል።

የመውጫ ፈተናው ከመጋቢት 6-11/2017 ዓ.ም ባለው ጊዜ እንደሚሰጥ ኢንስቲትዩቱ ገልጿል።

@tikvahuniversity

56k 0 22 11 60
20 last posts shown.