AddisWalta - AW


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.
For more updates please visit https://shorturl.at/ehosX https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


1600 ዓመታትን ያስቆጠሩ ቅርሶች የሚገኙበት የግል ሙዚየም

በሐረር ከተማ የሚገኘው የቀድሞው የተፈሪ መኮንን ታሪካዊ ጫጉላ ቤት አሁን ታሪካዊ ቅርሶች ተሰባስበው የተቀመጡበት የኢትዮጵያውያን፣ የውጭ አገር ዜጎችንና ቱሪስቶችን ቀልብም የሚስብ ልዩ ሙዚየም ሆኗል።

ታሪካዊ፣ ባህላዊ፣ ሃይማኖታዊ እና የተለያዩ እምነቶች እንዲሁም ብሔረሰቦች መገለጫ የሆኑ በ10ሺዎች የሚገመቱ ቅርሶችን አሰባስቦ የያዘ ነው፤ በበጎ ሰው ሽልማት ተሸላሚው በሀረሚያ ዩኒቨርሲቲ የክቡር ዶክትሬት በተበረከተላቸው ውልደት፣ እድገት፣ ትዳር እና ኑሯቸውም በሀረር ከተማ የሆነው አብደላ አሊ ሸሪፍ የመሰረቱት “ሸሪፍ ሙዚየም”።

ከ1600 ዓመታት በላይ ያስቆጠሩ ቅርሶች፣ ከአክሱም ዘመን ጀምሮ መገልገያ የነበሩ ሳንቲሞች፣ የትየለሌ ዓመታትን ህልው መሆን የቻሉ የሃይማኖት መጻሕፍት፣ የነገስታት ሰይፍ እና መሰል የጦር መሳሪያዎች፣ ንጉሳዊያን የተጻጻፏቸው ደብዳቤዎች፣ የተፈረሙ ውሎች እና ሌሎችም እጅን በአፍ የሚያስጭኑ ታሪካዊ ቅርሶችና ሰነዶች በሸሪፍ ሙዚየም ውስጥ በከፍተኛ ጥንቃቄ እና እንክብካቤ ተቀምጠዋል።

በቀደምት ሀረሬዎች የተዘጋጁ በአረብኛ ፊደል በኦሮሚኛ ቋንቋ የተጻፉ ሃይማኖታዊ ይዘት ያላቸው መጻሕፍት፣ በሀረር እናቶች በጥበብ እና በጥንቃቄ የተሳሉ የሃይማኖት መጻሕፍት ሽፋን እንዲሁም ሌሎች ረጅም ዓመታትን ያስቆጠሩ መጻሕፍት በሙዚየሙ ውስጥ እንደልብ ማግኘት ይቻላል፡፡

ሀረሬዎች ይገለገሉባቸው የነበሩ ሳንቲሞች እኛ በዚህ ዘመን ከምናውቃት አምስት ሳንቲም በመጠን 3 እጥፍ የሚያንሱ ሲሆን በአስገራሚ መልኩ በዚች እጅግ ጠባብ ዲያሜትር ባላት ሳንቲም ውስጥ “ነብዩ መሀመድ የአላህ መልዕክተኛ” የሚል ጽሑፍ ታትሞ ይታያል።

ከ1600 ዓመታት በፊት መገበያያ የነበሩትን የአክሱም ሳንቲሞችን ጨምሮ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ያሉ ገንዘቦች እና በምስራቅ አፍሪካ የተለያዩ አካባቢዎችም ግብይት ይፈጸምባቸው የነበሩ ጥንታዊ ገንዘቦች በሙዚየሙ ውስጥ ከአስፈላጊው ገለጻ ጋር በክብር ተቀምጠው ትውልድ ይጎበኛቸዋል፣ ይደነቅባቸዋል፣ ታሪክ ይማርባቸዋል።

ሙሉ ታሪኩን ለማንበብ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ👇
https://shorturl.at/pqtwx


አጓጊው ደሞ አዲስ በመጪው እሁድ ከቀኑ 9 ሰዓት ጀምሮ #በቀጥታ ስርጭት ለእናንተ ለተመልካቾቻችን ተወዳዳሪዎቹን ይዞላችሁ ይቀርባል።

በቀጥታ ስርጭትም ዳኞችና ተወዳዳሪዎች በተመልካቾች ድምፅ ይዳኛሉ። በዕለቱም በተሰጣቸው ኮድ በ8970 SMS ድምጽ ይስጡ!

ዮሐንስ ወርቁ በA1

አብርሐም ሸዋንቅጣው በA2

አብርሐም ኸይሩ በA4

ማትያስ ደርብ በA5

#ደሞ_አዲስ #አዲስ_ዋልታ #music #Idol

እሁድ ከቀኑ 9 ሰዓት ጀምሮ በቀጥታ ስርጭት ይጠብቁን 🎼🎹🥁🎤🎺🎷🎸🎻






የኢትዮጵያ ዓየር መንገድ ወደ ሩዋንዳ ኪጋሊ የሚያደርገውን ሣምንታዊ በረራ አሳደገ

ሚያዝያ 10/2016 (አዲስ ዋልታ) የኢትዮጵያ ዓየር መንገዱ ወደ ሩዋንዳ ኪጋሊ የሚያደርገውን ሣምንታዊ በረራ ማሳደጉን አስታወቀ፡፡

ዓየር መንገዱ ወደ ሩዋንዳ ኪጋሊ የሚያደርገውን ሳምንታዊ በረራ 12 እንደነበር አስታውሷል፡፡

ሆኖም ከሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ የሚያደርገውን ሳምንታዊ በረራ ወደ 18 ከፍ እንደሚያደርግ በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስታወቀ፡፡


ከቡልጋሪያ እስከ ሳይንስ ሙዚየም…….
“ወደዛ የምትጓዙ ሁሉ ተስፋ ማድረግ ጀምሩ” - ጋዜጠኛ መሀመድ ሀሰን

ዓለም በብዙ ነገር አርአያ የሚያደርጋት ጀርመን 50 በመቶ የሚሆኑ ተማሪዎቿን የ2ኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ሲያጠናቅቁ ወደ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ታስገባለች፡፡ እ.ኤ.አ በ2017 ከ279 ትሪሊየን ዩሮ በላይ በኤክስፖርት ያስገባው ሲመንስ የተሰኘው ካምፓኒዋም የተመሰረተው ይህን አይነት ስልጠና በወሰዱ ተማሪዎቿ ነው፡፡ በእውቀትም በክህሎትም በጣም የዳበሩ ዜጎች አሏት ተብሎ የሚታሰበው ደቡብ ኮሪያ፤ ከ69 በመቶ በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎቿ የ2ኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ሲጨርሱ ይህን ስልጠና ትሰጣለች፡፡ እነ ጀርመን ላይ ያመጣውን ለውጥ ያየችው አሜሪካም በአመት በዩኒቨርስቲዋ በኩል ከ25 ሺሕ እስከ 44 ሺሕ ዶላር እያስከፈለች የቴክኒክና ሙያን ትምህርት ታስተምራለች፡፡ ሀገራቱ የቴክኒክና ሙያ ትምህርቶችን መስጠት ያስፈለጋቸው የተማሪዎችን ክህሎት በማሳደግ ላይ ያላቸው ሚና ሰፊ በመሆኑ ነው፡፡ በዚህም የሰለጠኑ ሀገራት እኚህ ዓይነት ትምህርቶችን በመስጠት በፈጠራዎች፣ ስታርት አፖች እና ቴክኖሎጂዎች ላይ በስፋት እየሰሩበት ይገኛሉ፡፡

ወደ አፍሪካ እንምጣ…. ከሳህራ በታች ያሉ ሀገራት ላይ ያለው ሥራ ፈላጊ ሀይል 80 ከመቶ ስራውን የሚፈጥረው በዚሁ በስታርት አፕ ኢንዱስትሪ ነው፡፡ የአፍሪካ ልማት ባንክ ከአፍሪካ አጠቃላይ ምርት ውስጥ 55 ከመቶ ድርሻውን አሁንም ለስታርት አፕ ይሰጣል፡፡ በዘመኑ ልክ መፍጠን፣ በክህሎት መዳበር፣ ፈጠራ ላይ ትኩረት ማድረግና ስታርት አፕን ማበረታታት የአህጉሪቱ የችግር መውጫ መንገድ መሆኑ ይታመናል፡፡

ኢትዮጵያስ?

10 አመት ወደ ኋላ…......

ሙሉውን ለማንበብ ቀጣዩን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ
https://shorturl.at/adrJX


የብረት ምርትን ማሳደግ የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲያችን አካል ነው። የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በመጠቀም፣ ጥራት ያላቸው ከፍተኛ ኃይል አስተላላፊ የኤሌትሪክ ገመዶችን እና የኤሌትሪክ ማማዎችን ለኤሌክትሪክ ብሎም ለቴሌኮም ዘርፎች በሀገር ውስጥ ማቅረብን እየሠራንበት እንገኛለን። በተጨማሪም የተሽከርካሪዎችን እና የመለዋወጫዎችን የምርት ሥራ በመመልከቴም ተደስቻለሁ። ሀገር በቀል ኩባንያዎች ተሽከርካሪዎችን እና መለዋወጫዎችን ሲያመርቱ መመልከትም በእጅጉ ያበረታታል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢ አሕመድ


የአዲስ ዋልታ የወርቅ ደረጃ አጋር!
የአዲስ አበባ ኮሙኒኬሽን ቢሮ




የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳለፈ

ሚያዝያ 9/2016 (አዲስ ዋልታ) የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 30ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፡፡

በዚህም መሰረት፡-
1. ምክር ቤቱ በቅድሚያ የተወያየው የፌዴራል መንግስት ሰራተኞች ረቂቅ አዋጅ ላይ ሲሆን ረቂቁ በ29ኛው የሚኒስትሮች ም/ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ቀርቦ የፀደቀውን የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ፖሊሲ መሰረት በማድረግ ፖሊሲውን ለማስፈፀም እንዲቻል ተደርጎ የተዘጋጀ ነው።

በተጨማሪም ረቂቅ አዋጁ በ2010 ዓ.ም ጸድቆ ስራ ላይ የዋለው አዋጅ በትግበራ ሂደት የታዩ ክፍተቶችን በተለይም የመንግስት ሠራተኞች አስተዳደርን ነጻ፣ ገለልተኛ፣ ቀልጣፋ፣ ተደራሽነት እና ተጠያቂነት ላይ የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት፤ እንዲሁም ከጊዜው ጋር የሚራመድ የአስራር ስርአት ለመዘርጋት የሚያስችል ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምከር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ ተወያይቶ ግብዓቶችን በማከል ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

2. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው የሽግግር ፍትሕ ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ነው፡፡ በሀገሪቱ በተለያዩ ዘመናት የተከሰቱ እና የቀጠሉ ተደራራቢ እና ሰፊ የተጎጂና የአጥፊ ወሰን ያላቸው የሰብአዊ መብት ጥሰቶች፣ የእርስ በእርስ ግጭቶች፣ ያልጠሩ ትርከቶች እና በደሎችን ለመፍታት የተለያዩ ሙከራዎች ተደርገዋል፡፡ ሆኖም እነዚህ አሰራሮች በእውነት፣ በዕርቅ፣ በምህረት እና በፍትሕ ላይ የተዋቀረ እና በግልፅ ፖሊሲ የሚመራ ሁለንተናዊ የሽግግር ፍትሕ ስልትን አካታች፣ ሰብአዊ መብት-ተኮር በሆነ እና በተሰናሰለ መንገድ ባለመተግበራቸው የሚፈለገውን ዘላቂ መፍትሔ ማምጣት አልቻሉም።👇
https://shorturl.at/BGZ04


ዛሬ ምሽት በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ሁለት የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ይካሄዳሉ

ሚያዝያ 9/2016 (አዲስ ዋልታ) ዛሬ ምሽት በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ውድድር ሁለተኛ ዙር የሩብ ፍጻሜ መርኃ ግብር ሁለት ወሳኝ ጨዋታዎች ይካሄዳሉ።

ምሽት 4 ሰዓት ማንችስተር ሲቲ ከሪያል ማድሪድ የሚያደርጉት የሁለተኛ ዙር የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ በእግር ኳሱ አፍቃሪያን ዘንድ በከፍተኛ ጉጉት ይጠበቃል።

ሁለቱ ቡድኖች በጠንካራ አጨዋወት ሊጎቻቸውን በአንደኝነት ከመምራታቸው ባሻገር በመጀመሪያው ዙር ባደረጉት የሻምፒዮንስ ሊግ ግጥሚያ 3 ለ 3 በሆነ አቻ ውጤት መጠናቀቁ የዛሬ ምሽቱን ጨዋታ ተጠባቂ ያደርገዋል።

በሌላ በኩል ምሽት አራት ሰዓት ላይ ባየር ሙኒክ በሜዳው ከአርሰናል ጋር የሚጋጠም ሲሆን ሁለቱ ቡድኖች የመጀመሪያ ዙር የሩብ ፍጻሜ ጨዋታቸውን በሁለት አቻ ውጤት ማጠናቀቃቸው ይታወሳል።

በቡንደስ ሊጋው የውድድሩን ዋንጫ በዣቪ አሎንሶ የሚመራው ባየር ሊቨርኩሰን ማሸነፉን ተከትሎ ባየር ሙኒክ የአውሮፓ ትልቁን ክብር በማንሳት ለማካካስ ጠንክሮ እንደሚጫወት ይጠበቃል።

አርሰናል በበኩሉ በፕሪሚዬር ሊጉ በአስቶን ቪላ ከደረሰበት ሽንፈት ለመውጣት ጠንካራ ፉክክር እንደሚያደርግ ይገመታል።

ትናንት ምሽት በተካሄዱ ሁለት የሩብ ፍጻሜ ግጥሚያዎች አስገራሚ ውጤቶች የተመዘገቡ ሲሆን ፒ.ኤስ. ጂ ባርሴሎናን በሜዳው 4 ለ 1 አሸንፎ 6 ለ 4 በሆነ ድምር ውጤት ወደ ግማሽ ፍጻሜ ማለፉን አረጋግጧል። በሌላ በኩል የጀርመኑ ቦሩሲያ ዶርትመንድ አትሌቲኮ ማድሪድን 4 ለ 2 አሸንፎ 5 ለ 4 በሆነ ድምር ውጤት ወደ ቀጣይ ዙር አልፏል።

ፒ.ኤስ.ጂ እና ዶርትመንድ የመጀመሪያውን ዙር የሩብ ፍጻሜ ጨዋታዎች ተሸንፈው እንደነበር አይዘነጋም።


የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከተወሰደው ገንዘብ 95 በመቶ ማስመለሱን ገለጸ

ሚያዝያ 9/2016 (አዲስ ዋልታ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መጋቢት 7 ቀን 2016 ዓ.ም ከተከሰተው የሲስተም ችግር ጋር በተገናኘ ያለአግባብ ተወስዶ ከነበረው ገንዘብ 95 በመቶ የሚሆነውን ማስመለሱን አስታወቀ።

ባንኩ ከሲስተም ማሻሻያ ሥራ ጋር በተገናኘ በተጠቀሰው ዕለት በተፈጠረ ችግር ምክንያት ብር 801 ሚሊዮን 417 ሺሕ 747.81 ያለአግባብ ተወስዶ እንደ ነበር መገለጹ ይታወሳል።

ከተወሰደው ገንዘብ 762 ሚሊዮን 941 ሺሕ 341 ብር ማስመለስ መቻሉን ባንኩ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ላይ ባወጣው መረጃ አመልክቷል።

ይህም መሰብሰብ ከነበረበት ገንዘብ ውስጥ 95 በመቶ የሚሸፍን ሲሆን ቀሪውን 38 ሚሊዮን 474 ሺሕ 938 ብር የማስመለስ ስራ እንደሚቀጥልም ገልጿል።




የምሽቱን የሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታ ማን ያሸንፋል?
Poll
  •   ባርሴሎና
  •   ፒኤስጂ
  •   አቻ
302 votes




ፌዴሬሽኑ በአወዛጋቢው የማራቶን ውጤት ላይ ምርመራ እንደሚያከናውን አስታወቀ

ሚያዝያ 8/2016 (አዲስ ዋልታ) የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በአወዛጋቢው የቤጂንግ ግማሽ ማራቶን ውጤት ላይ ምርመራ እንደሚያከናውን አስታወቀ።

ባለፈው እሁድ በተደረገው የቤጂንግ ግማሽ ማራቶን ውድድር ላይ ሦስት አፍሪካዊያን አትሌቶች ሆን ብለው ሄ ጂ የተባለው ቻይናዊ አትሌት እንዲያሸንፍ ማድረጋቸውን የተለያዩ መገናኛ ብዙኃን መዘገባቸው ይታወሳል፡፡

ጉዳዩን በተመለከተ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ዮሐንስ እንግዳ ከአዲስ ዋልታ ጋር በነበራቸው ቆይታ በዕለቱ ውድድር ላይ የተሳተፈው ኢትዮጵያዊ አትሌት ጀደኔ ኃይሉ ከፌዴሬሽኑ እውቅና ውጭ ወደ ውድድሩ ስፍራ ማቅናቱን ገልጸው ያደረገውን ተግባር እንደሚያጣራ አስታውቀዋል።

የውድድሩ አዘጋጆች በምን መስፈርት ተወዳዳሪውን እንዳሳተፉት ፌዴሬሽኑ እንደማያውቅ አመልክተዋል። አትሌቱ ወደ ሀገር ሲመለስ ፌዴሬሽኑ ስለሁኔታው እንደሚያነጋግርም አንስተዋል።

በቤይጂንግ ግማሽ ማራቶን ላይ የተሳተፉት ኬኒያዊያኑ ሮበርት ኬተር፣ ዊሊ ምናንጋት እና ኢትዮጵያዊው ደጀኔ ኃይሉ ከስፖርታዊ ስነ ምግባር ባፈነገጠ መልኩ ሆን ብለው ሌላ ተወዳዳሪ እንዲያሸንፍ ፍጥነታቸውን በመቀነስ እንዲሁም በማበረታታት እንዲያሸንፍ ማድረጋቸው በተንቀሳቃሽ ምስል ይፋ መሆኑ ይታወሳል።

በሐብታሙ ገደቤ


ሮቦት እና ሰዎች የተሳተፉበት የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ፊልም ተመረቀ

ሚያዝያ 8/2016 (አዲስ ዋልታ) የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከሰዎኛ ፊልም ፕሮዳክሽንና ኢንተርቴይመንት ጋር በመተባበር ያቀረበው "አስተውሎት" የተሰኘ ፊልም በዛሬው ዕለት ተመረቀ።

በመርኃግብሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት ስራ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን በኢትዮጵያ ምድር የተሰሩ ሮቦቶችን በማሳተፍ ቀዳሚ የሆነ ፊልም እንደሆነም ተገልጿል።

የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና ኢትዮጵያን ከሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፍ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው ፊልሙን ሰርቶ ለማጠናቀቅ አንድ ዓመት ተኩል ጊዜ መፍጀቱን አመልክተዋል።

"አስተውሎት" ፊልም በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ ሳይንሳዊ ፊልም ሲሆን በሚካኤል ሚሊዮን ተዘጋጅቶ ተፈሪ ዓለሙ እና ሀረገወይን አሰፋን ጨምሮ አንጋፋና ወጣት ተዋንያን የተሳተፉበት መሆኑም በመርኃግብሩ ተገልጿል።

በአማረ ደገፋው


በኮሪደር ልማት ዝግ ሆነው የቆዩ መንገዶች ለተሽከርካሪ ክፍት ሆኑ

ሚያዝያ 8/2016 (አዲስ ዋልታ) በአዲስ አበባ ከተማ በተወሰኑ አካባቢዎች እየተከናወኑ በሚገኙ የኮሪደር ልማት ሥራዎች ምክንያት ዝግ ሆነው የቆዩ መንገዶች ለተሽከርካሪ ክፍት መደረጋቸውን ፖሊስ አስታወቀ፡፡

በዚህም መሰረት፡-

• ከደጃች ውቤ በአፍንጮ በር ወደ ራስ መኮንን ድልድይ

• ከባሻወልዴ ችሎት በቱሪስት ሆቴል ራስ መኮንን ድልድይ አፍንጮ በር

• ከዳኑ ሆስፒታል እስከ ቱሪስት ሆቴል በመውጣት ወደ ራስ መኮንን ድልድይ አፍንጮ በር

• ከአራዳ መስተዳደር ወደ ዳኑ ሆስፒታል መውረጃ በአንድ አቅጣጫ ብቻ አሽከርካሪዎች መጠቀም እንደሚችሉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ እየተከናወኑ ባሉ የልማት ሥራዎች ምክንያት ለአጭር ሆነ ለረጅም ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ በጥብቅ መከልከሉንም ነው ፖሊስ ያሳሰበው፡፡


ሻሸመኔ
#ከተሞቻችን

የምዕራብ አርሲ ዞን ዋና መቀመጫ የሆነችው የሻሸመኔ ከተማ ከአዲስ አበባ በስተደቡብ አቅጣጫ 255 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የምትገኝ ሲሆን በ1913 እንደተቆረቆረች ይነገርላታል።

ከከተማዋ ስያሜ ጋር በተያያዘ እንደ አፈታሪክ የምትነሳ አንዲት "ሻሼ" የምትባል እንግዳ ተቀባይ ሴት በአካባቢው ትኖር እንደነበር እና የሻሼ ቤት ወይም በኦሮምኛ "መነ-ሻሼ" የሚለው የስፍራው ስያሜ በጊዜ ሂደት ተቀይሮ ሻሸመኔ እንደተባለ በታሪክ ይወሳል።

ወይና ደጋ የአየር ንብረት ያላት የሻሸመኔ ከተማ ከባህር ጠለል በላይ 1937 ሜትር ከፍታ ላይ ትገኛለች።

ጀምበር የማይጠልቅባት የሻሸመኔ ከተማ የዞኑ ዋና የንግድ እና የትራንስፖርት ማዕከል ስትሆን ሐዋሳን ጨምሮ ወላይታ እና ዲላን የምታገናኝ ባለ5 በር ኮሪደር ከተማ ነች።

የተለያዩ ብሄረሰቦችን በጉያዋ ያቀፈችው ሻሸመኔ በ12 ወረዳ እና 4 ክፍለ ከተማዎች የተዋቀረች ስትሆን አቦስቶ፣ ጎፋ፣ አዋሾ፣ ኩዬራ እና አራዳ ከሰፈር ስያሜዎቹ መካከል ተጠቃሾች ናቸው።

ከበሀማስ፣ ከኮቤኮ፣ ከካሪቢያን እና ከጃማይካ የመጡ ዜጎች ለበርካታ ዓመታት ከትመው የሚኖሩባት ከተማ እንደሆነችም ይነገርላታል።

በከተማዋ ሻሸመኔ ሙዚየምና የተለያዩ የትምህርት ተቋማት የሚገኙ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ ሊድ ስታር ኢንተርናሽናል አካዳሚ፣ ሉሲ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ ሚሊኒየም ሻሸመኔ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ እናት ኮሌጅ እና የሻሸመኔ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ይገኙበታል።
👇👇
https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/pfbid0tqnYZqVyqH8k4ni2NZqrG57kTBLcjgagtMR986bCEyGm6CVVHv7gsMjX8ct6TbNpl


የአዲስ ዋልታ የኢድ አልፈጥር በዓል የወርቅ ደረጃ አጋር!
የአዲስ አበባ ኮሙኒኬሽን ቢሮ

20 last posts shown.