ወዳጄ ማስተዋል
አንድ ንጉሥ ካልመራህ ብዙ ሺህ ነገሥታት ይመሩሃል። አንዱን እግዚአብሔር ካልፈራህ የሚያስፈራሩ ብዙ ነገሮች ይገጥሙሃል። ትላንት የነበርህበት፣ ነገ የምትኖርበት ቢሆንም ዛሬ ግን ያለህበት ነው። ልብህን ካላስፈቀድኸው የፍቅር ሰው መሆን አትችልም። ትዕግሥትም ነገ የምትመነዝረው ሀብትህ ናት። አባቶችህ በአደባባይ የተሰየፉ ሰማዕታት ናቸውና የአደባባይ ክብርን አትሻ። ያልተፈቀደልህ የማይጠቅምህ ነውና ደስ ይበልህ። አበጀዋለሁ ብለህ ቢበላሽብህ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅ ነህና ደስ ይበልህ። አይነጋም ብለህ አልተኛህምና አይለወጥም ብለህ ተስፋን አትጣል።
#ዘሰዋስው
https://t.me/ZSewasw