Zemedkun Bekele (ዘመዴ)


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Blogs



Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Blogs
Statistics
Posts filter


Forward from: Fasil Ethiopian🇪🇹
ከጋብቻ በኋላ የጫጉላ ሽርሽር የተለመደ ነው።




#ሼር በማድረግ ተባበሩኝ🙏


👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇👇

                                   @emsmereja


Forward from: Fasil Ethiopian🇪🇹
ክሪስ ስማኝማ ልንገርህ👀
👉የአፍሪካ መሪዎች ከስልጣን ከወረዱ በኋላ፣ ህዝባቸው ምንም ጥቃት ፈፅሞባቸው አያውቅም። ምክንያቱም፦ ስልጣን የሚለቁት ሲሞቱ ብቻ ነው።

#ሼር በማድረግ ተባበሩኝ🙏


👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇👇

                                   @emsmereja


Forward from: Fasil Ethiopian🇪🇹
ዓርብ ምሽት! መጋቢት 22/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ልዑካን ቡድን አዲስ አበባ ውስጥ ከፌደራል መንግሥት ባለሥልጣናት ጋር እየተወያየ እንደኾነ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕስ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ መናገራቸውን የክልሉ ቴሌቪዥን ዘግቧል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው የመሩት የክልሉ ልዑካን ቡድንና የፌደራል መንግሥቱ ባለሥልጣናት እየተወያዩባቸው ከሚገኙባቸው አጀንዳዎች መካከል ዋነኛው፣ በትግራይ ክልል የመልሶ ማቋቋም እንቅስቃሴ ዙሪያ እንደኾነ ጣቢያው ገልጧል።

2፤ የብሄራዊ መልሶ ማቋቋሚያና ተሃድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ተሾመ ቶጋ በትግራይ ክልል የነፍስ ወከፍና የቡድን ጦር መሳሪያዎችን የማስፈታቱ ሂደት መዘግየቱን መናገራቸውን ዴይቸቨለ ዘግቧል። ኮሚሽነር ተሾመ ዛሬ ባሕርዳር ላይ በጉዳዩ ዙሪያ በተካሄደ የምክክር መድረክ ላይ፣ ለሂደቱ መዘግየት ምክንያቶቹ፣ አዲሱ ኮሚሽን በቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መጠመዱና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ምስረታ መዘግየቱ መማኾናቸውን መጥቀሳቸውን ዘገባው አመልክቷል። ኾኖም ኮሚሽነር ተሾመ፣ ከአሁን ጀምሮ የነፍስ ወከፍና ቀላል የጦር መሳሪያዎችን ትጥቅ የማስፈታቱ ሥራ በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሠረት ተግባራዊ መኾን ይጀምራል ማለታቸውን ዘገባው ጠቅሷል። በምክክር መድረኩ ላይ የአማራ ክልል ከፍተኛ ባለሥልጣናትና የመከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ መኮንኖች ተገኝተዋል ተብሏል።

3፤ የመንግሥታዊው የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎትን በዋና ሥራ አስፈጻሚነት ለስድስት ዓመታት የመሩት ሮባ መገርሳ ከሃላፊነታቸው መነሳታቸውን ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል። በሮባ ምትክ፣ በሪሶ አመሎ የኩባንያው ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኾነው እንደተሾሙ ዘገባው አመልክቷል። ተሰናባቹ ሮባ የኩባንያውን ዋና ሥራ አስፈጻሚነት ሃላፊነት ከመረከባቸው በፊት፣ በኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን በምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚነት ለዓመታት ያገለገሉና በዘርፉ የካበተ ልምድ ያላቸው እንደነበሩ ዘገባው ጠቅሷል። በተመሳሳይ፣ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር የኋላሸት ጀመረ ከሃላፊነት ተነስተው፣ በምትካቸው አብዱልበር ሸምሱ እንደተሾሙ ዜና ምንጩ ዘግቧል።

4፤ በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የኛንጋቶም ወረዳ አስተዳደር የአንድ እምነት ተከታይ ኡጋንዳዊያን ወደ ወረዳው የገቡት "የምጽዓት ቀንን በመሸሽ ነው" መባሉን እንዳስተባበለ ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል። የወረዳው አስተዳደር፣ 277 ኡጋንዳዊያን ወደ ወረዳው ባለፈው ታኅሳስ መግባታቸውን አረጋግጦ፣ ኾኖም ግን ኡጋንዳዊያኑ "በኡጋንዳ ይጀምራል ብለው ያመኑትን የምጽዓት ቀን ሽሽተው የተሰደዱ ናቸው" ተብሎ የተነገረው "የተሳሳተ መረጃ ነው" ማለቱን ዘገባው ጠቅሷል። ኡጋንዳዊኑ ለኛንጋቶም ብሄረሰብ "የቤተክርስቲያን መልዕክት ለማድረስና አካባቢውን ለመጎብኘት" የገቡ የሐይማኖት ተጓዦች እንደኾኑ የጠቀሱት የወረዳው ባለሥልጣናት፣ ኛንጋቶም ብሄረሰብ ከኡጋንዳ የፈለሰ ነው የሚል አፈ ታሪክ መኖሩንም ተናግረዋል ተብሏል። ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ ኡጋንዳዊያኑ "የምጽዓት ቀንን የሸሹ" መኾናቸውን ማረጋገጡን ትናንት ተናግሮ ነበር።

5፤ አሜሪካ የሱማሌላንድ ራስ ገዝ መንግሥት ወታደሮቹን የግጭት ቀጠና ከሆነችው ላስ አኖድ ከተማ እንዲያስወጣ ጠይቃለች። መንግሥትን የሚፋለሙ የላስ አኖድ የጎሳ ሚሊሻዎችም፣ በመንግሥት ኃይሎች ላይ ጥቃት ከማድረስ እንዲቆጠቡ አሜሪካ አሳስባለች። ሁለቱ ወገኖች ግጭቱን አብርደው ቀደም ሲል የተደረሰውን ተኩስ አቁም እንዲያከብሩ የጠየቀችው አሜሪካ፣ ሰብዓዊ ቀውሱ እንዳይባባስ ተፋላሚ ወገኖች በንግግር ግጭቱን መፍታት አለባቸው ብላለች። ባለፈው ኅዳር መካሄድ የነበረበት የሱማሌላንድ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ መዘግየቱ እንዳሳሰባትም አሜሪካ የገለጠች ሲሆን፣ የፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ መንግሥት ምርጫው የሚካሄድበትን የጊዜ መርሃ ግብር እንዲያሳውቅ ጥሪ አድርጋለች።

6፤ የዓለማቀፉ ወንጀል ፍርድ ቤት መመስረቻ ስምምነት ፈራሚዋ ደቡብ አፍሪካ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቱን ለ"ብሪክስ" አገራት የመሪዎች ጉባኤ ሲሄዱ እንደምታስተናግዳቸው ዛሬ በውጭ ጉዳይ ሚንስትሯ ናለዲ ፓንዶር በኩል አስታውቃለች። የዓለማቀፉ ወንጀል ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ፑቲን በዩክሬን "የጦር ወንጀል ፈጽመዋል" በማለት የእስር ማዘዣ ማውጣቱን ተከትሎ፣ በቀጣዩ ነሐሴ የ"ብሪክስ" አገራት የመሪዎች ጉባኤ አዘጋጇ ደቡብ አፍሪካ አቋሟ ምን እንደሚኾን በጉጉት ሲጠበቅ ነበር። ደቡብ አፍሪካና ሩሲያ በሌሎች አገራት ግፊት በድንገት ጠላት ሊኾኑ አይችሉም ያሉት ፓንዶር፣ ፑቲንን በጉባኤው እንዲገኙ እንደተጋበዙ ተናግረዋል። በዓለማቀፉ ፍርድ ቤት ስምምነት መሠረት፣ ደቡብ አፍሪካ ፑቲን ግዛቷን ከተረገጡ አስራ ለፍርድ ቤቱ የማስረከብ ግዴታ አለባት። "ብሪክስ" በፍጥነት በማደግ ላይ ያሉት ኃያላኑ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሩሲያ፣ ቻይና፣ ሕንድና ብራዚል የመሠረቱተ ቡድን ነው።

7፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 53 ብር ከ9017 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 54 ብር ከ9808 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 63 ብር ከ5330 ሳንቲም እና መሸጫው 64 ብር ከ8037 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ58 ብር ከ5545 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ59 ብር ከ7256 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። አንድ የቻይና ዩዋን ደሞ በ7 ብር ከ0868 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ7 ብር ከ2285 ሳንቲም ተሽጧል ተብሏል። #ሼር በማድረግ ተባበሩኝ🙏


👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇👇

                                   @emsmereja


Forward from: Fasil Ethiopian🇪🇹
ዓርብ ማለዳ! መጋቢት 22/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ መንግሥት ክስ የመሠረተባቸውን የሕወሃት ሲቪልና ወታደራዊ አመራሮች ከእስር መፍታቱን ከተከሳሾቹ ጠበቃና ቤተሰቦች ሰምታለች ። ትናንት ከእስር ከተፈቱት መካከል፣ የቀድሞው የትግራይ ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድር አብርሃም ተከስተ፣ አዲስዓለም ባሌማ እና የቀድሞዋ የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ኬሪያ ኢብራሂም ይገኙበታል። ከእስር የተፈቱት ተከሳሾች፣ በደብረጺዮን ገ/ሚካዔልና በጀኔራል ታደሠ ወረደ መዝገብ ስር ክስ ተመስርቶባቸው የነበሩ 16 ሲቪልና 20 ወታደራዊ መኮንኖች ናቸው። ተከሳሾቹ የተፈቱት፣ ፍትህ ሚንስቴር በፓርቲው ሲቪልና ወታደራዊ አመራሮች ላይ የከፈተውን ክስ ማቋረጡን ተከትሎ ነው።

2፤ የኤርትራ ወታደሮች ከተቆጣጠራቸው የኢሮብ ወረዳ አካባቢዎች እንዳልወጡ የወረዳዋ ነዋሪዎች መናገራቸውን ጠቅሶ ዶይቸቨለ ዘግቧል። ነዋሪዎቹ የሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦትና መሠረታዊ አገልግሎቶች እያገኙ እንዳልኾነ መግለጣቸውን ዘገባው ጠቅሷል። በሌላ ዜና፣ መከላከያ ሠራዊት በአማራ ክልል ዋግኽምራ ብሄረሰብ ዞን በሕወሃት ታጣቂዎች ቁጥጥር ስር የቆየችውን አበርገሌ ከተማን መቆጣጠሩ ተገልጧል። የዞኑ ጸግብጂ ወረዳ ግን እስካሁንም በሕወሃት ታጣቂዎች ስር እንደምትገኝ የወረዳው አስተዳደር ኮምንኬሽን ቢሮ መናገሩን ቪኦኤ ዘግቧል።

3፤ በጎረቤት ኬንያ የተቀሰቀሰው ጸረ-መንግሥት የቃውሞ ትናንትም ተባብሶ ቀጥሏል። የተቃዋሚው መሪ ራይላ ኦዲንጋ ለቀጣዩ ሰኞ አራተኛውን አገር ዓቀፍ የተቃውሞ ሰልፍ ጠርተዋል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ልዩ ልዑክ ሴናተር ክሪስ ኩንስ ወደ ናይሮቢ አቅንተው ውጥረቱን ለማብረድ ያደረጉት ሙከራ አለመሳካቱን የኬንያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ኩንስ ተልዕኳቸው የሽምግልና ጥረት ስለመኾኑ በይፋ ባይገልጡም፣ ከአገሪቱ ምክትል ፕሬዝዳንት ሪጋቲ ጋሻጉዋ እና ከራይላ ኦዲንጋ ጋር መነጋገራቸውን ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ይህንኑ ውይይት ተከትሎ፣ ምክትል ፕሬዝዳንቱ መንግሥት የተቃውሞ ሰልፉን ከሚያስተባብሩት ኦዲንጋ ጋር "በሥልጣን መጋራት" ዙሪያ ንግግር እንደማይኖረው ተናግረዋል ተብሏል።

4፤ አሜሪካ ለሱማሊያ አዲስ አምባሳደር መሾሟን አስታውቃለች። አሜሪካ በአምባሳደር ላሪ አንድሬ ምትክ አዲስ የሾመቻቸው፣ አምባሳደር ሪቻርድ ሪሌይ ናቸው። አሜሪካ አዲስ አምባሳደር የሾመችው፣ የሱማሊያ መንግሥት በአልሸባብ ላይ ሁለተኛውን ዙር አጠቃላይ ጦርነት ለመጀመር እየተዘጋጀ ባለበት ወቅት ላይ ነው። ተሰናባቹ አምባሳደር አንድሬ በሱማሊያ አምባሳደር ኾነው የተሾሙት ባለፈው ዓመት ጥር ወር ሲሆን፣ አምባሳደር አንድሬ በሱማሊያ መንግሥት እና በሱማሊያ ዓለማቀፍ አጋሮች መካከል የሠመረ ግንኙነት እንዲፈጠር ስለማድረጋቸው ይነገርላቸዋል።

5፤ የተመድ ጸጥታው ምክር ቤት በዲሞክራሲያዊት ኮንጎ የሚገኙ ሁሉም አማጺ ኃይሎችባስቸኳይና ለዘለቄታው ትጥቅ እንዲፈቱ አሳስቧል። ምክር ቤቱ፣ በተለይ ኤም-23 የተሰኘው አማጺ ቡድንተጨማሪ አካባቢዎችን እንዳይቆጣጠርና እስካሁን በኃይል የተቆጣጠራቸውን አካባቢዎችም በሙሉ እንዲለቅ ምክር ቤቱ አዟል። ምክር ቤቱ፣ ታጣቂ አማጺዎች ሴቶችን አስገድዶ መድፈርንና ሕጻናትን ለውጊያ መመልመልን ጨምሮ ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ይፈጽማሉ በማለት ከሷል። ምክር ቤቱ ይህን ውሳኔ ያሳለፈው፣ የምሥራቅ አፍሪካ ማኅበረሰብ አገራት በቀጠናው ማዕቀፍ ስር የአገሪቱን መንግሥት የሚያግዙ ወታደሮችን ወደ ምሥራቅ ኮንጎ መላክ በቀጠሉበት ወቅት ላይ ነው። ኡጋንዳ በቀጠናው ማዕቅፕፍ ስር፣ ከትናንት በስቲያ 5 ሺህ ወታደሮችን ወደ ምሥራቅ ኮንጎ ልካለች። #ሼር በማድረግ ተባበሩኝ🙏


👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇👇

                                   @emsmereja


Forward from: Fasil Ethiopian🇪🇹
ሐሙስ ምሽት!መጋቢት 21/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ ፍትህ ሚንስቴር በሕወሃት ከፍተኛ የሲቪልና የወታደራዊ መኮንኖች ላይ የመሠረተውን የወንጀል ክስ ማቋረጡን ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ሚንስቴሩ፣ ከሰሜኑ ጦርነት ጋር በተያያዙ ወንጀሎች ዙሪያ ያለው ተጠያቂነት "ዓለማቀፍ ተሞክሮን ታሳቢ ባደረገ መልኩ በሽግግር ፍትህ ማዕቀፍ ሊታይ እንደሚገባ ስምምነት ላይ ተደርሷል" ብሏል። ሚንስቴሩ፣ በሕወሃት ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖችና የሕወሃት ሊቀመንበር ደብረጺዮን ገ/ሚካዔልንና የአሁኑን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳን ጨምሮ በሲቪል የፖለቲካ አመራሮች ላይ የመሠረታቸውን ክሶች ያቋረጠው፣ ፌደራል መንግሥቱና ሕወሃት ፕሪቶሪያ ላይ በደረሱበት ሰላም ስምምነት መሠረት እንደኾነ ጠቅሷል። ሚንስቴሩ ክሶቹን ያቋረጠው፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሕወሃትን ከአሸባሪነት መዝገብ በሰረዘ ማግስት ነው።

2፤ የብሄራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን 250 ሺህ የሚደርሱ ተዋጊዎችን ትጥቅ አስፈትቶ መልሶ ለማቋቋም 29 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ወይም 555 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልገው መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ላደረጉ የውጭ ዲፕሎማቶች ባቀረበው የገንዘብ ልገሳ ጥያቄ መግለጡን ዋዜማ ሰምታለች። ኮሚሽኑ በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ተዋጊዎችንና ታጣቂዎችን ትጥቅ ለማስፈታት፣ ለመበተንና ወደ ኅብረተሰቡ ለመቀላቀል ባዘጋጀው ዝርዝር ሰነድ ዙሪያ፣ ከዲፕሎማቶች ጋር ሰሞኑን መወያየቱን ዋዜማ ተረድታለች። መንግሥት ከ20 እስከ 25 በመቶ የሚሆነውን ወጪ እንደሚሸፍንና፣ ላንድ የቀድሞ ተዋጊ መቋቋሚያ ከ36 ሺህ እስከ 60 ሺህ ብር እንደሚሰጥ በሰነዱ ተገልጧል። በመልሶ ማቋቋሙ፣ የትግራይ፣ አማራ፣ አፋር፣ ኦሮሚያ፣ ቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ ጋምቤላና ደቡብ ክልሎች ታጣቂዎችን ለማካተት የታቀደ ሲሆን፣ በመጀመሪያው ዙር ግን የትግራይ፣ አማራና አፋር ተዋጊዎች ብቻ ይካተታሉ ተብሏል።

3፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ የብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ረቂቅ አዋጅን ባንድ ድምጸ ተዓቅቦ አጽድቋል። አዋጁን ለምክር ቤቱ ያቀረበው የሕግና ፍትህ ቋሚ ኮሚቴ፣ ዲጂታል መታወቂያ ሁሉን ዓቀፍ፣ ወጥ እና አስተማማኝ በሆነ ሥርዓት የዜጎችን መረጃ ለመያዝ የሚረዳና በመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ግልጽነትንና ተጠያቂነት ያለበትን አሠራር ለመዘርጋት የሚያስችል መኾኑን ገልጧል። መንግሥት በጠቅላይ ሚንስትር ጽሕፈት ቤት ስር የተቋቋመው የዲጂታል መታወቂያ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ለወራት የሙከራ ሥራዎችን ሲተገብር መቆየቱ ይታወቃል።

4፤ ኢዜማ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ባለፈው ዓመት መጋቢት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርበው ያስሾሟቸው የመገናኛ ብዙኀን ባለሥልጣን ቦርድ አባላት ከሃላፊነታቸው እንዲነሱ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጠይቋል። ኢዜማ፣ የገዥው ፓርቲ አባላት የሆኑ የቦርድ አመራሮች የተሾሙት ከመገናኛ ብዙኀን አዋጅ በተቃራኒ ነው በማለት ተችቷል። ዐቢይ፣ መንግሥታቸው ነጻ መገናኛ ብዙኀንና ነጻ ሃሳብ እንዲኖር ጥረት እያደረገ መኾኑን ሰሞኑን ለምክር ቤቱ መናገራቸውን የጠቀሰው ኢዜማ፣ የሃሳብ የበላይነት ሊሰፍን የሚችለው ግን መንግሥት መገናኛ ብዙኀንን ነጻና ገለልተኛ ማድረግ ሲችል ብቻ ነው ብሏል። ኢዜማ፣ ገዥው ፓርቲ መገናኛ ብዙኀንን በተጽዕኖው ስር በማስገባቱ፣ ሃሳቦቼ የመደመጥ ዕድል ተነፍጓዋል በማለትም አማሯል።

5፤ ኢሰመኮ በፖለቲካ ፓርቲዎች "የመሰብሰብ መብት ላይ የሚጥሏቸው ገደቦች" እና በአባሎቻቸው ላይ የሚደርሱ እንግልቶች" ለዘለቄታው መቆም አለባቸው ሲል ዛሬ ባወጣው መግለጫ አሳስቧል። ኢሰመኮ፣ በእናት ፓርቲ እና በባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ የመሰብሰብ መብታቸው እንደተገደበ አረጋግጫለሁ ብሏል። የጎጎት የጉራጌ አንድነትና ፍትህ ፓርቲ ምስረታ አስተባባሪዎችም "እንግልትና እስራት" እንደደረሰባቸው ኢሰመኮ ገልጧል። በፓርቲዎች ላይ የሚፈጸሙባቸው ክልከላዎችና እገዳዎች፣ "የመሰብሰብ፣ የመደራጀትና የመሳተፍ መብቶች ጥሰቶች" እንደኾኑ ኢሰመኮ ጠቅሷል። መንግሥት በፓርቲዎች ላይ "ድንገተኛና ከታሰበላቸው ዓላማ በላይ የኾኑ ርምጃዎችን ከመውሰድ እንዲቆጠብ" እና ይልቁንም ለስብሰባ ተሳታፊዎች ጥበቃና ከለላ የመስጠት ግዴታ እንዳለበት ኢሰመኮ ገልጧል።

6፤ በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ወለጋ ዞን ነቀምቴ ከተማ የገዥው ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ደሳለኝ ቦኮንጆ ማንነታቸው ባያልታወቁ ታጣቂዎች ዛሬ መገደላቸውን የከተማ አስተዳደሩ በፌስቡክ ገጹ አስታውቋል። የከተማ አስተዳደሩ፣ የፓርቲው ሃላፊ ለሥራ ከቤታቸው ሲወጡ በተተኮሰባቸው ጥይት እንደተገደሉ ገልጧል። የኦሮሚያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤትም፣ ግድያውን የፈጸመው "የታጠቀ ኃይል" ነው በማለት በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል። በነቀምቴ ከተማ በመንግሥትና የፓርቲ ሃላፊዎች ላይ ግድያ ሲፈጸም የአሁኑ የመጀመሪያው አይደለም።

7፤ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ከኡጋንዳ የተነሱ ኡጋንዳዊያን የአንድ እምነት ተከታዮች የኢትዮጵያን ድንበር አቋርጠው ደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን ንያንጋቶም ወረዳ ውስጥ መስፈራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ መለስ ዓለም ዛሬ በሰጡት መግለጫ ማረጋገጣቸውን መግለጫውን የተከታተሉ የአገር ውስጥ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። በመቶዎች የሚቆጠሩ የአንድ እምነት ተከታዮች "የመጨረሻው ምጽዓት" ኡጋንዳ ውስጥ ሊጀምር ተቃርቧል በሚል እምነት ወደ ኢትዮጵያ እንደተሰደዱ ከሳምንታት በፊት የኡጋንዳ ዜና ምንጮች ዘግበው ነበር። መለስ፣ ኡጋንዳዊያኑ ስደተኞች የገቡበትን መንገድ ወይም ብዛታቸውን ይግለጡ አይግለጡ ግን ዜና ምንጮቹ አልጠቀሱም።

8፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 53 ብር ከ8978 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 54 ብር ከ9758 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 63 ብር ከ5273 ሳንቲም እና መሸጫው 64 ብር ከ7978 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ58 ብር ከ5007 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ59 ብር ከ6707 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። #ሼር በማድረግ ተባበሩኝ🙏


👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇👇

                                   @emsmereja


Forward from: Fasil Ethiopian🇪🇹
ኬሪያ ኢብራሂም፣ ዶ/ር አብርሃም ተከስተ እና ዶ/ር አዲስዓለም ባሌማ ከእስር ተፈቱ!
በዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል እና በጄነራል ታደሰ ወረደ መዝገብ ተከስሰው በእስር ላይ የነበሩ የህወሓት ሲቪል እና ወታደራዊ አመራሮች ዛሬ ሐሙስ መጋቢት 21፤ 2015 አመሻሽ ላይ ከእስር መፈታታቸውን የተከሳሾቹ ጠበቆች አስተባባሪ የሆኑት አቶ አቶ ሃፍቶም ከሰተ ተናገሩ።

በዛሬው ዕለት ከእስር ተለቅቀው ወደ ቤታቸው መግባታቸው ከተረጋገጡ ተከሳሾች ውስጥ፤ የህወሓት ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም፣ ዶ/ር አብርሃም ተከስተ እና ዶ/ር አዲስዓለም ባሌማ እንደሚገኙበት ጠበቃው አስታውቀዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

#ሼር በማድረግ ተባበሩኝ🙏


👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇👇

                                   @emsmereja


Forward from: Fasil Ethiopian🇪🇹
አቶ አዲሱ አረጋ አለቃዬ ተነኩ፥ ስልጣን ልቀቁ ተባሉብን አይነት ለስለስ ያለች ለቅሶ አድርሰውናል። 'የማይመቱት ልጅ ሲቆጡት ያለቅሳል' ን መተረት አልፈልግም። አቶ አዲሱ ሞራል፥ ህሊና፥ ይሉኝታ አፈር ከድሜ በጋጡባት ሀገር ይህን ማለታቸው ብዙም አያስደንቅም። ስለገደልነው፥ ስለበደልነው፥ ስላበላሸነው ሁሉ ለምን አልተሸለምን፥ ስለምንስ አልተመሰገንም አለማለታቸው በራሱ አንድ ነገር ነው። ከአንድ ወንዝ የሚቀዳ፡ እንደሳሙና ፋብሪካ አንድ ዓይነት አስተሳሰብ ከሚያመነጭ ቡድን የተለየ ሀሳብ፥ ስሜት የሚሰጥ ሙግት ለማግኘት እጅግ አስቸጋሪ ነው። አቶ አዲሱ ምንም ሊነግሩን አልመጡም። ሊነግሩንም የሚችሉት ሀሳብ የላቸውም። ለአለቃቸው ታማኝነታቸውን፡ ለተወላገደው አካሄዳቸው ጭብጨባቸውን ሊያሰሙን እንጂ ከጠ/ሚሩ የተለየ ምንም አልነገሩንም። ጆሮአችን በከንቱ ደነቆረ።

በእኔ በግል እይታ ጠ/ሚሩ ከህወሀት ጋር በነበሩት ሶስቱ ጦርነቶች በሰጡት አመራር ብቻ ከስልጣን መልቀቅ ባለፈ በህግ ሊጠይቁ በተገባቸው ነበር። ሌላ ሌላውን እንተወው። በመላ ሀገሪቱ በበረከተው ዕልቂት፡ በነገሰው ሞት፡ ምድሩን በሞላው መፈናቀል ይቅርታ ብናደርግላቸው እንኳን መንገድ ላይ እያዘረከረኩ ወደኋላ በመለሷቸውና አሁንም ድረስ መቋጪያ ባለበጁላቸው ጦርነቶች ብቻ በፍርድ መጠየቅ የሚገባቸው መሪ ናቸው። ይህ ሁሉ፥ በመንግስታዊ እንዝህላልነት በፓርቲያቸውና በግልም እሳቸው በነበራቸው ድርሻ የተከሰተ ግዙፍ ሀገራዊ ኪሳራና ሰብዓዊ ዕልቂት ነው። ጠሚ/ሩ ገና ከመነሻው እኔ አሻግራችኋለሁ ብለው ሃላፊነቱን በግል ወስደዋል። በቅርቡ በቤተክርስቲያኒቱ ጉዳይ ካቢኔአቸውን በሙሉ ''አይመለከታችሁም'' በሚል ቁጣ አዘል ማስጠንቀቂያ ተጠያቂነቱን ራሳቸው ላይ አሸክመዋል።

ኦቦ አዲሱ አረጋ የብሽሽቅ ፖለቲካ ሱሳቸው እንደሆነ ባውቅም በልካቸው ሊነገራቸው እንደሚገባ ስለማምን ነው ለአጭር መልዕክታቸው አጭር አስተያየት መስጠት የፈለኩት። በሀሳብ እንዳልሞግታቸው ሀሳብ ይዘው አልመጡም። በአመክኒዮ እንዳልከራከራቸው ደረቅ የካድሬ ትርክት እንጂ ሌላ መልክ ያለው ለሙግት የሚጋብዝ ነገር አልጻፉም። ዝም ብሎ ግትትት ያለ የ'ጌታዬ ለምን ተነካ' እሮሮ ነው ያቀለጡት። እናም በአጭሩ መልስ ለመስጠት ያህል ጠ/ሚሩ ስልጣን ልቀቁ መባላቸው ሊያስገርምዎት አይገባም። ከትንሹ እግዚያብሄር ከሆነው ህሊና ስለተጣሉ እንጂ የተጠየቀው በጣም ጥቂቱ፡ ከውቅያኖስ በጭልፋ እንደመጨለፍ ያህል የሚታይ ነው። መደመር በምትሉት ባዶ ፍልስፍና ሰክራችሁ ሀገር እያሳበዳችሁ በመሆናችሁ አሁን ላይ ምንም ላይሰማችሁ ይችላል። የስልጣን ስካር አይጣል ነው። ልቦና ያውራል። አይንን ይጋርዳል። ልክ እንደአረቄ ስካር ነው። ሲለቅና ሲበርድ ግን ያን ጊዜ ነው እናንተን ማየት።

ለማንኛውም አይደንግጡ። ኮንትራት ምናምን ያሉት ተራ መከራከሪያ ነው። ስልጣንኑን የሰጣችሁን ህዝብ መከራ በአናት አናቱ እየጋታችሁት ጊዜአችንን እስከምንጨርስ እየሞትክ ጠብቀን የሚሉት ፈሊጥ ብልጽግና መንደር ብቻ የሚሰራ ሎጂክ ሊሆን ይችላል። በነገራችን ላይ ከእርስዎ ጋር የሚያገናኘኝ አንድ ጉዳይ ከሰሞኑ ይኖረኛል። ለስልጣን እንዲህ አውሬ እንድትሆኑ ያደረጋችሁ የዘረፋ ጉዳይን በተመለከተ መረጃዎችና ማስረጃዎች እየመጡ ናቸው። በሱ ቋንቋ ብንነጋገር የሚሻል ይመስለኛል። ህዝብን ዘረኝነት እየጠቀጠቃችሁበት፡ በቤተሰብ፡ በአምቻና ጋብቻ ተጣምዳችህ ሀገርን በቁም እየዘረፋችሁ ስለመሆናችሁ ህዝብ እንዲውቀው የምናደርግ ይሆናልና ያን ጊዜ ስልጣን መልቀቅ ምን እንደሚመስል ይነግሩናል። ገለቶማ ጃል! #ሼር ብቻ Godhaa
#ሼር በማድረግ ተባበሩኝ🙏


👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇👇

                                   @emsmereja

✍️መሳይ መኮንን


Forward from: Fasil Ethiopian🇪🇹
ሐሙስ ማለዳ! መጋቢት 21/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ የአውሮፓ ኅብረት ኮሚሽን ለኢትዮጵያ ለሰብዓዊ ዕርዳታ የሚውል የ60 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዩሮ ለመስጠት መወሰኑን ትናንት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ኅብረቱ ለኢትዮጵያ የገንዘብ ዕርዳታ ለመስጠት የወሰነው፣ የሰሜኑ ጦርነት፣ ግጭቶች እና ድርቅ በአገሪቱ ላይ ከፍተኛ የሰብዓዊ ቀውስ እንዳስከተሉ በመጥቀስ ነው። ኅብረቱ ኢትዮጵያን ጨምሮ በከፍተኛ ሰብዓዊ ቀውስ ለተመቱ ሰባት የአፍሪካ ቀንድ አገራት ለመስጠት የወሰነው፣ 331 ሚሊዮን ዩሮ እንደሆነ ገልጧል። ኅብረቱ ለደቡብ ሱዳን ከፍተኛውን 82 ሚሊዮን ዶላር መድቤያለሁ ብሏል።

2፤ በሱማሌ ክልል ሲቲ ዞን የመከላከያ ሠራዊት አባላት ተኮሱት በተባለ ጥይት ሦስት ሰዎች መገደላቸውንና ስድስቱ መቁሰላቸውን ሰምቻለሁ ሲል አዲስ ስታንዳርድ ዘግቧል። ሰዎቹ የተገደሉት፣ ሰኞ'ለት የአይሻ ወረዳ ነዋሪዎች መከላከያ ሠራዊት በሱማሌ ክልልና አፋር ክልል የድንበር ውዝግብ የአፋር ክልል ልዩ ኃይልን ያደግፋል በማለት ተቃውሟቸውን ለማሰማት አደባባይ በወጡበት ወቅት እንደኾነ ዘገባው ጠቅሷል። የመከላከያ ሠራዊት አባላት ከመድረሳቸው በፊት፣ ተቃዋሚዎች የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ሐዲድ መስመርን ዘግተው እንደነበርና መስመሩን ለማስከፈት በተፈጠረ ውዝግብ ሰዎቹ እንደተገደሉ ምንጮች ነግረውኛል ሲል ዜና ምንጩ አትቷል።

3፤ 33 ኢትዮጵያዊያን "ሕገወጥ" ፍልሰተኞች ከሱማሊያዋ ፑንትላንድ ራስ ገዝ ወደ አገራቸው መመለሳቸውን ፋና ብሮድካስት ዘግቧል። ከተመላሾቹ መካከል፣ 12ቱ ሴቶች ሲሆኑ፣ ቀሪዎቹ ወንዶች እንዲሁም አራቱ ሕጻናት እንደሆኑ ዘገባው ጠቅሷል። ፍልሰተኞቹ የተመለሱት፣ ፑንትላንድ የሚገኘው የኢትዮጵያ ቆንስላ ከዓለማቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት ጋር በመተባበር ነው። ተመላሾቹ በሕገወጥ ሰው አዘዋዋሪዎች አማካኝነት ወደ የመን ለመሻገር ፑንትላንድ የገቡ መሆኑ ተገልጧል።

4፤ የተመድ አባል አገራት ዓለማቀፉ የዳኝነት ፍርድ ቤት የበለጸጉ አገራት ለአየር ንብረት ለውጥ ባለባቸው ሃላፊነት ላይ የሕግ አስተያየት እንዲሰጥ በአብላጫ ድምጽ ወስነዋል። ፍርድ ቤቱ የሕግ ውሳኔ እንዲሰጥ የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ 130 አገራት ደግፈውታል። አሜሪካና ቻይና የውሳኔ ሃሳቡን በግልጽ አልተቃወሙም ወይም አልደገፉም። የፍርድ ቤቱ የሕግ አስተያየት አስገዳጅ ባይሆንም፣ ወደፊት በሚደረጉ የአየር ንብረት ለውጥ ድርድሮችና ክሶች ላክ ግን ተጽዕኖ ይኖረዋል ተብሏል። ፍርድ ቤቱ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የሕግ አስተያየት የመስጠት ሥልጣን ሲያገኝ፣ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።

5፤ አሜሪካ የተቃውሞ ሁከት ወደቀጠለበት ኬንያ ሴናተር ክሪስ ኩንስን ልካለች። ሴናተር ኩንስ፣ ክኬንያ ባለሥልጣናት ጋር በሁለትዮሽ የጸጥታ እና ንግድ ግንኙነቶች ዙሪያ እንደሚነጋገሩ የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ኩንስ፣ በኬንያ ሰሞኑን ከተፈጠረው ሁከት የተቀላቀለበት ጸረ-መንግሥት የተቃውሞ ሰልፍ ዙሪያ ጭምር ከአገሪቱ ባለሥልጣናት ጋር ይነጋገሩ እንደኾነ ወይም ተልዕኳቸው ከዚሁ ጋር የተገናኘ ይኹን አይኹን ለጊዜው አልተገለጸም። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የኬንያ ተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ራይላ ኦዲንጋ የጠሩት ሦስተኛው አገር ዓቀፍ የተቃውሞ ሰልፍ ዛሬ ይካሄዳል። #ሼር በማድረግ ተባበሩኝ🙏


👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇👇

                                   @emsmereja


Forward from: Fasil Ethiopian🇪🇹
ጌታቸው ረዳ‼️
የትግራይ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳና ከፍተኛ ባለስልጣናት አዲስአበባ ውስጥ እየተዟዟሩ የፌደራሉ መንግስት ተቋማትን እየጎበኙ ሲሆን በቀጣይ በትግራይና በፌደራሉ መንግስት ሆነ ከሌሎች ክልሎች ጋር የሚኖረውን ግንኙነት መስመር እያስያዙ ይገኛል። በነገራችን ላይ ጌታቸው ረዳ የሚጠበቀው በUN High Security Agents ጠባቂዎች እንደሆነ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
ሰሞኑን በአዳማ ከኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ጋር ተገናኝተዋል። #ሼር በማድረግ ተባበሩኝ🙏


👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇👇

                                   @emsmereja


Forward from: Fasil Ethiopian🇪🇹
ረቡዕ ምሽት! መጋቢት 20/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ከኢትዮጵያ መንግሥት የቀረበልኝ የሰላም ንግግር ጥሪ የለም በማለት አስተባብሏል። የኢትዮጵያ መንግሥት የሰላም ጥረት አደረኩ የሚለው፣ የቡድኑን አመራሮችና አባላት የትጥቅ ትግላቸውን ትተው ለመንግሥት እጃቸውን እንዲሰጡ በአካባቢ ሽማግሌዎች አማካኝነት ያደረገውን ያልተሳካ ሙከራ ነው በማለት ቡድኑ ገልጧል። ቡድኑ፣ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ትናንት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ ላይ፣ ግጭቱን ለመፍታት 10 ያህል ሙከራዎች ተደርገዋል በማለት የተናገሩት ንግግር ተጨባጭ ሁኔታውን በትክክል አይገልጽም ብሏል። ሆኖም ቡድኑ አሁንም በገለልተኛ ሦስተኛ አካል ለሚደረግ ድርድር ዝግጁ መሆኗን በድጋሚ ገልጧል።

2፤ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ታጣቂዎች በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ 100 ያህል ሰዎችን አግተው እንደሚገኙ መስማቱን ጠቅሶ ሪፖርተር ዘግቧል። በአካባቢው የፌደራል ፖሊስ አባላት ሠፍረው እንደሚገኙ ነዋሪዎች መናገራቸውን የጠቀሰው ዘገባው፣ ሆኖም ፖሊሶች ታጋቾቹን ለማስለቀቅ የወሰዱት ርምጃ የለም ማለታቸውን ገልጧል። የወረዳው አስተዳዳሪ ሺበሺ አያሌው በበኩላቸው፣ ታጣቂዎቹ በተደጋጋሚ እገታ እንደሚፈጽሙ አምነው፣ ሆኖም የመንግሥት ጸጥታ ኃይሎች በቡድኑ ታጣቂዎች ላይ ርምጃ እየወሰዱ መሆኑን መናገራቸውን ዜና ምንጩ አመልክቷል። አጋቾቹ ላንድ ታጋች እስከ 200 ሺህ ብር ድረስ ይጠይቃሉ ተብሏል።

3. የዋጋ ንረት የኢትዮጵያን የውጭ ንግድ እየተፈታተነው መሆኑን ዋዜማ ካገኘቻቸው መረጃዎች መረዳት ችላለች። በተለይ የስጋ የወጪ ንግድ በውጭ ምንዛሬ እጥረት ሳቢያ በተያዘው ዓመት በከፍተኛ ደረጃ ያሽቆለቆለ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ወደ ዱባይ የምትልከው የስጋ ምርት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኬንያዊያን ስጋ ላኪዎች እንደተበለጠ ምንጮች ተናግረዋል። ስጋ ላኪዎች በተለይ የፍየል ስጋ ከአገር ውስጥ ገበያ የሚገዙበት ዋጋ በከፍተኛ ደረጃ መወደዱ፣ ኪሳራ ላይ እንደጣላቸው ጨምረው ገልጸዋል። ባለፈው ዓመት በሰባት ወራት ውስጥ ለውጭ ገበያ የቀረበው 13 ሺህ 800 ቶን ስጋ ሲሆን፣ ዘንድሮ በተመሳሳይ ወራት የቀረበው ግን 9 ሺህ 600 ቶን ስጋ ብቻ እንደሆነ ተገልጧል።

4፤ የኡጋንዳው ፋይንቴክ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ከኢትዮጵያው አዋሽ ባንክ ጋር የሥራ ትብብር መፍጠሩን የኡጋንዳው ዘ ሞኒተር ጋዜጣ ዘግቧል። ኩባንያው ከባንኩ ጋር የፈጠረው የሥራ ትብብር ስምምነት፣ ባንኩ በንግድ፣ በዕርዳታ ሥርጭት እና በኢንሹራንስ ዘርፎች አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እንዲተገበ እንደሚያስችለው የኩባንያው ሃላፊዎች መናገራቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ፋይንቴክ ኩባንያ በኡጋንዳ በሞባይል የገንዘብ ብድር መስጠት አገልግሎት፣ በባንክ እና ኢንሹራንስ ዘርፎች ሰፊ ልምድ ያለው ነው።

5፤ በአሜሪካ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፍሎሪዳ ግዛት ተወካይ ማት ገዓዝ አሜሪካ ወታደሮቿን ከሱማሊያ እንድታስወጣ የሚጠይቅ ረቂቅ የውሳኔ ሃሳብ ለምክር ቤቱ አቅርበዋል። የገዓዝ ረቂቅ የውሳኔ ሃሳብ፣ የአሜሪካ ወታደራዊ አመራሮች አሜሪካ ከምታሰለጥናቸው የሱማሊያ ወታደሮች መካከል ነገ የትኞቹ በመፈንቅለ መንግሥት እንደሚሳተፍ በማይገምቱበት ሁኔታ፣ የአሜሪካ ወታደሮች በሱማሊያ መገኘታቸው አሳማኝ አይደለም ይላል። ረቂቅ የውሳኔ ሃሳቡ፣ የፔንታጎን ባለሥልጣናት የአሜሪካ ወታደሮች ሱማሊያ ውስጥ መስፈራቸው የአሜሪካን ሕዝብ ምን ያህል እንደሚጠቅም ማብራራት አልቻሉም የሚል መከራከሪያም አቅርቧል። በምክር ቤቱ ሕግ መሠረት፣ በረቂቅ የውሳኔ ሃሳቡ ላይ በ18 ቀናት ውስጥ ውይይት ይደረግበታል። "ዳናብ" የተሰኘውን የሱማሊያ ልዩ ኮማንዶ ብርጌድ የሚያሰለጥኑት የአሜሪካ ወታደሮች ናቸው።

6፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 53 ብር ከ8887 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 54 ብር ከ9695 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 63 ብር ከ3673 ሳንቲም እና መሸጫው 64 ብር ከ6346 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ58 ብር ከ3453 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ59 ብር ከ5122 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። #ሼር በማድረግ ተባበሩኝ🙏


👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇👇

                                   @emsmereja


Forward from: Fasil Ethiopian🇪🇹
ረቡዕ ማለዳ! መጋቢት 20/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ አምነስቲ ኢንተርናሽናል ባለፈው የአውሮፓዊያን ዓመት በዓለም ላይ ከተከሰቱት ግጭቶች ሁሉ እጅግ አውዳሚው የትግራዩ ጦርነት እንደነበር ትናንት ባወጣው ሪፖርቱ ገልጧል። ድርጅቱ፣ በኢትዮጵያው ጦርነት ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች የተፈጸሙት ከዓለማቀፉ ኅብረተሰብ ትኩረት ውጭ በኾነ ሁኔታ እንደኾነ በሪፖርቱ ጠቅሷል። ዓለማቀፍ ድርጅቶች፣ በኢትዮጵያ፣ የመን፣ በርማ እና አፍጋኒስታን ለነበሩ ግጭቶችና ሰብዓዊ ቀውሶች በቂ ምላሽ አልሰጡም በማለትም አምነስቲ ወቅሷል።

2፤ የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ፣ የሰላምና ጸጥታ ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ በትግራይ ወቅታዊ ፖለቲካዊ እና የጸጥታ ሁኔታዎች ዙሪያ ከኅብረቱ የዓለማቀፍ አጋሮች ቡድን ጋር መወያየታቸውን ትናንት ምሽት በትዊተር ገጻቸው ላይ ባሠፈሩት መልዕክት አስታውቀዋል። አምባሳደር ባንኮሌ፣ የኅብረቱ አጋሮች ቡድን ኅብረቱ-መር ለኾነው የኢትዮጵያ መንግሥት እና ሕወሃት ለደረሱበት የሰላም ስምምነት ተግባራዊነት ድጋፍ ማድረጋቸውን እንዲቀጥሉ መጠየቃቸውን ጨምረው ገልጸዋል።

3፤ ከትናንት ወዲያ በ99 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት የፒያኖና ቫዮሊን ሙዚቃ አቀናባሪ የእማሆይ ጽጌማርያም ገብሩ ሥርዓተ ቀብር በመጭው ዕሁድ እየሩሳሌም ውስጥ እንደሚፈጸም መስማቱን ጠቅሶ ቪኦኤ ዘግቧል። እማሆይ ጽጌማርያም ለረጅም ዓመታት የተጫወቱበት የግል ፒያኗቸው፣ ለቅዱስ ያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት እንዲሰጥላቸው እንደተናዘዙ ዘገባው ጠቅሷል። እማሆይ ጽጌማርያም በሕይወት ዘመናቸው ከ300 በላይ ረቂቅ ሙዚቃዎችን ማቀናበራቸው የሚነገርላቸው ሲሆን፣ ከወጣትነት ዘመናቸው ጀምሮ እስከ ሕልፈታቸው ድረስ የኖሩት በምንኩስና ሕይወት ነው።

4፤ ኢጋድ በአፍሪካ ቀንድ የተከሰተው ድርቅ አሰቃቂ ሰብዓዊ ቀውስ እንዳያስከትል ለመከላከል ዓለማቀፍ ለጋሾች እጃቸውን እንዲዘረጉ የድርጅቱ ዋና ጸሃፊ ወርቅነህ ገበየሁ ጥሪ ማድረጋቸውን ዘ ኢስት አፍሪካን አስነብቧል። በቀጠናው 47 ሚሊዮን ሕዝብ ለከፍተኛ የምግብ እጥረት መጋለጡን የጠቀሱት ወርቅነህ፣ 70 በመቶዎቹ ተጋላጮች በኢትዮጵያ፣ ኬንያና ሱማሊያ እንደሚገኙ መናገራቸው ተገልጧል። ወርቅነህ፣ በቅርቡ ቀናት በቀጠናው አንዳንድ አካባቢዎች የዘነበው ከፍተኛ ዝናብ፣ የዝናብ ወቅቱን ትክክለኛ ገጽታ ላያሳይ እንደሚችል መናገራቸውንም ዘገባው ጠቅሷል። በኢትዮጵያ ድርቁ መጠነ ሰፊ ጉዳት እንዳያደርስ በቀጣዮቹ አራት ወራት 710 ሚሊዮን ዶላር፣ በሱማሊያ 1.6 ቢሊዮን ዶላር እንዲሁም በኬንያ 378 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ ወርቅነህ አውስተዋል ተብሏል።

5፤ በአፍሪካ ቀንድ የአውሮፓ ኅብረት ልዩ ልዑክ አኒታ ዌበር በተመድ ጸጥታው ምክር ቤት ዝግ ስብሰባ ላይ ስለ ሱማሊያ ገለጻ ማድረጋቸውን የሱማሊያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ዌበር በገለጻቸው፣ ጸጥታው ምክር ቤት በሱማሌላንድ ራስ ገዝ ላስ አኖድ ከተማ ለቀጠለው ደም አፋሳሽ ግጭት መፍትሄ እንዲፈልግ መጠየቃቸውን ዘገባዎቹ አመልክተዋል። የግጭቱ ተሳታፊ አካላት፣ ቀደም ሲል ታውጆ ለነበረው ተኩስ አቁም ተገዥ እንዲኾኑ፣ ለግጭቱ ዘላቂ መፍትሄ ለማስገኘት እንዲደራደሩና ለግጭቱ ተጎጂዎች ሰብዓዊ ዕርዳታ እንዲቀርብ እንዲፈቅዱ ዌበር ጠይቀዋል ተብሏል። #ሼር በማድረግ ተባበሩኝ🙏


👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇👇

                                   @emsmereja


የዘመዴ ቴሌግራም ፔጅ ተከታዮች የት አካባቢ ይኖራሉ? ለበጎ አላማ ተፈልጋችሁ ነው።
Poll
  •   ሀገር ውስጥ(ኢትዮጵያ)
  •   ከሀገር ውጪ
33 votes


Forward from: Fasil Ethiopian🇪🇹
ጠሚ/ሩ የአማራ ተወላጆች ወደአዲስ አበባ እንዳይገቡ የተደረገውን ክልከላ በቀጥታ እሳቸው ማዘዛቸውን ዛሬ ገልጸዋል። እስከአሁን ጉዳዩ ከኦሮሚያ ክልል አመራሮች ጋር በተያያዘ ነበር ሲነሳ የሰነበተው። በዛሬው የፓርላማ ውሎአቸው የጉዳዩ ባለቤት እሳቸው መሆናቸውን በግልጽ አሳውቀዋል። ታዲያ የፌደራሉ መንግስት ውሳኔ ከሆነ ለምን በኦሮሚያ ልዩ ሃይልና ፖሊስ ፍተሻና ብርበራው እንዲሁም ክልከላው እንዲከናወን እንዳስፈለገ ሊገልጹልን ግን አልቻሉም። ጠሚ/ሩ በቀጣይም ክልከላው ተጠናክሮ እንደሚካሄድ ገልጸዋል። ''ሰላማዊ ዜጎችን ለይተን ሌላውን አናስገባም'' ሲሉም ፈርጠም ብለው ተናግረዋል። መቼም ከሰውዬው የሚሰማው ሁሉ ጉድ የሚያሰኝ ነው። እሳቸው አእምሮ ውስጥ እየመጣ የሚያስበረግጋቸውና ስልጣናቸውን ሊነጥቅ የሚያስፈራራቸው ሃይል አዲስ አበባ እስኪመጣ ለምን ይጠብቁታል? ጎንደርም ካለ አሳይታ፡ ጂግጂጋም ይሁን ወላይታ በየትኛውም የኢትዮጵያ መሬት ላይ የእሳቸውን ስልጣን ለመቀማት የተዘጋጀ ሃይል ካለ እርምጃ መውሰድ ሲችሉ አራት ኪሎ ቤተመንግስት እስኪደርስ ለምን ይጠብቁታል? እንደዛ በማድረግስ ከግልበጣ መትረፍ ይቻላልን? እንዲህ እየበረገጉና እየደነበሩ እስከመቼ ይዘልቁታል?

በእርግጥ ይህ አባባላቸው እሳቸው ቤተመንግስታቸውንና ዙሪያቸውን ነው የሚጠብቁት፡ የአዲስ አበባው ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ቀርተዋል እያሉ ነቃፊዎቻቸው የሚናገሩት ሁሉ እውነት ለመሆኑ የሚያረጋግጥ ንግግር አድርጌ ውስጄዋለሁ። ለዚህ ነው ለካ በወለጋ ሰው ሲታረድ መታደግ ያልቻሉት? በዙሪያቸው የሚነደው እሳት መጥፋት ያቃተው እሳቱ አራት ኪሎ የሚደርስ አይደለም፡ እኔን አይነካኝም በሚል ተማምነው መሆኑን ዛሬ ከምንም ጊዜውም በላይ ማረጋገጫ ሰጥተዋል። አንድን ህዝብ በጅምላ መንግስቴን ሊገለብጥ ነው በሚል ፍራቻ የመንቀሳቀስ መብቱን ለመገደብ መወሰናቸው ዘመናዊ ባርነትን መንግስታቸው በይፋ አውጇል ማለት ይቻላል። ''ሰላማዊ ዜጎችን'' ለይቶ የሚያሳልፍ፡ መንግስታቸውን ለመፈንቀል የሚያሴረውን ደግሞ ነጥሎ የሚከለክል ዘመናዊ ማሽን ታጥቀው ከሆነ ቢያሳውቁን መልካም ነው። የዓይንህ ቀለም አላማረኝም በሚል ፍርሃት በወለደው ማን አለብኝነት የሚደረግ መሆኑ ነው እጅግ አደገኛውና አስፈሪው ነገር።#share Godhii
✍️mesay

👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇👇

                                   @emsmereja


Forward from: Fasil Ethiopian🇪🇹
ማክሰኞ ምሽት! መጋቢት 19/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ የዓለም ገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) አንድ የባለሥልጣናት ቡድን ድርጅቱ ለኢትዮጵያ ሊሰጥ ለሚችለው የገንዘብ ድጋፍ የቴክኒክ ዝግጅቶችን ለማድረግ አገሪቱ ውስጥ እንደሚገኝ ሮይተርስ ዘግቧል። መንግሥት ለአገር በቀል የኢኮኖሚ መርሃ ግብሩ ማስፈጸሚያ ድርጅቱ የገንዘብ ድጋፍ እንዲያደርግለት በይፋ ጥያቄ ማቅረቡን የድርጅቱ ቃል አቀባይ መናገራቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ድርጅቱ የድጋፍ ጥያቄውን ካጸደቀ፣ ድጋፉ የመንግሥትን የኢኮኖሚ ማሻሻያ ዕቅድ ለመተግበርና የአገሪቱን ኢኮኖሚ በማረጋጋት ሥራ ለመፍጠር፣ ለሰብዓዊ ዕርዳታና ድህነትን ለመቀነስ ይውላል ሲሉ ቃል አቀባዩ መግለጻቸውን ዜና ምንጩ አመልክቷል። መንግሥት በአገሪቱ ሰሜናዊ ክፍሎች ሰላም ለማስፈን እያደረገ ያለውን ጥረትና ከትግራይ ኃይሎች ጋር የደረሰበት የሰላም ስምምነት አተገባበርን አይ ኤም ኤፍ በአዎንታ ይመለከተዋል መባሉን በዘገባው ላይ ተመልክቷል።

2፤ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ዛሬ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ስለ ሰላም፣ ስለ ክልልነት ጥያቄ፣ ስለ ምጣኔ ሃብት፣ ስለ መፈናቀል እና በሌሎች በርካታ ጉዳዮች ዙሪያ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ዐቢይ፣ ከሥልጣን የመልቀቅ ዕቅድ ይኖራቸው እንደኾነ ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ ሥልጣን መልቀቅ አለመልቀቅ በምርጫ ብቻ የሚወሰን እንደኾነ ምላሽ ሰጥተዋል። ከአማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ መንገደኞች እንዳይገቡ ኦሮሚያ ክልል ላይ ስለሚገጥማቸው ክልከላ ደሞ፣ በከተማዋ ሁከት የመቀስቀስና መንግሥትን በኃይል የመገልበጥ ተልዕኮ ተሰጥቷቸው የሚገቡ አካላት እንዳሉ ዐቢይ ተናግረዋል። ከክልሎች ወደ አዲስ አበባ የሚደረገው ፍልሰት፣ በተያዘው ዓመት ከፍተኛ መሆኑንም ዐቢይ ጠቁመዋል። መንግሥታቸው አገር ለማፍረስ እየሠራ ነው ተብሎ ለበቀረበላቸው ጥያቄም፣ ጉዳዩን እንደ ቀልድ እንደሚወስዱትና የአገር መፍረስና መገነጣጠል አደጋ መቆሙን ገልጸዋል።

3፤ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ መንግሥታቸው ከኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ሰላም ለማውረድ እንቅስቃሴ መጀመሩን ዛሬ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ ላይ ተናግረዋል። መንግሥት ለበርካታ ዜጎች ሞትና መፈናቀል ምክንያት የሆነው በክልሉ የሚካሄደው ግጭት እንዲቆም ፍላጎት ያለው መኾኑን ዐቢይ ገልጸዋል። መንግሥት ለግጭቱ ሰላማዊ መፍትሄ ለማፈላለግ ሲል የገዥው ብልጽግና ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር የሚመሩት ኮሚቴ ማቋቋሙን የጠቀሱት ዐቢይ፣ እስካሁን 10 ያህል የሰላም ጥረቶችን እንደተሞከሩ ጠቁመዋል። ኾኖም ቡድኑ ማዕከላዊ አመራር ስለሌለው የሰላም ፍለጋ ሂደቱ መጓተቱን ጠቅላይ ሚንስትሩ ጨምረው ገልጸዋል።

4፤ የቤንሻንጉል ጉሙዝ መንግሥት ወደ ሰላማዊ ኑሮ ለተመለሱ የቀድሞ ታጣቂዎች በኢኮኖሚ ተጠቃሚ የሚያደርጉ አንዳንድ ጥቅማጥቅሞችን ለመስጠት መወሰኑን የክልሉ ብዙኀን መገናኛ ዘግቧል። የክልሉ መንግሥት ያሳለፈው ውሳኔ፣ ትጥቃቸውን የፈቱ የቀድሞ አማጺያን በማዕድን፣ ግብርና እና ንግድ እንዲሠማሩ የሚያስችሉ እንደኾኑ ዜና ምንጩ ጠቅሷል። ይህንኑ ውሳኔ ተግባራዊ ለማድረግም፣ የክልሉ መንግሥት የእርሻ ትራክተሮችን፣ የማዕድን ማውጫ መሳሪያዎችን እና የልማት ሥራ ማስጀመሪያ መነሻ ካፒታል እሰጣለሁ ማለቱን ዘገባው ጨምሮ ገልጧል። ክልሉ ለዚሁ ሥራ ምን ያህል በጀት እንደመደበ ግን ዘገባው አልገለጠም።

5፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በኦሮሚያ ክልል ወሊሶ ከተማ አካባቢ በተካሄደው "በሕገወጥ የቀኖና ቤተክርስቲያን ጥሰት" ተግባር ውስጥ የተሳተፉና "በሕገወጥ ሲመት ኤጲስ ጳጳስነት" የተፈጸመላቸው 17 ግለሰቦች ለቤተክርስቲያኗ ቅዱስ ሲኖዶስ የይቅርታ ደብዳቤ ማስገባታቸውን የቤተክርስቲያኗ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። 17ቱ ግለሰቦች የይቅርታ ደብዳቤያቸውን ያቀረቡት፣ ዛሬ በጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤት ከሲኖዶሱ ከፍተኛ ኃላፊዎች ከአቡነ አብርሃም እና ከአቡነ ጴጥሮስ ጋር ከተነጋገሩ በኋላ መኾኑን ዜና ምንጮቹ ጠቅሰዋል። አቡነ አብርሃም እና አቡነ ጴጥሮስም፣ የይቅርታ ደብዳቤውን ለቅዱስ ሲኖዶሱ ለማቅረብ ቃል መግባታቸው ተገልጧል። ቀሪዎቹ ግለሰቦች በቅርብ ቀናት ተመሳሳይ የይቅርታ ደብዳቤ ያስገባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ዜና ምንጮቹ ጨምረው ጠቅሰዋል።

6፤ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ሰሞኑን በኬንያ የተቀሰቀሰእ ጸረ-መንግሥት ሁከት እንዳሳሰባቸው ዛሬ ባወጡት መግለጫ አስታውቀዋል። ፋኪ፣ ሁሉም ወገኖች ሁከትን አስወግደው የአገር አንድነትን መሠረት ባደረገ መልኩ ልዩነቶቻቸውን በንግግር እንዲፈቱ ጥሪ አድርገዋል። ፋኪ በዚሁ መግለጫቸው፣ ባለፈው ነሐሴ በአገሪቱ በተደረገው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ዊሊያም ሩቶ ማሸነፋቸውን የአገሪቱ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ያረጋገጠው ሃቅ መሆኑን ጠቅሰዋል። ታዋቂው የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ራይላ ኦዲንጋ ትናንት በጠሩት የተቃውሞ ሰልፍ፣ በተቃዋሚዎች እና ፖሊስ መካከል ግጭትና ከፍተኛ የንብረት ውድመት መድረሱን የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ከተቃውሞ ሰልፉ ዓላማዎች መካከል፣ መንግሥት የኑሮ ውድነቱን እንዲፈታና ተቃዋሚዎች "ተጭበርብሯል" ለሚሉት ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ፍትህ መጠየቅ ይገኙበታል።

7፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 53 ብር ከ8833 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 54 ብር ከ9610 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 63 ብር ከ0933 ሳንቲም እና መሸጫው 64 ብር ከ3552 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ58 ብር ከ0269 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ59 ብር ከ1874 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። #ሼር በማድረግ ተባበሩኝ🙏


👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇👇

                                   @emsmereja


Forward from: Fasil Ethiopian🇪🇹
ያው አዲስ ነገር የለም። እንደተለመደው እሳቸው ሌላ ዓለም ላይ መሆናቸውን ዛሬም ከዚያው ቦታቸው ንቅንቅ ያላሉ እንደሆኑ ከማሳየት ያለፈ ፍሬ የሚቋጥር፡ እውነት የሆነ፡ ሀገርን ከመጣባት አደጋ የሚያድናትን መፍትሄ የሚናገሩ መሪ ሆነው አላገኘኋቸውም። በኢኮኖሚ የደቀቀች፡ በግጭቶች አቅሏን የሳተች፡ በዘርፈ ብዙ ችግሮች ጎሮሮዋ የታነቀ፡ ዘረኝነት የሚያምሳት፡ የዜጎቿ ሲዖል የሆነች ሀገር መሪ አይመስሉም። አሁንም ሌላ ቦታ ናቸው። ሀቅን ሊኖሯት አልቻሉም። መሬት ላይ ያለውን እውነታ መምሰል ተስኗቸዋል። የእሳቸውን ጉድፍ ለማየት ወኔ ያጠራቸው፡ በአብዛኛው ንግግራቸው የራሳቸውን ድክመትና ክፍተት ''የተቀደሰ'' የሌላውን ችግር ''ውእግዝ ከማዕሪዮስ'' የሆነ አድርገው ለማሳየት እዚህም እዚያም ሲረግጡ እንጂ ያየኋቸው ወገብ የሚቆርጥ ምጥ ይዟት የምትሰቃይን ሀገር የሚያስተዳድሩ መሪ ፈጽሞ አይመስሉም። እየራበው ያለን ህዝብ ነገ ስለምትበለጽግ ረሃቡን እንደበረከት ቁጠረው የሚሉ ደፋር ሰው ናቸው። ኢትዮጵያ እናንተ ጭንቅላት ውስጥ ነው የፈረሰችው ብለው ሲናገሩ ኢትዮጵያ በእሳቸው የአእምሮ ጓዳ ብቻ በልጽጋ እየታየች ስለመሆኗ ይዘነጉታል። ፍየል ወዲያ ቅዝምዝም ወዲህ። እሳቸው ወዲያ፡ ሀገሪቱ ወዲህ። አልተገናኝቶም።

አቶ ክርስቲያን ታደለ ''ስልጣንዎን ለመልቀቅ አያስቡምን?'' ብለው በትህትና ለጠየቋቸው ጥያቄ ለምን እንደዚያ እንደተገረሙ አልገባኝም። ስልጣን መልቀቅ እኮ ታላቅነት ነው። ለዚያውም ሀገሪቱን እንደዚህ ዓይነት መጠነ ሰፊ አደጋ ላይ የጣላትን መሪ ይቅርና ''ሴትን ልጅ ጎነተልክ'' ተብሎ የስልጣን መልቀቅ ጥያቄ የሚቀርብባት ዓለም ላይ መኖራቸውን ዘንግተውታል። እውነት ለመናገር ለእሳቸው ስልጣን ልቀቁ የሚለው ጥያቄ ሀቀኝነት ያለው፡ ምንም እንከን የማይወጣለት ተገቢ ጥያቄ ነው። በዚህ መልኩ በክብር መጠየቃቸውን ማመስገን ሲገባቸው ለመሳለቅና በተረት ዙሪያ ጥምጥም በመሄድ ጠያቂውን ለማበሻቀጥ መሞከር ትዝብት ላይ የሚጥላቸው ነው። ቀርበው የኢትዮጵያን ህዝብ ቢያዳምጡትና ስለእሳቸው ምን እያለ እንዳለ ቢያውቁ አቶ ክርስቲያን ያቀረቡላቸው ጥያቄ አያስደነግጣቸውም ነበር። የመለሱበት መንገድ ቅንነት የጎደለው ብቻ አይደለም። ለስልጣን ያላቸውን ጥልቅ ጥማት ያጋለጠባቸውም ጭምር ነው። ሀገሪቱን በዚህ በኩል እለውጣታለሁ ብለው ሞከሩ። አልተሳካም። ስለዚህ ለሌላው እድል ልስጥ የሚል ታላቅነትን የሚያንጸባርቅ፡ ከእኔነትነት ይልቅ ህዝቤንና ሀገሬን ላስቀድም ከሚል በሳልና አስተዋይ መሪ የሚጠበቅ ትንሹ እርምጃ መሆኑን ጭራሽ አያውቁትም። የኢትዮጵያ የብርሃን መንገድ የእኔ ብቻ ነው የሚል ክፉ ደዌ ደማቸው ውስጥ የተቀበረ መሆኑ እሳቸውንም ሀገሪቱንም መላቅጥ እንዲያጡ አድርጓቸዋል።

ስለዛሬው ውሎአቸው አንድ በአንድ፡ መስመር በመስመር መሞገት ትርጉም የለውም። እሳቸው አሁንም ሌላ ዓለም ላይ የጀመሩትን ኑሮ መቀጠል መፈለጋቸውን ነግረውናል። ወደእኛ ሊመጡ አልፈቀዱም። ወይም ወደእሳቸው ዓለም ሊወስዱን አልፈለጉም። እሳቸው እዚያ ህዝባቸው እዚህ እየኖሩ እንዴት መግባባት ይቻል ይሆን? #ሼር በማድረግ ተባበሩኝ🙏


👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇👇

                                   @emsmereja
መሳይ መኮንን


Forward from: Fasil Ethiopian🇪🇹
ምንም ለውጥ የለም


Forward from: Fasil Ethiopian🇪🇹
ክርስቲያን ታደለ ለጠቅላይ ሚንስትሩ ያቀረቡት ጥያቄ‼️
ዛሬ መጋቢት 19 ቀን 2015 ዓ.ም እየተካሄደ ባለው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ  የቀረበ ጥያቄ፤
**
አመሰግናለሁ የተከበሩ አፈጉባዔ፤

አመሰግናለሁ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር፤

ጥያቄዬን ከማቅረቤ በፊት ስለጥያቄዬ ትንሽ ማለት እፈልጋለሁ። ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር በዚህ ምክር ቤት እና በተለያዩ መድረኮች ስለእርስዎና ስለሚመሩት የአስፈፃሚ መንግስት ተጠየቅ ሲቀርብብዎ ለተጠየቁ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ጠያቂዎችን የሚያጥላላ አስተያየት ሲያራምዱ፤ አለፍ ሲልም ተጠየቅ የቀረበብዎት የወጡበት ብሔርን በመጥላት እንደሆነ አድርገው ምላሽ መስጠትዎ የቅርብ ትዝታ ነው። ክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር ቀጥዬ የማቀርብልዎ ጥያቄ ራስዎንና መንግስትዎን የሚመለከት እንጂ ሌላ ማንንም የማይመለከት መሆኑን ማረጋገጥ እፈልጋለሁ። እኔም ጥያቄውን የማቀርብልዎት በብሔር አይደለም። ምላሽ ሲሰጡም የመንግስት ግልበጣ ለማድረግ የተሼረበ ሴራ ነው የሚል እንደማይሆን ተስፋ አደርጋለሁ። ጥያቄዬ የሚከተለው ነው።

የዜጎችን ደኅንነት እና የአገርን ሉዓላዊነት መጠበቅ ዝቅተኛ የመንግስት ኃላፊነት ሆኖ ሳለ ዜጎች በማንነታቸው ምክንያት በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ይገደላሉ፤ ይፈናቀላሉ፤ ቤታቸው ይፈርሳል፤ ንብረታቸውም ይወድማል። የአገር ሉዓላዊነትን በሚዳፈር መልኩ የጎረቤት አገራት ሰራዊቶች በኢትዮጵያ ሰሜን ምዕራብና ደቡብ ምዕራብ ወሰኖች በርካታ ኪሎሜትሮችን ዘልቀው በመግባት ወረራ ፈጽመዋል። አሁን ላይ ባለው ተጨባጭ ሁኔታ የዜጎች ደኅንነትና የአገር ሉዓላዊነት ዋነኛ የስጋት ምንጭ ሆኖ የምናየው ራሱ መንግስትን ነው። እርስዎ  በአፍዎ «ኢትዮጵያ አትፈርስም» ቢሉንም በተግባር ግን ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነት በመንግስትዎ እየተናዱ ነው። የበርካታ አገራት መሪዎቸ መሰል ኃላፊነትን በወጉ ያለመወጣት ጉድለት ሲያሳዩ ሕዝብን ይቅርታ ጠይቀው ሥልጣናቸውን ሲለቁ ይታያል። በአገራችንም የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ኃይለማርያም ደሳለኝ ተመሳሳይ ሕዝባዊ ተጠየቅ ሲቀርብባቸው ሥልጣን መልቀቃቸው ይታወሳል።

እርስዎስ ሥልጣንዎን በመልቀቅ የመፍትሔው አካል ለመሆን አላሰቡም ወይ?  በሰብአዊነት ላይ በተፈፀሙ እንዲሁም የማንነት ተኮር የዘር ማጥፋት፣ የዘር ማጽዳትና የማንነት ማሳሳት ወንጀሎች ተጠያቂ ለመሆን ምን ያህል ዝግጁ ነዎት?

አመሰግናለሁ! #ሼርርር በማድረግ ተባበሩን🙏


👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇👇

                                   @emsmereja


Forward from: Fasil Ethiopian🇪🇹
ማክሰኞ ማለዳ! መጋቢት 19/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ በደቡብ ክልል ጌዲኦ ዞን ከሚገኙ 320 ትምህርት ቤቶች መካከል የትምህርት ሚንስቴርን መመዘኛ የሚያሟሉት 13ቱ ብቻ እንደኾኑ ዋዜማ ከዞኑ ትምህርት ቢሮ ሰምታለች። የትምህርት ቤት ግንባታ ጥራት ጉድለት፣ የሰው ኃይልና የቤተመጽሃፍት እጥረትና የትምህርት አመራርና አስተዳደር ጉድለት ዋነኞቹ የዞኑ ትምህርት ቤቶች ችግሮች ናቸው። በዘንድሮው ዓመት በዞኑ ለመማር ከተመዘገቡት 266 ሺህ 700 ተማሪዎች መካከል፣ ከ18 ሺህ በላይ ተማሪዎች ትምህርታቸውን አቋርጠዋል ተብሏል። ተማሪዎች ትምህርታቸውን ከሚያቋርጡባቸው ምክንያቶች መካከል፣ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች በአካባቢው የሚያደርጉት እንቅስቃሴ አንዱ እንደኾነ መረዳት ተችሏል።

2፤ የአማራ ክልል ልዩ ኃይል የቀድሞ ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጀኔራል ተፈራ ማሞ በውጭ አገር ሕክምና እንዳያገኙ ተከልክለዋል በማለት ቤተሰቦቻቸው ክስ ሊመሠርቱ መሆኑን ቪኦኤ ዘግቧል። ብ/ጀኔራል ተፈራ ወደ ውጭ አገር ሂደው ሕክምና እንዲያገኙ የሐኪሞች ቦርድ ትዕዛዝ የጻፈላቸው፣ ከአራት ወራት በፊት እንደነበር መናገራቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ብ/ጀኔራል ተፈራ ለሕክምና ሊጓዙ የነበሩት ወደ እስራኤል እንደነበር የተናገሩት ባለቤታቸው መነን ኃይሌ፣ የውጭ ጉዞ ክልከላ ትዕዛዙ የመጣው "ከበላይ አካል" ስለመሆኑ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ እንደተነገራቸው ገልጸዋል ተብሏል።

3፤ የፌደራል የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን በሰሜኑ ጦርነት በትግራይ፣ አማራና አፋር ክልሎች ለተጎዱ ዕርዳታ ፈላጊዎች 282 ሺህ 934 ሜትሪክ ቶን ዕርዳታ ማሰራጨቱን መናገሩን ፋና ብሮድካስት ዘግቧል። መንግሥት ብቻውን ያቀረበው፣ 15 ሺህ 666 ሜትሪክ ቶን ሰብዓዊ ዕርዳታ እንደኾነ የጠቀሰው ኮሚሽኑ፣ ቀሪውን ዕርዳታ ያቀረቡት ዓለማቀፍ ረድዔት ድርጅቶችና አጋሮች እንደኾኑ ገልጧል ተብሏል። ኮሚሽኑ ባሁኑ ወቅት በትግራይ ክልል ከ5 ነጥብ 2 በላይ ዕርዳታ ፈላጊዎች፣ በአማራ ክልል ከ2 ነጥብ 4 ሚሊዮን በላይ እንዲሁም በአፋር ክልል ከ715 ሺህ በላይ ዕርዳታ ፈላጊዎች እንደሚገኙ መግለጡን ዘገባው አመልክቷል።

4፤ የሱማሊያ ፌደራል መንግሥት የወከላቸው አሸማጋዮች ግጭት በተቀሰቀሰባት ሱማሌላንድ ራስ የሽምግልና እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ይገኛሉ። ከሱማሊያ የጎሳ ሽማግሌዎች የተውጣጡት አሸማጋዮቹ፣ የግጭት ቀጠና በሆነችው ላስ አኖድ ከተማ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎችን በማነጋገር ላይ እንደኾኑ የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። በሱማሌላንድ መንግሥት ወታደሮችና በሱማሌላንድ ስር መተዳደር አንፈልግም በሚሉ የላስ አኖድ ከተማ የአካባቢ የጎሳ ሚሊሻዎች መካከል የተፈጠረው ግጭት ሁለተኛ ወሩን የያዘ ሲሆን፣ ለግጭቱ እስካሁን ፖለቲካዊ መፍትሄ አልተገኘለትም።

5፤ የሱዳን ወታደራዊና የፖለቲካ ኃይሎች ሁለተኛውን ሲቪል የሽግግር መንግሥት ለመመስረት ወደ መጨረሻው ምዕራፍ ተቃርበዋል። ቅዳሜ እና ዕሁድ በረቂቅ የስምምነት ሰነድ ላይ የተወያዩት ወታደራዊ መሪዎችና የሲቪል የፖለቲካ ኃይሎች ተወካዮች፣ ረቂቅ የስምምነት ሰነዱን ከድርድር ሂደቱ ውጭ ለሆኑ የፖለቲካ ኃይሎች ለመስጠት መስማማታቸውን ሱዳን ትሪቡን ዘግቧል። የወታደራዊው መንግሥትና ሲቪል የፖለቲካ ኃይሎቹ፣ ሰነዱን መጋቢት 23 ቀን ለመፈረም ቀጠሮ ይዘዋል። ኾኖም ከግብጽ ጋር ግንኙነት ያላቸው የተወሰኑ ታጣቂና የፖለቲካ ቡድኖች የሲቪል ሽግግር መንግሥት ምስረታውን የድርድር ሂደት እስካሁን አለመቀላቀላቸው ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል። #ሼርርር በማድረግ ተባበሩን🙏


👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇👇

                                   @emsmereja


Forward from: Fasil Ethiopian🇪🇹
ሰኞ ምሽት መጋቢት 18/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1፤ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ነገ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሪፖርት እንደሚያቀርቡና ሪፖርቱን ተከትሎ የምክር ቤቱ አባላት ለሚያቀርቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እንደሚሰጡ ምክር ቤቱ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል። ለጠቅላይ ሚንስትሩ ጥያቄና ማብራሪያ የሚቀርብላቸው፣ በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሆነ ምክር ቤቱ ገልጧል። ዐቢይ፣ በተያዘው ዓመት ባለፈው ኅዳር ወር በምክር ቤቱ ተገኝተው ለጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ መስጠታቸው ይታወሳል። ዐቢይ፣ ነገ ለምክር ቤቱ አባላት ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጡት፣ ምክር ቤት በ61 ተቃውሞ ሕወሃትን ከአሸባሪነት ፍረጃ በሰረዘ ማግስት ነው።

2፤ የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን በብሄራዊ ምክክሩ ለመሳተፍ ፍቃደኛ ያልሆኑ 13 የፖለቲካ ኃይሎችን ለማግባባት ላለፉት 6 ወራት ያደረጋቸው ሙከራዎች እንዳልተሳኩ ዋዜማ ከምንጮቿ ሰምታለች። "ቡድን 13" ተብለው የሚጠሩት እነዚሁ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ በአገራዊ ምክክሩ አንሳተፍም ያሉት፣ በምክክር ኮሚሽኑ የፖለቲካ ገለልተኛነት እና በኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች አሿሿም ሂደት ላይ ጥያቄ በማንሳት ነው። ከአገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ጋር ለመስራት ፍቃደኛ ካልሆኑ ፓርቲዎች መካከል፣ ኦፌኮ፣ ኦነግ፣ የአፋር ሕዝብ ፓርቲ፣ የሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ እና ኦብነግ ይገኙበታል። የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤትም፣ ፓርቲዎቹ ወደ አገራዊው የምክክሩ ማዕቀፍ እንዲገቡ ጥረት እያደረገ መኾኑን የምክር ቤቱ ሊቀመንበር መብራቱ ዓለሙ ለዋዜማ ተናግረዋል።

3፤ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚንቀሳቀሱ ስምንት ፓርቲዎች ከግንቦት 30 በፊት በክልሉ ምርጫ እንዲካሄድ ለምርጫ ቦርድ ደብዳቤ ማስገባታቸውን የዋዜማ ሪፖርተር ዘግቧል። ጥያቄውን ለቦርዱ ካስገቡት ፓርቲዎች መካከል፣ ገዥው ብልጽግና ፓርቲ ይገኝበታል። ፓርቲዎቹ በክልሉ በ2013ቱ አገር ዓቀፍ ምርጫ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ለክልል ምክር ቤቶች ከተያዙ አብዛኞቹ ምርጫ ክልሎች ሳይካሄድ የቀረው ምርጫ ከዘንድሮው ክረምት መግባት በፊት እንዲካሄድ የጠየቁት፣ የክልሉ የጸጥታ ሁኔታ ተሻሽሏል በማለት ነው። ምርጫ ቦርድ ምርጫ ማድረግ የሚጠበቅበት፣ በ71 የክልል ምክር ቤትና በ6 የየሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ ክልሎች ነው።

4፤ የከፍተኛ ትምህርት ምዘናና የፈተናዎች አገልግሎት የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል አገር ዓቀፍ መልቀቂያ ፈተና ልክ እንደ ባለፈው ዓመት ሁሉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ቅጥር ግቢ ውስጥ እንደሚሰጥ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ማስታወቁን የአገር ውስጥ ዜና አውታሮች ዘግበዋል። ተቋሙ ለዘንድሮው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ምዝገባ ከቀጣዩ ረቡዕ ጀምሮ እስከ ሚያዝያ 15 ድረስ እንደሚካሄድና፣ በጠቅላላው 1 ሚሊዮን ተፈታኞች ይመዘገባሉ የሚል ቅድመ ግምት እንደተያዘ መግለጡን ዘገባዎቹ አመልክተዋል። የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል አገር ዓቀፍ ፈተና የሚሰጥበት ጊዜ ግን፣ የተፈታኞች ትክክለኛ ብዛት ከታወቀ በኋላ እንደሚወሰን ተቋሙ ገልጧል ተብሏል።

5፤ ጎረቤት ኬንያ ዛሬ በከፍተኛ ሁከት የታጀቡ ጸረ-መንግሥት የተቃውሞ ሰልፎችን አስተናግዳለች። የተቃውሞ ሰልፉ በተለይ በዋና ከተማዋ ናይሮቢ እና የኦዲንጋ የድጋፍ መሠረት በሆነችው ኪሱሙ ከተሞች በርትቷል። የተወሰኑ ሰልፈኞች ናይሮቢ ውስጥ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪው ራይላ ኦዲንጋ ቤተሰብ ንብረት በሆነ አንድ ኩባንያ ላይ ጥቃት የፈጸሙ ሲሆን፣ ሌሎች የተደራጁ ቡድኖች ደሞ በቀድሞው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ቤተሰብ ንብረት በሆነ ኩባንያ ላይ ዝርፊያ እንደፈጸሙ የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ፖሊስ የሰልፉ መሪ ኦዲንጋ የተሳፈሩባቸውን መኪኖች ጨምሮ፣ በሰልፈኞቹ ላይ አስለቃሽ ጭስ እንደተኮሰ ተገልጧል። ኦዲንጋ በሳምንት ሁለት ጊዜ አገር ዓቀፍ የተቃውሞ ሰልፍ የጠሩት፣ ለአገሪቱ የኑሮ ውድነት መንግሥትን ተጠያቂ በማድረግና የባለፈው ነሐሴ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ተጭበርብሯል በማለት ነው።

6፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 53 ብር ከ8752 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 54 ብር ከ9527 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 62 ብር ከ7288 ሳንቲም እና መሸጫው 63 ብር ከ9834 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ57 ብር ከ7542 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ58 ብር ከ9093 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። #ሼርርር በማድረግ ተባበሩን🙏


👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇👇

                                   @emsmereja


Forward from: Fasil Ethiopian🇪🇹
ሰኞ ማለዳ! መጋቢት 18/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች

1. የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከናይጀሪያ አየር መንገድ ጋር በፈጠረው ስምምነት መሠረት ከበረራ ውጭ የሆነውን የናይጀሪያ አየር መንገድ መልሶ በማቋቋም በመጭው ግንቦት በረራ ሊያስጀምር መሆኑን የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። አዲስ በሚቋቋመው የናይጀሪያ አየር መንገድ ውስጥ፣ የኢትዮጵያ አዩር መንገድ 49 በመቶ፣ ናይጀሪያዊያን ባለሃብቶች 46 በመቶ እንዲሁም የናይጀሪያ መንግሥት ቀሪውን 5 በመቶ የባለቤትነት ድርሻ እንዲይዙ ስምምነት ላይ እንደተደረሰ ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። አየር መንገዱን እንደገና በረራ ለማስጀመር የታቀደው፣ በ23 አውሮፕላኖች እንደሆነ ተገልጧል። የናይጀሪያ አየር መንገድ ከባድ ሙስና ባደረሰበት ኪሳራ ሳቦያ፣ ከበረራ ውጭ የሆነው ከ20 ዓመት በፊት ነበር።

2፤ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የአዲስ አበባ አገረ ስብከት የካቲት 23 ቀን በፒያሳው ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ላይ አስለቃሽ ጭስ የተኮሱ አካላት አጣርቶ ለሕዝብ ይፋ የሚያደርግ የሕግ ባለሙያዎች ቡድን ማቋቋሙን አስታውቋል። አገረ ስብከቱ፣ በአዲሱ ሸገር ከተማ ስር ከተካለሉ ቤተክርስቲያናት መካከል መንግሥት በግብረ ኃይሉ ያስፈረሰውን አንድ የጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን በራሱ ወጭ መልሶ እንዲያስገነባም አሳስቧል። አገረ ስብከቱ ጨምሮም፣ በቤተክርስቲያናት ላይ የሚፈጸመው "አድሏዊ" እና "ኢ-ሕገመንግሥታዊ" ድርጊት እንዲቆም ጠይቋል።

3፤ ብሄራዊ ባንክ ሦስት አዳዲስ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን መንደፉን ሪፖርተር አስነብቧል። ማሻሻያዎቹ የባንኩን ተቋማዊ ነጻነትና የቁጥጥር ሥልጣን በማጠናከር፣ የሰው ኃይልና ዲጂታል አቅሙን በማሳደግና የገንዘብ ፖሊሲውን በማሻሻል ላይ ያተኮሩ እንደሆኑ ዘገባው ጠቅሷል። የባንኩ ገዥ ማሞ ምኅረቱ፣ በሦስት ዓመታት ውስጥ 70 በመቶ ኢትዮጵያዊያን ለባንኩ የፋይናንስ አገልግሎት ተደራሽ እንዲኾኑ ግብ እንደተያዘ መጋቢት 14 ቀን በተካሄደ አንድ መድረክ ላይ መናገራቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ብሄራዊ ባንክ ለሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኩባንያ የሞባይል ገንዘብ ዝውውር ፍቃድ በቅርቡ እንደሚሰጥም ማሞ ተናግረዋል ተብሏል።

4፤ በሜጀር ጀኔራል ተስፋዬ አያሌው የተመራ የኢትዮጵያ ጦር ሠራዊት የከፍተኛ መኮንኖች ልዑክ ቅዳሜ'ለት በማዕከላዊ ሱማሊያ የሒራን ግዛት ከተማ በለደወይን መግባቱን የሱማሊያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። የኢትዮጵያ ጦር ሠራዊት ልዑክ ወደ ሱማሊያ ያቀናው፣ የሱማሊያ መንግሥት በአልሸባብ ላይ ሁለተኛውን ዙር የማጥቃት ዘመቻ በሚያውጅበት ዋዜማ ላይ ነው። ልዑኩ ከሱማሊያ ጦር ሠራዊት አቻዎቹ ጋር እንደሚወያይና፣ ኢትዮጵያ በቅርቡ ወደ ሱማሊያ ያዘመተቻቸው ቁጥራቸው ያልተገለጹ ወታደሮች ከአልሸባብ ጋር ለመዋጋት ያላቸውን ዝግጁነት እንደሚገመግም ዘገባዎቹ አመልክተዋል። ከልዑካን ቡድኑ ጋር የተወሰኑ የሱማሌ ክልል ባለሥልጣናት አብረው ተጉዘዋል ተብሏል።

5፤ የሱዳን ወታደራዊ መሪዎችና ሲቪል ተቃዋሚ የፖለቲካ ኃይሎች ትናንት ምሽት በዓለማቀፍ አደራዳሪዎች አማካኝነት ባደረጉት ስብሰባ ላይ የመጨረሻው የሲቪል ሽግግር መንግሥት ማቋቋሚያ ረቂቅ ሰነድ ተጠናቆ መቅረቡን የሱዳን ዜና ወኪል ዘግቧል። በስምምነት ረቂቅ ሰነዱ ላይ ገና በድርድር ላይ ያለው የጸጥታ መዋቅር ማሻሻያ ከታከለበት በኋላ፣ መጋቢት 23 እንደሚፈረም ዘገባው ጠቅሷል። ተሰብሳቢዎቹ፣ የመጀመሪያውን የፖለቲካ ማዕቀፍ ስምምነት ያልፈረሙ ኃይሎች የፖለቲካ ንግግር ሂደቱን ተቀላቅለው የመጨረሻውን ስምምነት እንዲፈርሙ ጥሪ ማድረጋቸው ተገልጧል። የስምምነት ማዕቀፉ አካል ያልሆኑት ቡድኖች ግን፣ ለፊርማ የተቃረበውን የሲቪል መንግሥት ማቋቋሚያ ሰነድ እንደማይቀበሉት በመግለጽ ላይ ናቸው። #ሼርርር በማድረግ ተባበሩን🙏


👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇👇

                                   @emsmereja

20 last posts shown.