Posts filter


አብን በቀጣዩ ምርጫ የመሳተፍ አቅም አይኖረውም-አባላቱ

ቅዳሜ ጥር 24 ቀን 2017 (አዲስ ማለዳ) የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) 300 የሚደርሱ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶቹ በሥራ ላይ ባለመኾናቸው በቀጣዩ ጠቅላላ ምርጫ የመሳተፍ አቅም አይኖረውም ሲሉ አንዳንድ አባላቶቹ ለዋዜማ ተናግረዋል።

ከፓርቲው አባላት የተወሰኑት መንግሥትን ለመግልበጥ ሙከራ አያደረጋችኋል ተብለው ለ6 ወራት ከታሠሩ በኋላ፣ ባለፈው ሳምንት እንደተፈቱም በዘገባው ተመላክቷል።

አብን መጋቢት 11 ቀን፣ 2014 ዓ፣ም በባሕርዳር ከተማ ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባኤ በምርጫ ቦርድ ተቀባይነት ባለማግኘቱ ጉባኤው በድጋሚ እንዲካሄድ ቦርዱ ቢያዝም፣ እስካኹን ድረስ ፓርቲው ጉባኤውን ማካሄድ አልቻለም።

የፓርቲው አመራሮች ከምርጫ ቦርድ ጋር ያላቸው ንግግር በግልጽ የማይታወቅ መኾኑ፣ የፓርቲውን ሕልውና አሳሳቢ እንዳደረገው አባላቱ ገልጸዋል።

የአብን አባላት በፓርቲው ወቅታዊ ቁመና ዙሪያ ላነሱት ቅሬታ፣ የፓርቲው አመራሮች ምላሽ እንዲሠጡ ዋዜማ ያደረገው ጥረት እንዳልተሳካም አስታውቋል።


ብናልፍ አንዷለም በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው በመሾም ከፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ የሹመት ደብዳቤና የሥራ መመሪያ ተቀበሉ

ዓርብ ጥር 23 ቀን 2017 (አዲስ ማለዳ) የቀድሞው የሰላም ሚንስትር ብናልፍ አንዷለም በአሜሪካ የኢትዮጵያ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው ተሹመዋል።

የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ለአምባሳደር ብናልፍ አንዷለም የሥራ መመሪያ በሰጡበት ወቅት፤ በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን የረጅም ዘመን ግንኙነት የሚመጥን ትጋትና ቁርጠኝነት የተላበሰ አመራር መስጠት እንደሚገባ አሳስበዋል።

ፕሬዝዳንቱ "የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆኖ መሾም የኢትዮጵያን ሕዝብና መንግሥት ሃላፊነትና አደራ መጎናጸፍ ነው" ብለዋል።

ኢትዮጵያና አሜሪካ ከ120 ዓመታት በላይ የዘለቀ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት መሆናቸውንም ገልጸዋል።

በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የረጅም ዘመን ግንኙነትን የሚያጠናክር ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ማድረግ እንደሚገባም አስረድተዋል።

በተጨማሪም አሜሪካ በርካታ ኢትዮጵያውያን የሚገኙባት ሀገር በመሆኗ፤ በኢትዮጵያ ልማትና እድገት ላይ በንቃት እንዲሳተፉ አምባሳደሩ ጠንካራ ስራ ማከናወን እንደሚገባቸውም ገልጸዋል።

በመሆኑም በአሜሪካ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው የተሾሙት አምባሳደር ብናልፍ አንዷለም አሜሪካ ትልቅ እሳቤን የሚጠይቅ ዲፕሎማሲ የሚከናወንባት መሆኑን ታሳቢ ያደረገ አመራር እንዲሰጡም አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ ወዳጅን ማብዛት ላይ የተመሰረተ መሆኑንም ገልጸዋል።


"ለባርነት ጨረታ" ቀርባ የነበረችው ኢትዮጵያዊት 700 ሺህ ብር ተከፍሎ ነጻ መውጣቷን ተናገረች

ዓርብ ጥር 23 ቀን 2017(አዲስ ማለዳ)ከጥቂት ሳምንታት በፊት በሊቢያ "ለባርነት ጨረታ ቀርባ" የነበረችው ኢትዮጵያዊቷ ነሒማ ጀማል ለአጋቾቿ 700 ሺህ ብር ተከፍሎ ነጻ መውጣቷን ተናገረች።

በፎቶዎች እና በቪዲዮዎች ላይ አፏ በጨርቅ ተለጉሞ ስቃይ ሲደርስባት ትታይ የነበረችው ነሒማ በቤተሰቧ አማካይነት ገንዘብ ከኢትዮጵያ ተሰባስቦ ከተላከ በኋላ ከሁለት ቀናት በፊት አጋቾቿ ወደ ከተማ አምጥተው እንደለቀቋቸው አስረድታለች።

ታግታ ከነበረችበት ስፍራ እሷን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ቢኖሩም የተለቀቁት ገንዘብ የተከፈለላቸው "ውስን ሰዎች ነበሩ" ማለቷን ከቢቢሲ ጋር ባደረገችው ቆይታ ገልጻለች፡፡

እንዱሁም በአሁኑ ወቅት በሊቢያ እንደምትገኛና "ከዚህ በኋላ ምን እንደሚፈጠር አላውቅም" ስትል ጭንቀት ላይ እንደሆነች ተናግራለች።

ተማሪ የነበረችው ነሒማ ከኦሮሚያ ክልል ሻሸመኔ፣ በአዲስ አበባ በኩል ወደ በጎንደር በማምራት ከኢትዮጵያ በመውጣት ነበር ስራ አለ ተብላ ወደ ሊቢያ ያቀናችው።

አዲስ አበባ የተዋወቃቻቸው ሁለት ኢትዮጵያውያን ወንዶች በሰሃራ በረሃ በውሃ ጥም ሕይወታቸው አልፏል ብላለች።

ለሌሎች ስደትን አማራጭ ለሚያደርጉ "አገራቸው ውስጥ ቢቀመጡ ይሻላቸዋል፣ መንገድ ላይ በሽታ አለ፣ ሞት አለ፤ ብዙ ጓደኞቼ መንገድ ላይ ሞተዋል" ስትል መክራለች።


ከቀጣይ አመት ጀምሮ የኢትዮጵያ መከላከያ የዩኒቨርስቲ የተማሪዎች ምርጫ ውስጥ እንደሚካተት ተገለጸ

ሐሙስ ጥር 22 ቀን 2017(አዲስ ማለዳ) የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ከቀጣይ ዓመት ጀምሮ የተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምርጫ ውስጥ እንደሚካተት የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ አስታውቀዋል፡፡

"መከላከያና መምህር የዚህ ሀገር ምሶሶዎች ናቸው" ያሉት ሚኒስትሩ ሰዎች ሙያውን ወደውት እና ዩኒቨርሲቲውን መርጠው እንዲገቡ የሚያስችሉ ሥራዎችን መስራት ይገባል ብለዋል።

እንዲሁም ከቀጣይ ዓመት ጀምሮ የተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ምርጫ ውስጥ የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርስቲም እንደ አንድ አማራጭ እንደሚካተት ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ብርጋዲየር ጀኔራል ከበደ ረጋሣ በበኩላቸው፤ ዩኒቨርሲቲው ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የሚመጥን በቂ ዕውቀት ያለው የሰው ኃይል ለማፍራት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡




የኤርትራ መንግሥት ተቃዋሚዎች አዲስ አበባ ውስጥ መወያየታቸው ተገለፀ

ረቡዕ ጥር 21 ቀን 2017(አዲስ ማለዳ)የኤርትራ መንግሥትን ለመለወጥ የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች ትናንት ውይይት ያካሄዱ ሲሆን ውይይቱም በአዲስ አበባ መደረጉን ተሳታፊዎች መግለጻቸው ተመላክቷል፡፡

ከሁለት ሺህ በላይ የሚሆኑ ኤርትራዊያን በዚህ ውይይት መሳተፋቸው የተገለጸ ሲሆን  የተደረገውን ውይይት በተመለከተ “የኢትዮጵያ መንግሥት ዕውቅና ሳይኖረው አልሆነም” ሲሉ የኤርትራ አፋር ብሔራዊ ኮንግረስ (EANC) ሥራ አስፈፃሚ አባል የሆኑት አቶ የሱፍ አብደላ መናገራቸውን ዶችቬለ ዘግቧል።

ይህንን ውይይት አዲስ አበባ ላይ ለማድረግ እድሉን እንዴት እንዳግፕኙ የተጠየቁት አቶ የሱፍ አብደላ ይህንን ለማድረግ "እድል ተገኝቷል፣ ያንን እድል ተጠቅመን ውይይቱን አድርገናል" በማለት ማብራሪያ አለመስጠታቸው ተጠቁሟል፡፡

የኤርትራ አፋር ብሔራዊ ኮንግረስ የተባለውና  የኤርትራን መንግሥት ለመለወጥ የሚንቀሳቀስ መሆኑን የሚገልፀው ድርጅት ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ የሱፍ አብደላ የፖለቲካ ትግላቸው ማጠንጠኛ የኤርትራ መንግሥት ኤርትራ ውስጥ በሚገኙ አፋሮች ላይ የሚፈጽመው ያሉትን "በደል" እና "ግፍ" ማስቀረት ነው ብለዋል፡፡

"መቼም  የኤርትራ መንግሥት ጓደኛ የለውም" ሲሉ የከሰሱት የኤርትራን መንግሥት የሚቃወመው የኤርትራ አፋር ብሔራዊ ኮንግረስ ሥራ አሥፈፃሚ አባል አቶ የሱፍ አብደላ፤ የኢሳያስ አፈወርቂን አስተዳደር "ዓለም ላይ ለጎረቤት ሀገሮች ችግር ነው፣ ለራሱ ሕዝብ ችግር የሆነ በአንድ ቡድን የሚመራ መንግሥት ስለሆነ ዛሬ ይህ እድል ተገኝቷል" ማለታቸውን ዘገባው አትቷል፡፡

ይህን ጉዳይ ተከትሎ የኤርትራ መንግሥትም እስካሁን ያለው ነገር እንደሌለ ተመላክቷል፡፡




በአማራ ክልል ያለውን የዘፈቀ የጅምላ እስር የሚያስቆም አስቸኳይ አለም አቀፍ እርምጃ እንደሚያስፈልግ ተገለጸ

ረቡዕ ጥር 21 ቀን 2017(አዲስ ማለዳ)በአማራ ክልል ያለውን የዘፈቀ የጅምላ እስር የሚያስቆም አስቸኳይ አለም አቀፍ እርምጃ እንደሚያስፈልግ ዓለም አቀፉ የመብቶች ተሟጋች ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል አስታወቀ፡፡

በክልሉ መንግስት የዘፈቀደ የጅምላ እስር መፈጸም ከተጀመረ ድፍን አራት ወራት ተቆጥረዋል ያሉት የድርጅቱ የምስራቅና ደቡብ አፍሪካ ዳይሬክተር ቲገሬ ቻጉታ በክልሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በጅምላ እየታሰሩ ባለበት ሁኔታ የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዝምታ ከማሳፈርም በላይ ነው ሲሉ ኮንነዋል፡፡

በመሆኑም የኢትዮጵያ የልማት አጋሮች አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የመብት ተሟጋቾች ጭምር በጅምላ ታፍሰው በግፍ የታሰሩት ሁሉ እንዲለቀቁ ተጽዕኗቸውን ተጠቅመው ግፊት እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የህግ የበላይነት ተረግጦ ከባድ ሰብዓዊ ቀውስ እየደረሰ ባለበት በዚህ ወቅት፤ ዓለም በኢትዮጵያ ያለውን የሰብዓዊ መብት ሁኔታ አይቶ እንዳላየ ማለፉን ሊያቆም ይገባልም ተብሏል፡፡

መንግስት በዘፈቀደ እያፈሰ በጅምላ ያሰራቸውን ሊለቅ ካልሆነም ደግሞ ዓለም አቀፍ ዕውቅና ባላቸው የተጠያቂነት የህግ መስፈርቶች ክስ ሊመሰርትና በህግ ሊጠይቃቸው እንደሚገባም ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡


ሀሙስ ደርሷል!! ፊንቴክስ ‹‹FINTEX›› የፈርኒቸር፣ የቤተ-ውበት እና የግንባታ አጨራረስ ምርቶች፣ አገልግሎቶች እና ቴክኖሎጂዎች ዓለም አቀፍ አውደ-ርዕይ ነገ ሃሙስ በድምቀት ይከፈታል። ዝግጁ?
በርካታ ታላላቅ ተቋማት ምርትና አገልግሎታቸውን ለማስተዋወቅ አዳዲስ የገበያ አማራጮችን ለመፍጠርና የዘርፉን ዕድገቶች ለማሳየት ከጥር 22-25 በሚኒሊየም አዳራሽ እርስዎን ይጠብቃሉ!!
ፊንቴክስ በፈርኒቸር፣ በቤተ ውበት ዲዛይን እና በፊኒሺንግ ምርቶች ዘርፍ የሚያስደንቁ አዳዲስ የፈጠራ ስራዎችን ለማየት የሚችሉበት ትልቁ እድል ነው። በዚህ መደረክ በርካቶች ዘርፉን ለማሳደግ ይመክሩበታል። ይጎብኙት ብዙ ያተርፉበታል።
በነጻ ለመጎብኘት https://bit.ly/fintexregistration ይመዝገቡ ወይንም በ0913356709 ወይም 0929308364 አሁኑኑ ይደውሉ!!
ድህረ ገጻችንን ይጎብኙ www.fintexaddis.com


አደገኛ የማጭበርበሪያ መተግበሪያ በማኅበራዊ ሚዲያ እየተዘዋወረ መሆኑን ንግድ ባንክ አስታወቀ

ማክሰኞ ጥር 20 ቀን 2017 (አዲስ ማለዳ)ደምበኞች በዋትስ አፕ እና በቴልግራም የሚሠራጭ Pharma+/CBE Vacancy መተግበሪያን እንዳይጭኑ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አሳስቧል።

ባንኩ ባስተላለፈው የማስጠንቀቂያ መልዕክት፤ ባደረገው ምርመራ መሠረት አደገኛ መተግበሪያ ማግኘቱን ገልጿል።

ይህ Pharma+/CBE Vacancy የተሰኘ አሳሳች መተግበሪያ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በሰፊው እየተሰራጨ እንደሆነ በመጥቀስ፤ ይህ መተግበሪያ በቴሌግራም እና ዋትስአፕ ወደ ደንበኞቹ እየደረሰ መሆኑን ጠቁሟል።

መተግበሪያው በስልክ ላይ ከተጫነ ያለ ፈቃድ ገንዘብ ማስተላለፍ እንደሚችልም አሳውቋል።

ባንኩ ከዚህ አይነት የመጭበርበር አደጋ ለመጠበቅ ከቴሌግራም ወይም ከዋትስአፕ መተግበሪያዎችን አታውርዱ ብሏል።

ደንበኞች መሰል ተግባራት ሲገጥሟቸው በ951 ነጻ የስልክ መስመር ደውለው እንዲያሳውቁ አሳስቧል።




በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሰውን የፋኖ ክንፍ የሚመሩት አቶ እስክንድር ነጋ ከመንግስት ጋር ልንደራደር ነው ማለታቸውን ተከትሎ የተለያ አስተያየቶች እየተሰነዘሩ ነው፡፡

ድርድሩ እንዴት ባለ መንገድ ይከናወናል? ሌሎቹ የፋኖ ሃይሎች ድርድሩን ይቀበሉታል ወይ አደራዳሪ ሆኖ የሚቀርበው ዋነኛ አካልስ ማን ነው?የሚሉና መሰል ስጋት ያዘሉ ጥያቄዎችም መነሳታቸውን ቀጥለዋል፡፡

ዝርዝር መረጃው ከዚህ በታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ይከታተሉ፡፡

https://youtu.be/svIm5UY3XZw




“የማዳበሪያ አቅርቦት ከገበሬው የመሬት ዝግጅት አንጻር አይመጣጠንም ”- የፓርላማ አባላት

ሰኞ ጥር 19 ቀን 2017(አዲስ ማለዳ)በተለያዩ ክልሎች የአፈር እና የማዳበሪያ አቅርቦት ከገበሬው የመሬት ዝግጅት አንጻር እንደማይመጣጠንና በገበሬው ዘንድ በተደጋጋሚ የሚነሳ ጥያቄ መሆኑ መንግስት ምን አይነት የመፍትሄ ሀሳብ እንዳለው የምክር ቤት አባል ወርቅነሽ መሀመድ ጠይቀዋል፡፡

ይህም የተጠየቀው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 1ኛ ልዩ ስብሰባ እየተካሄደ ባለበት ወቅት ነው፡፡

በተመሳሳይ ጥያቄ ያቀረቡት ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ስንዴ አምራች ገበሬዎች ምርቶቻቸውን በመንግስት የዋጋ ተመን እንዲሸጡ የሚገደዱበት አግባብ ምክንያቱ ምን እንደሆነ እና በነጻ ገበያ እንዳይገበያዩ መሆኑ በውድ ዋጋ ማዳበሪያ እየገዛ የሚያመርተውን ገበሬ የሚያሳድርበትን ጫና የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንዴት እንደሚመለከተው ጠይቀል፡፡

በተጨማሪም የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ከዘመቻ ነት ወጥቶ ወደ ተቋማዊ የችግኝ ማልማት እና የተራቆቱ አካባቢዎችን የማልማት ስራ የሚካሄድበትን ጊዜ እንዲገለጽ አመላክተዋል፡፡

በአባላቱ ለተነሱ ሀሳብ እና ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት የግብርና ሚኒስቴር ሚንስትር ግርማ አመንቴ 5.7 ሚሊዮን ማዳበሪያ ለመስኖ ወቅት እንደተዘጋጀ እና ስርጭቱ ላይ መስተጓጎሎች እንዳይኖሩም የመቆጣጠር ስራ እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡

በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚታረሰው መሬት 43 ከመቶ የሚሆነው በአሲዳማ አፈር የተጠቃ መሆኑን እና 7 ሚሊዮን ሄክታር የሚሆነው የአሲዳማ አፈር መሆኑን ሚኒስትሩ አስታውቀዋል፡፡

እንዲሁም መሬቱን ለግብርና ስራ ለማዋል በዓመት 6.2 ሚልየን ኩንታል ማዳበሪያ ጥቅም ላይ የሚውል ሲሆን 70 ከመቶ የሚሆነው የአፈር ማዳበሪያ ይባክናል ተብሏል።


የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነገ 1ኛ ልዩ ስብሰባውን ያካሂዳል

እሁድ ጥር 18 ቀን 2017 (አዲስ ማለዳ) 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ ልዩ ስብሰባ ነገ ይካሄዳል።

ምክር ቤቱ በስብሰባው የግብርና ሚኒስቴርን የ2017 በጀት አመት የ6 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት የሚያዳምጥ ሲሆን፤ ሁለት የብድር ስምምነቶችን መርምሮ እንደሚያጸድቅም ይጠበቃል።

የከተማ መሬት ይዞታ እና መሬት ነክ ንብረት ምዝገባ እንዲሁም የከተማ መሬትን በሊዝ ስለመያዝ የተዘጋጀ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ የከተማ መሰረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ አዋጁን እንደሚያፀድቅም ይጠበቃል።

በተጨማሪም የአጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ የሰው ሀብት ልማት፣ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ አዋጁን ያጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ከምክር ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

አዲስ ማለዳ የምክር ቤቱን ስብሰባ በዩቲዩብ በቀጥታ ስርጭት የምታስተላልፍ መሆኑን እየገለጽን መሰል ጉዳዮችን ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን በመጫን አዲስ ማለዳን ሰብስክራይብ ያድርጉ።
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA


በትግራይ ክልል የእርስ በርስ ጦርነት እንዳይቀሰቀስ ስጋት መኖሩን ነዋሪዎቹ ተናገሩ

ቅዳሜ ጥር 17 ቀን 2017 (አዲስ ማለዳ) የትግራይ ወታደራዊ አመራር ሰሞኑን መፈንቅለ መንግስት የማድረግ ዕቅድ መኖሩን በመግለጫቸው ካሳወቁ በኋላ በትግራይ ህዝብ ላይ ከፍተኛ ስጋት መፈጠሩን ነዋሪዎች ገልጸዋል።

በተለይም ውጥረቱን ተከትሎ በአካባቢው ግጭት ሊከሰት ይችላል በሚል ከወትሮው በተለየ መልኩ ገንዘብ ለማውጣት ባንኮች በሰልፍ ተጨናንቀዋል ሲሉ የአይን እማኞች ገልፀዋል።

በገበያ ማእከላት በተለይ የፍጅታ ሸቀጦች ላይ የፍላጎት መጠን በጣም ጨምሯል የሚሉት ነዋሪዎቹ ህዝቡ ጦርነት ይቀሰቀስ ይሆናል ብሎ የሰጋው ህዝብ ስጋት ላይ መውደቁን ይገልፃሉ።

ህዝቡ ስጋቱን ለመግለጽም የተቃውሞ ሰልፍ ማካሄድ ጀምሯል።

በተለይም የመኾኒና የአካባቢው ህዝብ «መንግስትን የሚያፈርስ የትኛውንም አካል አንታገስም» የሚል መፈክር በማንገብ በትላንትናው አለት መግለጫ የሰጠውን እና የትግራይ ሀይል የበላይ ሀላፊ ነኝ ያለውን ቡድን ተቃውመዋል።


የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር የመንገደኞች ትራንስፖርት አገልግሎት ሊጀምር መሆኑን ኢንጂነር ታከለ ኡማ ገለጹ

ቅዳሜ ጥር 17 ቀን 2017 (አዲስ ማለዳ) የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር አክሲዮን ማህበር ከመጪው የካቲት ወር ጀምሮ በኦንላይን ቦታ በማስያዝ የህዝብ መንገደኞች ትራንስፖርት አገልግሎት እንደሚጀምር የአክሲዮን ማህበሩ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ገልፀዋል።

ኢንጂነር ታከለ ኡማ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው፤ "ጥራት ያለዉና እና ቀልጣፋ የጉዞ አገልግሎት ለመስጠት ሲባል እንዲሁም ትክክለኛ የመንገደኛ መረጃን ለማረጋገጥ እና ከችግር የጸዳ ጉዞን ለማመቻቸት አስፈላጊ በመሆኑ ለሁሉም የሀገር ውስጥ ተሳፋሪዎቻችን ብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) በመጠቀም ኦንላይን ቦታ ለመያዝም  ሆነ ለመጓዝ  መስፈርት መሆኑን ለማስታወስ እንወዳለን" ሲሉ አስታውቀዋል።


በትግራይ ጦርነት የተጎዱ 1026 ሰዎች ለእያንዳንዳቸው ክልሉ 140 ካሬ ሜትር ቦታ ሰጣቸው

ቅዳሜ ጥር 17 ቀን 2017 (አዲስ ማለዳ) በትግራይ ጦርነት የተጎዱ ሰዎች ሁሉ መኖሪያ ቤት ብቻ ሳይሆን ብዙ ይገባቸዋል ሲል የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ገለፀ።

ፕሬዝደንት ጌታቸው ረዳ በጦርነት የተጎዱ የትግራይ ተወላጆች በሙሉ መኖሪያ ቤት ብቻ ሳይሆን ብዙ ይገባቸዋል ብለዋል።

በአጠቃላይ 1,026 የጦር ሰለባዎች ለእያንዳንዳቸው 140 ካሬ ሜትር ቦታ መመደቡን የከተማው የመሬት አጠቃቀምና አስተዳደር ኦፊሰር ገ/ሚካኤል እንሁን ገልጸዋል።

የትግራይ ጦርነት ጉዳት የደረሰባቸው ማኅበር ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጨርቆስ ወ/ማርያም መንግስት ላደረገው ድጋፍ አመስግኖ መንግስት በዚህ መልኩ መስራቱን አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል።


"የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደርን ለማፍረስ ወሰነናል መባሉን አውግዘናል"- ፓርቲዎች

ቅዳሜ ጥር 17 ቀን 2017(አዲስ ማለዳ)ዓረና ትግራይ፣ የትግራይ ነጻነት ፓርቲና ባይቶና በጋራ ባወጡት መግለጫ የትግራይ ጸጥታ ኃይሎች የተወሰኑ አዛዦች ጊዜያዊ አስተዳደሩን ለማፍረስ ወሰነናል ማለታቸውን አውግዘዋል፡፡

ፓርቲዎቹ የአዛዦቹ መግለጫ ሥልጣን የመቆጣጠር ወይም ሥልጣን ለሚፈልግ ኃይል ሥልጣን አሳልፎ የመስጠት እንቅስቃሴ ነው በማለት ተቋውሞአቸውን ገልጸዋል፡፡

በተመሳሳይ ሳልሳዊ ወያኔ በተናጥል ባወጣው መግለጫ የጸጥታ ኃይሉ አዛዦች ለአንድ የፖለቲካ ቡድን በመወገን የጊዜያዊ አስተዳደሩን ሥልጣን "በኃይል ለመንጠቅ" ሙከራ አድርገዋል በማለት በጽኑ አውግዟል።

ፓርቲው ይሄ አካሄድ የትግራይ ሕዝብ አጣዳፊ የሆኑትን የሰላም አካታች ሲቪል አስተዳደር የመመስረት የቅድመ-ጦርነት አስተዳደራዊ ወሰኖችን የማስመለስና ስደተኞችንና ተፈናቃዮችን ወደቀያቸው የመመለስ ዓላማዎችን አደጋ ላይ ይጥላል ብሏል።

ፓርቲው በትግራይ ለተፈጠሩት ችግሮች ዘላቂው መፍትሄ በፖለቲካ ፓርቲ ሽኩቻ ውስጥ ራሱን የማያስገባ ኹሉን አካታች ጊዜያዊ አስተዳደር እንደገና ማቋቋም እንደሆነም ጠቁሟል።

በአንጻሩ ጥር 15ቀን 2017 ዓ.ም  " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠውን መግለጫ የሚቃወም መግለጫ አውጥቶ እንደነበር ይታወሳል።

"የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን"  በሚል ያወጡት መግለጫ የ " ነሃሴው ህወሓት ህዝቡን እና ሰራዊቱ ለመበታተነ የሰራው ክፋት ውጤት ነው " በማለት የገለጸ ሲሆን " የነሃሴው ህወሓት ህዝብን እና የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ያልተቀበለው ጉባኤ  በማካሄድ ነባሩን ህወሓት እንዲዳከም ሰርቷል " ሲል በአቶ ጌታቸው የሚመራው ህወሓት ፤ " ወታደራዊ አምባገንነት ታግሎ ዴሞክራሲያዊ እና ህዝባዊ መንግስት የጨበጠ ህዝብ ወደ ኋላ አይመለስም " ብሎ ነበር፡፡



20 last posts shown.