የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ህንፃ የእሳት አደጋ ደረሰበት
ማክሰኞ ጥር 16 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) በትናንትናው ዕለት ምሽት 4፡48 ላይ ከፍተኛ ቴክኖሎጂና ግብዓት የፈሰሰበት የለሚ ኩራ ክ/ከተማ አስተዳደር ህንፃ የእሳት አደጋ ደርሶበት መሰረተ ልማቱ መውደሙን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ።
የህዝብ ፋይልና ዳታ እንዲሁም መረጃዎች ላይ የደረሰ አደጋ አለመኖሩን የጠቆው የከተማ አስተዳደሩ፤ የአደጋው ምክንያት እና መንስኤ በፖሊስ ምርመራ እየተካሄደበት እንደሚገኝ አስታውቋል።
ህንጻው የኢትዮ ቴሌኮም፣ የአርቴፊሻል ኢንተልጀንስ፣ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ተቋማት የተሳተፉበት እና የዲጂታል አገልግት መስጠት የሚያስችል ሥራ ተሰርቶበት የፊታችን ቅዳሜ ይመረቃል ተብሎ እንደነበር ተገልጿል፡፡
ባለ 7 ወለል ህንጻው ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ ከ1.6 ሚሊየን ብር በላይ የተገመተ ንብረት ሲወድም በ10 ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን የእሳት አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል፡፡ ከተጎጂዎቹ መካከል ሦስቱ የእሳት አደጋ ሰራተኞች መሆናቸውንም ገልጿል።
የእሳት አደጋዉ ከህንጻዉ ምድር ቤት የተነሳ ሲሆን እሳቱ እስከ ኹለተኛ ፎቅ ድረስ ጉዳት ማድረሱንም ኮሚሽኑ አስታውቋል።
የአደጋው ምክንያት እና መንስኤ ምርመራ እንዳለቀ ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግ የጠቆመው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፤ የአካባቢው ማህበረሰብም መንግስት የጀመረውን ጥረት ለመደገፍ ከዚህ አደጋ ጋር ተያይዞ ማንኛውንም መረጃዎች በመስጠት የተለመደ ትብብሩን እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል፡፡
በሌላ በኩል ትላንት ከቀኑ 10:46 በሸገር ከተማ ቡራዩ በሹፋን ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ ከ300 ሺሕ ብር በላይ የተገመተ ንብረት የወደመ ሲሆን፤ በተመሳሳይ ምሽት 3:55 ላይ በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 አስኮ መነሀሪያ በህዝብ ማመላለሻ አዉቶቢስ ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ 1 ሚሊየን ብር የተገመተ ንብረት መውደሙን የእሳት አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።
_______
ትክክለኛውን የአዲስ ማለዳ ሶሻል ሚዲያ በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Twitter ➲ t.ly/mxA4n
ማክሰኞ ጥር 16 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) በትናንትናው ዕለት ምሽት 4፡48 ላይ ከፍተኛ ቴክኖሎጂና ግብዓት የፈሰሰበት የለሚ ኩራ ክ/ከተማ አስተዳደር ህንፃ የእሳት አደጋ ደርሶበት መሰረተ ልማቱ መውደሙን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ።
የህዝብ ፋይልና ዳታ እንዲሁም መረጃዎች ላይ የደረሰ አደጋ አለመኖሩን የጠቆው የከተማ አስተዳደሩ፤ የአደጋው ምክንያት እና መንስኤ በፖሊስ ምርመራ እየተካሄደበት እንደሚገኝ አስታውቋል።
ህንጻው የኢትዮ ቴሌኮም፣ የአርቴፊሻል ኢንተልጀንስ፣ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ተቋማት የተሳተፉበት እና የዲጂታል አገልግት መስጠት የሚያስችል ሥራ ተሰርቶበት የፊታችን ቅዳሜ ይመረቃል ተብሎ እንደነበር ተገልጿል፡፡
ባለ 7 ወለል ህንጻው ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ ከ1.6 ሚሊየን ብር በላይ የተገመተ ንብረት ሲወድም በ10 ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን የእሳት አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል፡፡ ከተጎጂዎቹ መካከል ሦስቱ የእሳት አደጋ ሰራተኞች መሆናቸውንም ገልጿል።
የእሳት አደጋዉ ከህንጻዉ ምድር ቤት የተነሳ ሲሆን እሳቱ እስከ ኹለተኛ ፎቅ ድረስ ጉዳት ማድረሱንም ኮሚሽኑ አስታውቋል።
የአደጋው ምክንያት እና መንስኤ ምርመራ እንዳለቀ ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግ የጠቆመው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፤ የአካባቢው ማህበረሰብም መንግስት የጀመረውን ጥረት ለመደገፍ ከዚህ አደጋ ጋር ተያይዞ ማንኛውንም መረጃዎች በመስጠት የተለመደ ትብብሩን እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል፡፡
በሌላ በኩል ትላንት ከቀኑ 10:46 በሸገር ከተማ ቡራዩ በሹፋን ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ ከ300 ሺሕ ብር በላይ የተገመተ ንብረት የወደመ ሲሆን፤ በተመሳሳይ ምሽት 3:55 ላይ በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 አስኮ መነሀሪያ በህዝብ ማመላለሻ አዉቶቢስ ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ 1 ሚሊየን ብር የተገመተ ንብረት መውደሙን የእሳት አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።
_______
ትክክለኛውን የአዲስ ማለዳ ሶሻል ሚዲያ በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Twitter ➲ t.ly/mxA4n